en
Feedback
የልማድ አስደናቂ ኃይል/ Atomic Habits

የልማድ አስደናቂ ኃይል/ Atomic Habits

Open in Telegram

*ጥቃቅን ለውጦች- አስደናቂ ውጤት!!! ** የእለት ከእለት ልማዶችን በመጠቀም የላቀ ሕይወት መምራት *** ራስን የመቆጣጠር ምስጥር **** የአቶሚክ ልማድ አስደናቂ ኃይል ***** ዘላቂ ውጤቶችን የማምጣት ምስጢር

Show more
945
Subscribers
+124 hours
+47 days
+430 days
Posts Archive
አንዱን ምረጡ! “ውደዱት፣ ለውጡት፣ ወይም ተውት” - Henry Ford “Love it, Change it, or Leave it!” - Henry Ford እስቲ በአሁን ሰዓት የተወዛገባችሁበትን ወይም ለውሳኔ የተቸገራችሁበትን ማንኛውንም ነገርና ሁኔታ አስቡት፡፡ ያላችሁን ምርጫ ባጠበባችሁት ቁጥር ስኬታማነታችሁ የጎላ ከመሆኑም ባሻገር በድንዛዜ ወራትና አመታትን ከማባከን ትድናላችሁ፡፡ ሁኔታውን ጠበብ ለማድረግ ደግሞ ታዋቂው ሄንሪ ፎርድ የጠቆመንን መንገድ መከተል እንችላለን፡፡ በስራም ሆነ በመሳሰሉት የወቅቱ ሁኔታችሁ አንጻር በብርታት ወደፊት ለመንቀሳቀስ ከፈለጋችሁ የወቅቱን ሁኔታችሁን መውደዳችሁን እርግጠኞች ሁኑ፡፡ ካልወደዳችሁት ግን ዝም ብሎ ከመነጫነጭና ስለሁኔታው ሲያወሩ ከመክረም በተቻላችሁ መጠን ሁኔታውን ለመቀየር ሞክሩ፡፡ ሁኔታውን የመቀየሩ ጉዳይ የማይታሰብ ከሆነ ደግሞ አንደኛችሁን ሌላ አቅጣጫና መስመር በመያዝ መንገዳችሁን ብትቀጥሉ ተመራጭ ነው፡፡ እነዚህን እጅግ ቀላል የሚመስሉና ለመተግበር ግን አስቸጋሪ የሆኑ ሶስት ደረጃዎች የማይለማመዱ ሰዎች ትኩረት የሌላቸው፣ ሁል ጊዜ የሚነጫነጩ፣ ሰውን መውቀስ የሚወዱ፣ ስለግላቸው ሁኔታ ሰው ላይ ማሳበብ የሚያዘውትሩና በየጊዜው ባሉበት የሚረግጡ ሰዎች ናቸው፡፡

ምን እንደፈለኩኝ ለራሴም ግራ ገባኝ! አንዳንድ ነገር ለማድረግ ፍላጎቱ እያላችሁና የጉዳዩ አስፈላጊነትም ጉልህ ሆኖ ሳለ እርምጃ የምትወስዱበት ደረጃ ላይ ስትደርሱ መነሳሳትን የማጣት ልምምድ ካላችሁ ለምን እንደዚያ እንደምትሆኑ ግር ሊላችሁ ይችላል፡፡ ለምሳሌ ከዚህ በታች ለምሳሌነት የሰፈሩት ሁለት የተለመዱ አባባሎች የእናንተን ልምምድና ስሜት ከጠቆሙ በሁኔታው በሚገባ አስቡበት . . . • ስራ ለመስራት እፈልግና ለመቀጠር ያመለከትኩባቸው ቦታዎች ለኢነተርቪው ሲጠሩኝ፣ ቀኑ ሲደርስ የመሄድ ፍላጎቴን አጣለሁ፡፡ ከዚያም እንደገና የስራ ፍለጋ ጉዞዬን እቀጥላለሁ . . . ምን እንደፈለኩኝ ለራሴም ግራ ገባኝ፡፡ • የፍቅር ጓደኝነት ለመጀመር ፍላጎት አለኝ ነገር ግን ወደዚያ የሚያመራ አይነት ቀጠሮ ሲኖረኝና ከሰዎቹ ጋር የመገናኛው ጊዜ ሲደርስ የመሄድ መነሳሳቴን አጣዋለሁ፡፡ ከዚያም እንደገና ፍቅረኛ የመፈለግ ጉዞዬን እያያዘዋለሁ . . . ምን እንደፈለኩኝ ለራሴም ግራ ገባኝ፡፡ ከላይ የተጠቀሱት አይነትና መሰል ልምምድ ካላችሁ ፍላጎታችሁ ምን እንደሆነ ለራሳችሁም ሳይቀር ግር ሊላችሁ ይችላል፡፡ ሁለት ነገሮችን ጠርጥሩ . . . 1. የዝቅተኝነት፣ ያለመቻል ወይም ያለመመጠን ስሜት እያጠቃችሁ ይሆናል፡፡ አንድን ነገር ገፍታችሁ፣ ገፍታችሁ ልክ የእርምጃው ጊዜ ሲደርስ መጨረሻ ላይ ከሁኔታው መሰወር፣ መቅረት፣ ወይም ሰዎችን በማሳወቅ ማስተላለፍ የሚያጠቃችሁ ከሆነ ይህ የሚሆንበት አንዱ ምክንያት ያላችሁ የራስ-በራስ አመለካከት ዝቅተኛ ከመሆኑ የተነሳ ለሁኔታው የማትመጥኑ እንደሆናችሁ አምናችሁ ስለተቀበላችሁት ነው፡፡ 2. “እምቢ ብባልስ!” . . . “ብገፋስ!” . . . “ባይፈልጉኝስ!” አይነት ስሜት እያጠቃችሁ ይሆናል፡፡ መገፋትን (Rejection) መፍራት፣ በጣም ከሚያስፈልጋችሁና ብዙ ተመኝታችሁና ለፍታችሁ ጥጉ ካደረሳችሁት ነገር ሊገታችሁ ይችላል፡፡ ይህ የሚሆነው ተቀባይነት ከማግኘት ይለቅ ያለማግኘት እድላችሁ እንደሚሰፋና ያም ሆኔታ ከሆነ በጣም ልትጎዱ እንደምትችሉ ስለምታስቡ ነው፡፡ ይህ በአንድ ነገር ላይ ሄዶ ሄዶ መጨረሻ ላይ ወደኋላ የመመለስ ልምምድ እጅግ አደረገኛ የሆነና በተለማመዳችሁት ቁጥር የበለጠ በዚያው ስሜት እያዘቀጣችሁ እንድትሄዱ የሚያደርግ ጉዳይ ነውና ዛሬውኑ መፍትሄ ይፈለግለት፡፡ አንዱ መፍትሄ ያለው በራሳችሁ ላይ ያላችሁን አመለካከት በጤናማ መልኩ መቃኘት ላይ ሲሆን, ሁለተኛው ደግሞ አንድን ነገር ለማድረግ ስትሞክሩ ሰዎች “እሺም” አሉ “እምቢ” ሁኔታው ከማንነታችሁ ጋር ምንም ግንኙት እንደሌለው በማወቅ መረጋጋት ነው፡፡

አንድ እርምጃ ወደፊት! ሕይወት እንዳደረጋችሁት ነው፡፡ ስትንቀሳቀሱ ወደፊት ትሄዳላቸሁ፣ ስትቆሙ ወደኋላ ትቀራላችሁ፣ ስትወላውሉ ደግሞ ባላችሁበት ትረግጣላችሁ - ስሌቱ ይኸው ነው! በዙሪያችሁ የሚገኙትን ሰዎችን ተመልከቷቸው፡፡ አንድ ቀን ከእንቅልፋቸው ሲነቁ አይደለም እዚህ ብዙዎች የሚመኙበት ደረጃ ደርሰው ራሳቸውን ያገኙት፡፡ ተንቀሳቅሰው፣ ሰርተው፣ አጠራቅመው፣ ታግለው . . . ነው፡፡ ነገ ከዛሬው፣ የዛሬ ዓመት ደግሞ ከዘንድሮው የተሻለ ሕይወት ከፈለጋችሁ ያንን የማድረጊያው ብቸኛውና እርግጠኛው መንገድ መንቀሳቀስ ነው፡፡ ይህ እቅስቃሴ ደግሞ የግድ ትልልቅ መሆን የለበትም፡፡ በየቀኑ የሚደረጉ ትንንሽ እርምጃዎች በዓመት ውስጥ አንድ ግዙፍ ነገር እጃችሁ እንዲገባ ያደርጋል፡፡ ይህንን ከላይ የተጠቀሰውን የማበረታቻ ሃሳብ ተግባራዊ ለማድረግ ልቦናችሁ ከተነሳሳ የሚከተሉትን ልምምዶች ለመጀመር ሞክሩ፡፡ 1. አሁን ካላችሁበት ደረጃ በተሻለ መልኩ ለማወቅ በምትፈልጉት በአንድ እውቀት ዙሪያ መጽሐፍን የማንበብ ወይም አንድን ስልጠኛ የመውሰድን አንድ እርምጃ ተራመዱ፡፡ 2. ቀረብ ብላችሁ ብትተዋወቁትና ብታውቁት ለሕይወታችሁ እድገት የክህሎ ወይም የስብእና መዋጮ ያደርጋል ብላችሁ የምታስቡትን አንድ ሰው የመቅረብንና የመተዋወቅን አንድ እርምጃ ተራመዱ፡፡ 3. በእጃችሁ ላይ ያለውን ገንዘብ ወይም አንድ ንብረት በማዋል (ኢንቨስት በማድረግ) የተሻለ የኢኮኖሚ ደረጃ ላይ ለመድረሰ ጥንቃቄ በተሞላው መልኩ አንድ እርምጃ ተራመዱ፡፡ መልካም የእድገት ዓመት ይሁንላችሁ! @yikdem

አሸናፊ ነህ! ሰው ምንድነው ቢሉ ደጋግሞ ያሰበውን ነው ይባላል፤ ስለዚህ ለማን ብለህ ነው አብዝተህ የጎደለህን ከሰው ያሳነሰህን የምታስበው?! በቃ ተዓምር መስራት እንደምትችል ባንተ ምክንያት መጀመሪያ የራስህ ከዛ የቤተሰቦችህ ህይወት እንደሚቀየር አስብ እሱን እውነት ለማድረግ የምትችለው ጥግ ድረስ ጣር የቀረውን ለፈጣሪ ተወው!

🤔አንዳንዴ የውስጥህን ድምፅ የሚያፍኑ ውስጫዊ ጫጫታዎች ይበዛሉ፤ የምትፈልገውን እንዳትሆን በራስህ መንገድ እንዳትጓዝ የሚያደርጉ ጫናዎች ይበረታሉ፤ ፅናት ማለት ህልምህን ለመኖር የሚከፈለውን መስዋዕትነት ሁሉ ከፍሎ ሳያቆሙ መቀጠል ነው። https://t.me/joinchat/WT04n6phTN1iMzg0

አብዝተህ አስብ! ጠንክረህ መስራትህ ምንም ትርጉም ካልሰጠህ እስር ቤት ውስጥ ነህ! መስራት ስለምትፈልገው፣ መማር ስለምትፈልገው፣ መሆን ማሳካት ስለምትፈልገው አብዝተህ አስብ ምክንያቱም ወደ ፀሀይ ስትዞር ጥላህ ወደኋላ ይሸሻል። ወዳጄ ትርጉም ስለሚሰጥህ ነገር ብቻ አስብ! የማይጠገብ ምሽት ተመኘውላችሁ🙏

"ሁሉም ሰው ጂኒየስ ነው፤ ግን አሳ ከዛፍ ዛፍ በመዝለል ችሎታው ከተመዘነ እድሜ ልኩን የማይረባ እንደሆነ ያምናል" ይለናል አልበርት አንስታይን። ድክመታችንን ከሌሎች ጥንካሬ ጋር ካወዳደርነውማ ሁሌም የበታችነት ይሰማናል፤ ከሌሎች ዝቅ ያልን ይመስለናል። እኛን የሚዳኘን የራሳችን መስፈርት ነው፤ የሌሎች መንገድማ የሌሎች ነው!

🧤ተዘጋጅ! ህይወትህን የሚቀይረው የሆነ ቀን የሚመጣ ዕድል አይደለም ዝግጅት ነው፤ ራስህን ለማሻሻል ምን ያህል እየጣርክ ነው? እየተማርክ ነው? ቋንቋህን እያሻሻልክ ነው? ገንዘብ እያስቀመጥክ ነው? ለከፍታው ራስህን እያዘጋጀህ ነው? አየህ አንተ ስትዘጋጅ ዕድሎች ከመጡ ትጠቀምበታለህ ህይወትህን እስከመጨረሻው ትቀይርታለህ፤ ወዳጄ አትጠራጠር ያንተን ጉብዝና የሚጠይቁ ዕድሎች ይመጣሉ፤ በመጡ ሰዓት እንድትጠቀምበት ተዘጋጅ! ስኬት = ዝግጅት + ዕድል https://www.facebook.com/100447992411481/posts/110449304744683/?app=fbl

DON'T TALK UNTIL YOU DID IT!! እስክታደርገው ድረስ እንዳታወራው! ከማድረግ በፊት አስቀድሞ ማውራት አንዳች የማድረገን ሀይል የመቀነስ ባህሪ አለው ። ሳታደርገው ከአወራህ ያደረከው መስሎህ እንደተደረገ ሊሰማህ ይችላል ። አለመደረጉን ግን ጠንቅቀህ ታውቃለህ ። ሳታደርግ አወራህ ማለት ሳታሸንፍ አሸናፊነትህን አወጅክ ፣ አከበርክ ፣ ጨፈርክበት እንደማለት ነው ። አድርገህ አሳይ! አንተ ሳትሆን ተግባርህ ቀድሞህ ይናገር! Let your ACTION talks first rather than your Tongue did it. ግሩም ቀን ይሁንልን ጀግኖቼ!! 🌞😊🏞

ከደከመህ እረፍት አድርግ፣ ነገር ግን እንዳታቆም። ፨፨፨፨፨፨፨///////////፨፨፨፨፨፨፨ እዚህ ለመድረስ የመጣህበት መንገድ ሩቅ ነው፤ የገጠመህ ስንክሳር እልፍ ነው፤ ወድቀህ የተነሳህበት እንቅፋት
ከደከመህ እረፍት አድርግ፣ ነገር ግን እንዳታቆም። ፨፨፨፨፨፨፨///////////፨፨፨፨፨፨፨ እዚህ ለመድረስ የመጣህበት መንገድ ሩቅ ነው፤ የገጠመህ ስንክሳር እልፍ ነው፤ ወድቀህ የተነሳህበት እንቅፋት ብዙ ነው፣ የገረፈህ የሰው ፊት መዓት ነው። አዎ! ጥንካሬህ በብዙ ተፈትኗል፣ እንደ ብረት በእሳት አልፈሃል፣ በአሰልቺ ድግግሞሽ ተማረሃል፣ በህይወት መንገድ ረጅም ርቀት ክንዶችህ ዝለዋል። አይዞህ ጀግናዬ...! በር..ታ በህይወት እስካለህ ጉዞህ ይቀጥላል፣ ጉዞህ ከቀጠለ ዘንዳ በሰውነትህ መድከምህ፣ መዛልህ አይቀሬ ነው። እንኳን ረጅም የህይወት መንገድ ተጉዘህ ቀርቶ ተቀምጠህም ይደክምሃልና። አዎ! ከደከመህ እረፍት አድርግ፣ ነገር ግን እንዳታቆም። ድጋሜ ከእረፍትህ ባገኘሀው አዲስ መንፈስ፣ ወኔና ብርታት ጉዞህን ቀጥል። እረፍት ብክነት አይደለም ይልቅ ለመንገድህ ግብዓት እንጂ፣ ስለዚህ ግብዓትህን በድካምህ፣ በዝለትህ፣ በሚያስፈልግህ ጊዜ ሁሉ ከመጠቀም በፍፁም እንዳትቦዝን፤ የሀሳብ ዝለትም ይሁን እረፍት ካስፈለገህና ከደከመህ፣ አንዴ ከሀሳብህ ፋታ ውሰድ ረፍት አድርገህ እንደገና ማሰብህን ቀጥል።

የምታየውን ካላመንክ የሰማከው ባዶ ነው ወታደር ቆስሎ ያክምካል ወታደር ሞቶ ያድንሀል ወታደር እንቅልፍ አቶ አንተን ያስተኛካል ወታደር ሁሉም የፈራውን እሱ ብቻ ይደፍዋል ወታደር ፍቅርን ያስተምርካል
የምታየውን ካላመንክ የሰማከው ባዶ ነው ወታደር ቆስሎ ያክምካል ወታደር ሞቶ ያድንሀል ወታደር እንቅልፍ አቶ አንተን ያስተኛካል ወታደር ሁሉም የፈራውን እሱ ብቻ ይደፍዋል ወታደር ፍቅርን ያስተምርካል ወታደር ደስታን ይሰጥሀል ወታደር ሁሉንም ያስተምርካል ብትችል የወታደርን ግማሽ ባህሪ ተላበስ ያኔ መኖርን ታቅበታለክ ክብርና ሞገስ ለሀገር ብለው ለተሰው ሰማእታት ይሁን አንተ በደምህ ሀገርን ጠብቀሀልና 💚💛❤️ ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር

አስደናቂ አቅም አለህ! የውስጡ ሲቀየር የውጪውን ማንነት መቀየር በጣም ቀላል ነው፤ ትኩረትህ ነገሮች ሁኔታዎች እስኪቀየሩ መጠበቅ ላይ ከሆነ ግን ጊዜህ እየባከነ ነው። እንቁላል እንኳን ከውጪ ሲሰበር እኮ ጫጩቷ ነብስ የላትም፤ ከውስጥ ራሷ ሰብራ ስቶጣ ግን ነብስ ትዘራለች። ተጠቅመህ የማትጨርሰው አስደናቂ አቅም አለህ፤ የመለወጥና የማደግ ጉጉትህ ከውስጥህ ገንፍሎ ከወጣ በቃ አንተን ከምትፈልገው ነገር የሚያቆምህ ምድራዊ ሀይል የለም!

💧የህይወት ፈተናዎች የሚደጋገሙት ማን እንደሆንክ ይበልጥ እንድታውቅ ነው፤ በተለይማ መቋቋም ሲያቅትህ ሊበረቱ ይችላሉ። ብረት እንደ ጋለ ነው የሚቀጠቀጠው ምክንያቱም ያኔ የምንፈልገውን ቅርፅ ለማስያዝ ይመቻል። አንተም በደስታህ ወራት ፀባይህን ህይወትህን ማሻሻል ላይታይህ ይችላል ትዘናጋለህ፤ ፈጣሪ ሊያነቃህ ፈተናዎችን ይልካል ካልሰማህ ሌላም ይጨምራል እንደ ጋለ ነው ሚቀጠቀጠው ያልኩትን አትርሳ። ታዲያ ምን ይሻላል? መፍትሄው ፈጣሪ ምን ሊያስተምረኝ ነው ብሎ ማሰብ፤ ከዛ በዚህ ከባድ ፈተና ውስጥ ግዙፉና ሀያሉ ማንነትህ ሲወጣ ታየዋለህ! የምድራችን ታላላቆች ይሄን ነው ያደረጉት። የማይጠገብ ምሽት ተመኘውላችሁ🙏

ልማድ (Habit) በየጊዜው እየደጋገምን የምናደርገውን ነገር የሚገልፅ ቃል ነው፡፡