en
Feedback
Ethiopia Ortodox Mezmur Video🤲👏

Ethiopia Ortodox Mezmur Video🤲👏

Open in Telegram
2 299
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
" መስቀል አጋንንት ድል የተነሡበት ነው፡፡ መስቀል የኃጢአት ድል መንሻ የጦር ዕቃ ነው፡፡ መስቀል ጌታችን እባቡን የመታበት ሰይፍ ነው፡፡ መስቀል የአብ ፈቃድ ፣ የወልድ ክብር ፣ የመንፈስ ቅዱስ ደስታ ፣ የመላእክት ጌጥ ፣ የቤተ ክርስቲያን አጥር ፣ የቅዱስ ጳውሎስ ውዳሴ ፣ የቅዱሳን ጋሻ ፣ የዓለምም ብርሃን ነው፡፡ "

በዓለ ወልድ* ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በየወሩ በዚህች በ29ኛይቱ ዕለት ጌታችን አምላካችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በድንቅ ልደት የተወለደበትን በዓል ትዘክራለች። እለቱም በዓለ ወልድ ይባላል።* ሃይማኖተ አበው ስለዚህ ድንቅ ልደት እንዲህ ያስተምረናል* ፦ ከህሊናት ሁሉ ለራቀ እና ለረቀቀ ለዚህ ድንቅ ልደት ለዚህ ድንቅ ምስጢር አንክሮ ይገባል! ድንግል ፈጣሪዋን ወለደችው! እርሱም እናቱን ፈጠረ፤ ከእርሷም እርሱ የፈጠረውን ሥጋ ተዋሐደ*  :: ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ኤፍሬም 47:2 ድንግል ፈጣሪዋን ወለደችው፤ እርሱም ለመለኮት በሚገባ ልደት ተወለደ:: ይህ ምስጢር ታላቅ ነው!* ሰማያዊው አምላክ የምድራዊውን ሰው ሥጋ የለበሰበት፤ ምድራዊው ሰው የሰማያዊ አምላክነትን ክብር ያገኘበት ይህ እለት እንደምን ድንቅ ነው!* በእውነቱ በዚህ ድንቅ ልደት አምላክን ለመውለድ የታደለች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም እንደምን ድንቅ ናት!* ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ይህ የአምላክ እናት ድንቅነት ቀድሞ ቢታየው፤ ጸጋን የተሞላሽ ሆይ ደስ ይበልሽ ! እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነው። ከሴቶች ሁሉ ተለይተሽ አንቺ የተባረክሽ ነሽ! ብሎ ከፊቷ ወድቆ አመሰግኗታል።* ይህን ልደት ስንዘክር፡ ከትህትናው እና ለእኛ ካለው ፍጹም ፍቅር የተነሳ: በከብቶች በረት የተኛውን ጌታችንን፣ በፍጹም ድንግልና የወለደችው እናቱን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን በፊታቸው ወድቀን በማመስገን እና በመማጸን ነው።

ድንግል ማርያም ዘማሪት እየሩሳለም ጌታቸው

እናቴ አርሴማ ዘማሪት እየሩሳለም ጌታቸው

" ሥላሴ ለእኔ " ዘማሪት ሰላማዊት መኮንን

የቤተክርስቲያን አካሏ ይህ ነው። ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ደም የተመሠረተች ንጽሕት ቅድስት ናት። ለመዳን ወደእርሷ የተጠጉ ሰዎች ግን ከጨዋ እስከ ፓትርያርክ እስከ ሲኖዶስ ሊሳሳቱ ይችላሉ። በእነርሱ ምክንያት እርሷን መስደብና መንቀፍ ይቁም። ክርስቶስንምኮ ይከተሉት ከነበሩት አምስት ገበያ ሕዝብ ዓላማቸው ልዩ ልዩ ነበረ። አንዳንዶቹ ለከርሣቸው፣ አንዳንዶቹ ለትምህርቱ ተከትለውታል።                            ። አካሏ ክርስቶስ የሆነላትን ቅድስት ቤተክርስቲያን ደግሞ አንዳንዱ ለሆዱ፣ አንዳንዱ ለፖለቲካዊ ርእዮተ ዓለሙ፣ አንዳንዱ ለመዳን ይጠጓታል። ለመዳን የተጠጓት ነፍሳቸውንም ሥጋቸውንም ጠቀሙ። ለሌላ ዓላማ የተጠጓት ግን ራሳቸውን ከመጉዳት የዘለለ ምንም አያመጡም። ሰይፍን ቢመረኮዙ ራሳቸው ይጎዳሉ እንጂ።

#ቸርነትህ_ነው ቸርነትህ ነው ያደረሰኝ እስከ ዛሬ ቸርነትህ ነው የጠበቀኝ እስከዛሬ ላመስግንህ የኔ ጌታ በዝማሬ /2/         #አዝ ……………… መክሊቴን ቀብሬ ባሳዝንህ መብራቴንም ይዤ ባልጠብቅህ በታላቅ ይቅርታ እዳትረሳኝ በፍቅር ጎብኝተህ ከሞት አዉጣኝ ከቤትህ እርቄ መች ጠገብኩኝ በርሀብ በርዛት ተቸገርኩኝ አምናለሁ ከምላኬ እድትምረኝ በይቅርታ መጣሁ ተቀበለኝ        #አዝ ……………… አንዳች እዴለለኝ አዉቀዋለሁ ባንተ ቸርነት ግን እመካለሁ የከበደው ሸክሜ ይቀለኛል ይቅርታህ ለባሪያህ ይደርሰኛል በመቅደስህ ቁሜ ለመዘመር ስራህን ለትዉልድ ለመመስከር እኔ ማነኝ ብየ አስባለሁ አምላክ ቸርነትህን አደንቃለሁ                   #አዝ ……………… በሰዉ እጅ መመካት አቁሚያለሁ እረዳቴ አንተ ነህ አዉቄያለሁ አንተ ከጠበከኝ በህይወቴ ቅጥሬ አይደፈርም መድኃኒቴ የኔን ስራ ተወዉ ተግባሬንም የመስቀሉንም ነገር መርሳቴንም አዚሜን አንስተህ አንተን ልይህ ኢየሱስ ክርስቶስ አምላኬ ነህ

ሰንበተ ክርስትያን እሑድ ማለት"አሐደ" ከሚለው የግዕዝ ቃል የወጣ ሲኾን ትርጉሙ የመጀመሪያ እንደማለት ነው። ይኽች ዕለት በመጽሐፍ ቅዱስ "ከሳምንቱ በፊተኛው ቀን " በመባል ትታወቃለች። ዮሐንስም በራዕዩ "የጌታ ቀን" ያላት ናት (ራዕይ 1፥10) ቅዱስ ያሬድም በድጓው ላይ "ዕለተ እግዚአብሔር" የሚላት ዕለተ እሑድ ናት። መልካም ዕለተ ሰንበት ይኹንልን

[       ለምን ትቀናለህ ?      ] " ... በጆሮው የሆነ ነገር ነግሮት ወዲያው ተሰናብቶት ወጣ። ይህን ጊዜ አጋንንቱ እያዩት መነኩሴው መንፈሳዊ ገጽታው ተገፎ ፊቱ በቁጣና በንዴት ሲለዋወጥ ተመለከቱት። ... " " እንዳትበድል አትቅና።" [ መዝ. ፴፯ ፥ ፰ ]

"ኢያቄም ወሐና ወለዱ ሰማየ፤ ወሰማዮሙኒ አስረቀት ፀሐየ" እንዳለ ደራሲ። ኢያቄምና ሐና ሰማይን ወለዱ፤ ሰማይቷም ፀሐይን ወለደች። ፀሐይ ጽድቅ ክርስቶስን የወለደችው ሰማይ ተወለደች!! ልደትሽ ልደታ
"ኢያቄም ወሐና ወለዱ ሰማየ፤ ወሰማዮሙኒ አስረቀት ፀሐየ" እንዳለ ደራሲ። ኢያቄምና ሐና ሰማይን ወለዱ፤ ሰማይቷም ፀሐይን ወለደች። ፀሐይ ጽድቅ ክርስቶስን የወለደችው ሰማይ ተወለደች!! ልደትሽ ልደታችን ነው! እንኳን አደረሳችሁ።

ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን በዓቢይ ኃይል ወሥልጣን አሠሮ ለሰይጣን አግዓዞ ለአዳም ሰላም እምይዕዜሰ ኮነ ፍሥሐ ወሰላም ++++++++++++++++++++ እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ። ✝️መልካም የትንሳኤ በዓል

መልአከ ሰላም ቀሲስ እንግዳወርቅ በቀለ "የሁሉም አይን" የንስሃ መዝሙር

የተሰቀለውን ኢየሱስን ሳየው ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ

https://youtube.com/@EOTCTV?si=EnSIkaIECMiOmarE ሰብስክራይብ በማድረግ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቴሌቭዥን ጣቢያን እናግዝ።

"ዮሴፍም ደግሞ ከዳዊት ቤትና ወገን ስለ ነበረ ከገሊላ ከናዝሬት ከተማ ተነሥቶ ቤተ ልሔም ወደምትባል ወደ ዳዊት ከተማ ወደ ይሁዳ፥ ፀንሳ ከነበረች ከእጮኛው ከማርያም ጋር ይጻፍ ዘንድ ወጣ። በዚያም
"ዮሴፍም ደግሞ ከዳዊት ቤትና ወገን ስለ ነበረ ከገሊላ ከናዝሬት ከተማ ተነሥቶ ቤተ ልሔም ወደምትባል ወደ ዳዊት ከተማ ወደ ይሁዳ፥ ፀንሳ ከነበረች ከእጮኛው ከማርያም ጋር ይጻፍ ዘንድ ወጣ። በዚያም ሳሉ የመውለጃዋ ወራት ደረሰ፥የበኵር ልጅዋንም ወለደች፥ በመጠቅለያም ጠቀለለችው፤ በእንግዶችም ማደሪያ ስፍራ ስላልነበራቸው በግርግም አስተኛችው። በዚያም ምድር መንጋቸውን በሌሊት ሲጠብቁ በሜዳ ያደሩ እረኞች ነበሩ። እነሆም፥ የጌታ መልአክ ወደ እነርሱ ቀረበ የጌታ ክብርም በዙሪያቸው አበራ፥ ታላቅ ፍርሃትም ፈሩ። መልአኩም እንዲህ አላቸው። እነሆ፥ ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፤ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና። ይህም ምልክት ይሆንላችኋል፤ ሕፃን ተጠቅልሎ በግርግምም ተኝቶ ታገኛላችሁ። ድንገትም ብዙ የሰማይ ሠራዊት ከመልአኩ ጋር ነበሩ። እግዚአብሔርንም እያመሰገኑ። ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም ይሁን ሰላምም በምድር ለሰውም በጎ ፈቃድ አሉ።..." ሉቃ ፪፥፬-፳ እንኳን ለጌታችን ለአምላካችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አደረሰን አደረሳችሁ

እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አደረሳችሁ “የፍጥረት ናፍቆት ።” ሮሜ 8፥19 የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት የፍጥረታት ሁሉ ናፍቆት ነበር ለቤተ መንግስቱም ለቤተ ክህነቱም ፣ ለነገስታቱም ለባሪያዎቹም ፣ለካህናቱም ለምዕመናኑም ፣ ለተማረውም ላልተማረውም ፣ ለትንሹም ለትልቁም ፣ ለሐጥያተኛውም ለፃድቁም .........የጌታ መወለድ ለፍጥረት ሁሉ ናፍቆት ነበር ቀኒቱም በናፍቆት እና በጉጉት ትጠበቅ ነበር እግዚአብሔር አብ ለሰው ልጆች የሰጠው ውድ ስጦታ በለኪያ ፣ መተኪያ የሌለውን አንድያ ልጁን እግዚአብሔር ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስን ነው ። መልካም በዓል 2015 ዓ•ም ዲ/ዳዊት ፈለቀ

እንኳን ለአባታችን ለአቡነ ተክለሀይማኖት ልደት አደረሳችሁ
እንኳን ለአባታችን ለአቡነ ተክለሀይማኖት ልደት አደረሳችሁ

እንኳን ለቅዱስ ገብርኤል አመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ

ንስሃ ግቡ::ከእግዚአብሔርና ከቃሉ ታረቁ ከማይሉን ስጋዊና ምድራዊ የልባችን መሻትና ፍላጎት ከሚናገሩን ከዘመናችን ሀሰተኛ ነቢያት ተጠንቀቁ::ትንቢትን ፈትኑ::እኛ አገራችን በሰማይ ነው::

የገና መዝሙር እሠይ ተወለደ የአለም መድሀኒት