en
Feedback
Don Bosco Catholic High School (A.A)

Don Bosco Catholic High School (A.A)

Open in Telegram
6 269
Subscribers
-324 hours
-57 days
+10830 days
Posts Archive
እንኳን ደስአላችሁ!!! የ2018ዓም የ12ኛ ክፍል ከፍተኛ ውጤት 576 ዳግማዊ መርሻ ሆኖ ተመዝግቧል። ውድ ተማሪያችን ባስመዘገብከው እጅግ ከፍተኛ ውጤት ኮርተንብሃል።
እንኳን ደስአላችሁ!!! የ2018ዓም የ12ኛ ክፍል ከፍተኛ ውጤት 576 ዳግማዊ መርሻ ሆኖ ተመዝግቧል። ውድ ተማሪያችን ባስመዘገብከው እጅግ ከፍተኛ ውጤት ኮርተንብሃል።

የ12ኛ ክፍል ውጤት ስለተለቀቀ ከአሁን ሰዓት ጀምሮ በዚህ ሊንክ እየገባችሁ ማየት ትችላላችሁ

ለ12ኛ ክፍል ተመራቂ ተማሪዎች የGraduation ክፍያ ያላጠናቀቃችሁ ተማሪዎች እስከ ሰኞ ነሐሴ 18/2018ዓም ድረስ እንድታጠናቅቁ በጥብቅ እናሳስባለን።

ውድ ተመራቂ ተማሪዎች ከላይ ከተጠቀሰው ጉርድ ፎቶ ግራፍ በተጨማሪ ለCTE ትራንስክሪፕት እና ዲፕሎማ ሁለት ጉርድ ፎቶ ግራፍ ይዛችሁ እንድትመጡ እናሳስባለን።

የ2019ዓም መደበኛ ምዝገባ ያላጠናቀቃችሁ ተማሪዎችና ወላጆች ት/ቤቱ ባወጣው የመደበኛ ምዝገባ ፕሮግራም መሰረት 97% የሚሆኑት ተማሪዎቻችን የተመዘገቡ መሆኑን ከመረጃ ክፍል ማረጋገጥ ችለናል። በመሆኑ በምዝገባ ፕሮግራሙ መሰረት የተመዘገባችሁ ተማሪዎቻችን(ወላጆች) ኃላፊነታችሁን በአግባቡ ስለተወጣችሁ እያመሰገንን በተለያየ ምክንያት ያልተመዘገባችሁ ወይም ክፍያ ከፍላችሁ ትምህርት ቤት ቀርባችሁ ያላስመዘገባችሁ ተማሪዎች(ወላጆች) እስከ ነገ(ዓርብ 14/12/2018ዓም) ድረስ ብቻ ምዝገባ እንድታጠናቅቁ እናሳስባለን። ት/ቤቱ

የ2019ዓም የመደበኛ ትምህርት ምዝገባ ላላጠናቀቃችሁ ተማሪዎችና የተማሪ ወላጆች የ2019ዓም መደበኛ ትምህርት ምዝገባ ያላጠናቀቃችሁ ተማሪዎች(ወላጆች) ነገ ማክሰኞ(11/12/2018) የመጨረሻ ምዝገባ የሚካሄድበት ቀን መሆኑን እያሳወቅን የመመዝገቢያና የመስከረም ወር ክፍያ በ2018ዓም የመክፈያ ኮድ ክፍያ በመፈፀም የከፈላችሁበትን የባንክ ስሊፕ በመያዝ የትምህርት ቤቱ ካሸር ጋር በመቅረብ እንድትመዘገቡ እናሳስባለን። ት/ቤቱ

የ2018ዓም 12ኛ ክፍል ለተፈተናችሁ ተማሪዎች በሙሉ ውድ ተማሪዎች ለክሊራንስ ስትመጡ ለGraduation የከፈላችሁበትን ደረሰኝ ይዛችሁ እንድትመጡ እናሳስባለን። ት/ቤቱ

ለተማሪዎች እና ለተማሪ ወላጆች በሙሉ የ2019ዓም የመደበኛ ትምህርት ምዝገባ ይመለከታል ከነገ ነሐሴ 4  2019 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ማክሰኞ 12/2018ዓም ድረስ የሚካሄደውን የቀጣይ ዓመት  የመደበኛ ተማሪዎች የመመዝገቢያ ቀንና የአመዘጋገብ ሂደቱን በተመለከተ በማስታወቂያ መግለፃችን ይታወቃል። በዚህም መሠረት  ክፍያውን ከዚህ በፊት በተላከላችሁና እየተጠቀማችሁበት ባለው የባንክ የመክፈያ ኮድ ከከፈላችሁ በኋላ በት/ቤቱ የሂሳብ ክፍል በአካል በመገኘት መከፈሉን በማረጋገጥ መመዝገብ ይኖርባችኋል :: ጥብቅ ማሳሰቢያ 1ኛ) ወላጆች ክፍያውን  በኮዱ መሠረት መክፈላቸውን  በት/ቤቱ የሂሳብ ክፍል ተገኝተው ካልተመዘገቡ ተማሪዎች እንዳልከፈሉ ተቆጥሮ   ለ 2019 ዓ.ም በሚደረገው የክፍል ደልድል ዉስጥ የማይካተቱ ይሆናል:: 2ኛ) የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች በ 2018 ዓ.ም የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት ላይ የማይሳተፉ ተማሪዎች መመዝገብ የማይችሉና ለ 2019 ዓ.ም በሚደረገው የክፍል ደልድል ዉስጥ የማይካተቱ በመሆኑ ወላጆች ክፍያ ከመፈፀማችሁ በፊት ቤሮ ቀርባችሁ ሪፖርት እንድታደርጉ በጥብቅ እናሳውቃለን። 3ኛ) ወላጆች ወይም ተማሪዎች ወደ ት/ቤት ለማስመዝገብ ሲመጡ የተማሪውን/ዋን የ2018 ዓ.ም ካርድ መያዝ ይኖርባቸዋል :: ካርድ ይዘው ካልተገኙ የምዝገባ ሂደቱን ማከናወን የማይቻል መሆኑን እናሳውቃለን። ት/ቤቱ

የክላስተር የማጠናከሪያ ትምህርት ላይ የምትሳተፉ ተማሪዎች   ክፍያ ነገ (ዓርብ) የመጨረሻ ቀን መሆኑን እያሳወቅን ከነገ ውጪ ለሚመጡ ተማሪዎች ከክላስተር የሚወጡና ወደ School base በቅጣት ክፍያ የሚገቡ መሆኑን በጥብቅ እናሳስባለን