en
Feedback
የልማድ አስደናቂ ኃይል/ Atomic Habits

የልማድ አስደናቂ ኃይል/ Atomic Habits

Open in Telegram

*ጥቃቅን ለውጦች- አስደናቂ ውጤት!!! ** የእለት ከእለት ልማዶችን በመጠቀም የላቀ ሕይወት መምራት *** ራስን የመቆጣጠር ምስጥር **** የአቶሚክ ልማድ አስደናቂ ኃይል ***** ዘላቂ ውጤቶችን የማምጣት ምስጢር

Show more
945
Subscribers
+124 hours
+47 days
+430 days
Posts Archive
ሁሉ ይቻላል! ሁሌም አስደናቂ መልሶችን እናገኛለን እንዴት ሊሆን ቻለ የምንለው ጉድ የሚያሰኝ ነገር ሁሉ በኛም ህይወት ሆነ በሌሎች ሲከናወን እናያለን መፍታት ያቃተን ችግር የሆነ ሀይል አግዞን ስንፈታው እናያለን ፣  ይህ ሁሉ የሚሆነው አንድ ትልቅ ሀይል ስላለ ነው እሱም ሀይል ፈጣሪ ነው ፣ በሰው የማይቻሉ ሁሉ በፈጣሪ ዘንድ ይቻላል ከአቅሜ በላይ ሆነብኝ ያልከውን ችግርህን ለፈጣሪ ስጠው እሱ ይፈታልህና ከአቀምህ፣ ከእግርህም በታች ያስቀምጥልሀል! ደስ የሚል ምሽት ተመኘው 🙏

ጠላትህን እና ራስህን በሚገባ ካወቅክ በመቶዎች የሚቆጠሩ ፍልሚያዎች ቢኖሩህ እንኳን ውጤቱ አያሰጋህም!                 -- Sun Tzu --

የቴሌግራም ቻናላችን 👇👇👇👇👇👇👇👇😍 https://t.me/atomichabity

ራሳችንን ለፈጣሪ እንስጠው ! ሁሌም ቢሆን ፈጣሪ በህይወታችን አለ እኛ ፈለግነውም አልፈለግነውም የሚረዳን ከእኛ ምንም ሳይጠብቅ ብዙ የሚሰጠን ፣ የሚያስብልን ፣ የሚወደን ፈጣሪ አለን  በፍፁም እንድንወድቅ  አይፈቅድም ፣ እንድንጎዳም አያደርገንም ከእርሱ በላይ የሚያውቅልን የለም ታድያ ለምንድነው እየባከንን ያለነው ? ጭንቀት ፣ መረበሽ ፣ አለመረጋጋት ፣ ነፃ አለመሆን፣ ለፈጣሪ የሚገባውን አለመስጠት ያዋጣናል? መቼም ቢሆን  ቅድሚያ ራሳችንን ለፈጣሪ  እንስጠው  ከዛም የሚጠበቅብንን በሙሉ ማድረግ እንጀምር እመኑኝ እምነታችን ከፍ ሲል ሁሌም እናተርፋለን መባከን የሚባል ነገር አይኖርም !ስለዚህ እምነታችንን በእርሱ ላይ እናድርገው! መልካም አዳር ተመኘው 🙏

ሳታልፍ በፊት ኑር! በዚህ አለም የሚያረጋጋ ቃል ቢኖር አንዱ "ሁሉም ያልፋል" የሚለው ነው፤ ሀዘኑም ያልፋል፣ደስታውም ያልፋል፣ ንዴቱም ያልፋል፣ እርካታውም ያልፋል፤ ሌላውን ተወው አንተም እኔም እናልፋለን! በፍጥረት አለም ፀንቶ የሚኖር ነገር ቢኖር አምላክ ብቻ ነው። ታዲያ ለሚያልፍ ችግር ለምን አብዝተህ ትጨነቃለህ? ለሚያልፍ ቀን ለምን ራስህን ትጎዳለህ? ህይወትህን ነብስ ዝራበት፤ የምትወደውን ስራ፣ የምትወዳትን የራስህ ለማድረግ ተዘጋጅ፣ መንፈሳዊነትህን ሳትለቅ የምድርን በረከት ሁሉ አጣጥም፤ ሳታልፍ በፊት ኑር ወዳጄ! ድንቅ ምሽት ተመኘውላችሁ🙏

ከሌሎች ተማር! ህይወትን የመሰለ ከባድ መምህር የለም ምክንያቱም ፈተናውን ከፈተነ በኋላ ነው ትምህርቱን የሚሰጠን፤ ወዳጄ ሞኝ ብቻ ነው ለሁሉም ጥያቄ መልስ ያለው፤ አንተ ከሌሎች ህይወት መማር አለብህ! የተባረከ ምሽት ተመኘውላችሁ🙏

በህይወት እያለን ማድረግ ያለብን 20 ነገሮች 1.ትላንትናን እና ነገን እያሰባችሁ አትጨነቁ፡፡ ትናንት አልፏል ነገ አልመጣም ስለዚህ ዛሬን ቀን በሙላት ፣ በደስታ ፣በሰላም ለመኖር ጥረት አድርጉ፡፡ 2.የበደሏችሁን ሰዎች ይቅርታ አድርጉላቸው ፡፡ 3.ሁሉንም ሰው በእኩል ዓይን እዩ፡፡ 4.ወደዚህ ምድር ያመጧችሁን እናትና አባታችሁን ውደዱ ፣ አክብሩ ፣ ታዘዙ ። * 5.የምትጠሉትን ስራ አትስሩ፡፡ 6.የሕይወት ግባችሁን በመለየት በቅጡ ኑሩ፡፡ 7.መስታወት ውስጥ ራሳችሁን ተመልክታችሁ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ራሳችሁን ውደዱ፡፡ 8.እዚህ ምድር የመጣችሁት በፈጣሪ አላማና እጅግ በጣም ጠቃሚ ሰዎች እንደሆናችሁ አስቡ ፡፡ 9.ዘወትር መሄድ እፈልጋለሁ ወደምትሉት ስፍራ ሂዱ፡፡ 10.በየቀኑ ለሌሎች ቢያንስ አንድ መልካም ነገር አድርጉ፡፡* 11.ለውጥን በፀጋ ለመቀበል ዝግጁ ሁኑ፡፡ 12.ሁሉንም ዓይነት የሕይወት ትምህርት በፀጋ ተቀበሉ፡፡ 13.የሕይወት ፈተና ውስጥ ያለውን መልካም አጋጣሚ አስተውሉ እንጂ ተስፋ አትቁረጡ፡፡ 14.በአስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ አዎንታዊ እና በጎ አሳቢ ሆናችሁ ዝለቁ፡፡ 15.በሰው ሁሉ ለመወደድ ሳይሆን ሰውን ሁሉ ለመውደድ ጣሩ ፡፡* 16.ከቁሳ ቁስ ጋር ያላችሁን ትስስር አላሉ፡፡ 17.ልባችሁን ተከተሉ፡፡ 18.ሁልጊዜም ትልቅ በመሆን ሌሎችን አነቃቁ፡፡ 19.ከሰዎች ሁሉ ጋር ተጫወቱ በሰላም በመግባባት ኑሩ  20.የተቸገሩትን ደግፉ ፡፡ ደግሞም ይህን ጽሑፍ #Share አርጉ ፡፡*😍😍😍 የዘለልኩት እስቲ እኔ ያልጠቀስኩት መደረግ ያለበት ነገር #Comment እንድታረጉልኝ ነው

የቆራጥ ሰው እጣፋንታ ቆራጥ መሆን ስትጀምርና ወደ ራስህ ስታተኩር ምድራዊ ጥያቄህ መመለስ ይጀምራል፤ እጣፋንታህ በሰዎች እጅ መሆኑ ያቆማል። ህይወትህን የሚቀይረው ከሰዎች በምታገኘው እርዳታ ወይ ትብብር አይደለም ወይ ሁኔታዎች በሚያመጡት ዕድል አይደለም! ህይወትህ የሚቀየረው ቆራጥ በመሆንህ አምላክህ በሚያዘጋጀልህ ስጦታ ነው! ለዛ ነው መጠንከር ስትጀምር ሰዎች የሚያከብሩህ፣ ስራው ዕድሉ ገንዘቡ የፍቅር ግንኙነቱ ሁሉ የሚስተካከለው። ወዳጄ መጠንከር እንደጀመርክ አውቃለው ከዛ ግን ወደኋላ ማየት የለም! ተአምረኛ ምሽት ተመኘውላችሁ🙏

እኔ እችላለሁ💪 ለራስህ እንዲህ ብለህ ንገረው አይምሮህ መሬት ነው የዘራህበትን ነው የሚያበቅለው። 1. እኔ ልዩ ነኝ! እኔ ድንቅ ነኝ! 2. እኔ እችላለሁ! 3. በጎ አሳቢ አይምሮ አለኝ! 4. የጀመርኩትን የህይወትና ጉዞ በድል እጨርሳለሁ! 5. ስኬታማም፤ ደስተኛም፤ መንፈሳዊም ነኝ! ይሄን ለራስህ መንገር ወይ ድምፅ አውጥተህ ማንበብ ብቻ ስሜትህን ይቀይረዋል፤ ቀንህን ስለ ድክመትህ፣ ስለ ጭንቀትህ፣ ስለ ችግርህ በማሰብ አትጀምር! ምክንያቱም ጭንቀትና ችግር ከዘራህ ጭንቀትና ችግር ነው ምታጭደው፤ አይምሮህ ውስጥ አሪፍ ነገር ዝራ ወዳጄ! 💖☀️የደስታ ቀን☀️💖 🙏ተመስገን ዛሬ ቀኑ ደስ ሲል

እንደገና ትበረታለህ! ማንነትህን የሚገልፀው ፊትለፊት ያለው ስጋዊ ሁኔታህ አይደለም፤ የሰው ልጅ ስትሆን መንፈስ የሚባል ድንቅ ስጦታ ተሰጥቶሀል። መንፈስህ እስካልተሰበረ ድረስ መልሰህ ትነሳለህ! እንደገና ትሞክራለህ! ስጋህ ቢዳከም ሁሉም ነገር የጨለመ ቢመስልህም እንኳን ጨዋታው ገና ነው ምክንያቱም ሀያሉ መንፈስህ አፈር ልሶ የመነሳት ጥበብ አለው። ቀን ቢያስጎነብስህ መልሶ የሚያነሳ ጥሎ የማይጥል ፈጣሪ አለህ! ወዳጄ መቼም አያበቃልህም! የሚደንቅ ምሽት ተመኘውላችሁ🙏

መልካምነት ዋጋ ይጨምራል ! ለሰው መልካም መሆን በምንም ሁኔታ ይጠቅመናል እንጂ በፍፁም ሊጎዳን አይችልም ! እኛ ሀላፊነታችን ከእኛ የሚጠበቅብንን ማድረግ እንጂ ሌሎች የሚሰጡንን ምላሽ መቆጣጠር አይደለም ! መልካም በሆንን ቁጥር ውስጣችን ይፀዳል ክፋና መርዛማ የሆኑ ውስጣችንን የሚጎዱ ነገሮች ሁሉ ከላያችን ይወጣሉ ፣ በስተመጨረሻ እነሱ ከሚሰጡን ምላሽ በላይ እኛ የምናገኘው እርካታ ተወዳዳሪ የለውም ! ስለዚህ በምንም ሁኔታ ውስጥ ብትሆን መልካምነትህን ዝም ብለህ ቀጥል! መልካም አዳር ተመኘው🙏😊

እድል ተሰጥቶናል ! ፈጣሪ የተመሰገነ ይሁን ዛሬ ከእንቅልፋችን ነቅተናል ፣ ከትላንት ተሸጋግረናል የመኖር የመለወጥ ደስተኛ የመሆን ሌላ እድል  ተሰጥቶናል ትላንትን ማረሚያ ነገን ማሳመሪያ ቀን ተሰጥቶናል! ስለዚህ ፈጣሪያችንን አመስግነን ቀና እንበል! የደስታ ቀን ተመኘው 🙏

አስቀድመህ ተማር! ፨፨፨፨///////፨፨፨፨ የዛሬ አሸናፊነትን ትልቅነት ማወቅ ከፈለክ የነገውን ቁጪት ጠብቀህ ተመልከት። የዛሬ ልፋትህን ዋጋ መረዳት ከፈለክ ከዓመታት ቦሃላ የት እንደሆንክ እራስህን ተመልከት። በጊዜዎችህ ውስጥ ዋጋ የሌለው ነገር የለም። ያደርሰኛል ብለህ የመረጥከው እርምጃ ሳታቋርጥ ስትጓዝ በእርግጥም ያደርስሃል። ዛሬ ነገ እያልክ ስታስተላልፈው የነበረው እቅድህ ዛሬ ነገ ሳይል ያስቆጭሃል፤ ዋጋ ያስከፍልሃል፤ ያሳምምሃል። እያንዳንዱ ተግባርህ ትልቅ ዋጋ አለው። ስታሸንፍ ብቻ ህይወትን በፈለከው መንገድ ትመራለህ፤ ህይወትህን ስትቆጣጠር ብቻ የተሻልክ ሰው እየሆንክ ትመጣለህ፤ ሁሌም የተሻልክ ስትሆን ብቻ የተሻሉ ነገሮችን ታገኛለህ። ሁሉም የጥረትህ ውጤት ነው። በእራስህ ላይ ሃላፊነት በወሰድክ ቁጥር ማንነትህን ታሳድጋለህ፣ ስብዕናህን ትገነባለህ፣ ትሻሻላለህ፣ ትበለፅጋለህ። አዎ! አስቀድመህ ተማር! ከቅጣቱ በፊት ተማር፣ ከመከራው በፊት ይግባህ፣ ከችግሩ በፊት ችግሩን ተረዳ፣ ሳይደርስብህ ከደረሰባቸው ትምህርት ቅሰም፣ እራስህን አንድ እርምጃ አስቀድም። ዛሬ የሚያስቡትን በማድረግ ከሚገኘው ድል በላይ ለነገ የሚቀመጠው የቁጪት ሸክም ይበልጣል። ምክንያቱም ድሉ ባለህ ላይ ሲጨምር ቁጪቱ ግን ህመም ይሆንብሃል፣ እራስህን ያሳጣሃል፣ ዋጋህን ያሳንሰዋል፣ ለበታችነት ይዳርግሃል። ህይወት ብዙ አማራጭ ስታቀርብልህ፣ እድሎችን ስትፈጥርልህ በጋፋሃቸው ልክ የግፊቱን ዋጋ፣ የቸልተኝነቱን ውጤት ሳይውል ሳያድር ትከፍላለህ። ከዛሬ የተሻለ ነገ የሚያመጣልህ እድል የለም፤ ከዛሬ በላይ ነገ የምታገኘው አጋጣሚ አይኖርም። የሁሉም ነገር ጠዓም በዛሬ ውስጥ፣ በአሁን ውስጥ ነው። The real feeling is only NOW. እውነተኛው፣ የሚጨበጠው፣ የሚዳሰሰው፣ የሚኖረው ስሜት አሁን ብቻ ነው። ቀሪው ጉም መሳይ የሚበተን ሃሳብ ነው፣ አይጨበት፣ አይዳሰስ፣ አይኖር። አዎ! አሁንን ከመኖር፣ አሁንን ከመምረጥ በላይ አዋጭና ስኬታማ ምርጫ የለም። ከምንም፣ ከማንም በፊት በአሁንህ ላይ ንገስ፣ አሁንን ተቆጣጠር፣ አሁን ላይ ሰልጥን፣ አሁን በሙላት ኑር፣ የአሁን ዋጋ አሁን ይሰማህ። ብልህ ከጊዜ ሳይሆን ጊዜ ከእርሱ እንዲማር ያደርጋል። የእያንዳንዱ ተግባሩ ዋጋ ከውጤት ቦሃላ ሳይሆን ከውጤቱ በፊት ይገባዋል። "ምን ባደርግ ከምን እድናለሁ? ምንስ አተርፋለሁ? ለማንስ እተርፋለሁ?" የሚለውን ቀድሞ ያውቀዋል። የሚጨበጠውን አሁን መጨበጥ፣ የሚኖረውን አሁን መኖር ለድርድር የሚቀርብ ጥልቅ ሃሳብ ሳይሆን በስሜት የሚኖርና ከልብ የሚደረግ ነው። ከዚህች ቅፅበት በላይ ልዩ ቅፅበት በፍፁም አይኖርም። ባለንበት እንዳለን አሁንን እናጣጥም፤ አሁንን እንኑር፤ ዋጋ እንስጣት፤ ለተሻለና ለላቀ ውጤት እንብቃባት፤ አስደናቂውን የህይወት አቅጣጫም እንያዝባት፤ ከቅጣት በፊት እንማርባት። ውብ ቀን ይሁንልን! 🏞🌞🌅 የልማድ አስደናቂ ኃይል ለተሻለ ነገ! 🦋

ትልቅ ደረጃ መድረስ ከፈለጋችሁ! በእድሜ ቆጠራ ብቻ፣ በገንዘብ ብዛት ብቻ፣ በአእምሮ እውቀትም ብቻ . . . ትልቅ ደረጃ መድረስ አይቻልም፡፡ እነዚህንና ሌሎችም ነገሮች ኖሯቸው በሕብረተሰቡ መካከል
ትልቅ ደረጃ መድረስ ከፈለጋችሁ! በእድሜ ቆጠራ ብቻ፣ በገንዘብ ብዛት ብቻ፣ በአእምሮ እውቀትም ብቻ . . . ትልቅ ደረጃ መድረስ አይቻልም፡፡ እነዚህንና ሌሎችም ነገሮች ኖሯቸው በሕብረተሰቡ መካከል ትልቅ ደረጃ የደረሱ ሰዎች የመኖራቸውን ያህል፣ እነዚህ ነገሮች እያሏቸው ለአናሳ ነገር ሰክነውና አናሳ ሕይወት ኖረው የሚያልፉ ጥቂቶች አይደሉም፡፡ ትልቅ ደረጃ መድረስ ከፈለጋችሁ፡- 1. ከትንሽነት አመለካከት መውጣት አስፈላጊ ነው፡፡ አመለካከታችን ዛሬ ካለንበት ደረጃችን ወደላቀ ከፍታ የሚያወጣንን ራእይና አላማ ካላካተተ ይህ የአመለካከታችን ትንሽነት የማንነት አናሳነት መፍጠሩ አይቀርም፡፡ 2. ከትንንሽ ንግግሮች መላቀቅ የግድ ነው፡፡ የምናወራቸው ነገሮች በእለቱ ከሚናፈሰውና የሰውን ነገር ከመብላት አልፎ ካልሄደ የንግግራችን አናሳነት የማንነት ትንሽነት መፍጠሩ አይቀርም፡፡ 3. ከትንንሽ ገጠመኞች በላይ መኖር ወሳኝ ነው፡፡ በየቀኑ የሚገጥሙንን ጥቃቅን አስቸጋሪ ገጠመኞች አልፈን በመሄድ ትኩረታችንን ዋናውና ዘላቂው የሕይወታችን አላማ ላይ ካላደረግን ሁኔታው የማንነት አናሳነት መፍጠሩ አይቀርም፡፡፡፡ 4. ከትንንሽ ዘሮች ዘልቆ መሄድ ጠቃሚ ነው፡፡ ትንሽ ዘር፣ ትንሽ ፍሬ … ትንሽ ሙከራ፣ ትንሽ ስኬት … ትንሽ መስዋእትነት ትንሽ ዋጋ … ትንሽ እቅድ፣ ትንሽ ውጤት ስሌቱ ይኸው ነው፡፡ ከዚህ አዙሪት ወጥተን በትልቁ መዝራት ካልጀመረን ሁታው የማንነት አናሳነት መፍጠሩ አይቀርም፡፡ Source ዶ/ር ኢዮብ ማሞ

በህይወታችሁ "ፀሀይ" ሊሆኑ ያሰቡላችሁን ሳይሆን "ጨረቃ" የሚሆኑት ጋ አመዝኑ። ምክንያት... ጨረቃ በቀን ተደብቃ ብትኖርም ቅሉ በይበልጥ ደምቃ የምትወጣው ሲመሻሽ/ሲጨልም ነውና... በብርሃናችሁ ጊዜ የሚመጣውን ፀሀይ ሰው ተዉት ጨለማችሁ ላይ አለሁ የሚለውን "ጨረቃ" ውደዱት

ፉክክሩን አቁም! የፉክክር ቤት ሳይዘጋ ያድራል፤ ራስህን ከሰዎች ጋር የምታወዳድር ከሆነ መቼም አትደሰትም፤ ደስ ቢልህ እንኳን ደስታህ ብዙ አይቆይም! ከራሱ ጋር የሚወዳደር ሰውን ግን ማንም አያቆመውም። በራስህ ለውጥ ደስ ይበልህ፤ ዛፎች ሁሉ እኩል አያድጉም ግን ማደግ እስከሚችሉት ከፍ ይላሉ። ወዳጄ አይንህን ከሌሎች ላይ ነቅለህ ወደ ራስህ ባየህ ቁጥር እድገትህ ፈጣን ነው፤ ከሁሉ በላይ ደግሞ የአይምሮ ሰላም አለህ! ሰላማዊ ምሽት ተመኘንላችሁ🙏 @Inspire_Ethiopia የእናንተው ምርጥ ጓደኛ!

ልማድህን አስተካክል! አብዛኛዎን ግዜ ስኬታማ የሆኑ ሰዎችን ስናይ እሱማ ፈጣሪ ይወደዋል አሳክቶለታል እንላለን ሁሌም ያገኘውን ስኬት እንጂ ከጀርባ ሆኖ ሲለፋ የነበረውን ልፋት አናየውም አትሌቶቻችን ይሄን ያህል ድል ሲያስመዘግቡ እድለኛ ሆነው ሳይሆን ሌላው የማያረገውን ሁሉ ልፋት ሳያወላውሉ ስለለፋት ነው! ስለዚህ ቁጭ ብለን እድል ከመጠበቅ ለስኬታችን የሚገባውን እኛን እንስጠው! ተነሳ አሸናፊ መሆን ካቀድህ የአሸናፊ ሰው ልማድ ይኑርህ! የተባረከ ሰንበት ተመኘን🙏 @Inspire_Ethio

አንድ መተማመኛ! ፈጣሪ ባይረዳህ ፅናትና ትዕግስቱን ባይሰጥህ የማታልፋቸው ጊዜያት ነበሩ፤ አየህ ከዚህ በኋላ ለሚገጥሙህ ከባድ ፈተናዎች ሁሉ አንድ መተማመኛ አለህ! ወዳጄ ዝቅ ያልክ ሲመስልህ ከፍ የሚያደርግህ፤ ብታጎነብስም ቀና አርጎ በናቁህ ፊት የሚያከብርህ ፈጣሪህ አለና ተመስገን በል! የምስጋና ምሽት ተመኘንላችሁ🙏

ተዘጋጅ! ወዳጄ አሁን ያለህበት ሁኔታ ነገ የምትደስበትን አያሳይም፤ ስለዚህ ከጓደኞቼ አነስኩ ብለህ አትሸማቀቅ። እነሱ በአለባበስና በሁኔታህ ሊያሸማቅቁህ ቢሞክሩ የዛሬ 10 ዓመት ያገናኘን በላቸው። ቃልህን ለመጠበቅ ግን እያንዳንዱን ቀን ተዘጋጅ፣ ስራው ትንሽ ነው ብለህ ሳትንቅ ስራ፣ ተማር ራስህን አሳድግ እውነተኛ ለውጥ ጊዜ ይጠይቃል ከፍ ማለት ስትጀምር ግን ማንም አይመልስህም ምክንያቱም አቋራጭ ተጠቅመህ እዛ አልደረስክማ! ቶሎ ለውጥ የምትፈልግ ከሆነ ግን ልትሳሳት ነው ይሄን አስታውስ!