2 823
Subscribers
No data24 hours
-247 days
-10430 days
Posts Archive
2 823
🎵 Start Your Musical Journey
▷ Music lovers, join the fastest growing telegram music community - Audius! Featuring artists across the globe, there's no better place to discover, share, and explore.
🎧 Join Now
2 823
ዛሬ እኔና ውዴ የተገናኘንበት ቀን ነው በመሀላችን ፍቅር ቢኖርም ሳንጣላ የዋልንበት ቀን ትዝ አይለኝም#በቃሽኝ #በቃህኝ ተባብለን ወድያው መልሠን እንታረቃለን አይገርምም? በዛሬው ቀን ራሡ ተጣልተን ነበር😄
#እሱ "እንኳን አደረሠሽ ለማንኛውም ለተገናኘንበትም ለተለያየንበትም ቀን" የሚል Message ላከልኝ፡፡
#እኔ ቅጥል ብዬ "ብርቄ አይደለም መለያየት እኔም ሰልችቶኛል"
#እሱ " የእውነት ግን ሰልችቶሻል? ምንድነው ሚሠማሽ ንገሪኝ?"
#እኔ " ሚሠማኝ.... መንደድ፣ መቃጠል፣ ማበድ፣ የልብ ህመም.....
#እሱ "እኔም እንደዛ ነው የሚሠማኝ ከዛም በላይ በጣም ሰልችቶኛል እና አሁን ምን አሠብሽ?"
#እኔ "ምን አስባለው ምን አማራጭ አለኝ?"
#እሱ "ok አማራጭ ብታገኚ ትሔጃለሽ ማለት ነው?"😏
እዮት እንግዲ ነገረኛነቱን😊
#እኔ " አይ አልፈልግም😍 ምክንያቱም ከአንተ ውጪ መኖር አልችልም ግን አንተስ ምን ወሠንክ?"
#እሱ እንደዚው መቀጠል ከአንቺ ጋር እየተቃጠሉ እየነደዱ መኖሮ ደሞ በጣም ናፍቀሽኛል"😍
ከዚያ ሁሉ ነገር ተረሥቶ ፍቅር በፍቅር ሆነን ዋልን😍😍😍 መፋቀር ማለት አለመጣላት አይደለም፡፡
#የፍቅር_አምላክ_ሆይ_ውዴን_ጠብቅ ❤️❤️❤️
♡ ㅤ ⌲ ✉️
ˡᶦᵏᵉ ˢʰᵃʳᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ
jᵒⁱⁿ⇝ @Lyrics_profile
2 823
በ20 ደቂቃ የህልምዎን ሥራ ያግኙ!
▪️ በየ 20 ደቂቃ አዳዲስ የስራ እድሎች
▪️ ከ50 በላይ የተለያዩ የስራ ዘርፎች
▪️ የቋሚ ፤ የርቀት እና የፍሪላንስ የስራ አይነቶች
▪️ ከ ሺህ በላይ የስራ ቅጥሮች/ማገናኘቶች
የሌለ ስራ የለም!
Instagram • TikTok • LinkedIn • YouTube • Twitter • Facebook
2 823
#በዛው_ያስቀረው ...
«ዘውድአለም ታደሰ»
ON @Lyrics_profile
⚡️⚡️⚡️⚡️⚡️
ማስጠንቀቂያ!🚫
(ይሄን ፅሁፍ እድሚያቸው ከሁለት ወር በታች የሆኑ ህፃናት እንዳያነቡት)
ኮንዶሚኒየም ውስጥ የመኖር ዋነኛ ችግሩ ሚስጥር በቤትህ ማውራት አለመቻልህ ነው። ቤትህ ቁጭ ብለህ ኮምጨጭ ያለ ሚስጥር ከሚስትህ ጋር ስታወራ ጎረቤትህ ሲያዳምጥህ ቆይቶ «በእውነቱ እጅግ የሚያሳዝን ነገር ነው» ሲል ትሰማዋለህ። በቃ የግል የሚባል ወሬ አይኖርህም ስልህ!
ባለፈው ከሚስቴ ጋር አልጋ ላይ አንዳንድ አልባሌ ነገሮች ለማድረግ ሞክረን ነበር። (መቼም ሰው ከበላ ፣ ከጠጣ ፣ ካገባ ፣ አልባሌ ነገር መፈፀሙ አይቀርም)
ግን በሚያሳዝን ሁኔታ እንትኔ አልነሳ አለ። ብንሞክር ብንሞክር እሱቴ! “ተነሳ ተራመድ” እያልኩ የደርጎች መዝሙር ሁሉ ብዘምርለት ወንድሜ ገገመ
ሚስቴ እላዬ ላይ ሆና «ተነስ የኔ አንበሳ ፣ ተነስ ጀግናው ፣ ተነስ ወንዱ» ብትል ብትሰራው ሰውየው ማደንዘዣ እንደተወጋ ታካሚ አልነቃነቅ አለ ... እላዬ ላይ ወጥታ አለቅጥ ስትጨምቀኝ
«አረ እሱን አስነሳለሁ ብለሽ አስሜን እንዳታስነሽው» አልኳት ቁና ቁና እየተነፈስኩ። እያጉረመረመች ከላዬ ላይ ወረደች። በሁኔታው በጣም ተሸማቅቄ ዝም ብዬ አይን አይኗን አያት ጀመር።
የዛሬን አያርገውና አሁን እንዲህ ሊለግም የተጋባን ሰሞን ገና መኝታ ቤቴን ሳየው እንደሮም ወታደር ቀጥ ብሎ ይቆም ነበር።
ሚስቴ ተስፋ አልቆረጠችም። ያቅሟን ታገለች። እቺ ልጅማ በዚህ ሞራሏ ታጋይ ብትሆን የሆነ ብሄር ነፃ ታወጣ ነበር እላለሁ እኔ በሆዴ። ብቻ እንዲህም ሆና አልሳካ ሲላት ተበሳጭታ ወደጉዳዩ እየጠቆመች ..
«ይሄ ነገር ግን ነፍስ አለው?» አለችኝ።
«አረ እንዲህ አይባልም ውዴ» አልኳት።
«ታዲያ ምናባቱ ሆኖ ነው ተጋድሞ የቀረው?»
«እንጃለቱ» አልኳት ልክ ስለሌላ ሰው እንደሚያወራ ሆኜ።
«ደሞ እንጃለቱ ይላል እንዴ?» ብላ ገላመጠችኝ።
«ካልሆነ ያ ቫያግራ የሚሉትን መድሃኒት ልዋጥ እንዴ?» አልኳት ግራ ቢገባኝ .. የዚህ ግዜ ያ ከውካዋ ጎረቤቴ ..
«እኔም በሱ ነው ያለሁት ቫያግራ ጥሩ ነው» ብሎ ቀልባችንን ገፈፈው። ለካ ይሄን ሁሉ ነገር እየሰማን ነበር። አይ ኮንዶሚኒየም።
ከዚያን ቀን ወዲህ እኔና ሚስቴ እንዲህ አይነት የግል ነገሮችን ማውራት ስንፈልግ በቴክስት ለማውራት ተስማማን። በማግስቱ አልባሌ ነገር መፈፀም አማራትና በቴክስት
«አሁንም ተጋድሟል?» አለችኝ።
«አዎ ማሬ»
«በዛው ያስቀረው!»
♡ ㅤ ⎙ㅤ ⌲ ✉️
ˡᶦᵏᵉ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ
jᵒⁱⁿ⇝ @Lyrics_profile
2 823
የሴቶች ቅሬታ
ሚስቶች ተሰበሰቡና እግዜርን ሊያናግሩ ሄዱ አሉ....
(በአሌክስ አብርሃም)
እግዜር - ምን ሆናችሁ ልጆቸ
ሚስቶች -መረረን !
እግዜር - ምነው ምን የሚያማርርነገር ተፈጠረ
ሚስቶች - እኛ ሴቶች ጫናው በዛብን አንገፈገፈን እኛ አርግዘን፣ እኛ አምጠን ፣እኛው አጥብተን... አልቻልንም ! ይሄ ጉዳይ ስራ እንዳንሰራ ሆነ ተብሎ ወንዶችን ለመተባበር የተደረገ ሴራ ነው ይስተካከልልን አሉ እያለቀሱ፡፡
እግዜር -ጥሩ! ምን እንዲደረግላችሁ ትወዳላችሁ ታደያ
ሚስቶች -ቢያንስ ከማርገዝ ፣ከማማጥ ወይም ከማጥባት ወንዶች አንዱን የተፈጥሮ ግዴታ ያግዙን
(እግዜር ቅዱስ ገብኤልን ጠራና‹‹ እስቲ ወንዶችን ጥራልኝ ››አለው ወንዶች ገቡ)
እግዜር - ሴቶቻችሁ ተማረዋል ተመካከሩና ከማርገዝ ፣ከማማጥ ወይም ከማጥባት አንዱን አግዟቸው
ወንዶች ተመካከሩ 9 ወር መሸከም ይደብራል ....ማጥባትማ የባሰ ነው ....ያው ቢያምም ምጥ ይሻለናል አጠር ያለ ሰአት አምጠን ወደድራፍት ቤት በቃ!! ወሰኑ!
እግዜር- ‹‹እንግዲህ ይህ ውሳኔ ከተወሰነበት ቀን ጀምሮ ሴቶች ያረግዛሉ ልክ ምጥ ሲጀምር ያስረገዘው ወንድ ያምጣል !በሰላም ሂዱ›› ብሎ ሸኛቸው !!
ከውሳኔው በኋላ የመጀመሪያዋ እርጉዝ በመንደሩ ስሟ የተጠራ ቆንጆ እና ሃብታም ወ/ሮ ሄለን ነበረች ባለቤቷ አቶ ዘሩ ጋር ያላቸው ፍቅር ሁሉን የሚያስቀና እግዜር ሁሉን ያሟላላቸው የተራበ የሚያበሉ የታረዘ የሚያለብሱ ወዘተ ነበሩ .....ይህን ደግነታቸውና ፍቅራቸው ነው የአዲሱ ህግ አስጀማሪ ያደረጋቸው ተብሎ በመንደሩ ተወራ...6..7..8...9 ወር ሞላት ወ/ሮ ሄለን ! ባለቤቷ አቶ ዘሩ ተዘጋጀ የህዝብ ጆሮ አይን አቶ ዘሩ ላይ ሆነ ወንድ ሲያምጥ ለማየት .....ቀኑ ገፋ ምጥ የለም !ልክ 9 ወር ከ9 ቀን ሆነ ምንም የለም! ....በቀጣዩ ቀን ማታ ይህን ተአምር ሊያይ ግቢውን የሞላው ሰው ሁሉ ግቢው በር ላይ ተንጫጫ... ምንድነው ብለው ቤት ውስጥ ያሉት ሲወጡ የነወይዘሮ ሄለንን ‹‹ ዘበኛ ምጥ እያጣደፈው ነበር !›› ያስረገዘው ወንድ ያምጥ አልነበር ውሳኔው ! አቶ ዘሩ እራሳቸውን ሳቱ!!
ሴቶችም ያኔውኑ ማታ ይሄ ውሳኔ ይነሳልን ሲሉ ወደግዜር ቀርበው ጮሁ የሚበዙት ቀናቸው የደረሰ ነፍሰ ጡር ሴቶች ነበሩ!
♡ ㅤ ㅤ ⌲ ✉️
ˡᶦᵏᵉ ˢʰᵃʳᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ
jᵒⁱⁿ⇝ @Lyrics_profile
