cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

𝐀𝐒𝐈𝐘𝐀 𝐓𝐔𝐁𝐄

አሰላሙ አለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱህ በዚህ ቻናል ላይ የምናገኛቸው ትምህርቶች 📚ሀዲሶች 📚አጫጭር አስተማሪ የሆኑ ነገሮች 📚 ኢስላማዊ ጥቅሶች 📚 የተለያዩ የቁርዓን አንቀፆች 📚 አስተማሪ ፅሁፎች አስተያየትና ጥያቄ ካሎት 👇👇👇👇 @Zelu_bint_baba @Abuatikah110 @Allahis1God @Bint_fulan1 @yene_azang_nebiy_mohamed

Show more
Advertising posts
861
Subscribers
+624 hours
+387 days
+8130 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ግብሽኝ ከማንም በላይ ለመሆን አታድርጊው፤ ግን ከቀድሞው የተሻልሽ ለመሆን አድርጊው! 𝑏𝑖𝑛𝑡 𝑓𝑢𝑙𝑎𝑛🖊 https://t.me/Asiya_tubee https://t.me/Asiya_tubee
Show all...
𝐀𝐒𝐈𝐘𝐀 𝐓𝐔𝐁𝐄

አሰላሙ አለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱህ በዚህ ቻናል ላይ የምናገኛቸው ትምህርቶች 📚ሀዲሶች 📚አጫጭር አስተማሪ የሆኑ ነገሮች 📚 ኢስላማዊ ጥቅሶች 📚 የተለያዩ የቁርዓን አንቀፆች 📚 አስተማሪ ፅሁፎች አስተያየትና ጥያቄ ካሎት 👇👇👇👇 @Zelu_bint_baba @Abuatikah110 @Allahis1God @Bint_fulan1 @yene_azang_nebiy_mohamed

👍 3👏 1
ሟቹ "ጌታ!" ~ ወሎ ውስጥ ነው። አንድ ቆለኛ ሙስሊምና አንድ ደገኛ ክርስቲያን ጓደኛሞች ይሆናሉ። ክርስቲያኑ ሙስሊሙን ግብዣ ጠራው። የገና በአል ነበር። ሙስሊሙ ሲመጣ ምግቡ፣ መጠጡ፣ ሁሉ ነገር ተትረፍርፏል። ሰዎቹ ፌሽታ በፌሽታ፣ ፈንጠዝያ በፈንጠዝያ ሆነዋል። · * ሙስሊሙ:– "ድግሱ ምንን ምክንያት በማድረግ ነው?" ብሎ ጠየቀ። – "ጌታ ተወልዶ ነው" አሉት። · ለሙስሊሙ ይሄ አስደንጋጭ ነበር። ጌታ ይወለዳል?! ግን ከሰው ቤት ነው ያለው ምን ይላል? "ህምምም" ብሎ የሆዱብ በሆዱ አድርጎ ዝም ይላል። ይህን ጉድ አይቶ ተመለሰ። · ሌላ ጊዜ ተጠራ። ጥምቀት ነበር። ሲመጣ ድግሱ አሁንም እንደባለፈው የደመቀ ነው። ሰዎቹም ደስታ በደስታ ናቸው። * "እሄስ በአል ምንድን ነው ምክንያቱ?" ብሎ ጠየቀ። – "ጌታ ተጠምቆ ነው" አሉት። ዘንድሮ ጉድ ተአምር እያየ ነው። እንዲያም ነው፤ እንዲህም ነው ሳይል ወደ ቤቱ ተመለሰ። · አሁንም ተጠራ። ስቅለት ነበር። ሲመጣ ከወትሮው የተለየ ነገር አየ። ሰዎቹ የባለፈው አይነት ደስታ አይታይባቸውም። አዝነዋል። በባዶ እግር ይሄዳሉ። የሚበሉት ንፍሮ ነው። ግንባራቸውን በሳር መሳይ ነገር አስረዋል። ምን ጉድ ነው?! ቆለኛው ግራ ገብቶታል። · * "ምንድን ነው የሆናችሁት?" አላቸው። – "ጌታ ሞቶ ነው" አሉት። * "ያ ባለፈው የተወለደው?" ሲል ጠየቀ። – "አዎ" አሉት። · ከዚያ ምን ቢል ጥሩ ነው:– "እኔኮ ቀድሞም ፌሽታ ስታበዙ እንደማያድግ አውቄያለሁ!!" … የታሪኩ ምንጭ አንድ የደሴ ክርስቲያን ነው። … መወለድ፣ ማደግ፣ መሞት ለፈጣሪ የማይመጥኑ የደካማ ፍጡሮች መታወቂያ ናቸው። እባካችሁ ያገሬ ሰዎች ቆም ብላችሁ አስቡ። "ፍፁም ሰው፣ ፍፁም አምላክ" እያሉ "ተጨፈኑ እናሙኛችሁ" ሲሉ እጅ አትስጡ። "ሁሉን ምርምሩ። መልካሙን ያዙ።" በአባቶች የውርስ ጋቢ ተጠቅልላችሁ፣ በይሉኝታ ጆሯችሁን ደፍናችሁ፣ በምስጢረ ሥላሴ ትብታብ ታስራችሁ እንጂ ህሊናችሁን ፋታ ሰጥታችሁ በእርጋታ ብታዳምጡት የሚነግራችሁ ሐቅ አለ። "ዝግ ብሎማ ያሰበ እንደሁ ይነግርሀል አንዳች እውነት" ይላል ገጣሚው። · ዳሰሳ ከማርቆስ ወንጌል ምዕ. 12 ቁ 29 እስከ 34። ---------- "ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው። #ከትእዛዛቱ_ሁሉ ፊተኛይቱ። እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ #ጌታ_አምላካችን #አንድ_ጌታ ነው፥" (የማርቆስ ወንጌል 12:29) · ማነው ይህን ያለው? እየሱስ እራሱ!! "ጌታ አምላካችን" ማለቱን አስምርበት። እየሱስ ፍጡር እንጂ ጌታ እንዳልሆነ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ጥቅስ ነው። ይሄ ቀዳሚ ትእዛዝ ግን በክርስቲያኖች ተገፍቷል። እንቀጥል። "አንተም በፍጹም ልብህ በፍጹምም ነፍስህ በፍጹምም አሳብህ በፍጹምም ኃይልህ ጌታ አምላክህን ውደድ የምትል ናት። ፊተኛይቱ ትእዛዝ ይህች ናት።" (የማርቆስ ወንጌል 12:30) · ልብ በል! በዚህ መልኩ "ጌታህን ውደድ" እያለ የሚያስተምረው እየሱስ እራሱ ነው። ይህም እሱ አስተማሪ እንጂ ጌታ እንዳልሆነ የሚያሳይ ነው። እንቀጥል። "ሁለተኛይቱም። ባልንጀራህን እንደ ራስህ ውደድ የምትል እርስዋን የምትመስል ይህች ናት። ከእነዚህ የምትበልጥ ሌላ ትእዛዝ የለችም። ጻፊውም። መልካም ነው፥ መምህር ሆይ፤ #አንድ_ነው። #ከእርሱም_በቀር_ሌላ_የለም ብለህ በእውነት ተናገርህ፤" (ማርቆስ 12:31–32) እያስተዋልክ ነው?! እውነት የምትፈልግ ከሆንክ "አምላክ አንድ ነው። ከርሱ በቀር ምንም የለም" ብለህ በልብህ ዝከር። በምላስህ አስተጋባ። በተግባር ኑር። ይሄ በኢስላም "ላ ኢላሀ ኢለላህ" ("ከአላህ በስተቀር እውነተኛ አምላክ የለም") ከሚለው ምስክርነት ጋር መሳ ነው። እንቀጥል። "በፍጹም ልብ በፍጹም አእምሮም በፍጹም ነፍስም በፍጹም ኃይልም እርሱን መውደድ፥ ባልንጀራንም እንደ ራስ መውደድ በሙሉ ከሚቃጠል መሥዋዕትና ከሌላው መሥዋዕት ሁሉ የሚበልጥ ነው አለው።" (ማርቆስ 12:33) ይህን ነው የምልህ። ስላሴ፣ ቅብጥርሴ የሚባለውን ወደ ኋላህ አሽቀንጥረህ ጣልና ለመፅሐፋዊ መልእክቱ በፍጹም ልብህ፣ በፍጹም አእምሮህ፣ በፍጹም ነፍስህ፣ በፍጹም ኃይልህ እደር። ሥላሴ ልብ ወለድ እንጂ እውነታ አይደለም። ሥላሴ ጤነኛ ጭንቅላት የማይፈታው እንቆቅልሽ እንጂ ምክንያታዊ አይደለም። "ያልገባህ መንፈስ ቅዱስ ስላላደረብህ ነው" እያሉ አይሸውዱህ። ይሄ ምእመኑ እንዳይመረምር የሚያስተኙበት የእንቅልፍ ክኒን ነው። በክኒኑ እራሳቸውን ያስተኙበት። አንተ ግን ንቃ። ይህን ስታደርግ፣ ወደ አእምሮህ ስትመለስ "ለመንግስተ ሰማያት" ትቀርባለህ። አብረን እናንብብ። "ኢየሱስም በአእምሮ እንደ መለሰ አይቶ። አንተ ከእግዚአብሔር መንግሥት የራቅህ አይደለህም አለው። ከዚህም በኋላ ማንም ሊጠይቀው አልደፈረም።" (ማርቆስ 12:34) (ኢብኑ ሙነወር፣ የካቲት 11/2011) የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor
Show all...
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

كناشة ابن منور

👍 2👏 1😁 1
وَقَوْلِهِمْ إِنَّا قَتَلْنَا الْمَسِيحَ عِيسَى ابْنَ مَرْيَمَ رَسُولَ اللَّهِ وَمَا قَتَلُوهُ وَمَا صَلَبُوهُ وَلَٰكِن شُبِّهَ لَهُمْ ۚ وَإِنَّ الَّذِينَ اخْتَلَفُوا فِيهِ لَفِي شَكٍّ مِّنْهُ ۚ مَا لَهُم بِهِ مِنْ عِلْمٍ إِلَّا اتِّبَاعَ الظَّنِّ ۚ وَمَا قَتَلُوهُ يَقِينًا «እኛ የአላህን መልክተኛ የመርየምን ልጅ አልመሲሕ ዒሳን ገደልን» በማለታቸውም (ረገምናቸው)፡፡ #አልገደሉትም #አልሰቀሉትምም፡፡ ግን ለእነሱ (የተገደለው ሰው በዒሳ) ተመሰለ፡፡ እነዚያም በእርሱ ነገር የተለያዩት ከእርሱ (መገደል) #በመጠራጠር ውስጥ ናቸው፡፡ #ጥርጣሬን ከመከተል በስተቀር በእርሱ ነገር ምንም ዕውቀት የላቸውም፡፡ #በእርግጥም_አልገደሉትም፡፡
Show all...
👍 3👌 3👏 1
አሳማኝ መረጃ ሳይኖር በግድ ተሰ'ቅሏል ማለት የኢየሱስ ጠ'ላት ያስብላል።ስ'ቅለት የወን'ጀል ቅጣት እንጂ ለሌላው ምህረት አይሆንም።
Show all...
👌 6👍 2
ሱረቱል ካህፍን የቻለ ይቅራ📖 ያልቻለ ያድምጥ 🎧 ‏﴿إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَاأَيُّهَاالَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيما﴾ ‏اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ وَبَارِكْ عَلَى نبيِّـنَا مُحَمَّدٍ ﷺ 🌺🌺🌺
Show all...
👍 4
[➪ሱረቱል ካህፍ] በቃሪዕ [Bilal Darbali] ◦◦◦◦◦◦◦◦◦🌹◦◦◦◦◦◦◦
Show all...
💯 4
ጌታዬ ሆይ! • አንተ ይህንን ቀልቤን ፈጠርከው፣ በፈቃድህም በዉስጤ አኖርከው፣ የምትሻዉን ነገር አኖርክበት፣ በምትፈልገው ነገርም ሞላኸው።ሕያዉን ከሙታን በሚቀሰቅሰው ችሎታህና ኃያልነትህ ለመንኩህ፣ ምድር ሰማይን በሞላው እዝነትህ ተማፀንኩህ... •ልቤን በዲንህ ላይ አፅናልኝ፣ላንተ ፈቃድና ትዕዛዝ ያደረ አድርገው፣በጨለማ ዉስጥ እንዲዋልል አትተወው፣ጥቅሙን ሁሉ አሳየው፣ ጉዳቱንም አሳውቀው፣ጨለማዉንም አብራለት፣ነገርን ሁሉ አግራለት። =t.me/AbuSufiyan_Albenan
Show all...
💯 6👍 2
ولمن خاف مقام ربه جنتان ጌታው ፊት መቆምን ለፈራ ሰው ሁለት ጀነቶች አሉለት። 🥀🥀🥀 @asiya_tubee
Show all...
👍 7
እኛስ ለወላጆቻችን እንዴት እንሆን? ...
Show all...
💔 2👍 1
አንድ ልጁ ታስሮበት ብቻውን የቀረ ገበሬ እስር ቤት ላለ ልጁ እንዲህ ሲል ፃፈ፦ "ውድ ልጄ ፤ ይኸውልህ አንተ በመታሰርህ ምክንያት በዚህ አመት እርሻ ቦታው ላይ ድንች ሳልዘራ ጊዜው ሊያልፍብኝ ነው፤ እኔ እንደሆንኩ ከእንግዲህ ደክሜያለሁ፤ ምነው በኖሮክልኝ ኖሮ" አፍቃሪ አባትህ ። ከሳምንት በኋላ ገበሬው መልስ መጣለት፤ ምላሹም፦ "አባባ፤ የድንቹን መደብ እንዳትቆፍር፤ ሰዎቹን የቀበርኳቸው እዚያ ነው። ያንተው ልጅህ" ይላል። በሚቀጥለው ንጋት ላይ ፖሊስ መዓት መጥቶ የድንቹ ማሳ ላይ ፈሰሰ፤ የተቀበሩትን አስክሬኖች ለመፈለግ ሲቆፍሩ ቢውሉም ምንም ሊያገኙ አልቻሉም። ስለዚህ ገበሬውን ይቅርታ ጠይቀው ሄዱ። ወዲያው ልጁ ለአባቱ እንዲህ የሚል ሌላ ደብዳቤ ፃፈለት፦ "አባቴ አሁን ድንችህን መዝራት ትችላለህ፤ ካለሁበት ችግር አንፃር ላደርግልህ የምችለው ነገር ቢኖር ይሄ ብቻ ነው" ካነበብኩት ውስጥ 𝑏𝑖𝑛𝑡 𝑓𝑢𝑙𝑎𝑛✍️ https://t.me/Asiya_tubee https://t.me/Asiya_tubee https://t.me/Asiya_tubee
Show all...
𝐀𝐒𝐈𝐘𝐀 𝐓𝐔𝐁𝐄

አሰላሙ አለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱህ በዚህ ቻናል ላይ የምናገኛቸው ትምህርቶች 📚ሀዲሶች 📚አጫጭር አስተማሪ የሆኑ ነገሮች 📚 ኢስላማዊ ጥቅሶች 📚 የተለያዩ የቁርዓን አንቀፆች 📚 አስተማሪ ፅሁፎች አስተያየትና ጥያቄ ካሎት 👇👇👇👇 @Zelu_bint_baba @Abuatikah110 @Allahis1God @Bint_fulan1 @yene_azang_nebiy_mohamed

👍 6🍓 3👌 2👏 1💯 1