en
Feedback
Don Bosco Catholic High School (A.A)

Don Bosco Catholic High School (A.A)

Open in Telegram
6 271
Subscribers
-324 hours
-57 days
+10830 days
Posts Archive
ለ10ኛ ክፍል ተማሪዎችና ወላጆች በሙሉ የ11ክፍል የትምህርት ዘርፍ(Stream) እና የሙያ ትምህርት(CTE) ምርጫ እና የተማሪዎች ድልድል ነገ ቅዳሜ 27/2018ዓም እንደምናሳውቅ ገልፀን የነበረ ቢሆንም ትምህርት ቤቱ የ12ኛ ክፍል ፈተና መፈተኛ ማዕከል በመሆኑ ምክንያት እና ለተማሪዎች መግባት የማይፈቀድ በመሆኑ ለነገ ተይዞ የነበረው ፕሮግራም በቀጣይ ሳምንት ቅዳሜ ሃምሌ 04/2018ዓም ጠዋት 3:00 ሰዓት በማስታወቂያ ሰላዳ ላይ የምናሳውቅ መሆኑን እንገልፃለን። ት/ቤቱ

ውድ ተማሪዎች የመፈተኛ አይዲ እና ፋይዳ መታወቂያ እንዳይረሳ። ሊብሬቶ ይዛችሁ መምጣት አይጠበቅባችሁም።

ለ12ኛ ክፍልተማሪዎችና የተማሪ ወላጆች በሙሉ ከሰኔ 23 - 25/2018ዓም ለ3 ቀናት የተሰጠው የመጀመሪያ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና በሰላም የተጠናቀቀ በመሆኑ ተማሪዎችና ወላጆች እንኳን ደስ አላችሁ እያልን የ2ኛ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና ከነገ ሰኔ 26/2018ዓም ጀምሮ እስከ ማክሰኞ ሰኔ 30/2018ዓም ባሉት 3 የስራ ቀናት ለሚሰጠው ፈተና ት/ቤቱ በቂ ዝግጅት አድርጎ ተማሪዎቻችን ለመቀበል በጉጉት እየጠበቅን እንገኛለን። በመሆኑም ውድ ነገ ለተማሪዎች የመጀመሪያ ቀን እንደመሆኑ ተረጋግተው ፈተናውን መጀመር እንዲችሉ ጠዋት እስከ 1:30 ተጠቃለው መግባት እንዲችሉ ወላጆች ድጋፍ እንድታደርጉላቸው እናሳስባለን። ማሳሰቢያ 👉 ጥብቅ ፍተሻ የሚደረግ በመሆኑ ከታች የተጠቀሱት የተከለከሉ ቁሳቁሶችን ይዛችሁ እንዳትመጡ እናሳስባለን 1) ማንኛውንም አይነት ሰዓት እና ጌጣጌጥ(የጆሮ ጌጥ : የአንገት አብል የእጅ ጌጣጌጦች የመሳሰሉት) ይዞ መምጣት የተከለከለ ነው። 2) ከመደበኛ አይነት እስክብሪቶ ውጪ ያሉትን ይዞ መምጣት አይፈቀድም 3) ከመደበኛ ዩኒፎርም ውጪ ባለ አለባበስ የሚመጣ ተማሪ ወደ ት/ቤት ግቢ የማይገባ ይሆናል። 4) ማንኛውንም አይነት ኤሌክትሮኒክስ በጥብቅ የተከለከለ ነው። 5) ማንኛውንም አይነት ወረቀት ይዞ መምጣት አይፈቀድም። 6) የሃኪም ማዘዣ የሌለው መነፅር አይፈቅድም። ሆኖም ግን ማዘዣ ያለው ከሆነ ማዘዣውን በማሳየት መግባት ይቻላል።

Message from parent committees Dear Don Bosco Catholic High School Students,As you step into this important chapter of your academic journey, may your hard work, discipline, and determination shine through. The ESSLCE is not just an exam it’s a gateway to the future you’ve been preparing for. Trust in the knowledge you’ve gained, the guidance of your teachers, and the strength of your faith.Remember:Perseverance will carry you through challenges.Confidence will help you face each question with clarity.Faith will remind you that you are never alone in this journey.May success crown your efforts, and may you emerge from this exam season with joy, pride, and hope for the bright future ahead.With best wishes and prayers, go forward with courage and shine brightly! Don Bosco Parent Committee

ለ12ኛ ክፍል የተማሪ ወላጆች በሙሉ የተከበራችሁ ወላጆች ተማሪዎቻችን የጠዋቱን የእንግሊዘኛ ፈተና በጥሩ ሁኔታ አጠናቀው የከሰዓቱን የሂሳብ ፈተና በመፈተን ላይ የሚገኙ ሲሆን ከማዕከል ባጋጠመ የፈተና መቋረጥ ምክንያት 12: 00 ሰዓት ላይ ይጠናቀቅ የነበረው ፈተና ፈተናው የተቋረጠበት ሰዓት ተጨምሮ ፈተናው ከምሽቱ 1: 30 ላይ የሚጠናቀቅ መሆኑን እያሳወቅን ወላጆች በተገለፀው ሰዓት ት/ቤት ተገኝታችሁ ልጆቻችሁን መቀበል የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን። ት/ቤቱ

ለ12ኛ ክፍል የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በሙሉ ውድ ተማሪዎቻችን እንዴት ናችሁ 👉ነገ ሰኞ(ሰኔ 22/2018) ለተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የፈተና ኦረንቴሽን ስለሚሰጥ ከታች በተቀመጠው የሰዓት ፕሮግራም መሰረት ትምህርት ቤት ተገኝታችሁ ኦረንቴሽን እንድትወስዱ እናሳስባለን። 👉 1ኛ:- ሰኞ ጠዋት 1:30 ላይ የተፈጥሮ ሳይንስ /Natural / 1st Round ላይ የተመደባችሁ ተማሪዎች 👉2ኛ:- ሰኞ ከሰዓት 6:30 ላይ የተፈጥሮ ሳይንስ/Natural // 2nd Round የተመደባችሁ ተማሪዎች የፈተና ኦረንቴሽን የምትወስዱ ይሆናል 👉ማሳሰቢያ 1ኛ:- 2ኛ:- ሁላችሁም ተማሪዎች ኦረንቴሽ ላይ መገኘት  ይኖርባችኋል። 2ኛ:- ሁላችሁም ተማሪዎች የጠዋቱም ሆነ የከሰዓቱ ኦረንቴሽን ላይ መታወቂያና አድሚሽን ካርድ ይዞ መምጣት ይጠበቅባችኋል። 3ኛ:- ወደ ትምህርት ቤት መግባት የሚቻለው በመደበኛ ዩኒፎርም ብቻ ይሆናል። ከዩኒፎርም ውጪ የሆነ አለባበስ ወይም የባች ልብስ ለብሶ የሚመጣ ተማሪ ወደ ት/ቤት የማይገባና ኦረንቴሽን ላይ የማይሳተፍ ይሆናል። 4ኛ:- የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎች ኦረንቴሽን በሌላ ቀን የምትወስዱ ስለሆነ ነገ መምጣት አይጠበቅባችሁም። ት/ቤቱ

ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ የመለማመጃ ፈተና(Online mock exam) ነገ(ሃሙስ ሰኔ 18/2018ዓ.ም) እንደሚሰጥ ከትምህርት ቢሮ በተላከለን ፕሮግራም የተገለፀልን ስለሆነ ከታች በተቀመጠው ፕሮግራም መሰረት በሰዓቱ ት/ቤት በመገኘት የመለማመጃ ፈተናውን(mock exam) እንድትወስዱ እናሳስባለን። 👉  ጠዋት 2: 30 ላይ የተፈጥሮ ሳይንስ ዙር1(Round 1) 👉 ጠዋት 3:30 ላይ የተፈጥሮ ሳይንስ ዙር 2(Round 2)  👉 ከሰዓት በኋላ 7 :00 ላይ የማህበራዊ ሳይንስ ዙር 4(Round 4) 👉 ከሰዓት በኋላ 8 :00 ላይ የማህበራዊ ሳይንስ ዙር 5(Round 8) ** ውድ ተማሪዎች የተመደባችሁበትን ምድብ ነገ በት/ቤቱ የማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ ስለሚገለፅላችሁ 👉 ሁላችሁም የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ጠዋት 2: 00 ሰዓት ላይ ት/ቤት መገኘት ይጠበቅባችኋል ። 👉 ሁላችሁም የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ከሰዓት 7: 00 ሰዓት ላይ ት/ቤት መገኘት ይጠበቅባችኋል ። ** ከአለባበስ ጋር ተያይዞ በመደበኛ ዩኒፎርም ብቻ መሆኑን እያሳወቅን የባች ልብስ ለብሶ የሚመጣ ተማሪ ት/ቤት ግቢ የማይገባ መሆኑን እንገልፃለን። ** የመፈተኛ ካርድ(ID card) አይረሳ                       ት/ቤቱ

ለተማሪዎችና ለተማሪ ወላጆች በሙሉ ነገ ሰኞ ሰኔ 15/2018ዓም የ2018ዓም የ4ኛ ሩብ ዓመት የማጠቃለያ ፈተና ታርሞ ለተማሪዎች የሚመለስና ከ100% ያላቸውን ውጤት የሚገለፅላቸው መሆኑን እያሳወቅን ወላጆች ልጆቻችሁ በሰዓቱ ትምህርት ቤት ተገኝተው ውጤታቸውን እንዲወስድ እንድታደርጉ እናሳስባለን። ማሳሰቢያ 👉ነገ ትምህርት ቤት ተገኝቶ ውጤቱን ያልወሰደ(ያላየ) ተማሪ ከማርክ ጋር ተያይዞ ለሚነሳ ማንኛውንም ቅሬታ ኃላፊነቱን ተማሪው ወይም ወላጅ የሚወስድ መሆኑን እናሳውቃለን 👉 ተማሪዎች ት/ቤት ግቢ መግባት የሚችሉት ዩኒፎርም የለበሱ ብቻ መሆናቸውን እያሳወቅን ከዩኒፎርም ውጪ ለብሶ የሚመጣ ተማሪ ት/ቤቱ የማያስተናግድ መሆኑን ከወዲሁ እንገልፃለን። ት/ቤቱ

ለ10ኛ ክፍል ቸማሪዎችና ወላጆች በሙሉ ተማሪዎች ለ2019ዓም 11ኛ ክፍል የሚማሩትን የትምህርት ዘርፍ(Stream) እና የሙያ ትምህርት(CTE) ከወላጅ ጋር በመመካከር መምረጥ እንዲችሉ ነገ(ሰኞ) የመምረጫ ፎርም የምንልክ መሆኑን እያሳወቅን ሆኖም ግን ፎርሙን የምንሰጠው የ2018ዓም የት/ት ክፍያ ሙሉ ለሙሉ ከፍለው ላጠናቀቁ ተማሪዎች ብቻ መሆኑን አውቃችሁ ያለባችሁን ክፍያ በማጠናቀቅ ተማሪዎች ፎርሙን እንዲወስዱ እንድታደርጉ እናሳስባለን። ት/ቤቱ

ለተማሪዎች ወላጆች / አሳዳጊዎች በሙሉ   ጉዳዩ። የ2018 ዓ.ም የት/ት ክፍያን                በተመለከተ የ2018ዓ.ም የትምህርት አገልግሎት ክፍያ በተለያዩ ምክንያቶች ከፍላችሁ ያላጠናቀቃችሁ ወላጆች/አሳዳጊዎች የዓመቱ የት/ት ጊዜ የተጠናቀቀ ስለሆነ ወርሃዊ እና ውዝፍ ክፍያችሁን ነገ ሰኞ ሰኔ 15/2018ዓ.ም ከፍላችሁ እንድታጠናቅቁ በጥብቅ እያሳሰብን ይህ ተፈጻሚ ካልሆነ ግን ት/ቤቱ የተማሪዎችን ውጤት የሚይዝ ከመሆኑም ባሻገር በቀጣይ የተማሪው በት/ቤት ቆይታ ላይ  ጥብቅ ውሳኔን የሚያስተላልፍ መሆኑን ከወዲሁ እናሳውቃለን ።                     ት/ቤቱ

ከ9 እስከ 11ኛ ክፍል ያላችሁ ተማሪዎችና የተማሪ ወላጆች በሙሉ ከነገ ሰኔ 09 - ዓርብ ሰኔ 12/2018ዓም ድረስ የማጠቃለያ ፈተና እንደሚሰጥ በወጣው የፈተና ፕሮግራም መግለፃችን ይታወቃል። ስለሆነም ተማሪዎች የፈተና ውጤታቸው ማሻሻል እንዲችሉ ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ ወላጆች ክትትልና ድጋፍ እንድታደርጉላቸው እያሳሰብን ከፈተና አፈታተን ጋር ተያይዞ ተማሪዎች ከታች የተቀመጡትን ተግባራዊ እንዲያደርጉ ወላጆች ክትትል እንድታደርጉ እናሳስባለን። 1. ማንኛውንም አይነት ሰዓት አድርጎ ት/ቤት መምጣት የተከለከለ ነው። 2. ሞባይል ስልክ በምንም አይነት ምክንያት ት/ቤት ይዞ መምጣት በጥብቅ የተከለከለ ነው 3. ካልኩሌተር ወይም ማንኛውንም አይነት አዲንግ ማሽን ይዞ መምጣት የተከለከለ ነው። 4. ጃኬት ወይም ሹራብ ተከናንቦ ወይም ደርቦ እንዲሁም ማስክ አድርጎ ፈተና ክፍል ውስጥ መግባት የተከለከለ ነው 5.ማንኛውንም አይነት አጫጫር ማስታወሻዎች(አጠሪራ) ይዞ ፈተና ክፍል መግባት በጥብቅ የተከለከለ ነው 👉የተከበራችሁ ወላጆች ከላይ የተከለከሉትን ተግባራት ተማሪዎች ከቤት ይዘው እንዳይወጡ ክትትል በማድረግ ከኩረጃ ነፃ የሆነ ፈተና ተማሪዎች መፈተን እንዲችሉ የበኩላችሁን አስተዋፅዖ እንድታደርጉ እንጠይቃለን። ት/ቤቱ

+1
Grade_11_History_note_AMERICA_WAR_INDEPENDENCE_French_Revolution.pptx5.18 MB

Grade 11 CHS 2018 Summary module 6 and 7.pdf1.41 MB

+1
Grade_11_Agriculture_note_Introduction_to_Human_Nutrition_unit_15.pptx1.22 MB