National youth Volunteers
Open in Telegram
Ministry of peace, youth volunteers channel #ይህ ቻናል የተዘጋጀው ለብሔራዊ በጎ ፈቃደኞች መረጃን በቀላሉ ለማድረስ ነው
Show more1 087
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ዘመን ከዘመን ሲሻገር አዲስ ዓመት ሲመጣ... አዲስ አየር ንብረት> ዓደይ አበባ> አበባ አየሽ ወይ አበባ አየህ ወይ > እንቁጣጣሽ ተባብለን🌼🌼🌼 መጪው ዓመት በአዲስ ሃሳብ እና በአዲስ ማንነት ያሰብናችዉ አዳዲስ ሃሳቦች እንዲሳኩልን የምንመኝበት እና # ተስፋ የቆረጥንባቸዉ ጉዳዮች ላይ እንደ አዲስ ተስፋ የምንዘራበት ነዉ❤️☺️☺️
አዲስ ዓመት ሲመጣ... የኛ እድሜ እየጨመረ አዲስ ለሚመጣው ትዉልድ ቦታ እየለቀቅን መሄዳችን ረስተናል🙇:: ስለዚህ ጥለን ለምንሄደው አለም እስካለንበት ድረስ ፍቅርን እና መቻቻልን ዘርተን እንለፍ👍🙏🙏
በጎ ሰው ተስፋ አይቆርጥም 👏
በጎ ሰው ከራሱ አና ከቤተሰቡ አልፎ አካባቢው ላይ ያለዉን የሱን እርዳታ ሚፈልግ ሰው ያስተዉላል👏
አዲሱ ዓመት ያሰብነው ሁሉ ሚሳካበት
ለሀገራችን ሰላም የሚመጣበት
ራሳችን ለዉጠን ዙሪያችን ያሉ ሰዎችንም የምንለዉጥበት ያድርግልን 😊😊😊
መልካም አዲስ ዓመት 🙏
National youth volunteers!
@MOPAddis1st
@MOPAddisFirst
ከሥራና ክሕሎት የክልል የአሻራ ምዝገባ ጋር በተያያዘ ከ አዲስአበባ ዉጭ የምትገኙ ልጆች የት የት እየተሰጠ አንደሆነ share አድርጉን.. በፊት የምታዉቁአቸዉን በጎፈቃደኞችን በማስገባት ሃሳብ እንዲሰጡን እናድርግ ::
በድጋሚ መልካም ምሽት 🙏🙏
@MOPAddis1st
@MOPAddisFirst
ይህ ቻናል ከአዲስአበባ በጎፈቃደኞች ወደ ብሔራዊ በጎ ፈቃድ ቻናል ከፍ ማለቱን ልናሳዉቅ እንወዳለን...👏👏
አብራችሁን የነበራችሁ የአዲስ አበባ 1ኛ አና 2ኛ ዙር በጎፈቃደኞን ከልብ እናመሰግናለን😊
ይሄንን ቻናል እና ግሩፕ ለምታዉቁቸዉ ሁሉም ክልል ላይ ያሉ ሁሉም ዙር በጎፈቃደኞች ሼር አድርጉ👍
ከሥራና እድል ፈጠራ ጋር በተያያዘ እንዲሁም ሌሎችም የስራ እድሎችን በጋራ የምናይበት እና የምንወያይበት ይሆናል::
መልካም ምሽት🙏
@MOPAddis1st
@MOPAddisFirst
Thank you 🙏
ሌሎችም ክልሎች ላይ አሻራ መስጠት የተጀመረባቸዉን ቦታዎች ምታዉቁ ካላችሁ አሳዉቁን👍
@MOPAddis1st
@MOPAddisFirst
Thank you 🙏
ሌሎችም አሻራ መስጠት የተጀመረባቸዉን ቦታዎች ምታዉቁ ካላችሁ አሳዉቁን🙏
@MOPAddis1st
@MOPAddisFirst
Notice:
የአንድ ማአከል አገልግሎት የሚገኘው በተመረጡ ወረዳዎች ሲሆን የሚገኙትም በወረዳ የሥራ ኢንተርፕራይዝ: ኢንዱስትሪ ቢሮ ነዉ::
ለምሳሌ አዲስአበባ አካባቢ የምትገኙ ቦሌ ክ/ከተማ (ወረዳ 3(ቦሌ አትላስ አካባቢ) ~5(ገርጂ አካባቢ)~6(ቦሌ ክ /ከተማ ጀርባ )~11) የሥራ ኢንተርፕራይዝ: ኢንዱስትሪ ቢሮ የሚገኙ ሲሆን በምዝገባ ወቅት የተሰጣችሁን የማረጋገጫ ቁጥር ብቻ በመያዝ biometrics መረጃ መስጠት ይቻላል::
አዲስአበባ በተጨማሪ የካ~ቃሊቲ~አዲስከተማና ኮልፌ ክ/ከተማ ላይ በተመረጡ ወረዳዎች አገልግሎቱ ይሰጣል::
ስለዚህ የተመረጡ ወረዳዎችን ለማወቅ ክ/ከተሞች ላይ ሥራ ኢንተርፕራይዝ: ኢንዱስትሪ ቢሮ በመግባት information መጠየቅ ይቻላል :: ሌሎች የተዘረዘሩ ክልሎችም ላይ በተመሳሳይ ገብቶ መጠየቅ ይቻላል::
ትክክለኛ አድራሻ ሄዳችሁ ያረጋገጣችሁ በዉስጥ መስመር ብታሳውቁን ሌሎች እንዳይቸገሩ post የምናረግላችሁ ይሆናል::
መልካም እድል 🙏🙏🙏
ሰላም👏
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በሃገር ውስጥና በውጭ ሃገር በሚፈጠሩ የሥራ ዕድሎች ተጠቃሚ ለማድረግ ባስተላለፈው የምዝገባ ጥሪ መሰረት በድረ-ገጽ (በኦን ላይን) ተመዝግበው የባዮሜትሪክስ ምዝገባ በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ፡፡
በቅርቡ በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳድሮች በሚገኙ የተመረጡ 400 ለሚሆኑ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎች ሥርዓቱን ተደራሽ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ ነው፡፡
በመሆኑም የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓቱ
👉በኦሮሚያ ክልል
(በአምቦ፣ በሻሸመኔ፣ በአዳማ፣ በአሰላ፣ በቡራዩ፣ በምስራቅ ሃረርጌ፣ በመትሃራ፣ በፉሪ፣ በጉደር እና በጅማ)
👉በአዲስ አበባ
(በቦሌ፣ በየካ፣ በአቃቂ ቃሊቲ፣ በአዲስ ከተማ እና በኮልፌ ክፍለ ከተሞች)
👉በሲዳማ ክልል
(በሃዋሳ፣ ባንሳ፣ አለታ ወንዶ እና በወንዶ ገነት)
👉በደበብ ምዕራብ
(በቴፒና ሌሎች ከተማ)
በሚገኙ የተወሰኑ አንድ ማዕከላት አገልግሎት መስጠት ተጀምሯል።
ስለሆነም ከላይ በተጠቀሱትና በሚቀርባቸው የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎች ተገኝተው አስፈልጊውን አገልግሎት ማግኘት ይችላሉ::
ሌሎች ቦታዎች ላይ በቀጣይ የሚዳረስ ይሆናል::
