en
Feedback
የላፍቶ ቱሉ ኤጀርሳ ብልጽግና ፓርቲ

የላፍቶ ቱሉ ኤጀርሳ ብልጽግና ፓርቲ

Open in Telegram
213
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
አርሶ አደርና ከተማ ግብርና ልማት ጽ/ቤት የ6 ወራት አፈፃፀም ከባለድርሻ አካላት ጋር ገመገመ። የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ አስተዳደር አርሶ አደርና ከተማ ግብርና ልማት ጽ/
+6
አርሶ አደርና ከተማ ግብርና ልማት ጽ/ቤት የ6 ወራት አፈፃፀም ከባለድርሻ አካላት ጋር ገመገመ። የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ አስተዳደር አርሶ አደርና ከተማ ግብርና ልማት ጽ/ቤት በ6 ወራት ውስጥ የተከናወኑ ዝርዝር ተግባራትን ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሒዷል። በሪፖርቱ የታዩ ጠንካራና ደካማ ጎኖች በስፋት ቀርበው ውይይት የተካሔደባቸው ሲሆን በተነሱ ሃሳብና አስተያየቶች ላይ የወረዳው አርሶ አደርና ከተማ ግብርና ልማት ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ታምሩ ተፈራ ገልፀዋል። በመጨረሻም በጽህፈት ቤቱ የተሻለ አፈፃፀም እንዲኖር አስተዋጽኦ ላበረከቱ ባለድርሻ ተቋማትና የሴክተሩ ባለሞያዎች የምስጋና የምስክር ወረቀት ተበርክቷል። #lafto_tullu_ejersa_party_media ታህሳስ 16/2016

ሰላም የፖለቲካ መረጋጋት ከማረጋገጡም በላይ ለአዎንታዊ የህዝብ ለህዝብ ትስስር ከፍተኛ ሚና አለው፦ ኢትዮጵያ የተለያዩ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦች ፣ ህዝቦች እና ሀይማኖቶች ተዋደውና ተከባብረው የሚኖሩባት
ሰላም የፖለቲካ መረጋጋት ከማረጋገጡም በላይ ለአዎንታዊ የህዝብ ለህዝብ ትስስር ከፍተኛ ሚና አለው፦ ኢትዮጵያ የተለያዩ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦች ፣ ህዝቦች እና ሀይማኖቶች ተዋደውና ተከባብረው የሚኖሩባት ሀገር ናት። ሠላም የፖለቲካ መረጋጋትን በማስፈን ውጤታማ አስተዳደር እንዲኖር እና የዴሞክራሲ ተቋማትን መመስረት ያስችላል። ለኢኮኖሚ ዕድገት ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል፣ ኢንቨስትመንቶችን ይስባል፣ ለህዝቡ የስራ እድል ይፈጥራል። በተጨማሪም ሰላም ለሰብአዊ መብቶች መከበር እና መሰረታዊ አገልግሎቶችን እንደ ትምህርት፣ ጤና አጠባበቅ እና የመሰረተ ልማት ዝርጋታ አቅርቦት ወሳኝ ነው። ኢትዮጵያ ሰላምን በማስቀደም የውስጥ ግጭቶችን በሰላማዊ መንገዶች ብቻ በመፍታት በሀገር ግንባታ ላይ በማተኮር ለዜጎቿ ብሩህ ተስፋን ለማስፈን ተግታ እየሰራች ትገኛለች። የኢትዮጵያ ሰላም ከውስጥ ተጠቃሚነት በተጨማሪ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ጠቀሜታ አለው። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ስትራተጂካዊ ቦታ ላይ ስለምትገኝ የኢትዮጵያ ሰላም ለቀጣናችን መረጋጋት ወሳኝ ሚና አለው። ኢትዮጵያ የድንበሯን ሰላም በማስጠበቅ ለአካባቢው ሰላምና መረጋጋት የበኩሏን አስተዋጽኦ ማድረግ ትችላለች ለዛም እየሰራች ትገኛለች። ከዚህም በላይ ኢትዮጵያ ለሰላም የሰጠችው ቁርጠኝነት ለሌሎች ተመሳሳይ ፈተናዎች ለሚጋፈጡ ሀገሮች መነሳሳት ሆኖ የሚያገለግል ሲሆን ይህም በውይይት፣ በዕርቅና በሰብዓዊ መብቶች መከበር ግጭቶችን መፍታት እንደሚቻልና ማህበረሰቦችም ሊያድጉ እንደሚችሉ ያሳያል። ዞሮ ዞሮ በኢትዮጵያ ያለው ሰላም የራሱን ህዝቦች ብቻ ሳይሆን የበለጠ ሰላም የሰፈነበት እና የበለፀገ አለም እንዲሰፍን አስተዋፅዖ ያደርጋል።

"ከዕዳ ወደ ምንዳ'' በሚል መሪ ሀሳብ ለብልፅግና ፓርቲ አባላት የሚሰጠው ስልጠና የትምህርት ቤት እና ቢሮ አባላት ዛሬም እንደቀጠለ ነው ። #ላፍቶ_ቱሉ_ኤጀርሳ_ፓርቲ_ሚዲያ ታህሳስ 15/2016
+3
"ከዕዳ ወደ ምንዳ'' በሚል መሪ ሀሳብ ለብልፅግና ፓርቲ አባላት የሚሰጠው ስልጠና የትምህርት ቤት እና ቢሮ አባላት ዛሬም እንደቀጠለ ነው ። #ላፍቶ_ቱሉ_ኤጀርሳ_ፓርቲ_ሚዲያ ታህሳስ 15/2016

በወረዳ ደረጃ "ከዕዳ ወደ ምንዳ" 5ተኛ ዙር የአባላት ስልጠና ተጠናቀቀ። በብልጽግና ፓርቲ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ ከዕዳ ወደ ምንዳ በሚል መሪ ሀሳብ ለብልፅግና ፓርቲ አ
+6
በወረዳ ደረጃ "ከዕዳ ወደ ምንዳ" 5ተኛ ዙር የአባላት ስልጠና ተጠናቀቀ። በብልጽግና ፓርቲ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ ከዕዳ ወደ ምንዳ በሚል መሪ ሀሳብ ለብልፅግና ፓርቲ አባላት የሚሰጠው ስልጠና በ7ቱም ማህበራዊ መሰረቶች በግሩፕ ሀበመሆን ውይይት ሲካሄድ ቆይቶ በአንድ ማዕከል ማጠቃለያ በማድረግ ተጠናቋል። በማጠቃለያ መርሀ ግብሩም የመኖሪያ ፣ የሥራ እድል ፈጠራ ፣ የአርሶ አደር ፣ የወጣተ ሊግ እንዲሁም የሴት ሊግ አባላት የተሳተፉ ሲሆን የቢሮና የትምህርት ቤት አባላት በቀጣይ ስልጠናው ሲጠናቀቅ የሚጠቃለል እንደሚሆን ለማወቅ ተችሏል። መድረኩን ያጠቃለሉት የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ዘሪሁን አሰፋ እንዲሁም የፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ጌትሽ ጀማነህ በተነሱ ሃሳብ አስተያየትና ጥያቄዎች ላይ ሰፊ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። በስልጠናው ላይ የተሳተፉ አባላት በተከታታይ ቀናት በተሰጡ ስልጠናዎች ላይ ያገኙት ግንዛቤ የተሻለ መሆኑንን በመግለፅ ይህ ስልጠና በተጠናከረ ሁኔታ መቀጠል እንዳለበት ያነጋገርናቸው ተሳታፊዎች ገልፀዋል። #ላፍቶ_ቱሉ_ኤጀርሳ_ፓርቲ_ሚዲያ ታህሳስ 15/2016

"ከዕዳ ወደ ምንዳ " የአባላት ስልጠና የማጠቃለያ መድረክ በመካሔድ ላይ ነው። በብልጽግና ፓርቲ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ ከዕዳ ወደ ምንዳ በሚል መሪ ሀሳብ ለብልፅግና ፓር
+8
"ከዕዳ ወደ ምንዳ " የአባላት ስልጠና የማጠቃለያ መድረክ በመካሔድ ላይ ነው። በብልጽግና ፓርቲ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ ከዕዳ ወደ ምንዳ በሚል መሪ ሀሳብ ለብልፅግና ፓርቲ አባላት የሚሰጠው ስልጠና በ7ቱም ማህበራዊ መሰረቶች በግሩፕ በመሆን ውይይት ሲካሔድ መቆየቱ የሚታወስ ነው። በዛሬው እለትም የመኖሪያ ፣ የሥራ እድል ፈጠራ ፣ የአርሶ አደር ፣ የወጣተ ሊግ እንዲሁም የሴት ሊግ አባላት የማጠቃለያ መርሃ ግብር በመካሔድ ላይ ይገኛል። በማጠቃለያ መድረኩ ላይ በሁሉም የውይይት መድረኮች የተነሱ ዋና ዋና አንኳር ሃሳቦች በወረዳው ምክትል ፓርቲና የፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ አቶ ዳዊት በቀለ በማጠቃለያ መድረኩ ምላሽና ማብራሪያ እንዲሰጥባቸው ቀርበዋል። #ላፍቶ_ቱሉ_ኤጀርሳ_ፓርቲ_ሚዲያ ታህሳስ 14/2016

ከፊታችን ባሉ ቀናት በሚደረገው የአባላት ስልጠና አስመልክቶ ከበታች አመራሮች ጋር ውይይት ተካሔደ። በብልጽግና ፓርቲ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ ቅ/ጽ/ቤት ከፊታችን የሚደረገ
+3
ከፊታችን ባሉ ቀናት በሚደረገው የአባላት ስልጠና አስመልክቶ ከበታች አመራሮች ጋር ውይይት ተካሔደ። በብልጽግና ፓርቲ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ ቅ/ጽ/ቤት ከፊታችን የሚደረገውን የአባላት ስልጠና አስመልክቶ እየተደረገ በሚገኘው የቅድመ ዝግጅት ስራ ከበታች አመራሮች ጋር ውይይት በመካሔድ ላይ ይገኛል። #ላፍቶ_ቱሉ_ኤጀርሳ_ፓርቲ_ሚዲያ ታህሳስ 10/2016

''የዘመነ ንግድ ስርዓት ፤ ለላቀ ገቢ እድገት'' በሚል መሪ ቃል ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር ውይይት ተካሔደ። በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ አስተዳደር ንግድ ጽ/ቤት ''የዘመነ ን
+7
''የዘመነ ንግድ ስርዓት ፤ ለላቀ ገቢ እድገት'' በሚል መሪ ቃል ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር ውይይት ተካሔደ። በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ አስተዳደር ንግድ ጽ/ቤት ''የዘመነ ንግድ ስርዓት ፤ ለላቀ ገቢ እድገት'' በሚል መሪ ቃል ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር ውይይት ተካሒዷል። የወረዳው ም/ፓርቲ እና የፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ አቶ ዳዊት በቀለ ለውይይት መነሻ የሚሆን ሰነድ አቅርበዋል። መድረኩን የመሩት የን/ስ/ላ/ክ/ከተማ የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አባተ አበበ እንዲሁም የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ዘሪሁን አሰፋ ከተሳታፊዎች ለተነሱ አስተያየትና ጥያቄዎች ሰፊ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል። የወረዳው ንግድ ጽ/ቤት ሃላፊ ሲ/ር የሺ ሶዶ በበኩላቸው ነጋዴዎች በየትኛውም መልኩ ከመንግስት ጎን የቆሙና ለመንግስት ተገቢውን ግብር በመክፈል ሃላፊነታቸውን ለሚወጡ ነጋዴዎች ምስጋና አቅርበዋል። #ላፍቶ_ቱሉ_ኤጀርሳ_ፓርቲ_ሚዲያ ታህሳስ 07/2016 ዓ.ም

ከተማችንን ጽዱ እና ውብ የማድረግ ሃላፊነት የእኛ የነዋሪዎቿ በመሆኑ ሁሉም ማህበረሰብ ሃላፊነቱን መወጣት አለበት። ወ/ሮ በረከት ጤናው በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ ጽዳት አስ
+9
ከተማችንን ጽዱ እና ውብ የማድረግ ሃላፊነት የእኛ የነዋሪዎቿ በመሆኑ ሁሉም ማህበረሰብ ሃላፊነቱን መወጣት አለበት። ወ/ሮ በረከት ጤናው በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ ጽዳት አስተዳደር በዛሬው እለት ሳምንታዊ የጽዳት ዘመቻ ተካሔደ። የወረዳው ጽዳት አስተዳደር ጽ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ በረከት ጤናው ይህ የጽዳት ዘመቻ በተለያዩ በተለያዩ ተቋማት ክላስተርና ብሎኮች በተጠናከረ መልኩ እየተከናወነ የሚገኝ ተግባር መሆኑን በመግለጽ ከተማችንን ጽዱ እና ውብ የማድረግ ሃላፊነት የእኛ የነዋሪዎቿ በመሆኑ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል ሃላፊነቱን መወጣት አለበት። #ላፍቶ_ቱሉ_ኤጀርሳ_ፓርቲ_ሚዲያ ታህሳስ 06/2016 ዓ.ም

በፍጥነት በመገንባት ላይ የሚገኘው የዳቦ ፋብሪካ እንዲሁም የተማሪዎች መመገቢያ ምልከታ ተከናውኗል። በ60 ቀናት ዕቅድ በልዩ ትኩረት እየተከናወኑ ከሚገኙ ተግባራት መካከል አንዱ የሆነውና በፍጥነት በ
+9
በፍጥነት በመገንባት ላይ የሚገኘው የዳቦ ፋብሪካ እንዲሁም የተማሪዎች መመገቢያ ምልከታ ተከናውኗል። በ60 ቀናት ዕቅድ በልዩ ትኩረት እየተከናወኑ ከሚገኙ ተግባራት መካከል አንዱ የሆነውና በፍጥነት በመገንባት ላይ የሚገኘው የዳቦ ፋብሪካ እንዲሁም የተማሪዎች መመገቢያ ከክፍለ ከተማ በመጡ በወ/ሮ አለምፀሃይ በሚመራው መዛኝ ልዑክ ቡድን ምልከታ ተካሒዶበታል። #ላፍቶ_ቱሉ_ኤጀርሳ_ፓርቲ_ሚዲያ ታህሳስ 05/2016 ዓ.ም

በ60 ቀናት ዕቅድ በመከናወን ላይ የሚገኘው የሌማት ትሩፋት ተግባር በመስክ ምልከታ ተረጋግጧል። በ60 ቀናት ዕቅድ በልዩ ትኩረት እየተከናወኑ ከሚገኙ ተግባራት መካከል አንዱ የሆነው የሌማት ትሩፋት
+6
በ60 ቀናት ዕቅድ በመከናወን ላይ የሚገኘው የሌማት ትሩፋት ተግባር በመስክ ምልከታ ተረጋግጧል። በ60 ቀናት ዕቅድ በልዩ ትኩረት እየተከናወኑ ከሚገኙ ተግባራት መካከል አንዱ የሆነው የሌማት ትሩፋት ስራ ከክፍለ ከተማ በመጣ መዛኝ ልዑክ ቡድን ምልከታ ተካሒዶበታል። #ላፍቶ_ቱሉ_ኤጀርሳ_ፓርቲ_ሚዲያ ታህሳስ 05/2016 ዓ.ም

በመጠናቀቅ ላይ የሚገኘው የህፃናት ማቆያ በመዛኝ ቡድኑ ምልከታ ተካሔደ። በ60 ቀናት ዕቅድ በልዩ ትኩረት እየተከናወኑ ከሚገኙ ተግባራት መካከል አንዱ የሆነው እና በመጠናቀቅ ላይ የሚገኘው የህፃናት ማቆያ ከክፍለ ከተማ በመጣ መዛኝ ልዑክ ቡድን ምልከታ ተካሒዶበታል። #ላፍቶ_ቱሉ_ኤጀርሳ_ፓርቲ_ሚዲያ ታህሳስ 05/2016 ዓ.ም

የሰራተኛ ሪፎርም እየተካሄደ ያለበት ደረጃ ምልከታ ተካሔደ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ ቱሉ ኤጀርሳ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሃብት ልማት ጽ/ቤት የሰራተኛ ሪፎርሙ መከናወን መ
+3
የሰራተኛ ሪፎርም እየተካሄደ ያለበት ደረጃ ምልከታ ተካሔደ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ ቱሉ ኤጀርሳ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሃብት ልማት ጽ/ቤት የሰራተኛ ሪፎርሙ  መከናወን መጀመሩ ይታወቃል ሆኖም ተግባሩ ያለበት ደረጃ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ጽህፈት ቤት አማካሪ አቶ ፋሲል ተገኝተው ምልከታ አከናውነዋል። #ላፍቶ_ቱሉ_ኤጀርሳ_ፓርቲ_ሚዲያ ታህሳስ 5/2016

የተደራጀ የሚዲያ ሰራዊት ለዘላቂ ሰላም ዋስትና ነው! የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ በስሩ ለሚገኙ ወጣቶች የማህበራዊ ሚዲያ ስልጠና ሰጠ። የወረዳው
+8
የተደራጀ የሚዲያ ሰራዊት ለዘላቂ ሰላም ዋስትና ነው! የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ በስሩ ለሚገኙ ወጣቶች የማህበራዊ ሚዲያ ስልጠና ሰጠ። የወረዳው የብልጽግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ሰብሳቢ ወጣት ሩት አስማማው ወጣቶች በሚዲያ የነቃ ተሳትፎ በማድረግ የፀረ ሰላም ሃይሉን እንቅስቃሴ ማክሸፍ እንደሚገባ አሳስበዋል። #ላፍቶ_ቱሉ_ኤጀርሳ_ፓርቲ_ሚዲያ ታህሳስ 4/2016

ተልዕኮን በስኬት በመፈፀም ስራን በውጤት ማጠናቀቅ የብልጽግና ፓርቲ አመራር መገለጫ ነው! በንፋስ ሰልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ ጠቅላላ አመራር በ60 ቀን ዕቅድ በልዩ ሁኔታ በሚከናወኑ
+4
ተልዕኮን በስኬት በመፈፀም ስራን በውጤት ማጠናቀቅ የብልጽግና ፓርቲ አመራር መገለጫ ነው! በንፋስ ሰልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ ጠቅላላ አመራር በ60 ቀን ዕቅድ በልዩ ሁኔታ በሚከናወኑ ተግበራት ዙሪያ ውይይት አካሒዷል። ከአጀንዳዎቹ :- 👉 ስራ ዕድል ፈጣራ 👉 ሌላማት ትሩፋት 👉 ማዕድ ማጋራት በአጀንዳዎቹ ላይ የወረዳው ም/ስራ አስፈፃሚና የስራ ዕድል ፈጠራ ኢንተርፕራይዝ ልማት ጽ/ቤት ሃላፊ ወ/ሪት አስረሳሽ አለሙ እንዲሁም የወረዳው ፓርቲ ጽ/ቤት ምክትል እና የፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ አቶ ዳዊት በቀለ የቀጣይ የስራ ስምሪት ሰጥተዋል። #ላፍቶ_ቱሉ_ኤጀርሳ_ፓርቲ_ሚዲያ ታህሳስ 4/2016

ለተገልጋዩ ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት የህብረተሰባችንን እርካታ ማረጋገጥ ያስፈልጋል። አቶ ጌትሽ ጀማነህ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ አስተዳደር የአገልግሎት ቀንን በተለየ ሁ
+6
ለተገልጋዩ ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት የህብረተሰባችንን እርካታ ማረጋገጥ ያስፈልጋል። አቶ ጌትሽ ጀማነህ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ አስተዳደር የአገልግሎት ቀንን በተለየ ሁኔታ ለህብረተሰቡ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል። በዛሬው እለትም የወረዳ ፓርቲ ኮሚቴ የአገልግሎት አሰጣጡ ምን ይመስላል በሚል በአገልግሎት ሰጪ ተቋማት በመዘዋር ምልከታ አካሒዷል። የወረዳው ፓርቲ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ጌትሽ ጀማነህ ለተገልጋዩ ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት የህብረተሰቡን እርካታ ማረጋገጥ እንደሚገባ አሳስበዋል። #ላፍቶ_ቱሉ_ኤጀርሳ_ፓርቲ_ሚዲያ ታህሳስ 3/2016 ዓ.ም

ብልፅግና ፓርቲ የብዝኃ ዘርፍ የኢኮኖሚ መዋቅርን ማዕከል ያደረገ አካታች የኢኮኖሚ ስርዓት ለመገንባት አበክሮ እየሰራ ነው። ሀገራችን ኢትዮጵያ በሁለንተናዊ ብልፅግና የአፍሪካዊ የብልፅግና ተምሳሌት ለ
ብልፅግና ፓርቲ የብዝኃ ዘርፍ የኢኮኖሚ መዋቅርን ማዕከል ያደረገ አካታች የኢኮኖሚ ስርዓት ለመገንባት አበክሮ እየሰራ ነው። ሀገራችን ኢትዮጵያ በሁለንተናዊ ብልፅግና የአፍሪካዊ የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ ፓርቲያችን ሲነሳ የሀገራችንን ህዝቦች የአሁኑንና የመጭውን ትውልድ ጥቅምና ፍላጎትን ማዕከል ያደረገ አካታች የኢኮኖሚ ስርዓት ለመገንባት ነው። ኢኮኖሚያዊ ብልፅግናችን ሁሉን አቀፍ ማህበረሰብ ለመገንባት የምናደርገውን ጥረት የሚደግፍና አንድ የኢኮኖሚና የፓለቲካ ማህበረሰብ የመገንባት ትልም ያለው እንዲሆን ይሰራል። ስለሆነም በኢኮኖሚ ፕሮግራሙ የብዝኃ ዘርፍ የኢኮኖሚ መዋቅር የመገንባት፣ ሀብት ፈጠራን የሚያሳድግ ዕውቀት መር የኢኮኖሚ ስርአት፣በከተማ ልማትንና ፍትሀዊ ተጠቃሚነትን ያማከለ እና ጥራት ያለው የኢኮኖሚ ልማትና ምርታማነትን መሰረት ያደረገ የኢኮኖሚ ስርአት እየገነባ ይገኛል። በመሆኑም ፓርቲያችን በኢኮኖሚ ፕሮግራሙ በሀገራችን ምርትና ምርታማነትን እና ፍትሀዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የኢኮኖሚ ዋነኛ ተዋናይ መንግስት ፣ የግሉ ዘርፍና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ወሳኝ ናቸው ብሎ ያምናል። የለውጡ አመራር ወደ ፊት ከመጣ በኋላ በኢኮኖሚ ስርአት ውስጥ ያለውን የስርአት ጉድለት በማስተካከል ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት፣ አሰተማማኝ የውጭ ምንዛሬ ማስገኘትና የእዳ ጫና የማያጎብጠው ጠንካራ አገራዊ አቅም መፍጠር ተችሏል። ለሀገራችን እድገት የኢኮኖሚ ዘርፉ መጠናከር፣ የኢኮኖሚ ተዋናዮች ወደ ተጨባጭ የለውጥ ምህዋር ውስጥ እንዲገቡ ብልፅግና ያላሰለሰ ጥረት ያደርጋል።

ተልዕኮን በስኬት ስራን በውጤት! ብልፅግና ሀሳብም ውጤትም ነው። ፓርቲያችን እሩቅ ያልማል፣ አስቦ ያቅዳል፣ ያቀደውን በመፈፀም ስኬት ያስመዘግባል። ብልፅግና ፓርቲ የገንዘብን ብቻ ሳይሆን የጊዜ ስርቆ
ተልዕኮን በስኬት ስራን በውጤት! ብልፅግና ሀሳብም ውጤትም ነው። ፓርቲያችን እሩቅ ያልማል፣ አስቦ ያቅዳል፣ ያቀደውን በመፈፀም ስኬት ያስመዘግባል። ብልፅግና ፓርቲ የገንዘብን ብቻ ሳይሆን የጊዜ ስርቆትን ለማስቀረት እየተጋ ነው። የፕሮጀክት አፈፃፀሞቻችን ለዚህ አባባላችን ማሳያ ናቸው። በወር፣ በሶስት ወር፣ በግማሽ ዓመት ወይም በዓመት ለመፈፀም ታቅዶ በተያዘላቸው ጊዜ እየተከናወኑ ያሉ ፕሮጀክቶቻችን ከለውጡ በፊት በነበረው የአተገባበር ልማድ ለዓመታት ሊያዘግሙ የሚችሉ ብቻም ሳይሆን የመሰረተ ድንጋይ ተጥሎ ተረስተው የመቅረትም ዕድል እንደነበራቸው በዚሁ ምክንያት የመልካም አስተዳደር ችግር ሰለባ የነበረው ህዝባችን ምስክር ነው። መደበኛ ዕቅዶቻችን ብቻም ሳይሆኑ በ60 እና በ90 ቀናት ዕቅድ አፈፃፀሞቻችንም ቆጥሮ ወስዶ ቆጥሮ የማስረከብ አሰራር በማዳበራችን ከዕቅዳችን ዝንፍ ሳንል አንፀባራቂ ስኬቶችን አስመዝግበናል። የከተማ አስተዳደሩ የተሻለ አሰራርና ስርዓት ዘርግቶ የህዝባችንን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ በሚያደርጋቸው ጥረቶች የባለሀብቶችና የአጠቃላይ ህዝባችንም የልማት ተነሳሽነት ከፍ ብሏል። በተጨባጭም በርካታ ሰው ተኮርና የበጎ ፈቃድ ተግባራት በህዝባችን የገንዘብ የጉልበትና የእውቀት ተሳትፎ የተከናወኑ ናቸው። ህዝባችን ካለበት ውስብስብ ችግር እና ካለው ከፍተኛ የልማት ፍላጎት አንፃር ወገባችንን ጠበቅ አድርገን የብልፅግና ጉዟችንን እንድናፈጥን የሚጠይቁ ስራዎች ከፊታችን ናቸው። በየተሰማራንበት የስራ መስክ ተልዕኳችንን እንወስዳለን፣ በስኬት ፈፅመን ውጤት እናስመዘግባለን፤ የህዝባችንን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እናረጋግጣለን፣ ከተማችንንም የኢትዮጵያ ብልፅግና ተምሳሌት እናደርጋታለን! በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት

በተከናወኑ የፓርቲና የፖለቲካ ተግባራት ላይ ውይይት በማድረግ የቀጣይ ቀናት የስራ አቅጣጫ ተሰጠ። በብልጽግና ፓርቲ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ ቅ/ጽ/ቤት ፓርቲ ኮሚቴ በመደበ
+2
በተከናወኑ የፓርቲና የፖለቲካ ተግባራት ላይ ውይይት በማድረግ የቀጣይ ቀናት የስራ አቅጣጫ ተሰጠ። በብልጽግና ፓርቲ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ ቅ/ጽ/ቤት ፓርቲ ኮሚቴ በመደበኛ የፓርቲ እና የፖለቲ ተግባራት ላይ ውይይት ማካሔድ ተችሏል። የወረዳው ፓርቲ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ጌትሽ ጀማነህ በቀጣይ ቀናት በሚከናወኑ ተግባራት ዙሪያ የስራ   አቅጣጫ ሰጥተዋል። #ላፍቶ_ቱሉ_ኤጀርሳ_ፓርቲ_ሚዲያ ተሕሳስ01/2016

በሁለት ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ለወረዳ እና የበታች አመራሮችና ስልጠና ተሰጠ። በብልጽግና ፓርቲ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ ቅ/ጽ/ቤት በሁለት ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ለወረዳው አመራሮ
+9
በሁለት ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ለወረዳ እና የበታች አመራሮችና ስልጠና ተሰጠ። በብልጽግና ፓርቲ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቱሉ ኤጀርሳ ወረዳ ቅ/ጽ/ቤት በሁለት ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ለወረዳው አመራሮችና ለመሰረታዊ ፓርቲ አመራሮች የሚሰጠው የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ። ''የፖለቲካ ብልጽግናን የማረጋገጥ ትልም እና ፈተናዎቹ'' እንዲሁም የፓርቲው አይዲዎሎጂ ላይ ባተኮሩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የክ/ከተማው የፖለቲካና አቅም ግንባታ ሃላፊ አቶ መስፍን ግዛው እንዲሁም የፓርቲ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ ሃላፊ አቶ ግዛቸው ገ/ሚካኤል ስልጠናውን ሰጥተዋል። ይህ የአቅም ግንባታ ስልጠና የአመራርና አባላትን አቅም በተለየ ሁኔታ መገንባት ላይ ትኩረት ያደረገ ስልጠና መሆኑን በመግለፅ እስከ አባላት ድረስ ቀጣይነት እንደሚኖረው የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ጌትሽ ጀማነህ ገልፀዋል። ህዳር 28/2016 #ላፍቶ_ቱሉ_ኤጀርሳ_ፓርቲ_ሚዲያ