en
Feedback
የላፍቶ ቱሉ ኤጀርሳ ብልጽግና ፓርቲ

የላፍቶ ቱሉ ኤጀርሳ ብልጽግና ፓርቲ

Open in Telegram
213
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ለወረዳ አመራርና ለበታች አመራሮች የሚሰጠው የአቅም ግንባታ መድረክ በመሰጠት ላይ ይገኛል። በብልጽግና ፓርቲ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ ቅ/ጽ/ቤት ለወረዳው አመራሮችና ለበታ
+9
ለወረዳ አመራርና ለበታች አመራሮች የሚሰጠው የአቅም ግንባታ መድረክ በመሰጠት ላይ ይገኛል። በብልጽግና ፓርቲ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ ቅ/ጽ/ቤት ለወረዳው አመራሮችና ለበታች አመራሮች የሚሰጠው የአቅም ግንባታ ስልጠና የክ/ከተማው ኮር አመራሮች በተገኙበት መሰጠት ጀምሯል። በአቅም ግንባታ መድረኩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉር የክ/ከተማው ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አለልኝ ወንዴ ይህ የአቅም ግንባታ ስልጠና ፓርቲው በልዩ ትኩረት እየሰራበት መሆኑን በመግለጽ ስልጠናውን መስጠት ብቻ ሳይሆን ወደ ተግባር መለወጥ እንደሚገባ ገልፀዋል። የክ/ከተማው ም/ፓርቲ እና የፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ አቶ ፍራኖል ሞሲሳ በበኩላቸው ብልጽግና ፓርቲ ሁሉን ብሔር ብሔረሰቦች ያቀፈ በህብረ ብሔራዊነት ያሸበረቀ ፓርቲ በመሆኑና ይህ ስልጠና በብሔር ብሔረሰቦች በአል አከባበር ወቅት የተከናወነ በመሆኑ ስልጠናው የተለየ ያደርገዋል ብለዋል። የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ዘሪሁን አሰፋ በወረዳው ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት እየተከናወነ የሚገኘው የአቅም ግንባታ መድረክ ከስልጠና በዘለለ በንባብ ሳምንት እንዲሁም በጥያቄና መልስ ውድድሮች አባላትን መገንባት ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል። ስልጠናው ቀጥሏል... ህዳር 28/2016 #ላፍቶ_ቱሉ_ኤጀርሳ_ፓርቲ_ሚዲያ

''በጊዜ የአርሶአደሯችን ምርት በመሰብሰብ የምግብ ዋስትናችንን እናረጋግጥ''! በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ አዘጋጅነት የአርሶ አደር የመኅር የምርት መሰብሰብና የበጋ መስኖ ማስጀመሪየ መርሃ ግብር ተካሔደ። በምርት መሰብሰብና በበጋ መስኖ መሰስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ ፣ የከተማ ግብርና እና አርሶ አደር ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር መኮነን ሽመልስን ጨምሮ የክ/ከተማና የወረዳ አመራሮች እንዲሁም ወጣቶች ተሳትፈዋል። የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ብርሃኑ አበራ የአርሶ አደሩ ተጠቃሚነት ማረጋገጥና  የከተማዋ ኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ውስጥ የበኩላቸውን እንዲያበረክቱ በትኩረት ይሰራል ሲሉ  ተናግረዋል:: ዋና ስራ አስፈፃሚውና ምክትል ኮሚሽነሩ መኮነን ሽመልስ አርሶ አደሮች በይዞታቸው ላይ የሚሰራውን የልማት ስራ ጎብኝተዋል። ከዚህ በፊት ግንባታው ተጀምሮ የቆመ የዳቦ ፋብሪካ ግንባታም አስጀምረዋል። #ላፍቶ_ቱሉ_ኤጀርሳ_ፓርቲ_ሚዲያ ህዳር 13/2016

''በጊዜ የአርሶአደሯችን ምርት በመሰብሰብ የምግብ ዋስትናችንን እናረጋግጥ''! በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ አዘጋጅነት የአርሶ አደር የመኅር የምርት መሰብሰብና የበጋ መስኖ ማስጀመሪየ መርሃ ግብር ተካሔደ። በምርት መሰብሰብና በበጋ መስኖ መሰስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ ፣ የከተማ ግብርና እና አርሶ አደር ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር መኮነን ሽመልስን ጨምሮ የክ/ከተማና የወረዳ አመራሮች እንዲሁም ወጣቶች ተሳትፈዋል። የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ብርሃኑ አበራ የአርሶ አደሩ ተጠቃሚነት ማረጋገጥና  የከተማዋ ኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ውስጥ የበኩላቸውን እንዲያበረክቱ በትኩረት ይሰራል ሲሉ  ተናግረዋል:: ዋና ስራ አስፈፃሚውና ምክትል ኮሚሽነሩ መኮነን ሽመልስ አርሶ አደሮች በይዞታቸው ላይ የሚሰራውን የልማት ስራ ጎብኝተዋል። ከዚህ በፊት ግንባታው ተጀምሮ የቆመ የዳቦ ፋብሪካ ግንባታም አስጀምረዋል። #ላፍቶ_ቱሉ_ኤጀርሳ_ፓርቲ_ሚዲያ ህዳር 13/2016

በ60 ቀናት ዕቅድ ዙሪያ ከጠቅላላ አመራሩ ጋር ውይይት ተካሔደ። በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ አስተዳደር በቀጣይ የ60 ቀናት የሚከናወኑ ተግባራት እቅድ ዙሪያ በጠቅላላ አመራር
+3
በ60 ቀናት ዕቅድ ዙሪያ ከጠቅላላ አመራሩ ጋር ውይይት ተካሔደ። በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ አስተዳደር በቀጣይ የ60 ቀናት የሚከናወኑ ተግባራት እቅድ ዙሪያ በጠቅላላ አመራር ውይይት ተካሒዶበታል። በውይይቱ ላይ የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ዘሪሁን አሰፋ እንዲሁም ፓርቲ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ጌትሽ ጀማነህ ይህንን የ60 ቀን እቅድ ተግባራት በጊዜ የለኝም ስሜት በመንቀሳቀስ ሙሉ በሙሉ ተፈፃሚ ማድረግ እንደሚገባ ተገልጿል። #ላፍቶ_ቱሉ_ኤጀርሳ_ፓርቲ_ሚዲያ ህዳር 11/2016

የክፍለ ከተማው ከፍተኛ አመራሮች በወረዳው ውስጥ ያሉ ሼዶችን ምልከታ አካሔዱ። በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ አስተዳደር ውስጥ የሚገኝ በከተማ ግብርና የተደራጁ ኢንተርፕራይዞች
+8
የክፍለ ከተማው ከፍተኛ አመራሮች በወረዳው ውስጥ ያሉ ሼዶችን ምልከታ አካሔዱ። በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ አስተዳደር ውስጥ የሚገኝ በከተማ ግብርና የተደራጁ ኢንተርፕራይዞች ሼድን በክ/ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ የተመራ ልዑክ ቡድን ምልከታ አካሒዷል። በምልከታው ላይ በሼዶቹ ውስጥ ያሉ የመሰረተ ልማት ችግሮች መኖራቸውን በመረዳት ከወረዳ አስተዳደሩ ጋር በመሆን በቀጣይ ቀናት መፍታት በሚያስችልበት ሁኔታ አቅጣጫ ተቀምጧል። #ላፍቶ_ቱሉ_ኤጀርሳ_ፓርቲ_ሚዲያ ህዳር 11/2016 ዓ.ም

በፓርቲያችን አባላት መካከል የጥያቄና መልስ ውድድር መርሃ ግብር ተካሔደ። በብልጽግና ፓርቲ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ ቅ/ጽ/ቤት በተለያዩ ማህበራዊ መሰረቶች የሚገኙ አባላት
+4
በፓርቲያችን አባላት መካከል የጥያቄና መልስ ውድድር መርሃ ግብር ተካሔደ። በብልጽግና ፓርቲ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ ቅ/ጽ/ቤት በተለያዩ ማህበራዊ መሰረቶች የሚገኙ አባላት መካከል የጥያቄና መልስ ውድድር ተካሒዷል። ይህ የጥያቄና መልስ መርሃ ግብር ከውድድር ባለፈ አስተማሪ በመሆኑ በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል። #ላፍቶ_ቱሉ_ኤጀርሳ_ፓርቲ_ሚዲያ ህዳር 10/2016

የክፍለ ከተማው ከፍተኛ አመራሮች በጎርፍ ምክንያት አደጋ የደረሰባቸውን ወገኖች በስፍራው በመገኘት አጽናኑ። በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ በቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ አስተዳደር በሰሞኑ በዘነበው ከባድ ዝ
+5
የክፍለ ከተማው ከፍተኛ አመራሮች በጎርፍ ምክንያት አደጋ የደረሰባቸውን ወገኖች በስፍራው በመገኘት አጽናኑ። በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ በቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ አስተዳደር በሰሞኑ በዘነበው ከባድ ዝናብ ሳቢያ  ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች የክፍለ ከተማው አስተባባሪ ኮሚቴ እና ሌሎች አመራሮች በቦታው በመገኘት በአደጋው በደረሰው የንብረት ጉዳት የተሰማቸውን ሀዘን በመግለጽ ተጎጂዎችን አጽናንተዋል። በቦታው የተገኙት የክፍለ ከተማው ከፍተኛ አመራሮች ጉዳት የደረሰባቸውን የህብረተሰብ ክፍሎች የመደገፍና መልሶ የማቋቋም ስራ ከክፍለ ከተማው አስተዳደር እንደሚደረግላቸው በመግለጽ በቀጣይም መሰል አደጋዎች እንዳይፈጠር አስተዳደሩ ከዛሬ ጀምሮ ወደ ተግባር በመግባት አፋጣኝ ምላሽ  እንደሚሰጥ በመግለጽ በአካባቢው የሚገኘውን ወንዝ የማስተካከልና የማጽዳት ስራ አስጀምረዋል። #ላፍቶ_ቱሉ_ኤጀርሳ_ፓርቲ_ሚዲያ ህዳር 9/2016

18ኛው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ቀን "ብዝሃነትና እኩልነት ለሀገራዊ አንድነት" በሚል መሪ ቃል የማስ ስፖርት ተከናወነ። የወረዳው ስፖርት ጽ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ ሶስና ምህረት በበኩላቸው ስፖርት ጤ
+7
18ኛው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ቀን  "ብዝሃነትና እኩልነት ለሀገራዊ አንድነት" በሚል መሪ ቃል የማስ ስፖርት ተከናወነ። የወረዳው ስፖርት ጽ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ ሶስና ምህረት በበኩላቸው ስፖርት ጤንነትን ከመጠበቅ ባሻገር፣ አንድነትን፣ ወንድማማችነትን፣ ለማጎልበት ትልቅ ሚና አለው በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል። #ላፍቶ_ቱሉ_ኤጀርሳ_ፓርቲ_ሚዲያ ህዳር 9/2016

ፅዳትን ባህል ያደረገ ማህበረሰብ ለመፍጠር ሳምንታዊ የፅዳት ዘመቻዎቻችንን አጠናክረን እንቀጥላለን! በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ ጽዳት አስተዳደር ጽ/ቤት ከወረዳው የብልጽግና
+9
ፅዳትን ባህል ያደረገ ማህበረሰብ ለመፍጠር ሳምንታዊ የፅዳት ዘመቻዎቻችንን አጠናክረን እንቀጥላለን! በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ ጽዳት አስተዳደር ጽ/ቤት ከወረዳው የብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ጋር በመሆን የአንድ ማዕከል ሳምንታዊ የፅዳት ዘመቻ በዛሬው እለት አካሒዷል። ይህ ሳምንታዊ የፅዳት ዘመቻ በክላስተሮች ፣ በብሎኮች ፣ በት/ት ቤቶች እንዲሁም በተለያዩ የመንግስትና የግል ተቋማት በተጠናከረ መንገድ እንደሚካሔድ የወረዳው የጽዳት አስተዳደር ፅ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ በረከት ጤናው ገልፀዋል። ወጣቶች በተለያዩ የንቅናቄ ስራ እንደሚሳተፉ በመግለፅ በጽዳት ዘመቻ ላይ በልዩ ትኩረት መሳተፍ እንደሚጠበቅባቸው የወረዳው ወጣቶች ሊግ ሰብሳቢ ወጣት ሩት አስማማው አሳስበዋል። #ላፍቶ_ቱሉ_ኤጀርሳ_ፓርቲ_ሚዲያ ህዳር 09/2015 ዓ.ም

በአለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ ጊዜ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ19ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀን አስመልክቶ የፓናል ውይይት መካሄዱ እንደቀጠለ ነው ! በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወ
+4
በአለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ ጊዜ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ19ኛ ጊዜ የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀን አስመልክቶ የፓናል ውይይት መካሄዱ እንደቀጠለ ነው  ! በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ አስተዳደር በአለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ ጊዜ  በኢትዮጵያ ለ19ኛ ጊዜ ''ሙስና የጋራ ጠላታችን ነው በህብረት እንታገል'' በሚል መሪ ቃል የሚከበረውን የፀረ-ሙስና ቀንን በማስመልከት ከወረዳው  ሴት አደረጃጀቶች ጋር ውይይት ተካሒዷል። በውይይቱም የወረዳው የሴቶችና ህፃናት ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ ሌንሳ በላይነህ በፓናል ውይይቱ ወቅት ሙስና የሀገርን ኢኮኖሚ የሚጎዳና የዜጎችን የጋራ ተጠቃሚነት የሚያሳጣ  ድንበር ዘለል ወንጀል በመሆኑ ሁላችንም በጋራ ልንታገለው ይገባል ብለዋል፡፡ የወረዳው ሴቶች ሊግ ሰብሳቢ ወ/ሮ ወርቃለም ጥላሁን በበኩላቸው የጋራ ጠላታችን የሆነውን ሙስናን በህብረት ታግለን በማጥፋት በብዝሀነት እና እኩልነት ሀገራዊ እድገታችንን እናፋጥናለን በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል። #ላፍቶ_ቱሉ_ኤጀርሳ_ፓርቲ_ሚዲያ ህዳር 08/2016

የወረዳው የሲቪል ምዝገባና የነዋሪዎች አገልግሎት በወረዳው ከሚገኙ የተለያዩ ምክር ቤቶች ጋር የውል ስምምነት ተፈራረመ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪዎች
+5
የወረዳው የሲቪል ምዝገባና የነዋሪዎች አገልግሎት  በወረዳው ከሚገኙ የተለያዩ ምክር ቤቶች ጋር የውል ስምምነት ተፈራረመ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪዎች አገልግሎት በወረዳው ከሚገኙ የሃይማኖት ተቋማት የጋራ ምክር ቤት እንዲሁም የእድር ተቋማት ምክር ቤታ ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል የውል ስምምነት ተፈራርሟል። የወረዳው የሲቪል ምዝገባና የነዋሪዎች አገልግሎት ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ቶሌራ ጅዳ በጽ/ቤቱ ላይ የሚመጡ ማንኛውም ቅሬታዎችን እየፈታን የወረዳችንን የህብረተሰብ ክፍሎች እያሳተፍን ቀልጣፋ አገልግሎት እንሰጣለን ብለዋል። በመድረኩ ላይ ስለ ጽ/ቤቱ ተቋማዊ አሰራር እንዲሁም አገልግሎቶችን አስመልክቶ ለተቋማቱ ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራ ተሰርቷል። #ላፍቶ_ቱሉ_ኤጀርሳ_ፓርቲ_ሚዲያ ህዳር 08/2016

ወደ ተግባር የተቀየረ የከተማ ምግብ ዋስትና የተሻለ የቤተሰብ ምግብ ዋስትናን ያረጋግጣል፡፡ ========================== በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14(ቱሉኤጀርሳ) አስተዳ
+4
ወደ ተግባር የተቀየረ የከተማ ምግብ ዋስትና የተሻለ የቤተሰብ ምግብ ዋስትናን ያረጋግጣል፡፡ ========================== በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14(ቱሉኤጀርሳ) አስተዳደር ስራ ኢንተርፕራይዝ ኢንዱስትሪ ልማት ጽ/ቤት በተለያዩ አጀንዳዎች ማለትም 1/በመልካም አስተዳደር 2/በጸረ-ሙስና ትግል እና ብልሹ አሰራር 3/ቀጣይ በሚሰሩ ተግባራት ላይ ለተጠቃሚዎች ግንዛቤ ሰጥቷል የግንዛቤ መድረኩን የመሩት የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14አስተዳደር ስራ ኢንተርፕራይዝ ኢንዱስትሪ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሪት  አስረሳሽ ዓለሙ ይህ መድረክ በከተማ ምግብ ዋስትና እና ልማታዊ ሴፍትኔት  ለዘላቂ ኑሮ ማሻሻያ ለተመራቂ የሴፍትኔት ተጠቃሚዎች በሚለቀቅላቸው ጋራንት ድጋፍ ቤተሰባቸውን ከድህንነት የሚያወጡበት ከዛም አልፎ ለሌሎች የስራ እድል የሚፈጥሩባቸውን መንገድ ግንዛቤ የሚሰጥበት ስለሆነ ተሳታፊዎች በንቃትና በትኩረት እንዲያዩት አሳስበዋል፡፡ በተጨማሪም በተሰጡት አጀንዳዎች ላይ ተጠቃሚዎች ባነሱት ሀሳብ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥቷል። #ላፍቶ_ቱሉ_ኤጀርሳ_ፓርቲ_ሚዲያ ኅዳር 08/2016ዓ.ም

“ሙስና የጋራ ጠላታችን መሆኑን በመገንዘብ በቁርጠኝነት ለመታገል በሚደረገው ርብርብ ወጣቶች የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ ይገባል'' በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ “ሙስናን የጋራ ጠላ
+3
“ሙስና የጋራ ጠላታችን መሆኑን በመገንዘብ በቁርጠኝነት ለመታገል በሚደረገው ርብርብ ወጣቶች የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ ይገባል'' በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ “ሙስናን የጋራ ጠላታችን ነው በሕብረት እንታገል” በሚል መሪ ቃል በሃገራችን ለ19ኛ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ ጊዜ የሚከበረውን የዓለም የፀረ-ሙስና ቀንን በማስመልከት ከወረዳው ወጣቶች ጋር ውይይት ተካሂዷል፡፡ በውይይቱም በሙስና ምንነት፤ የሙስና ወንጀል ልዩ ባህሪያት፤ የፀረ-ሙስና የህግ ማዕቀፎች፤አለም አቀፋዊ ተሞክሮዎችና በኢትዮጵያ የፀረ-ሙስና ትግል አስቸኳይ ሁኔታና ተግዳሮቶች፤ የመንግስት፣ የትምህርት ተቋማት፣ የሀይማኖት ተቋማት፣ ሚዲያዎች ፤ የቤተሰብ እና የሲቪክ ማህበራት ሚና ዘርዘር ባለ መልኩ ለተሳታፊዎች ገለፃ ተደርጓል፡፡ የሙስና ተግባር ከንግግር ባለፈ ተግባራዊ እርምጃ የሚሻ በመሆኑ የፀረ ሙስና ትግል ውስጥ በዋናነት እንደወረዳ የሚነሱ ተቋማት ላይ ቴክኖሎጂና ግልፅ አሰራርን መዘርጋትና ወጣቱ ሙስናን በቁርጠኝነት ለመታገል ሃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባም ከመድረኩ ተገልጿል፡፡ #ላፍቶ_ቱሉ_ኤጀርሳ_ፓርቲ_ሚዲያ ህዳር 08/2016

የወረዳው ስፖርት ምክር ቤት ጉባኤ ተካሔደ። በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት የስፖርት ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ አካሔደ። ስፖርት ምክር ቤቱ በ
+5
የወረዳው ስፖርት ምክር ቤት ጉባኤ ተካሔደ። በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት የስፖርት ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤ አካሔደ። ስፖርት ምክር ቤቱ  በመደበኛ ጉባኤዉ ተቋሙ ባሳለፍነው 2015 በጀት አመት ያከናወናቸውን ተግባራት አፈፃፀም እና የ2016 በጀት አመት  ዕቅድ የምክር ቤቱ አባላት እና ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ቀርቧል። ጉባኤውን የመሩት የወረዳው ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ እና የስራ ኢንርኘራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ፅህፈት ቤት ሃላፊ ወ/ሪት አስረሳሽ አለሙ እና የወረዳው ወጣቶችና ስፓርት ፅህፈት ቤት ሃላፊ ወ/ሮ ሶስና ምህረት የአሰራር ማዕቀፎች እና የሚስተዋሉ ጉድለቶችን ማረም በሚያስችሉ ጉዳዬች ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተደርጓል። #ላፍቶ_ቱሉ_ኤጀርሳ_ፓርቲ_ሚዲያ ህዳር 07/2016

ሙሰና የጋራ ጠላታችን ነው በህብረት እንታገል ! በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ አስተዳደር ሙሰና የጋራ ጠላታችን ነው በህብረት እንታገል በሚል መሪ ቃል በወረዳው ከሚገኙ የመንግ
+8
ሙሰና የጋራ ጠላታችን ነው በህብረት እንታገል ! በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ አስተዳደር ሙሰና የጋራ ጠላታችን ነው በህብረት እንታገል በሚል መሪ ቃል በወረዳው ከሚገኙ የመንግስት ሰራተኞች ጋር ውይይት ተካሔደ። በመድረኩ ላይ በመሪ ቃሉ መነሻነት ለውይይት መነሻ የሚሆን ሰነድ ቀርቦ ሰፋፊ ሃሳብ አስተያየትና ጥያቄዎች ተነስተው ውይይት ተካሒዶባቸዋል። ውይይቱን የመሩት የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ዘሪሁን አሰፋ ከተሳታፊ የመንግስት ሰራተኞች በተነሱ ሃሳቦች ላይ ምላሽና ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን የሙስና ፅንሰ ሃሳብ ከመወያየት በዘለለ በጋራ በመፀየፍ መታገል ይገባናል በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል። #ላፍቶ_ቱሉ_ኤጀርሳ_ፓርቲ_ሚዲያ ህዳር 06/2016

ፕሬስ ሪሊዝ በክረምት የበጎ ፈቃድ ስራ መገንባት የጀመሩ 2 የአቅመ ደካማ ቤቶች በነገው እለት ተመርቀው ለባለቤቶቹ ይረከባሉ። በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ በክረምቱ ወቅት ከተ
+4
ፕሬስ ሪሊዝ በክረምት የበጎ ፈቃድ ስራ መገንባት የጀመሩ 2 የአቅመ ደካማ ቤቶች በነገው እለት ተመርቀው ለባለቤቶቹ ይረከባሉ። በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ በክረምቱ ወቅት ከተከናወኑ የበጎ ፈቃድ ተግባራት መካከል አንዱ የሆነውን የአቅመ ደካማ ቤት እድሳት ለማከናወን ግንባታውን ማስጀመሩ ይታወሳል ሆኖም ወረዳ አስተዳደሩ ባለሃብቶችን በማስተባበር የሁለት አቅመ ደካማ ቤቶችን በፍጥነት በማስገንባት በነገው እለት ለባለቤቶቹ የሚያስረክብ ይሆናል። #ላፍቶ_ቱሉ_ኤጀርሳ_ፓርቲ_ሚዲያ ህዳር 5/2016 ዓ.ም

በትምህርት ቤቱ ያሉ ቀሪ የመሰረተ ልማት ችግሮችን ለመፍታት ከወላጆች ጋር ውይይት ተካሔደ። የህብረተሰቡን የረጅም አመት ጥያቄ አፋጣኝ ምላሽ በመስጠት የተገነባው ''የመልካ ዳንሴ'' ትምህርት ቤት ተ
+8
በትምህርት ቤቱ ያሉ ቀሪ የመሰረተ ልማት ችግሮችን ለመፍታት ከወላጆች ጋር ውይይት ተካሔደ። የህብረተሰቡን የረጅም አመት ጥያቄ አፋጣኝ ምላሽ በመስጠት የተገነባው ''የመልካ ዳንሴ'' ትምህርት ቤት ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመሩ ይታወሳል ሆኖም በዛሬው እለት ቀሪ የመሰረተ ልማት ችግሮችን መፍታት በሚያስችል መልኩ የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ በተገኙበት ከተማሪ ወላጆች ጋር ውይይት ተካኃሒዷል። በውይይቱም የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ዘሪሁን አሰፋ እንደ አስተዳደር የሚጠበቅብንን በማድረግ የተማሪ ወላጆችን በማሳተፍ ትምህርት ቤቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ አስፈላጊ መሰረተ ልማትና ግብአት እንዲሟሉለት እናደርጋለን በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል። #ላፍቶ_ቱሉ_ኤጀርሳ_ፓርቲ_ሚዲያ ህዳር 2/2016

የህብረተሰባችንን የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመፍታት ተግተን እንሰራለን! አቶ ዘሪሁን አሰፋ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ አስተዳደር የህብረሰተቡ መሰረታዊ ችግር የ
+8
የህብረተሰባችንን የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመፍታት ተግተን እንሰራለን! አቶ ዘሪሁን አሰፋ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ አስተዳደር የህብረሰተቡ መሰረታዊ ችግር የተባሉትን በመለየት ለመፍታትና መንግስታዊ አገልግሎትን ማግኘት እንዲችል በትኩረት በመስራት ላይ ይገኛል። በዛሬው እለት በክላስተር 2 ብሎክ 10 የረጅም ጊዜ ጥያቄ የነበረ የመብራት ጥያቄ ምላሽ በማግኘቱና ለቀጣይ መሟላት ባለበት የመሰረተ ልማት ጥያቄ እንዲሁም የፀጥታ ሁኔታ ላይ ከህብረተሰቡ ጋር ውይይት ተካሒዷል። በውይይቱ ላይ በመገኘት መልዕክት ያስተላለፉት የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ዘሪሁን አሰፋ የህብረተሰባችንን የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመፍታት ተግተን እንሰራለን ብለዋል። የወረዳው ዋና ስራ አስኪያጅ ሲ/ር ቃልኪዳን ዮሐንስ በበኩላቸው ህብረተሰቡን በማሳተፍ የትኛውንም የልማት ስራ ለመስራት ሃላፊነታችንን እንወጣለን በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል። በመድረኩ ላይ የወረዳው የብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ምክትልና የፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ አቶ ዳዊት በቀለ ፣ የፖሊስ አባላት እንዲሁም የክላስተሩ ነዋሪዎች ተገኝተዋል። #ላፍቶ_ቱሉ_ኤጀርሳ_ፓርቲ_ሚዲያ ህዳር 02/2016 ዓ.ም