6 269
Subscribers
-324 hours
-57 days
+10830 days
Posts Archive
ማስታወቂያ
የ2018 ዓ.ም. የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ በመደበኛው የትምህርት መርሃ ግብር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ውጤት ላስመዘገባችሁ ተማሪዎች በሙሉ፡-
Ø የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና የትምህርት መስክ ምርጫችሁን ከነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ከታች የተቀመጠውን ማስፈንጠሪያ (Link) በመጠቀም ምርጫችሁን ት/ቤት መሄድ ሳይጠበቅባችሁ ባላችሁበት ቦታ እራሳችሁ በመሙላት እንድታሳውቁ እንገልጻለን።
Ø ማስፈንጠሪያ (Link) https://student.ethernet.edu.et/
ማሳሰቢያ፡-
v የህክምና፣ የአካል ጉዳተኝነት፣ ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መንትያዎች እና ከ6 ወር በታች ህፃን የሚያጠቡ እናቶች አስፈላጊውን ሕጋዊ ማስረጃ ማያያዝ ይኖርባችኋል።
የትምህርት ሚኒስቴር
ውድ ተመራቁ ተማሪዎቻችን የምርቃት ጋወን ዛሬ እስከ ረፋድ 5:ዐዐ ድረስ እንድትመልሱ በጥብቅ እናሳስባለን።
ለ11ኛ እና 12ኛ ክፍል የክላስተር ማጠናከሪያ ትምህርት ለምትከታተሉ ተማሪዎች በሙሉ
ውድ ተማሪዎቻችን የ2018ዓም የክረምት ክላስተር የማጠናከሪያ ትምህርት ነገ ዓርብ (22/12/2018ዓም) ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ የማጠቃለያ እና ለተሳተፉ ተማሪዎች የሰርተፊኬት ሽልማት መርሃ- ግብር የሚካሄድ መሆኑን መሆኑን እያሳወቅን ሁላችሁም ተሳታፊ ተማሪዎች በሰዓቱ ት/ቤት እንድትገኙ እናሳስባለን።
ውድ ተማሪዎች ለባነር ፎቶ ለመውሰድ ከላይ ከተገለፀው በተጨማሪ ከ450 በላይ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች ነገ(እንድትገኙ) እናሳስባለን።
ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች
ከ475 በላይ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች ለባነር ፎቶ ስለምንወስድ ነገ(ዓርብ) 3:00 ሰዓት ላይ ት/ቤት እንድትገኙልን እናሳስባለን።
