en
Feedback
ነፃ ዓለም✨✨✨

ነፃ ዓለም✨✨✨

Open in Telegram

✨አጫጭር ወጎች ✨ልቦለዶች ✨መፃህፍት ✨profile picture ✨የተለያዩ ሰዎች ድንቅ አባባል ✨ግጥሞችን ያገኛሉ። ለሀሳብ ለአስተያየት @netsi2_9

Show more
Ethiopia7 941The category is not specified
2 659
Subscribers
+3324 hours
+1157 days
+13230 days
Posts Archive
ያለማቋረጥ ማንበብ በአስደናቂ ታሪኮች መመሰጥ ና መርካት በመቀጠል ቀጣዩን መጠበቅ ይህ  ከሆነ ፍላጎታቹ ይኸዉ !!!!! 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/addlist/RrQMv0KciDJmMzE0

photo content

ከዕለት ተዕለት ውጥረት እረፍት የሚሰጡ፣ መንፈስን የሚያስደምሙና ልብን የሚነኩ ምርጥ የስነ-ጽሁፍ ቻናሎችን በአንድ ላይ ​📜 ጥቃቅን ስሜቶችን የሚገልጹ ድንቅ ግጥሞች ​☕️ ከቡና ጋር የሚነበቡ ውብ አጫጭር ወጎች ​💡 ህይወትን በአዲስ መነፅር የሚያሳዩ ጥቅሶች ​እርስዎም የጥበብ ረሃብዎን ይወጡ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 ​ https://t.me/addlist/RrQMv0KciDJmMzE0

እንመኛለን....." እንጥራለን.... ተስፋችን ብዙ ነው። ከትላንት መንጭቆ ያወጣን ዛሬን ያሳያን ነገንም ያስናፈቀን ተስፋ ነው። ተስፋ በልብ ያለው ሰው ነገ አያስፈራራውም....ከተራራው ጀርባ ያለው
እንመኛለን....." እንጥራለን.... ተስፋችን ብዙ ነው። ከትላንት መንጭቆ ያወጣን ዛሬን ያሳያን ነገንም ያስናፈቀን ተስፋ ነው። ተስፋ በልብ ያለው ሰው ነገ አያስፈራራውም....ከተራራው ጀርባ ያለውን ሜዳ አቅርቦ ያያል። ህይወት ያለ ተስፋ አሰልቺ እዳ ናት...!!! ✍ነፂ_ነኝ #ነፃሁኑልኝ ✨✨✨
@NetsaAleme

የ24 ዓመቷ ሰናይት ከስድስት ዓመታት የፍቅር አየር ላይ ከተንሳፈፈች በኋላ በመጨረሻም የሰርጓ ዕለት ደረሰ። የሳሎኑ አየር በዕጣንና በሚጣፍጥ የቡና ጠረን ታውኳል። ነጭ ካባዋን አድርጋ፣ ዓይኖቿ በፍቅርና በደስታ እያበሩ ሙሽራዋ በፍቅር ዓይኖቿን እያየ ሊወስዳት የሚመጣበትን ደቂቃ በጉጉት ትቆጥራለች። ​በዚያው ቅጽበት ግን ስልኳ በእጇ ላይ ተንቀጠቀጠ። የፍቅረኛዋ ዳዊት ስም ማያ ገጹ ላይ በራ። ​"ዳዊቴ... መጣህ?" አለች ድምጿ በፍቅር ተሞልቶ። ​ከሌላው ጫፍ ግን የሚሰማው የእርሱ የመተንፈስ ድምፅ ብቻ ነበር። ከጥቂት ሰከንዶች ዝምታ በኋላ በቅዝቃዜ የተሞላ ድምፅ ከስልኩ ወጣ... ​"ሰናይት... ይቅርታ አድርጊልኝ። ይሄን ሰርግ መቀጠል አልችልም አትጠብቂኝ።" ​ቃላቱ እንደ ጦር ልቧን ወጉት። ከማመን በላይ ሆነባት "ዳዊት... ምን ማለትህ ነው? ቀልድ ነው አይደል?" ብላ ሳትጨርስ ስልኩ ተዘጋ። ​ዓለም በፊቷ ጨለመች ሳሎን ውስጥ የተቀመጡት ዘመዶቿ በፍርሃት እያዩአት ሳትታወቃት ከቤት ወጥታ በከባድ ዝናብ ውስጥ በባዶ እግሯ መሮጥ ጀመረች የእንባዋና የዝናቡ ውኃ ተቀላቅሎ ፊቷን ያጠበው ነበር መንገድ ስታቋርጥ የፍሬን ድምፅ ተሰማ... ከዚያም ሙሉ በሙሉ ጸጥታ። ​ከሶስት ቀናት በኋላ... ​ሰናይት በነጭ የሆስፒታል አልጋ ላይ ተኝታ ዓይኖቿን በዝግታ ከፈተች የመድኃኒት ጠረን አፍንጫዋን መታውከጎኗ በእድሜ ጠንከር ያለና በወዛም ፊቱ ላይ የጭንቀት ምልክት የሚታይበት አንድ እንግዳ ሰው ተቀማጭ ተመልከታለች። ​"እንኳን ማርያም ማረችሽ..." አለ ሰውየው ድምፁ በሩህሩህነት ተሞልቶ። ​ሰናይት በደረቀ ጎሮሮዋ "እኔ... እኔ የት ነኝ? እርሶስ ማን ነዎት?" ስትል በስስት ጠየቀች። ​ሰውየው በእርጋታ ተነስተው ከጎኗ ተቀመጡ "አደጋ አጋጥሞሽ መንገዱ ላይ ወድቀሽ ያገኘሁሽ እኔ ነኝግን... ሆስፒታል ካደረስኩሽ በኋላ፣ ከኪስሽ ውስጥ የወደቀውን ደብዳቤ አነበብኩት..." ​የሰውየው ዓይኖች በእንባ ተሞሉ። ሰናይት ደንግጣ "ምን ደብዳቤ?" አለች። ​"ሰናይት... ይህ ደብዳቤ ከመሞቱ በፊት አባቴ የፃፈው ደብዳቤ ነው ላለፉት ሃያ ዓመታት ስፈልገው የነበረው፣ የቤተሰባችንን ሚስጥር የሚፈታው ደብዳቤ በእጅሽ ውስጥ እንዴት ሊገኝ ቻለ?" ​ሰውየው እጁን ወደ ኪሱ ሰዶ የታጠፈውን ያረጀ ወረቀት ሲያወጣ ሰናይት በድንጋጤ አፏን ያዘች! ምክንያቱም ደብዳቤው ላይ የተጻፈው ስም የእርሷ ሳይሆን... ​ ሙሉ ታሪኩን ለማግኘት 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 ​https://t.me/addlist/RrQMv0KciDJmMzE0

ቀጣዩ ክፍል መቼ ነው የሚለቀቀው?" ብለህ በጉጉት የምትጠብቁት ታሪክ ይፈልጋሉ? ⏳🔥 ​💫 ልብ የሚያሞቁ የፍቅር ወጎች 🎭 ያልተጠበቁ ውሳኔዎችና 🥀 የማይረሱ የሕይወት ገጠመኞች ​ጊዜያቹን በከንቱ አታጥፋ ድንቅ ታሪኮችን አሁኑኑ ማንበብ ጀምሩ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/addlist/RrQMv0KciDJmMzE0

ቀጣዩ ክፍል መቼ ነው የሚለቀቀው?" ብለህ በጉጉት የምትጠብቁት ታሪክ ይፈልጋሉ? ⏳🔥 ​💫 ልብ የሚያሞቁ የፍቅር ወጎች 🎭 ያልተጠበቁ ውሳኔዎችና 🥀 የማይረሱ የሕይወት ገጠመኞች ​ጊዜያቹን በከንቱ አታጥፋ ድንቅ ታሪኮችን አሁኑኑ ማንበብ ጀምሩ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/addlist/RrQMv0KciDJmMzE

ከማያውቁት መላክ የሚያውቁት ሰይጣን ይሻላል። ያሳደገኝ አባባል ነው። የሚያቁት የተላመዱት ሰይጣን ቁጡ ነው ወይስ ሳቂታ ...መላመድ መግባባትን ያመጣል አይደል። ቢቆጣም ቁጣውን እንለምደዋለን...ወይ
ከማያውቁት መላክ የሚያውቁት ሰይጣን ይሻላል። ያሳደገኝ አባባል ነው። የሚያቁት የተላመዱት ሰይጣን ቁጡ ነው ወይስ ሳቂታ ...መላመድ መግባባትን ያመጣል አይደል። ቢቆጣም ቁጣውን እንለምደዋለን...ወይም የሚያስቆጣውን ስለምናውቅ እንዳይቆጣን እንጠነቀቃለን። የሚያውቁት ሰይጣን ...ቀንዱ አያስፈራማ ...ጭራውም ትልቅ ቢሆንም ኖርማል ነው። ምክንያቱም ተላምደነዋል። መላአኩስ....ብርሀኑ ራሱ ይገፈትረን ይሆናል። ጨለማን እያየ ያደገ ልጅ በብርሀንፊት አይኑን ቢገልጥም ጨረሩ ሊያውረው ይችል ይሆናላ....? በዛ እሳቤ ነው ያደኩት....ጨለማዬን አዝዬው ኑሬለሁ....ብርሀን እንዳይረታብኝ ከብርሀን ስሸሸግ.....እንደ ምርግ ትከሻዬን ያጎበጠውን በረዶ ከፀሀይ ስከልለው ሟሙቶ እንዳያልቅብኝ ስፈራ....እንደዛ ነው እድገቴ....! የተዘጋብኝን በር መክፈት እየቻልኩኝ። የማልከፍተው....ከአዲስ አለም ጋር መኖርን ስለምፈራው ነው.....አዲስ ግኝት ያሰጋኛል። እጠረጥራለሁ....ጨለማ ውስጥ ስሆን ምንም ስለማይታየኝ ማንም እንደማያየኝ እርግጠኛ ነኝ። ብርሀን ሲሆን ሁሉምን ሳይ...ሁሉንም ሳይ ግን የምዋጥ የምሰለቀጥ ይመስለኛል። ብርሀኑን ተጠቅሜ ከሚያስፈራራኝ አውሬ ለማምለጥ አልመኝም። የኔ መሻት በጨለማው ውስጥ አድብቶ ከሚጠብቀኝ አውሬ ተከልሎ ተደብቆ መኖር ነው። ከመቼ መቼ በላኝ እያሉ በጨለማው እያፈገፈጉ መኖር...! ✍ነፂ #ነፃሁኑልኝ ✨✨✨
@NetsaAleme

📖✨ ከዕለታዊ ሕይወትህ ለጥቂት ደቂቃዎች ሸሽተህ… ወደ ሌላ ዓለም መግባት ትፈልጋለህ? ❤️ አፍቃሪ ነብሶች 💔 ልብ ሰባሪ ታሪኮች 🔐 ምስጢር የተሞሉ ታሪኮች 🥀በ  ናፍቆት የተሞሉ ገፀ ባህሪያት 📚 በአጠቃላይ አስደናቂ ልቦለዶች… ሁሉንም በአንድ ቦታ! ✨ አንድ ታሪክ ትጀምራለህ… ከዚያም “ቀጣዩ ምን ይሆን?” ብለህ መጠበቅ አትችልም። 😍📖 አሁኑኑ ቤተሰቡን ተቀላቀል 👇👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/addlist/ntI4_0yP4Gk0ZmM0

🥀 በዚያች ዝናባማ ምሽት የተቀየረው ህይወት... ​እሁድ ምሽት ነበር። ዝናቡ በኃይል እየጣለ የካፌውን መስኮት ይመታል። እጄ ላይ ያለውን የሞቀ ካፑቺኖ እየተጎነጨሁ በበር በኩል የሚገቡትን ሰዎች  እመለከታለሁ። ​በድንገት በሩ ተከፈተና እርሷ ገባች። ከዝናቡ ለመጠለል እየሮጠች ስለነበር የለበሰችው ረጅም ካፖርት በትንሹ ረሷል። ፀጉሯ ላይ የወደቁትን የዝናብ ዘጠቢዎች እያረገፈች ዓይኖቿን ወደ ካፌው አማተረች። ሁሉም ወንበሮች ተይዘዋል። ብቸኛው ክፍት ቦታ... ከእኔ ፊት ለፊት ያለው ወንበር ብቻ ነበር። ​አይኖቻችን ተገናኙ። ፈገግ ብላ ወደ እኔ ተራመደች። ​"ይቅርታ... እዚህ መቀመጥ እችላለሁ?" አለችኝ—ድምጿ ልክ እንደ ዝናቡ ዜማ ለስላሳ ነበር። ​"ተቀመጪ" አልኳት፣ ልቤ ባልተለመደ ፍጥነት ይመታ ጀመር። ​ተቀመጠች። ቦርሳዋን ስታስተካክል ከውስጡ አንድ አሮጌ መጽሐፍ ወድቆ እግሬ ስር ወደቀ። ጎንበስ ብዬ አነሳሁት። የመጽሐፉን ርዕስ ስታየው ደነገጥኩ—ለዓመታት ስፈልገው የነበረው፣ የእኔው የሚወደደው ደራሲ  ይስማአከ ወርቁ ድንቅ ስራ ነበር ​"ይህንን መጽሐፍ ታነቢዋለሽ?" አልኳት እየገረመኝ። ​ቀና ብላ አየችኝና ዓይኖቿ በደስታ በሩ "አዎ! የሚገርምህ ይሄን መጽሐፍ ያገኘሁት ዛሬ ከሰአት አሮጌ መጻሕፍት መሸጫ ውስጥ ነው። በተለይ ገጽ 42 ላይ ያለው ግጥም..." ​"...የነፍስን ረሃብ ይቆርሳል!" ብዬ አቋረጥኳት። ​ሁለታችንም በአንድ ጊዜ ሳቅን። በዚያች ቅጽበት በዙሪያችን ያለው የካፌ ድባብ  የዝናቡ ድምፅ... ሁሉም ነገር ቆመ። በዓለም ላይ እኔና እሷ ብቻ ያለን ያህል ተሰማኝ። እስከ ሌሊቱ 5 ሰዓት ድረስ ስለ መጻሕፍት፣ ስለ ህይወት፣ ስለ ፍቅር አወራን። ስንለያይ ስልክ ቁጥሯን በወረቀት ላይ ፅፋ ሰጠችኝ። ​ቤት ደርሼ ወረቀቱን ስከፍተው ግን ከቁጥሩ ስር የተጻፈውን አጭር መልእክት አየሁና ደነገጥኩ... ​ ​❤️ ሙሉውን የፍቅር ታሪክ ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ፡ 👇👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/addlist/wj1FH6fJLSExZmM0

ተወራርጃለሁ ባርያሽ ከአለም ጋራ..." እንዳታሳፍሪኝ እመቤተ አደራ ...."!!! ጷጉሜ 1
ተወራርጃለሁ ባርያሽ ከአለም ጋራ..." እንዳታሳፍሪኝ እመቤተ አደራ ...."!!!
ጷጉሜ 1

ከሌሊቱ ስምንት ሰዓት። የዝናቡ ውሽንፍር የጥንታዊውን ሕንፃ መስኮቶች ያንቀጠቀጣቸዋል። መብራቱ ድንገት ጠፍቶ ሙሉ በሙሉ በጨለማ ስንዋጥ የእርሷ  አየር አወጣጥ ብቻ ነበር በክፍሉ ውስጥ የሚሰማው። ​እጄ ላይ ያለው የቆየ ማስታወሻ ደብተር በደም የተበከሉ ገጾች አሉት። ደብተሩን ያገኘሁት ከሃያ ዓመታት በፊት በድንገት ከተሰወረው ወንድሜ አልጋ ስር ነበር። ገጹ ላይ ከተጻፉት አጫጭር ዓረፍተ ነገሮች መካከል አንዱ መስመር የልብ ምቴን አፈጠነው ​"ይህንን ካነበብክ እኔ በሕይወት የለሁም። ነገር ግን በሩን ከከፈትከው... እርሷን ታገኛታለህ። እባክህን ወደ ምድር ቤቱ እንዳትወርድ!" ​ከእግሬ ስር ያለው እንጨት የወለል ሳህን "ክራክ..." ብሎ ሲሰነጠቅ ድንገት ከጀርባዬ የሚቃጠል የእንፋሎት ትንፋሽ ተሰማኝ። ዞሬ ለማየት ስቃዥ፣ የቀዝቃዛ እጅ ጣቶች ከአንገቴ በስተጀርባ በዝግታ ይዳብሱኝ ጀመር... ​ ​ ሙሉውን ታሪክ ለማግኘት 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/addlist/wj1FH6fJLSExZmM0

የታሪክ አፍቃሪያን የታላቹ? ​የሀገራችንን ድንቅ ስነ-ፅሁፎች፣ ወጎች፣ ግጥሞች እ የሚያቀርቡ ምርጥ የቴሌግራም ቻናሎችን በአንድ ቦታ አዘጋጅተንላችኋል። ​📖 ልብ ወለድ እና አጫጭር ታሪኮች ​✍️ ልብ የሚነኩ ግጥሞች እና ቅኔዎች ​🧠 የፍልስፍና እና የ ስነ-ልቦና ፅሁፎች ​📜 የታሪክ እና የባህል ማስታወሻዎች ​ ሁሉንም በአንድ ላይ 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 ​https://t.me/addlist/wj1FH6fJLSExZmM0

ናፍቆት ያነጫንጫል ናፍቆት አመል ይነሳል ናፍቆት እንባን ያፈሳል.. ..ናፍቆት ልክ እንደ ፍቅር የማያብራሩት ግን ጥልቅ ስሜት ነው። እና ምን ልልሽ ነው ናፍቀሽኛል መቋቋም ከምችለው በላይ አልፎ የማ
ናፍቆት ያነጫንጫል ናፍቆት አመል ይነሳል ናፍቆት እንባን ያፈሳል..
..ናፍቆት ልክ እንደ ፍቅር የማያብራሩት ግን ጥልቅ ስሜት ነው። እና ምን ልልሽ ነው ናፍቀሽኛል መቋቋም ከምችለው በላይ አልፎ የማወራው እስከማይመስለኝ ድረስ። ራሴን በራሴ ማበርታቱ የዝብዘባ ተረት እስኪመስለኝ የሰወች የማፅናኛ ቃል እኔን ካለመረዳታቸው የፈረዱብኝ እስኪመስለኝ ድረስ ውስጥ ውስጤን ብርድ እስኪያንቀጠቅጠኝ...ልቤ የጭንቅ ምት እስክትመታ....ተኝቼም እስከማይሽ ግን እንደማልነካሽ ሳስብ እስከሚከፋኝ ድረስ ማርያም እማዬ ናፍቀሽኛል። ✍ነፂ

«በዚህ መልኩ ባታዬኝ ደስ ይለኝ ነበር።» አለች በሚያሳዝን ድምፅ። «እኔን ከዚህ በባሰ ሁኔታ አይተሽኝ የል?» አልኩ! «እእእእ.....ልጆቹ ደህና ናቸው?» «ደህና ናቸው።» «ጥሩ!» ዝም ዝም ተባባልን። ዝም አባባሏ የበፊቱን ዝመታዋን እያስታወሰ ረበሸኝ። «በጣም ይቅርታ!» አልኩ በጭንቀት! አሁንም ዝም አለችኝ። «አውቃለሁ ብዙ ነገር እንዳበላሸሁብሽ። ግን እመኝኝ ያንቺ ብቻ አይደለም የኔም ህይወት ተመሰቃቅሏል። ዛሬም ድረስ እወድሻለሁ ሩሀማ። ያንድ ቀን ስህተት ነው ሒወቴን ያበላሸው። እወድሻለሁ ብያት ራሱ አላውቅም። እሷ ለኔ ሀላፊነት ብቻ ነች።» ከመሔዷ በፊት የሚሰማኝን ሁሉ እንድታውቅልኝ ቀበጣጠርኩ። እሷ ግን በዝምታዋ ፀናች። ራይዱ ሲመጣ ዝም እንዳለች ጥላኝ ልትገባ ስትል አልቻልኩም። «በናትሽ የሆነ ነገር በይኝ! ዛሬም በዝምታ ከሔድሽ አብዳለሁ!» ብዬ ጮህኩባት። በቀስታ ወደኔ ዞረች። «አይቻሀለሁኮ የዛን ቀን!» አለችኝ በቀዘቀዘ ድምፅ። ፊቷ ላይ ያለው ጭካኔ ስካሯን አጥፍቶታል። ፍርሀት ተሰማኝ። «አይቼሀለሁኮ የዛን ቀን! የአንድ ቀን ስህተትማ አይደለም። ድንገት የተሳሳተ ሰው ጧት ሲነሳ እንደዛ አይደለም የሚሆነው። አንተ ማመን አልፈለግክም እንጂ ከኔ 'ህግ' የበዛበት ህይወት ማምለጫ ስትፈልግ ነው የኖርከው... «አይቼዋለሁ አስተቃቀፍህን! ከ'እወድሻለሁ'ም ይበልጣል። 'ታስፈልጊኛለሽ' ነው ያልካት። ለሴት ልጅ ከዚህ የበለጠ ምን አለ? ለዛ ነው በፍጥነት የወለደችልህ። ከንግግርህ ይልቅ አስተቃቀፍህ መተማመኛ ሰጥቷት ነው ያመነችህ። አንተም ቃል አውጥተህ እወድሻለሁ የማትላት ስለማትወዳት አይደለም። የጥፋተኝነት ስሜት ስለሚሰማህ ነው። በኔ በኩል ይቅርታ ካደረኩልህ ቆይቻለሁ። አንተ ነህ ራስህን ይቅር ያላልከው።» ብላኝ ወደ መኪናው ገባች። መኪናው ሲሔድ እኔ ቁሜ ቀረሁ። መውጣት የጀመረው እንባዬ ደርቆ ሁለመናዬ ደነዘዘብኝ። የያዝኩትን ወተት እና ቢራ መሬት ላይ አስቀመጥኩት። እኔም ተቀመጥኩ። ህመም ተሰማኝ። ያጠጣችኝ መድሀኒት መስራት ጀመረ። ፨፨፨፨ #መፅሀፍ_ማሙሽ #ደራሲ_ማይክል_አዝመራው #ምንጭ_Facebook @NetsaAleme

የዛን ቀን... ከስራ እንደወጣሁ ሻወር ወሰጄ ችብሴን አቀራርቤ፣ ሪሞት አንስቼ ልክ ፊልሜን ሳስጀምር...አንድ ወታደር ብቻ የምትመራው ጄነራሏ ፍቅረኛዬ ደወለች። «ላይብረሪ ውስጥ እያዬሁህ አይደለም!» አለችኝ እንዳነሳሁት። መርህ ትወዳለች። መርህ አልባ ሰው ደግሞ ትጠላለች። እኔም ከሷ እኩል ለመሔድ ከአባቱ ጋር ገበያ እንደሚሔድ ህፃን በሶምሶማ እከተላታለሁ። «ገና አሁን ቤት መግባቴ ነው። ትንሽ ላረፍድ እችላሁ!» አልኩ የቲቪውን ድምፅ እየቀነስኩ። «ተነስ ተነስ አትስነፍ!  ረሳኸው እንዴ?...ይሔን ማስተርስ እንደጨረስን እንጋባለንኮ! አልጓጓህም?» ያዝ እንግዲህ! ወደ ላይብረሪ ልሔድ ስነሳ ጓደኛዬ ብሩክ እየተጣደፈ ገባ። ሩሀማ "ከብሩክ ራቅ! ማሰቢያህን ደፍኖ በልቡ ብቻ የሚመራ በግ ነው የሚያደርግህ!" ብላ የመከረችኝ ትዝ ብሎኝ ምንም ቢለኝ እሽ እንደማልለው ለራሴ ቃል ገባሁ። «በፍጥነት ተዘጋጃጅ  ዴት አለብህ!» አለኝ ለመረጋጋት እየሞከረ። «የምን ዴት?» አልኩ ግራ እየተጋባሁ። «ማርቲን ላገኛት ነበር። አሁን ደውላ 'ጓደኛዬ አብራኝ ነች ጓደኛህን ይዘኸው ና' ብላኛለች።» «አላውቅልህም! እኔ ያንተ ማሟያ ነኝ እንዴ?» «ይሔኮ ለጓደኝነት ብለህ የምታደርገው ነገር ነው። በዛ ላይ ልጅቷ ሁሉ ነገሯ አንተ የምታስባት አይነት ነች!» «ሰውዬ ብቻዬን መኖሬን ነው'ዴ የምታዬው? ትዳር አለኝኮ!» «እኔስ መች ተፋታ አልኩህ?» «እና ምንድን ነው የምትለኝ?» «እየውልህ! ፈተና ወድቃ ልታፅናናት ነው ያመጣቻት። ከፈለካት አንዴ ለምጠሀት ወደ ትዳርህ ትመለሳለህ። ካልፈለካት ደግሞ ማርቲን ለይቼ እስክወስዳት ብቻ ትይዝልኛለህ።» "አልፈልግም" እያልኩ እየተከራከርኩት ልብሴን ለባብሼ ወጣሁ። ሩሀማ እንደፈራችው በቁሜ በግ ያደረገኝ መሰለኝ። ራሴን ጠላሁት። ሳወራ ራሱ "በኧኧኧኧ" የሚል ድምፅ ነው የሚሰማኝ። ክለብ እንደገባን ማርቲ ቀድማ ተነስታ ሰላም ስትለን ተንጠራርቼ በማርቲ ትከሻ በኩል ልጅቷን ለማዬት ሞከርኩ። እስከ እግሯ የሚደርስ ጃኬት ለብሳ ፀጉሯ ላይ ሻርፕ ጣል አድርጋለች። ከቅላቷ ጋር የሶሪያ ስደተኛ ነው የምትመስለው። ሩሀማ ስትደውል "ነገ እንገናኝ ደክሞኛል!" የሚል ቴክስት ላኩላት። ልጅቷ አርባ ደቂቃ ያህል ምንም አላወራችም። ፊትለፊቷ የተደረደሩት ባዶ ጠርሙሶች እየጨመሩ ሲመጡ አፏ እየተላቀቀ መጣ። ማውራት ስትጀምር እንደገና ዝም ብላ የቆዬችበት አርባ ደቂቃ ናፈቀኝ። ቆንጅዬ ደደብ ነች። በዚህ እወቀቷ ወደቅኩ ብላ ማዘኗ ገረመኝ! ምን ጠብቀሽ ነበር ሙኒት? «ና እንደንስ!» አለችኝ ድንገት ከወንበሩ እየወረደች። «እኔን?» አልኩ በድንጋጤ። ራሷን በአወንታ ነቀነቀች። «እንደሱ ብለሽ?» አልኳት ጃኬቷን እያዬሁ። አውልቃ አስቀመጠችው። ከጃኬቱ ውስጥ የሆነች የምታምር ሰው ወጣች። አባቴ በጋዜጣ ጠቅልሎ የሚያመጣልኝን ኬክ አስታወሰችኝ። ስትውረገረግ ሰውነቷ ገረመኝ! መካከለኛ ቁመት፣ ሸንቅጥ ያለች፣ ነፍሰ ቀላል ነች። እንዲህ አይነት ሴቶች መኝታ ቤት ለአያያዝ ምቹ ስለሚመስሉኝ ያሻፍዱኛል። አልጋው ካልተመቸህ ብድግ አድርገህ ወደ ሶፋው... እያዬኋት ሽፍደት መላ ሰውነቴን ተቆጣጠረው። ሴክስ ካደረኩ ምን ያህል ጊዜ ሆነኝ? ጥጥጥጥንት በቅድመ ሩሀማ ጊዜ...እቴጌ ሜላት የተሰኘች ኤክሴ ጋር  እንዳደረኩ ነኝ። ተጠራቅሞ መጣብኝ መሰለኝ መላ ሰውነቴ በእንትኔ መመራት ጀመረ። እንደዚህ ሸፋዳ ነኝ? እየደነሰች በጨረፍታ አዬት ታደርገኝና ፈገግ ትላለች። ጥርሷን ሳዬው ደግሞ ልቤ ሙሙት ይልብኛል። የፈጣሪ ያለህ! የፈጣሪ ያለህ! የፈጣሪ ያለህ! አዳሬን እንዲሁ ስል አነጋሁ። አዳም ሔዋንን ካወቃት በኋላ ለተወሰነ ደቂቃ "እንኳን ከገነት ተባረርኩ" የሚል ስሜት ተሰምቶት ነበር እየተባለ ይታማል። እኔም እንደዛች ያለች ሀሴት ተሰማችኝ። አንሶላ ውስጥ እንዳለሁ ያቺን ለማቀፍ የምትመች ሰው ከጀርባዋ እቅፍ አደረኳት። አውቃለሁ እንደዚህ ማድረግ እንደሌለብኝ። ግን ራሴን ማስቆም አልቻልኩም። ሀምሳ ፐርሰንቱ እኔ መቶ ፐርሰንት ወዷታል። ወዲያው "ቀጭ" የሚል ድምፅ ከወደ በሩ ስሰማ ደንብሬ ተነሳሁ። የሆነ ሰው ገብቶ ተመልሶ የወጣ መሰለኝ! ያገኘሁትን ታጥቄ ወደ ሳሎን ወጣሁ። ማንም የለም። ዞር ስል የሳሎኑ በር ተከፍቶ እየተወዛወዘ ነው። በፍጥነት በመስኮቱ በኩል አየሁ። ሩሀማ ነች። ፈጠን ፈጠን እያለች ወጥታ ሔደች። አልተመለሰችም። አንዳንድ ሰው እንደዚህ ነው። ሲገባ አታዬውም። ሲወጣ ግን አፈራርሶህ ነው የሚወጣው። መሔዱን ትሒድ እሺ! እንዴት ዝም ብላ ትሔዳለች? ምናለ ትንሽ ብታዋርደኝ? ምናለበት በሆነ ነገር አናቴን ብላኝ...ተፍታብኝ ብትወጣ? እንዴት ዝም ብላ ወጥታ ትሔዳለች? ፨፨፨ ከዛን ቀን ቡኃላ... ሙኒት ምን እንደተፈጠረ ስላላወቀች ወደኔ ቤት መምጣቷን አላቆመችም።  እኔም ብቻዬን መሆን ስላልፈለኩ "አትምጭብኝ" አልላትም። በጣም ከማፍርበት ባህሪዬ አንዱ አሁንም ድረስ ሙኒት ታሻፍደኛለች። ገና "ሙኒት" የሚለውን ስም ስሰማ ሁሉ ይቆምብኛል። አፈር ልብላ! አፈር ያስበላኝ! ንጥር ንጥር እያለች በአጠገቤ ስታልፍ ቅልም አድርጌ አንሶላ ውስጥ አስገባታለሁ። እሷ ደግሞ በአመቱ ወንድ ልጅ ከነቃጭሉ ዱብ ታደርጋለች። በሁለት አመት ውስጥ ሁለት ወለድን።  እበላለሁ፣ እጠጣለሁ፣ እዋሰባለሁ፣ እተኛለሁ። በቃ። በግ በሉኝ። አሳማ በሉኝ። በሬ በሉኝ። ብቻ ሰው እንዳትሉኝ። ሁሌም ቢራዬን ይዤ ቁጭ ስል የማስበው ስለዛች ምሽት ነው። ምናለበት የዛን ቀን ሙኒት "እንደንስ" ስትለኝ እምቢ ብዬ ቢሆን...ምናለበት ያ ብሩክ "ና ክለብ እንሒድ" ሲለኝ "ሰውዬ ውጣልኝ...ቀጠሮ አለብኝ" ብዬ አስደንግጨው ቢሆን...ኧረ እሱንም ተውት ምናለበት ቤት መቀመጡን ትቼ ላይብረሪ ሒጄ ቢሆን...! ፨፨፨ አንድ የመጨረሻ ቀን... ከስራ እንደወጣሁ ወደቤት ልገባ ስል ለልጆቹ ወተት ሸምቼ ለኛ ደግሞ ቢራ ነገር ልያዝ ብዬ የሆነ ባር ውስጥ ገባሁ። ባርቴንደሩ ጋ ቁሜ እየገበዬሁ አንዲት እየጮኸች የምታወራ ሴት ጆሮዬን ነጠቀችኝ። አውቄያታለሁ። ጀርባዋን ሰጥታኝ ስለተቀመጠች ሳታዬኝ ለመውጣት ቸኮልኩ። ሁኔታዋ ግን ጥያት እንዳልወጣ ጠፍሮ ያዘኝ። «ማነህ ና ሙላው ይሔን ብርጭቆ!» አለች እየጮኸች። መጥቶ ሲቀዳላት «ወደዳርም በደንብ እያፈሰስከው! እከፍልሀለሁ» አለችው። ልጁ እንደተባለው አደረገ። ከፊትለፊቷ ያለው ጎልማሳ እንደተናደደባት ያስታውቃል። «አስደበርኩህ እንዴ ወንድሜ? chaos አትወድም?» ስትለው «አልወድም!» አላት! «ታዲያ ኑሮ እንዴት እያደረገህ ነው?» «ከባድ ነው!» «ህግን መጣስ ካልለመድክ ገና እየከበደህ ይሔዳል!» ዝም ሲላት ቀጠለች። «ህግ ካልተጣሰ ምን ጥቅም?» አሁንም ዝም አላት። በጣም እንደተናደደ ያስታውቃል። «ዝም ብለህም ንዴትህን መቆጣጠር እንዳቃተህ ታስታውቃለህ። ለቀቅ በል ወዳጄ። እዚህ ላንተ ስሜት ግድ ያለው የለም። ቀውስ ውስጥ መኖርን ብትለምድ ይሻልሀል። የአጥብቆ መያዝ ትርፍ ከሁሉ ቀድሞ መልቀቅ ነው!» ሹልክ ብዬ ልወጣ ነበር። ሰውዬው ቦግ ብሎ ሲነሳባት ሳልፈልግ ጣልቃ ገባሁ። ስታዬኝ ደንግጣ ፊቷን ደረቴ ውስጥ ደበቀች። የኔ ሩሀማ...የኔ ምህረት የሚገባት ሴት! እኔ አንገቴን ልድፋ! ከባሩ አፋፍሼ ካስወጣኋት ቡኃላ ራይድ ጠራሁላት።

photo content

የአልበርት አንስታይን እና የቻርል ቻፕሊን አስደናቂ ንግግር ሊንኩን ነክታችሁ አንብቡት 👇👇👇 🔗https://t.me/BIOGRAPHY_TEACH/1036 🔗https://t.me/BIOGRAPHY_TEACH/1036

Repost from Dn Eyuel Habtamu
ሰው እኛን ባለመውደዱ ሲከፋን ያለምክንያት ያፈቀረን ክርስቶስ ይከፋዋል ። ስንጨነቅ ሲያይ ሁሉን ቻይ አምላክ ባለመታመኑ ልቡ ይደማል ። ከምንም ከምንም ግን " በቃ አይምረኝም " ያልን ቀን እጅጉን ይቆስላል ።

Repost from Dn Eyuel Habtamu
ነገ ብሞት ስለ እኔ የመጨረሻ ትዝታቸው ምንድነው ? እኔስ ከእነርሱ ጋር በነበረኝ ነገር የመጨረሻ ቢሆን ደስተኛ ነኝ ?