6 269
Subscribers
-324 hours
-57 days
+10830 days
Posts Archive
የክላስተር የማጠናከሪያ ትምህርት ላይ የምትሳተፉ ተማሪዎች ሰኞ የመጨረሻ ቀን መሆኑን እያሳወቅን ያልከፈላችሁ ተማሪዎች 1000ብር በክላስተር የመክፈያ አካውንት በመክፈል የከፈላችሁበትን የባንክ ደረሰኝ ሪከርድ ኦፊስ እንድታስመዘግቡ እናሳስባለን።
ለ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች
እስከአሁን ለክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት ያልተመዘገባችሁ እና ትምህርት ያልጀመራችሁ ተማሪዎች ሰኞ ሃምሌ 20/2018ዓም የመጨረሻ
መመዝገቢያ ቀን መሆኑን እናሳውቃለን።
ማሳሰቢያ
👉 የክረምት ማጠናከሪያ ላይ የማይሳተፉ ተማሪዎች የ2019ዓም መደበኛ ትምህርት ምዝገባ ላይ የማናስተናግዳቸው መሆኑን ከወዲሁ እናሳውቃለን።
ት/ቤቱ
ለ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎችና የተማሪ ወላጆች በሙሉ
የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል የክረምት የማጠናከሪያ ትምህርት ተማሪዎች በሁለት ዘርፍ:-
👉 Cluster base(ቶፕ 25) ተማሪዎች እና
👉 School base(ከ25ኛ በላይ የክፍል ደረጃ ያላቸው) ተማሪዎች እንዲሳተፉ ከት/ቢሮ መመሪያ የተላለፈ መሆኑን እያሳወቅን እስካሁን ያልተመዘገባችሁና ትምህርት ያልጀመራችሁ ተማሪዎች ጥብቅ የአቴንዳንስ ቁጥጥር የምናደርግ በመሆኑ ነገ አርብ ሃምሌ 17/2018ዓ.ም ምዝገባ እንድታከናውኑ እና የማጠናከሪያ ትምህርቱ ላይ እንድትሳተፉ በጥብቅ እናሳስባለን።
👉 የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት የማይሳተፉ ተማሪዎች የመደበኛ ትምህርት ላይ ምዝገባ የማናከናውን መሆኑን ከወዲሁ እናሳውቃለን።
ት/ቤቱ
የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል የክላስተር ማጠናከሪያ ትምህርት የምትሳተፉ ተማሪዎች እስከ ነገ(ዓርብ) ብቻ 1000ብር በክላስተር የመክፈያ አካውንት በመክፈል የከፈላችሁበትን የባንክ ደረሰኝ ሪከርድ ኦፊስ በማስገባት እንድታስመዘግቡ በጥብቅ እናሳስባለን።
የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት ያልተመዘገባችሁ ተማሪዎች ነገ አርብ ሃምሌ 17/2018ዓም ምዝገባ የሚጠናቀቅ ስለሆነ ተመዝባችሁ የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት ላይ እንድትሳተፉ እናሳስባለን።
ውድ ተማሪዎችና ወላጆች የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት ላይ ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያሉ ሁሉም ተማሪዎች እንዲሳተፉ ከት/ቢሮ መመሪያ የተላለፈ መሆኑን እያሳወቅን ከላይ በማስታወቂያ በተገለፀው መሰረት ምዝገባ እንድታከናውኑ በጥብቅ እናሳስባለን።
ት/ቤቱ
ለ11ኛ እና 12ኛ ክፍል የክላስተር የማጠናከሪያ ትምህርት ተከታታይ ተማሪዎች በሙሉ
ዛሬ የመጀመሪያ ቀን የክረምት የማጠናከሪያ ትምህርት በተገኙ ተማሪዎች በጥሩ ሁኔታ የተካሄደ ሲሆን የትምህርት ቢሮ አቅጣጫ ብሎም የትምህርት ቤቱን ስርዓት አክብረው ሊዛ ትም/ት ቤት ተገኝተው የተከታተሉ ተማሪዎቻችንን እያመሰገንን የተላለፈውን መልዕክት ችላ በማለት ያለተገኙ ተማሪዎች ላይ ከት/ጽ/ቤት በሚተላለፍልን ህግ መሰረት እርምጃ የምንወስድ መሆናችንን እያሳወቅን ነገ 2:ዐዐ ሰዓት ላይ በሊዛ ትምህርት ቤት ተገኝታችሁ የማጠናከሪያ ትምህርቱን እንድትከታተሉ በጥብቅ እናሳስባለን።
ት/ቤቱ
ለ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ቶፕ 25 ተማሪዎች በሙሉ
ነገ ሃምሌ 06/2018ዓም የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል የክረም ማጠናከሪያ ትምህርት(Summer cump tutorial class) የሚጀምር ስለሆነ የክፍል ደረጃችሁ ወይም አማካይ ውጤታችሁ ከታች በተገለፀው መሰረት ነገ(ሰኞ) ሊዛ ትምህርት ቤት 2:00ሰዓት ላይ እንድትገኙ እናሳስባለን።
👉 12ኛ ክፍል በየ ክፍላችሁ ከ1ኛ - 25ኛ ደረጃ የወጣችሁ ተማሪዎች በሙሉ
👉 11ኛ ክፍል በተመደባችሁበት የትምህርት ዘርፍ(stream) ሆኖ
** የማህበራዊ ሳይንስ የተመደባችሁ የክፍል አማካይ ውጤታችሁ 71.4 እና ከዚያ በላይ የሆናችሁ ተማሪዎች
** የተፈጥሮ ሳይንስ የተመደባችሁ የክፍል አማካይ ውጤታችሁ 83.5 እና ከዚያ በላይ የሆናችሁ ተማሪዎች ሁላችሁም የክላስተር ተሳታፊ መሆናችሁን አውቃችሁ ነገ በተጠቀሰው ሰዓት ሊዛ ትምህርት ቤት ተገኝታችሁ የማጠናከሪያ ትምህርት እንድትከታተሉ እናሳስባለን።
ማሳሰቢያ
👉 ትምህርት የሚሰጠው ለግማሽ ቀን እስከ 6:30 ይሆናል።
👉 ጥብቅ የአቴንዳንስ ክትትል የሚደረግ ስለሆነ ሁላችሁም እንድትገኙ እናሳስባለን።
👉 ፀጉርና ዩኒፎርም በት/ቤቱ ደንብ መሰረት መሆን አለበት።
👉 ለአንድ ሳምንት በተመሳሳይ ሊዛ ትምህርት ቤት የሚቀጥል ይሆናል።
👉 ከክፍያና ምዝገባ ጋር ተያይዞ በቀጣይ ወደ ዶን ቦስኮ ስትመለሱ የምናሳውቃችሁ ይሆናል።
👉 ሰዓት ይከበር!!!
ት/ቤቱ
ለ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎችና የተማሪ ወላጆች በሙሉ
ከሰኔ 23 - 30/2018ዓም በሁለት ዙር የተሰጠው የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና በሰላም የተጠናቀቀ በመሆኑ ተማሪዎችና ወላጆች እንኳን ደስ አላችሁ እያልን የ4ኛ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ፈተና ከነገ ሰኞ ሃምሌ 06/2018ዓም ጀምሮ እስከ ረቡዕ ሃምሌ 08 /2018ዓም ድረስ ለ3 ቀናት ለሚሰጠው ፈተና ት/ቤቱ በቂ ዝግጅት አድርጎ ተማሪዎቻችን ለመቀበል በጉጉት እየጠበቅን እንገኛለን። በመሆኑም ነገ ለተማሪዎች የመጀመሪያ ቀን እንደመሆኑ ተረጋግተው ፈተናውን መጀመር እንዲችሉ ጠዋት እስከ 1:30 ባለው ሰዓት ተጠቃለው መግባት እንዲችሉ ወላጆች ድጋፍ እንድታደርጉላቸው እናሳስባለን።
ማሳሰቢያ
👉 ጥብቅ ፍተሻ የሚደረግ በመሆኑ ከታች የተጠቀሱት የተከለከሉ ቁሳቁሶችን ይዛችሁ እንዳትመጡ እናሳስባለን።
1ኛ) ማንኛውንም አይነት ሰዓት እና ጌጣጌጥ(የጆሮ ጌጥ : የአንገት አብል የእጅ ጌጣጌጦች የመሳሰሉት) ይዞ መምጣት የተከለከለ ነው።
2ኛ) ከመደበኛ አይነት እስክብሪቶ ውጪ ያሉትን ይዞ መምጣት አይፈቀድም
3ኛ) ከመደበኛ ዩኒፎርም ውጪ ባለ አለባበስ የሚመጣ ተማሪ ወደ ት/ቤት ግቢ የማይገባ ይሆናል።
4ኛ) ከፀጉር ጋር ተያይዞ በር ላይ ጥብቅ ቁጥጥር የምናደርግ በመሆኑ ከት/ደንብ ውጪ ፀጉር አሳድጎ ወይም ተቆርጦ ለሚመጣ ተማሪ ከፈተና ክፍል አቀማመጥ አንስቶ ሌሎች አስተዳደራዊ እርምጃ የምንወስድ በመሆኑ ውድ ተማሪዎቻችን በት/ቤቱ ደንብና ስርዓት እንድትመጡ እናሳስባለን።
5ኛ) ማንኛውንም አይነት ኤሌክትሮኒክስ ይዞ መምጣት በጥብቅ የተከለከለ ነው።
6ኛ) ማንኛውንም አይነት ወረቀት ይዞ መምጣት አይፈቀድም።
7ኛ) የሃኪም ማዘዣ የሌለው መነፅር አይፈቅድም። ሆኖም ግን ማዘዣ ያለው ከሆነ ማዘዣውን በማሳየት መግባት ይቻላል።
👉 የተፈቀዱ
1ኛ) ምሳ ይዞ መምጣት የተፈቀደ ሲሆን ሆኖም ግን በር በሚዘጋጅላችሁ የምሳ እቃ ማስቀመጫ ካርቶን ውስጥ ማስቀመጥ እና በምሳ ሰዓት ወስዳችሁ በጀርባ በር የወጣቶች ማዕከል አዳራሽ መመገብ የምትችሉ ይሆናል።
2ኛ)እንደ አየሩ ነባራዊ ሁኔታ ተማሪዎች ሹራብ እና ጃኬት ለብሰው መምጣት የሚችሉ ሲሆን ሆኖም ግን በር ላይ በሚዘጋጅላቸው ካርቶን ውስጥ ማስቀመጥ ይጠበቅባቸዋል።ወደ ውስጥ ግን ለብሶ መግባት አይቻልም።
ት/ቤቱ
ከ9ኛ እስከ 11ኛ ክፍል ተማሪዎችና ወላጆች በሙሉ
ውድ ተማሪዎችና ወላጆች ነገ(ቅዳሜ) የተማሪዎች ሪፖርት ካርድ የምንሰጠው ለወላጆች ብቻ መሆኑን እያሳወቅን ወላጆች ነገ 3:00ሰዓት ላይ በወጣቶች ማዕከል አዳራሽ በሰዓቱ እንድትገኙ እናሳስባለን።
ማሳሰቢያ
👉 ት/ቤቱ የፈተና ጣቢያ ስለሆነ ከነገ ውጪ የተማሪ ሪፖርት ካርድ ጥያቄ የማናስተናግድ ይሆናል።
👉 የ2019ዓም ምዝገባ የሚካሄደው በሪፖርት ካርድ መሆኑን ከወዲሁ እናሳውቃለን
👉 ነገ ሪፖርት ካርድ የምንሰጠው የት/ቤት ክፍያ ላጠናቀቁ ብቻ ይሆናል።
👉የ2019ዓም የ11ኛ ክፍል የትምህርት ዘርፍ ምርጫ ነገ በማስታወቂያ ሰሌዳ የምናሳውቅ ይሆናል
ት/ቤቱ
ለ12ኛ ክፍል ማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በሙሉ
ውድ ተማሪዎች ነገ(ዓርብ) 3:00 ላይ በፈተና አሰጣጥ ሂደት ላይ ኦረንቴሽን ስለሚሰጥ በተጠቀሰው ሰዓት ት/ቤት እንድትገኙ እናሳስባለን።
ማሳሰቢያ
* ኦረንቴንሽን ላይ መገኘት ግዴታ ነው
* ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት መግባት የሚችሉት በመደበኛ ዩኒፎርም ብቻ ይሆናል።
* የባች ልብስ ለብሶ የሚመጣ ተማሪ ወደ ትምህርት ቤት ግቢ የማይገባ ይሆናል
* ወንዶች ፀጉር በመደበኛ የትምህርት ቤቱ ደንብ ብቻ ተቆርጠው የሚመጡ ተማሪዎች ብቻ የሚስተናገዱ ይሆናል።
* ሊብሬቶ መያዝ አይጠበቅባችሁም ሆኖም ግን የፋይዳ መታወቂያና የመፈተኛ አይዲ ካርድ መረሳት የለበትም።
ት/ቤቱ
የ2018ዓም የት/ቤት ክፍያ ያላጠናቀቃችሁ የተማሪ ወላጆች በሙሉ
የ2018ዓም የተማሪዎች ሪፖርት ካርድ ለወላጅ የሚሰጠው ቅዳሜ ሃምሌ 04/2018ዓም መሆኑ ይታወቃል። ስለሆነም የትምህርት አገልግሎት ክፍያ ከፍላችሁ ያላጠናቀቃችሁ ወላጆ ነገ ረቡዕ ሃምሌ 01 እና ሃሙስ ሃምሌ 02/2018ዓም ከፍላችሁ እንድታጠናቅቁ እያሳስብን አርብ ክፍያ ያላጠናቀቁ ተማሪዎች ሪፖርት ካርድ የመለየት ስራ የምንሰራ እና ቅዳሜ ሪፖርት ካርዱን የምንይዝ(የማንሰጥ) መሆኑን እያሳወቅን ማንኛውንም ክፍያ ያላጠናቀቃችሁ በአፋጣኝ(ከላይ በተጠቀሱት ቀናት ብቻ) ከፍላችሁ እንድታጠናቅቁ በጥብቅ እናሳስባለን።
ማሳሰቢያ
👉ክፍያ ላላጠናቀቁ ተማሪዎች ካርድ የማንሰጥ መሆኑን እያሳወቅን ሪፖርት ካርድ ባለመውሰዳችሁ ከምዝገባ ጋር ለሚፈጠር ማንኛውም ችግር ኃላፊነቱን ወላጅ የሚወስድ መሆኑን እናሳውቃለን።
ት/ቤቱ
