ተግባራዊ ክርስትና
Open in Telegram
{ ከቅዱሳን ሕይወት ተማሩ ብለን እንለምናችኋለን } "" ቃሉን የምታደርጉ ሁኑ እንጂ ፤ ራሳችሁን እያሳታችሁ የምትሰሙ ብቻ አትሁኑ ! "" /ያዕ 1÷22/
Show more5 800
Subscribers
-524 hours
-37 days
+2130 days
Posts Archive
5 800
ከእራት በኋላ ያለው ጊዜ የምስጋና ጊዜ ነው። ምስጋናን የሚያቀርብ ደግሞ ንቁና የተረጋጋ ይሆናል። ከእራት በኋላ ወደ ጸሎት እንጂ ወደ መኝታ አንሂድ። ያለበለዚያ ግን በደመ ነፍስ ከሚመሩት አውሬዎች የበለጠ በደመ ነፍስ የምንመራ እንሆናለን።
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
JOIN @Applied_CHRISTIANITY
5 800
🔴 እግዚአብሔር ይመስገን ፫
""እግዚአብሔር ይመስገን እራትና ምሳዬ እርሱ ነው። ለልብስም ለምንም አልጨነቅም። ሀብትም ምንም አልፈልግም ። እስከምሞት ድረስ ዳዊቴን እየደገምኩ እኖራለሁ።""
JOIN @Applied_CHRISTIANITY
5 800
🔴 የአባታችን የዲያቢሎስ ምኞት !
"ብዙዎቻችን በማወቅም ሆነ ባለማወቅ የዲያቢሎስን ምኞት እያሳካን ነው ።"
ሙሉ ትምህርት ተለቋል !
YouTube - https://youtu.be/h6HMqg87g_Y?si=Dxw7Y8f5rYUXAzNh
5 800
✝ ልብ ብለህ አስተውል !
ያለፈውን በትምህርትነቱ ፣ ነገን በብልጫነቱ ፣ ዛሬን ግን በተጨባጭነቱ ውደደው ፡፡ ከትላንት ከመማር በቀር ወደ ኋላ መልሰህ ማደስ አትችልም ፡፡ ትላንት ላይ መዘግየት አመድ ላይ እንደ መንከባለል ነው ፡፡ መቆሸሽ እንጂ መንጻት የለውም ፡፡ ታሪክን ትማረዋለህ እንጂ አትቀየመውም ፡፡ ዛሬ ከትላንት የተሻለ እንደሆነ ነገም ከዛሬ የተሻለ ይሆናል ፡፡ ከትላንት ዛሬ እውቀትህ ጨምሯልና ዛሬ ከትላንት ትሻላለች ፡፡ ነገም ከዛሬ የተሻለ ታውቃለህና ብልጫ አላት ፡፡ ነገ እንደፈራኸው አይደለም ፣ ትላንት ላይ ዛሬ ነገ ነበረች ፡፡ እንደ ፈራሃት ግን አይደለችም ፡፡ ቀኑ ላይ ኃይል አለ ፡፡ እግዚአብሔር በቦታው አቅም ይሰጥሃል ፡፡ ራስህን እንደ ገመትከው አይደለህም ፡፡ በአስቸጋሪ ቦታዎች ላይ አቅም ይሰጥሃል ፡፡ በክፉ ቀኖች ቆራጥ ያደርግሃል ፡፡
የከሰርከውን ነገር በገንዘብ እንደ ተማርከው ትምህርት ቁጠረው ፡፡ ያገኘኸውን እንደምታጣው አድርገህ ያዘው ፡፡ የምትመኘውን በትዕግሥት ጠብቀው ፡፡ ወደፊት ምን ይመጣ ይሆን ብለህ አትጨነቅ ፡፡ የፈራኸው ቢመጣም ከዚህ በላይ አትታወክም ፡፡ ባልመጣ ቀን የመጣውን ቀን አትረብሸው ፣ የመጣውን ቀን ትተህም ባልመጣ ቀን አከናውናለሁ አትበል ፡፡ አንተ የአሁን ሰው ነህ ፡፡ ስትተኛ ለመንቃትህ ፣ ስትወጣ ለመመለስህ ምንም ዋስትና የለህም ፡፡ በማይረቡ ነገሮች አእምሮህን አታጣብ ፡፡ ችግሮችን ከምንጫቸው ትተህ ከወራጁ ከገደብህ ይደገማሉ ፡፡ እነዚያን ክፉ ቀኖች ካልረሳህ ዛሬን ይረብሻሉ ፡፡ ፍቅር የሰጡህን ሰዎች ካላመሰገንህ ነፍስህ በውለታ እስረኛ ትሆናለች ፡፡ ሞተህም የምትወቀሰው አደራ በማጥፋትህ ነውና ታማኝ ሁን ፡፡ የሞተ ሰው የገደለውን ያውቃል ፣ ነገር ግን ነቅቶ አይከስስም ፡፡ ትልቁ ዳኛ ጋር እየሄደ ነውና ፡፡ እግዚአብሔር ከተናገረልህ አንተ ዝም በል ፡፡ እግዚአብሔር ሲናገር አንተ ከተናገርህ ሁሉን ነገር ታበላሻለህ ፡፡
- .....እንዴት #አደራችሁ ?
- .....እንዴት #አረፈዳችሁ ?
- .....እንዴት #ዋላችሁ ?
- .....እንዴት #አመሻችሁ ?
JOIN @Applied_CHRISTIANITY
5 800
❖ እንኳን ለእመቤታችን ትንሣኤ እና ዕርገት በሰላም አደረሳችሁ! ❖
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጥር 21 ቀን በ64 ዓመቷ ከዚህ ዓለም ውጣ ውረድና ድካም ባረፈች ጊዜ ቅዱሳን ሐዋርያት ሊቀብሯት ወደ ጌቴሴማኒ ይዘዋት ሔዱ፡፡ በዚህ ጊዜ አይሁድ "እንደ ልጇ 'ተነሣች፤ ዐረገች' እያሉ እንዳያውኩን በእሳት እናቃጥላት" ብለው ሥጋዋን ሊያጠፉ በዓመፃ ተነሡ፡፡ ታውፋንያ የሚባል አይሁዳዊም አጎበሩን ይዞ ሊያወርዳት ሲል የእግዚአብሔር መልአክ ሁለት እጆቹን ቀጣው፡፡
ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር አምላክ ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስን ጨምሮ እመቤታችንን በደመና ነጥቆ ወደ ገነት ወስዶ ከዕፀ ሕይወት ሥር አስቀመጣት ቅዱሳን ሐዋርያትም እመቤታችን ያለችበት ቦታ እንዲገለጥላቸው ከነሐሴ 1 ቀን ጀምረው ሱባዔ ገብተው እግዚአብሔርን በጸሎት መጠየቅ ጀመሩ፡፡
ቅዱሳን ሐዋርያት ሁለት ሱባዔ (ዐሥራ አራት ቀናት) ካደረሱ በኋላም የነገሩትን የማይረሳ፣ የለመኑትን የማይነሳ እግዚአብሔር አምላካችን ጸሎታቸውን ሰምቶ የእመቤታችንን ሥጋ ሰጥቷቸው በክብር ገንዘው በጌቴሴማኒ ቀብረዋታል፡፡ በሦስተኛው ቀንም እንደ ልጇ እንደ ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይታ ተነሥታለች፡፡
ትንሣኤዋን "ከመ ትንሣኤ ወልዳ (እንደ ልጇ ትንሣኤ)" ያሰኘውም ይህ ምሥጢር ነው፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ ሲሰብክ ቆይቶ ደመና ጠቅሶ ከሀገረ ስብከቱ ወደ ኢየሩሳሌም ሲመጣ እመቤታችን ከሙታን ተለይታ ተነሥታ ወደ ሰማይ ስታርግ ጠፈር ላይ አገኛት፡፡ በዚህ ጊዜ "ቀድሞ የልጅሽን ትንሣኤ፤ ዛሬ ደግሞ ያንቺን ትንሣኤ ሳላይ ቀረሁን?" ብሎ ትንሣኤዋን ባለማየቱ ኀዘን ስለ ተሰማው ከደመናው ይወድቅ ዘንድ ወደደ፡፡
እመቤታችንም "አይዞህ! አትዘን፤ ባልንጀሮችህ ሐዋርያት ያላዩትን ትንሣኤዬን አንተ አይተሃልና ደስ ይበልህ!" ብላ ከሙታን ተለይታ መነሣቷንና ማረጓን ለሐዋርያት እንዲነግራቸው አዝዛ የያዘቸውን ሰበን ሰጥታ ሰደደችው፡፡ ከዚያም እርሷ ወደ ሰማይ ዐረገች፤ እርሱም ወደ ኢየሩሳሌም ወረደ፡፡
ቅዱስ ቶማስ ትእዛዟን ተቀብሎ በክብር ከተሰናበታት በኋላ ወደ ሐዋርያት ሔዶ እንዳልሰማ እንዳላየ መስሎ "የእመቤታችን ነገር እንደምን ሆነ?" ሲል ጠየቃቸው፡፡ እነርሱም "አግኝተን ቀበርናት" ሲሉት "ሞት በጥር በነሐሴ መቃብር እንዴት ይኾናል?" አላቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ቅዱስ ጴጥሮስ ከዚህ በፊት የክርስቶስን ትንሣኤ መጠራጠሩን ጠቅሶ እየገሠፀ መከራከሩንና መጠራጠሩን ትቶ ስለ እመቤታችን መቀበር እነርሱ የሚነግሩትን ዅሉ አምኖ መቀበል እንደሚገባው ለቅዱስ ቶማስ አስረዳው፡፡
ቅዱስ ቶማስም የያዘውን ያውቃልና ጸጥ ብሎ ሲሰማው ቆየ፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም ተቈጥቶ የእመቤታችንን ክቡር ሥጋ ለቅዱስ ቶማስ ለማሳየት ሔዶ መቃብሯን ቢከፍት የእመቤታችንን ሥጋ ሊያገኘው አልቻለም፡፡ በዚህ ጊዜ ቅዱስ ጴጥሮስ ደንግጦ ቆመ፡፡
ቅዱስ ቶማስም "ወንድሞቼ! አታምኑኝም ብዬ ነው እንጂ እመቤታችንስ ከሙታን ተለይታ ተነሥታ ስታርግ አግኝቻታለሁ" ብሎ እመቤታችን የሰጠችውን ሰበን ለሐዋርያት ሰጥቷቸዋል፡፡ እነርሱም በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ትንሣኤና ዕርገት እየተደሰቱ ሰበኑን ለበረከት ተካፍለውታል፡፡
ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እንደሚያስተምሩን በቅዳሴ ጊዜ ሠራዒ ዲያቆኑ በሚይዘው መስቀል ላይ የሚታሠረው መቀነት መሰል ልብስ፤ እንደዚሁም አባቶች ካህናት በመስቀላቸው ላይ የሚያደርጉት ቀጭን ልብስና በራሳቸው ላይ የሚጠመጥሙት ነጭ ሻሽ የእመቤታችን ሰበን ምሳሌ ነው፡፡
ከበዓሉ ረድኤት በረከት ያሳትፈን የእናታችን የእመቤታችን የንጽህተ ንጹሐን ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም አማላጅነቷ አይለየን!!!
JOIN @Applied_CHRISTIANITY
5 800
✝ ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረ ታቦር ብርሃነ መለኮቱን ፣ ክብረ መንግሥቱን ለገለጠበት በዓለ ደብረ ታቦር በሰላምና በጤና አደረሰን አደረሳችሁ ። መልካም በዓል !
"" እስመ ውእቱ ቀደመ አእምሮ ወዜነዎሙ ለአርዳኢሁ በደብረ ታቦር በእንተ መንግሥቱ ዳግመ ምጽአቱ በዐቢይ ስብሐት ። "" #ትርጉም ፦ እርሱ አስቀድሞ አውቆ ለሐዋርያት በደብረ ታቦር ስለመንግሥቱ ፍጻሜና ዳግመኛ ስለመምጣቱ ነገራቸው ። /ቅዱስ ያሬድ/
JOIN @Applied_CHRISTIANITY
5 800
❖ ደብረ ታቦር ❖ [ ክፍል 3 ]
የጴጥሮስ ልመና
ሊቀ ሐዋርያ ቅዱስ ጴጥሮስም በትሕትና ሁኖ አንዱን ላንተ፣ አንዱን ለሙሴ አንዱንም ለኤልያስ ሦስት ዳስ እንሥራና በዚህ እንኑር ብሎ ጠየቀ፤ ለእርሱና አብረውት ለነበሩት ወንድሞቹ ግን እንሥራ ባለማለቱ ትሕትናውን ገለጠ።
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ "የመብራት ፈትል ያለ ዘይት፤በጾምና ጸሎት መትጋትስ ያለ የዋህነት፣ ቤተክርስቲያንን መከተል ለድሆች ያለ መራራት፣ ድንግልናም ያለ ትሕትና ምን ይጠቅማል?" በማለት ገልጦታል። መ.ምሥጢር 30፥26
[ ኢየሱስ ክርስቶስ ከተራራው ወረደ]
/ማቴ 17፥9/
ለምኑ ይሰጣችኋል፣ ፈልጉ ታገኛላችሁ፣ አንኳኩ ይከፈትላችኋል ያለ አምላክ ቅዱስ ጴጥሮስ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው ብሎ እየለመነው እርሱ ግን ከተራራው ወረደ።
ለምንድነው የወረደው ስንል ከተራራው ካልወረደ የሰው ልጅ አይድንምና ነው።
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በመጽሐፈ ምሥጢር የደብረ ታቦርን ምንባብ በጻፈበት ክፍል ላይ " ጴጥሮስ ሆይ ላንተ በታቦር ተራራ ላይ ድምጹን እየሰማሁ የሙሴ የኤልያስ ጌታ ይበሉህ እንጂ ሙሴ፣ ኤልያስ ልትባል አይገባህም የሚለውን ምሥክርነት እያደመጥክ በዚያ መኖር መልካም ነው። ለእኛ ግን ከተራራው ወርዶ በጥፊ ካልተመታልን ( ካልተሰቀለልን) አንድንምና በተራራው እንዲኖር አትለምነው።" በማለት ጌታ ከተራራው የወረደበትን ዓላማ በግልጥ አስቀምጦልናል።
[ደብረ ታቦር የምን ምሳሌ ነው?]
ደብረ ታቦር ቤተክርስቲያን ናት ። ደብረ ታቦር ከፍ ያለ ተራራ እንደሆነ ሁሉ ቤተክርስቲያን በዚህ ዓለም ካሉ ቤቶች ሁሉ ክብሯ ከፍ ያለ ነውና " የመቅደሳችን ስፍራ ከጥንት ጀምሮ ክፍ ያለ የክብር ዙፋን ነው። "እንዲል /ኤር 17፥12/
እመቤታችን ደብረ ታቦር ትባላለች። ቅዱስ ያሬድ "ያቺ ተራራ የረጃጅሞች ተራሮች ራስ ቅድስት ድንግል ማርያም ናት፤ በማለት ቅዱስ ተራራ እመቤታችን መሆኗን ገልጧል።
ልበ አምላክ ዳዊትም "መሠረታቲሃ ውስተ አድባር ቅዱሳን" በማለት ክብራቸው ከከበሩ አበው እንደተወለደች ተራራ በማለት መስክሯል።
ደብረ ታቦር በወንጌል ትመሰላለች ። ተራራ ከፍ ያለ ነው ወንጌልም ከመጻሕፍተ ምኑናት፣ ከመጻሕፍ ርኵሳት፣ መጻሕፍተ ዕዳ ይልቅ የከበረች ናትና።
አንድም ተራራን ሲወጡት ያደክማል፣ ወንጌልን ሲፈጽሟት ያደክማል። ተራራ ከወጡት ኋላ ሁሉን እንዲያሳይ ወንጌልን ከተማሯት ኋላ ጽድቅን ከኃጢአት ለይታ ታሳያለችና ነው።
ደብረ ታቦር የመንግሥተ ሰማያት ምሳሌ ነው። ተራራ ላይ በብዙ ጥረት እንደምንወጣ ሁሉ መንግሥተ ሰማያትም በብዙ መከራና ሕማም እንገባለንና ነው። /ሐዋ 14፥21/
ከዚህ ሁሉ የተነሣ ቅዱስ ጴጥሮስ ደብረ ታቦርን “ቅዱስ ተራራ” ብሎታል፡፡ /2 ጴጥ 1፥18/
ለሐዋርያት ብርሃነ መለኮቱን የገለጠ አምላክ የእኛንም ዓይነ ልቦናችንን ይብራልን!- .....እንዴት #አደራችሁ ? - .....እንዴት #አረፈዳችሁ ? - .....እንዴት #ዋላችሁ ? - .....እንዴት #አመሻችሁ ?
JOIN @Applied_CHRISTIANITY
5 800
መጣሁኝ ከደጅሽ ፍቅርሽ ይጠራኛል
ስዕልሽ ስር ቆሜ ዕንባዬ ይቀድመኛል
🔴 ሙሉ መዝሙር ተለቋል - https://youtu.be/vq4VwYlmz2I?si=KTn4I23Re0Imq0-X
