Katbare pro ቃጥባሬ ፕሮ
Open in Telegram
አሰላሙዐለይኩም ወራሕመቱላሂ ወበረካቱሁ ይህ የማዲህ Tewfik Selahudin የቴሌግራም ቻናል ነው :: https://t.me/tewfikalinaya ለአስተያየት ወይም ለጥያቄ @Tewfiqselahadin መሃባው ጮሌ ነው ሀድራ መገስገሻ ፤ መሃባው ታጅም ነው የስንቱ መንገሻ ፤ መሃባው መደድ ነው የአላህ መለገሻ ፤ 🍀🍀🍀🍀🍀
Show more212
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
+230 days
Posts Archive
ከሞት በላይ የሆነ ፍቅር…
በአንድ ወቅት የነቢዩ ﷺ ሶሓቦች ወደ አንድ አካባቢ ለዳዕዋ ተልከው ነበር። ነገር ግን ከሃዲያን በመንገድ አጥምደው ያዙአቸው። በግፍ የገደሉትን ገድለው የተወሰኑትን ወደ መካ በእስር አመጧቸው።
ከእነርሱም መካከል ዘይድ ኢብኑ ደሲናህ [ረዲየላሁ ዐንሁ] ነበሩ። ወደ መካ ወስደው ለሶፍዋን ኢብኑ ኡመያህ ሸጧቸው። ሶፍዋንም ዘይድን የአባቱን ሞት ለመበቀል ሊገድላቸው አሰበ።…
የግድያው ቀን ደረሰ። ዘይድ [ረዲየላሁ ዐንሁ] ከሞት ጋር ፊት ለፊት ቆሙ።…
በዚያን ጊዜ አቡ ሱፍያን ወደ እርሳቸው ቀርቦ እንዲህ አላቸው፦
«ዘይድ ሆይ! ሙሐመድ [ﷺ] አሁን በአንተ ቦታ ቢሆንና አንተ በቤተሰቦችህ መካከል ብትሆን፣ ሙሐመድ [ﷺ] ላንተ ቤዛ እንዲገደሉ ትመኛለህ?»
ዘይድ [ረዲየላሁ ዐንሁ] ምንም ሳያመነቱ መለሱ፦
«በአላህ እምላለሁ! ሙሐመድ [ﷺ] አሁን ባሉበት ቦታ እሾህ እንኳን እንዲወጋቸው፣ እኔ ግን በቤተሰቦቼ መካከል በሰላም እንድሆን አልወድም!»
ሱብሐነላህ!
እኔ ድኜ ቤተሰቦቼ ጋር ለመመለስ እርሳቸው በዚያ ፈንታ አይደለም መገደል እሾህ እንዲወጋቸው እንኳን አልሻም አሉ!…
አቡ ሱፍያን በዚህ መልስ በጣም ተደንቀው እንዲህ አሉ: ‐
«የሙሐመድ [ﷺ] ሶሓቦች ለሙሐመድ [ﷺ] ያላቸውን ፍቅር ያህል አንድ ሰው ሌላን ሰው ሲወድ አላየሁም!»
:
ተመልከቱ!
የዘይድ ንግግር የአንድ ሰው የመጨረሻ ቃል ብቻ አልነበረም። ሶሐቦች ለነቢዩ [ﷺ] የነበራቸውን የማይነጥፍ ፍቅር የሚመሰክር ቃል ነበር።
ከዚያም ዘይድ [ረዲየላሁ ዐንሁ] ተገደሉ። ሰውነታቸው ወደ አፈር ተመለሰ፤ ነገር ግን ታሪካቸው በየዘመኑ የሚመነዘር የአፍቃሪዎች ፈለግ ሆነ።
ፍቅር ማለት የአንደበት ጨዋታ አይደለም። በመስዋዕትነትና በታማኝነት የሚረጋገጥ ተመን አልባ እንቁ ነው።
ዘይድ [ረዲየላሁ ዐንሁ] ለራሳቸው ሕይወት ሲሉ የነቢዩ [ﷺ] ሕይወት እንዲጎዳ ማሰብ እንኳን አልፈለጉም። እሾህ እንዲወጋቸው ማሰብ እንኳን ልባቸው አልፈቀዱም!
ረዲየላሁ ዐንሁ ወዐን አስሓቢ ነቢይ [ﷺ]
:
አላህ የሰይዳችንን ፍቅር በልባችን ያኑርልን! ሱናቸውን ይርዘቀን! ከባንዲራቸው ስር ይቀስቅሰን! በእጃቸው ሐውዷቸውን ያጠጣን!
አሚን!
አንድ ሰው ወደ ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) ዘንድ በመምጣት ይምከሩኝ አላቸው። እንዲህ አሉት፦
أُوصيكَ أن تَستَحيَ مِنَ اللهِ تعالى، كما تَستَحي مِن الرَّجلِ الصّالِحِ مِن قومِكَ
“ልክ ከህዝቦችህ ውስጥ ጥሩ የሚባልን ሰው ሐያዓ እንደምታደርገው (እንደምታከብረው) የላቀውን አላህንም ሐያዓ እንድታደርገው (በድብቅም በግልፅም ትዕዛዙንና ክልከላውን እንድታከብር) እመክርሃለው።”
📚 ሶሂህ አልጃሚ፡ 2541
*እውነትን መቀበል የእውቀት ከፍታ ነው!*
ኢብኑ ሐዝም [ረሒመሁላህ] እንዲህ ይላሉ፦
«ከጓደኞቻችን አንዱ ጋር በአንድ ጉዳይ ላይ ተከራከርኩ። በንግግሩ [በምላሱ] ላይ የነበረበትን ጉድለት ተጠቅሜ በክርክሩ አሸነፍኩት። ስብሰባችንም እኔ ትክክል እንደሆንኩ በሚመስል ሁኔታ ተጠናቀቀ።
ወደ ቤቴ ከገባሁ በኋላ ግን ስለዚያ ጉዳይ አንድ ነገር በልቤ ውስጥ ጥርጣሬ አሳደረ። ስለዚህ በአንዳንድ መጻሕፍት ውስጥ እውነቱን መፈለግ ጀመርኩ። በመጨረሻም የእኔ አቋም ስህተት መሆኑንና የተከራከርኩት ሰው አቋም ትክክል መሆኑን የሚያረጋግጥ ጠንካራ ማስረጃ አገኘሁ።
በዚያ ስብሰባ ላይ ከእኛ ጋር የነበረ አንዱ ጓደኛችን ነበር። ያገኘሁትን ማስረጃ ነገርኩት። ከዚያም በመጽሐፉ ውስጥ ማስረጃው ያለበትን ቦታ ምልክት ሳደርግ አየኝና፦
‘ምን ልታደርግ ነው?’ አለኝ።
እኔም፦
‘ይህንን መጽሐፍ ይዤ ወደ ተከራከርኩት ሰው ሄጄ፣ እርሱ ትክክል እንደሆነና እኔ ግን ተሳስቼ እንደነበር እነግረዋለሁ። እንዲሁም ወደ እርሱ አቋም እንደተመለስኩ እነግረዋለሁ’ አልኩት።
እርሱም በዚህ ነገር በጣም ተደነቀና፦
‘እንዲህ ለማድረግ ነፍስህ ትፈቅዳለችን?!’ አለኝ።
እኔም፦
‘አዎን። አሁኑኑ ሄጄ ማድረግ ብችል ኖሮ፣ እስከ ነገ እንኳን አላዘገየውም ነበር’ አልኩት።»
🔹 ከዚያም ኢብኑ ሐዝም [ረሒመሁላህ] እንዲህ አሉ፦
«እንደዚህ ያለ ተግባር የሚያስገኝልህ እጅግ የሚያምር መልካም ዝና እንደሆነ እወቅ። ከዚህም ጋር ወደር የለሽ የሆነውን ፍትሐዊነት ትላበሳለህ።
ዓላማህ ግን የተሸነፍከው አንተ ሆነህ ሳለ፣ ራስህን ‘እኔ አሸንፌያለሁ’ ብለህ ለማሳመን፣ ወይም በአንተ የሚያምኑና ፍርድህን በቀላሉ የሚቀበሉ ሰዎችን ‘እርሱ አሸንፏል’ ብለው እንዲያስቡ ማድረግ አይሁን! እንዲህ ካደረግህ እጅግ ዝቅተኛ፣ የተናቀ፣ ሞኝና የወደቀ ምኞት ያለው ሰው ትሆናለህ!»»
🌱 ትልቁ ድል ተቃዋሚን ማሸነፍ ሳይሆን፣ እውነት በተገለጠ ጊዜ ለእውነት መገዛት ነው።
📚 ረሳኢል ኢብኑ ሐዝም
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
السَّاعِي عَلَى الْأَرْمَلَةِ وَالْمِسْكِينِ كَالْمُجَاهِدِ فِي سَبِيلِ اللَّهِ، أَوِ الْقَائِمِ اللَّيْلَ الصَّائِمِ النَّهَارَ
“የምስኪንን ጉዳይ ለመሙላት የሚሯሯጥ ሰው፤ በአላህ መንገድ ላይ እንደሚታገል (ሙጃሂድ) ነው። ወይም ደግሞ ሌሊት በሰላት እንደሚቆምና ቀን በፆም እንደሚያሳልፍ ነው።” 📚 ቡኻሪ ዘግበውታል: 5353
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
﴿إذا سَبَّكَ رجلٌ بِما يَعلَمُ مِنكَ، فلا تَسُبَّهُ بِما تَعلَمُ مِنهُ، فيَكونُ أجرُ ذلكَ لكَ ووبالُهُ عليهِ﴾
“ሰውዬው አንተ በማታውቀው ጉዳይ ከሰደበህ (ከወነጀለህ)፤ አንተ መልስህ ባላወከው ነገር ላይ አትስደበው (አትወንጅለው)። በተወነጀልክበት ነገር ላንተ ምንዳ ሲኖርህ ውንጀላው ደግሞ ወደራሱ ይሆናል።”
📚 ሶሂህ አልጃሚ: 594
መውሊድ ሙባረክ😍
ኣሚና ቢንት ወህብ የአላህን መልዕክተኛ በወለደች ጊዜ እናቴ አብራት ነበረች ይላል ዑስማን ቢን አቢል ዓስ፡ እንዳወጋችኝም "ቤቱ ውስጥ የምመለከተው ነገር ሁሉ ኑር ነበረው፡ ወደ ከዋክብት ሳማትር ወደቁብኝ ብዬ እስከምሰጋ ድረስ ይቀርቡን ነበር"
የረሱለላህ ወላጅ እናት አሚና ሙሐመድን (ሰለላሁ ዓለይሂ ወኣሊሂ ወሰለም) ቅሪት ሳለች መልዐኩ መጥቶ እንዲህ አላት
"አንቺ የተሸከምሽው የዚህን ሕዝብ ሹም ነው፡ ወደ ምድር በሚመጣ ጊዜ
ምልክቱ ከሻም ምድር የቡስራ አብያተ-መንግስታት የሚሞላ ብርሃን ከእሱ ጋር ይወጣል፡ ስትወልጂው ሙሐመድ ብለሽ ሰይሚው፡ ተውራትና ኢንጂል ላይ ስሙ አሕመድ ነው፡ የሰማይ እና የምድር ኗሪዎች ያመሰግኑታል፡ ስሙ በቁርኣን ሙሐመድ ነው" አላት። በወለደችውም ጊዜ ሙሐመድ አለችው
አልሀምዱሊላህ ዑመታቸው ያደረገን🥰
ሰሉ አለ ነቢ🥰
አለይኩም ቢዱዓ🤲
በአሏህ ቁድራና ድንበር የለሽ ችሎታው ከተፈጠረና ከተሰራ ነገራቶች ሁሉ ሰይዳችንንﷺ የመሰለ ምርጥና ውስጣዊም ውጫዊም ውበትን የተላበሰ ምንም ነገር የለም::
እንደሳቸውምﷺ አሏህ ጋር የተወደደና እሳቸውን ሊወዳደር የሚችል አንድም ነገር የለም::
እሳቸውንﷺ ከመሰጠትም በላይ ትልቅ ውለታ የለም::
አሏህ ረሕመቱን ሊቸር የሻ ግዜ የፈጠራቸው ትልቁ የረሕመቱ በር ናቸውﷺ::
ራሕመታችንንﷺ ያገኘንበት ወር በመግባቱ እንኳን ደስ አለን .. ☺️
ሰይዳችንምﷺ አይተውን የሚደሰቱብንን ስራ የምንሰራበት፣ በኡመታቸውም የሚደሰቱበት፣ ሀገራችንም አማንን የምትላበስበት ወር አሏህ ያድርግልን
#ረቢዑልቁሉብ
ሰይዲና አነስ [ረዲየላሁ ዐንሁ] እንዲህ ይላሉ፦
የአላህ መልእክተኛ [ﷺ] ከሰዎች ሁሉ የላቀ ሥነ ምግባር ነበራቸው። አንድ ቀን ለአንድ ጉዳይ ላኩኝ። እኔም፦ «በአላህ እምላለሁ፣ አልሄድም» አልኩኝ፤ ነገር ግን በውስጤ የአላህ ነቢይ [ﷺ] ያዘዙኝን ለመፈጸም ለመሄድ ወስኜ ነበር።
ከዚያም ወጥቼ በገበያ ላይ ይጫወቱ የነበሩ ሕፃናት አጠገብ አለፍኩ። [በጨዋታቸው ተጠመድኩም።] ከዚያም የአላህ መልክተኛ [ﷺ] ከኋላዬ መጥተው ጫንቃዬን ያዙኝ። ወደ እርሳቸው ተመለከትኩ፤ እርሳቸውም እየሳቁ፦
«ያ ኡነይስ! ወደ ላክሁህ ቦታ ሄደሃልን?» አሉኝ።
«አዎን፣ የአላህ መልክተኛ ሆይ! እየሄድኩ ነው!» አልኳቸው።
:
አነስ [ረዲየላሁዐንሁ] እንዲህ ይላሉ፦
«በአላህ እምላለሁ! ለሰባት ዓመት ወይም ለዘጠኝ ዓመት አገለገልኳቸው። በዚያ ጊዜ ሁሉ ያደረግሁትን ነገር በመመልከት ‘ለምን እንዲህ አደረግህ?’ ብለው አያውቁም፤ የተውኩትንም ነገር ‘ለምን እንዲህ አላደረግህም?’ ብለው አያውቁም።»
🌹ተመልከት ይህ ነቢያችን [ﷺ] ለአገልጋያቸው የነበራቸው ታላቅ ርህራሄ፣ ትዕግሥትና ውብ ሥነ ምግባር ነው። ፈለጋቸውንም ያዝ!
#ረቢዕ
ታላቁ የነቢያችን ﷺ ልደት
የተወዳጁ ነቢይ ﷺ ልደት በልዩ ክብር የተከበበና በመለኮታዊ እንክብካቤ የተሞላ ነበር። አላህ በልደታቸው ጊዜ የነቢይነታቸው ቅድመ-ምልክት [ኢርሃስ]፣ የመልእክታቸው መግቢያና የታላቅ ደረጃቸው ማሳወቂያ የሆኑ አስደናቂና ያልተለመዱ ነገሮችን አሳይቷል። ይህም እርሳቸው ታላቅ ክብርና ልዩ ደረጃ እንዳላቸው ያመለክታል።
ከእነዚህም መካከል፦ በወሊዳቸው ጊዜ ከእናታቸው ማህፀን የወጣ ብርሃን ተይቷል። ብርሃኑ ተስፋፍቶም የሻም አብያተ መንግስታት ድረስ አብርቷል። ኢማም አሕመድ ከዒርባድ ኢብኑ ሳሪያህ [ረዲየላሁ ዐንሁ] እንደዘገቡት፣ የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
«አደም በጭቃቸው ላይ ተጋድመው ሳለ እኔ በአላህ ዘንድ የነቢያት መጨረሻ ነበርኩ። ስለዚህ ነገር እነግራችኋለሁ፦ እኔ የኢብራሂም ዱዓ፣ የዒሳም ምሥራች ነኝ፤ እናቴም ያየችው ራእይ እንዲሁም የነቢያት እናቶች የሚያዩት ራእይ ነው። የአላህ መልእክተኛ ﷺ እናት እርሳቸውን በወለደች ጊዜ ከእርሳቸው ጋር የወጣ ብርሃን አየች፤ ይህም የሻምን ቤተ መንግሥቶች አበራ።»
📚 ''ሰይዲና ሙሐመድ ረሱሉላህ ﷺ መልካም ባሕርያቸውና የተከበሩ መገለጫዎቻቸው"፣ ገጽ 466፣ በዓላማ ሸይኽ ዐብዱላህ ሲራጁዲን [ረሒመሁላህ]
የረቢዕ ነገር ይደንቃል። በወር መጠሪያነት፤ በወቅት ስያሜነት መገደብ ይጠናል። ብራማነቱ ልብን ይዘልቃል። መዓዛው ሩህን ያነቃል። ስፋቱ ሽምጥ ያስጋልባል። አንድምታው ምናብ ያባክናል። "እንዲህም ነው ..እንዲያም ነው.." እያሰኘ ያብከነክነናል። ብዙ ማለትን፤ ብዙ መክተብን ያሰኛል። ልክ እንደ ያኔው፤ እንደ አለማቱ ብስራቱን የመጠባበቅ ሂደት ውስጥ መንፈስን ይደባልቃል። ጉጉትን አስቀድሞ በናፍቆት ይንጣል።
ለዚህም መድረስ ..ለዚህም መታጨት ..ይህም ከረቢዕ ነው። እንኳንም ደረስን..!
አላሁመሶሊ ወሰሊም ወባሪክ ዐላ ሩሂል ውጁድ 🤍
ነሲም ሚራዥ
የአላህ መልክተኛ [ﷺ] አንድ ሰው: ‐ «ያዘልጀላሊ ወል‐ኢክራም (የክብርና የታላቅነት ባለቤት ሆይ!)» እያለ በዱዓው ላይ ሲጣራ በአጠገቡ አለፉና፦ «ተመልሶልሃል፤ አሁን ጠይቅ» አሉት።»
📚 ኢማም አህመድና ቲርሚዚ ዘግበውታል፤ ቲርሚዚም ሐዲሱን 'ሐሰን' ብለውታል።
