en
Feedback
Kolfe Woreda 06 Communication - ኮልፌ ወረዳ 06 ኮሙኒኬሽን

Kolfe Woreda 06 Communication - ኮልፌ ወረዳ 06 ኮሙኒኬሽን

Open in Telegram

This is a governmental media, News organization ; based in Kolfe Keranio Subcity Woreda 6 Administration.

Show more
206
Subscribers
No data24 hours
-17 days
-230 days
Posts Archive
የወረዳው ካቢኔ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ። ኮልፌ ወረዳ 06ኮሙኒኬሽን መስከረም 27/2017ዓ.ም የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ የወረዳ 06 አስተዳደር ካቢኔ ውሳኔ በሚያስፈልጋቸው
+6
የወረዳው ካቢኔ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ። ኮልፌ ወረዳ 06ኮሙኒኬሽን መስከረም 27/2017ዓ.ም የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ የወረዳ 06 አስተዳደር ካቢኔ ውሳኔ በሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ላይ የተወያየ ሲሆን ውሳኔ በሚሺ የቀጥታ ድጋፍ ተጠቃሚ ልየታ ዙሪያ እና በወረዳው የተሻለ እና ቀልጣፋ አገለግሎት ለመስጠት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይቶች በማካሄድ ውሳኔዎችን አሳልፈዋል።

የልጅነት ልምሻ(ፖሊዮ) ክትባት ዘመቻ በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ በሚገኙ በሁሉም ወረዳዎች ተጀመረ። ኮልፌ ኮሙኒኬሽን መስከረም 27/2017 ዓ.ም በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ በሚገኙ 11 ዱም ወረዳ
+9
የልጅነት ልምሻ(ፖሊዮ) ክትባት ዘመቻ በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ በሚገኙ በሁሉም ወረዳዎች ተጀመረ። ኮልፌ ኮሙኒኬሽን መስከረም 27/2017 ዓ.ም በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ በሚገኙ 11 ዱም ወረዳዎች ላይ የልጅነት ልምሻ (ፖሊዮ) ክትባት ዘመቻ በዛሬው እለት በመካሄድ ላይ ይገኛል። በክፍለ ከተማው ወረዳ 06 ጤና ጣቢያ በተካሔደው የፖሊዮ ክትባት ማስጀመሪያ መርሀ ግብር ላይ የተገኙት የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው መንግስት የጤናው ዘርፍን ለማጠናከር ብዙ ተግባራትን እየከወነ እንደሚገኝ ገልፀው ከዚህም ውስጥ የህፃናትን ጤና በመጠበቅ የቅድመ መከላከል ስራ ላይ የክትባት ዘመቻዎች አንዱ ነው ሲሉ ገልፀው፡፡ ከዛሬ ጀምሮ ለሚሰጠው የልጅነት ልምሻ(ፖሊዮ ክትባት) ህብረተለቡ ህፃናትን እንዲከተቡ ግንዛቤዎች መፍጠር ሀላፊነቱን እንዲወጣ አሳስበዋል። የክፍለ ከተማው የጤና ፅህፈት ቤት ሀላፊ ወ/ሮ ሂሩት ባንጃው በክፍለ ከተማው እድሜያቸው ከ5 ዓመት በታች ለሆኑ ከ83 ሺ በላይ ህፃናት በትምህርት ቤቶች፣በህፃናት ማቆያ፣እንዲሁም ቤት ለቤት ከመስከረም 27 እስከ መስከረም 30 ድረስ የህፃናት የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ይካሄዳል ሲሉ ገልፀዋል። የልጅነት ልምሻ (ፖሊዮ) ያልተከተቡ ህፃናት ዘላቂ የአካል እስከ ሞት የሚያደርስ ጉዳት የሚያስከትል በመሆኑ ከዚህ በፊት የተከተቡም ይሁኑ ያልተከተቡ እድሜያቸው እስከ 5 ዓመት የሆናቸው ህፃናት በተጠቀሱት ቀናቶችና ቦታዎች ክትባት መከተብ እንደሚገባቸው አሳስበዋል። በማስጀመሪያ መርሀ ግብሩ ላይ የሀይማኖት አባቶች፣የትምህርት ቤት ተወካዮች፣የእድር መሪዎች፣ ከማህበረሰቡ የተወጣጡ ተፅእኖ ፈጣሪ በጎፍቃደኞች ተሳታፊ ሆነዋል።

የ2016 ዓ/ም እቅድ አፈጻፀም እና የ2017 ዓ/ም ዕቅድ ዙሪያ ውይይት አካሄዱ፡፡ ኮልፌ ወረዳ 06 ኮሚኒኬሽን መስከረም 27/2017 የኮልፌ ቀራንዬ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር ንግድ ጽ/ቤት
+7
የ2016 ዓ/ም እቅድ አፈጻፀም እና የ2017 ዓ/ም ዕቅድ ዙሪያ ውይይት አካሄዱ፡፡ ኮልፌ ወረዳ 06 ኮሚኒኬሽን መስከረም 27/2017 የኮልፌ ቀራንዬ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር ንግድ ጽ/ቤት የ2016 ዓ/ም የስራ አፈጻፀም እና በ2017 ዓ/ም ዕቅድ ዙሪያ ከባለ ድርሻ አካላ ጋር ውይይት አደረጉ፡፡ የኮልፌ ቀራንዬ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 ንግድ ጽ/ቤት ቡድን መሪ አቶ ሰለሞን የ2016 ዓ/ም የስራ አፈጻፀም እና በ2017 ዓ/ም ዕቅድ ያቀረቡ ሲሆን በ2017 ዓ.ም ዘመናዊና ቀልጣፋ አገልግሎቶችን በመስጠት፣ ቅንነት የተሞላባቸው አገልግሎቶችን በመስጠትና ቅንጅታዊ አሰራሮቸን በማጎልበት ህብረተሰብ ተሳትፎ በማጠናከር የተሸሉ ስዎራችን መሰራት እንዳለባቸው ገልፀዋል፡፡ በመቀጠልም የአዲስ አበባ ከተማ ዘመናዊ፣ ፍትሀዊና ተወዳዳሪ የንግድ ማዕከል ከሆኑ የአፍሪካ ከተሞች ግንባር ቀደም ሆና መታየት እንድትችል ጠንካራ የክክትትልና ቁጥጥር ስርዓት በመዘርጋት እና የሸማቾችን መብትና ጥቅም በማስጠበቅ ፍትሀዊ ግብይትን ማስፈንና ጥራት ያለው አገልግሎት አስጣጥ በማዘመን የዜጎችን ደህንነት ማረጋገጥ ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች ነበሩ፡፡ በስተመጨረሻም ከባለድርሻአካላቱ የተነሳውን ሃሳብ አስተያየት በመቀበልና ምልሽ በመስጠት ውይይቱን አጠናቀዋል፡፡

Irreechi Keenya, Haaromsa Aadaa Keenyaaf! እሬቻ ለባህላችን ህዳሴ! በሚል መሪ ቃል በኢሬቻ በዓል አከባበር ዙሪያ ፓናል ውይይት ተካሄደ፡፡ ኮልፌ ወረዳ 06 ኮሙኒኬሽን መስከረም 21/2017 ዓ.ም በወረዳው እየተከበረ በሚገኘው የኢሬቻ በዓል ሳምንት መርሃ ግብር ላይ የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው፣ የወረዳዉ የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ማስተባበሪያ ፅ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ አልማዝ ፍሮምሳ፣ የወረዳዉ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አሸናፊ ይርጋ፣ እና የወረዳ አመራሮች እንዲሁም አባ ገዳዎች፣ሀደ ሲንቄዎች፣ ፎሌዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው የወረዳው ነዋሪዎችና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች በመርሃ ግብሩ ላይ ተሳታፊ ሆነዋል። የኮልፌ ወረዳ 06 ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ አሸናፊ ይርጋ በከተማችን ሚከበረዉ የሆራ ፊንፍኔ በአል በአብሮነትና በወንድማማችነት ልናከበረዉ ይገባል ሲሉ መልክት አስተላልፈዋል፡፡ የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ንጋቱ ዳኛቸው ባስተላለፍት መልእክት ከሁሉም በማስቀደም በአለም በማይደሰሱ ቅርሶች ዩኒስኮ ለተመዘገበው የዴሞክራሲ ስርአት መነሻ ለሆነው የገዳ ስርአት ለሚከበረው ለሆራ ፊንፊኔ እና ለሆራ አርሰዴ የኢሬቻ በአል ዋዜማ አደረሳቹ አደረሰን በማለት መልእክት ያስተላለፍ ሲሆን የኢሬቻ በአል የእኛ በአል ነው የሁሉም ኢትዮጵያዊ በአል የአፍሪካ እና የአለም ታላቅ በአል ነው ብለዋል። ወ/ሮ አልማዝ ፍሮምሳ የወረዳ6 ዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተብስበሪያ ጽ/ቤት ሀላፊ በመድረኩ ላይ ባስተላለፉት መልእክት ኢሬቻ የኦሮሞ ህዝብ ፈጣሪውን ከክረምት ጨለማ እንኳን ወደ ጸደይ ብርሀን በሰላም አሸጋገረን በማለት የሚያመሰግኑበት ስርዓት ምሆኑን ጠቅሰው በዓሉ የኦሮሞ ህዝብ ብቻ ሳይሆን የታላቋ ኢትዮጵያ እና የአለም ህዝብ በመሆኑ በአንድነትና በፍቅር ልናከብረው ይገበባል ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። በስነስርዓቱ ላይ የኪነጥበብ ድግስ፣የባህላዊ ምግቦች ትይንት፣የአባገዳዎችና ምርቃት ቀርቧል።

የሆረ ፊንፊኔ እሬቻ በዓል በልዩ ሁኔታ በኮልፌ ወረዳ 06 ተከበረ። በኮልፌ ቀራንዮ ከፍለ ከተማ ወረዳ 06 ቤቴል አካባቢ በድምቀት ተከብሯል። በዚህ ዝግጅት ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የኮል
+9
የሆረ ፊንፊኔ እሬቻ በዓል በልዩ ሁኔታ በኮልፌ ወረዳ 06 ተከበረ። በኮልፌ ቀራንዮ ከፍለ ከተማ ወረዳ 06 ቤቴል አካባቢ በድምቀት ተከብሯል። በዚህ ዝግጅት ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አሸናፊ ይርጋ ከገዳ ስርዓት አንዱ በሆነው የእሬቻ በዓል እንኳን አደረሳችሁ ያሉ ሲሆን እሬቻ የመላው ኢትዮጵያውያን በዓል መሆኑን ገልጸዋል። በአለም ቅርስነት የተመዘገበ ድንቅ የቱሪዝም መስህብ መሆኑንም ገልጸዋል። የኮልፌ ቀራንዮ ከፍለ ከተማ ወረዳ 06 የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ አልማዝ ፍሮምሳ በበኩላቸው የእሬቻ በዓል በርካቶች እንዳያከብሩ ተነፍገው የነበር መሆኑን ገልጸው አሁን ባለው ለውጥ ሆረ ፊንፊኔ በታላቅ ድምቀት እየተከበረ መሆኑን ገልጸዋል። በዐሉ ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ድርሻቸውን የተወጡ አካላትን ሁሉም አመስግነዋል። ከ1000 ሰዎች በላይ የተሳተፉበት ይህ ዝግጅት ወጣቶች፣ አባቶች፣ እናቶች፣ተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በዚህ ዝግጅት ላይ የተሳትፈዋል። በዋናነት ዝግጅቱ እንግዶችን ከመቀበል ባለፈ ከሆራ ፊንፊኔ መልስ በመሰባሰብ በድምቀት የሚከበር ነው።

የወረዳ 06 አስተዳደር የኢሬቻ በዓል በማስመልከት ወደ ከተማችን ለመጡ እንግዶች የሚሆን በሬዎችን በአባቶች ምርቃት እርድ ተካሄዷል ።
+9
የወረዳ 06 አስተዳደር የኢሬቻ በዓል በማስመልከት ወደ ከተማችን ለመጡ እንግዶች የሚሆን በሬዎችን በአባቶች ምርቃት እርድ ተካሄዷል ።

Irreecha_Keenya_Haaromsa_Aadaa_Keenyaaf #እሬቻ_ለባህላችን_ህዳሴ #Irreechaa_for_Our_Cultural_Renaissance የኮልፌ ወረዳ 06 አስተዳደር በወረዳ 08 አስ
+9
Irreecha_Keenya_Haaromsa_Aadaa_Keenyaaf #እሬቻ_ለባህላችን_ህዳሴ #Irreechaa_for_Our_Cultural_Renaissance የኮልፌ ወረዳ 06 አስተዳደር በወረዳ 08 አስተዳደር በገኘት የኢሬቻን ክብረ በዓል ለማክበር ለሚመጡ እንግዶች በወንድማማችነት በመቀበል ውሃ ኤና የማዕድ በማጋራት በዓሉ የፍቅር፤የሠላም፤የወንድማማችነት እንዲሆን ያለውን አክብሮትና ፍቅር ገልፃል ። በኢሬቻ ቂም በይቅርታ ይሻራል፣ ጨለማ ለብርሀን እጁን ይሰጣል፣ የተለያየ ይገናኛል፣ የተጣላ ይታረቃል፣ ጥላቻ ቦታውን ያጣል ወንድማማችነት፣ እህትማማችነት እና አብሮነት ይነግሳል። #እሬቻ_ለባህላችን_ህዳሴ ኢሬቻ: የሰላም፣ የፍቅርና የአንድነት እሴት!

#የአካባቢየን_ሰላም_ለመጠበቅ_ዝግጁ ነኝ" የኮልፌ ቀራንዬ ክ/ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር የአካባቢየን ሰላም ለመጠበቅ ሁሌም ዝግጁ ነኝ " "በሚል መርህ የሰላም አምባሳደር ለሆኑት ለሰላም ሰራዊት የ
+9
#የአካባቢየን_ሰላም_ለመጠበቅ_ዝግጁ ነኝ" የኮልፌ ቀራንዬ ክ/ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር የአካባቢየን ሰላም ለመጠበቅ ሁሌም ዝግጁ ነኝ " "በሚል መርህ የሰላም አምባሳደር ለሆኑት ለሰላም ሰራዊት የወረዳ 06 ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አሸናፊ ይርጋ ስምሪት ሰተዋል ። ስምሪቱም በቅንጅት ከፀጥታ አካላት ጋር በመሆን ነገ ለሚከበረው የኢሬቻ በዓል በሰላም እንዲጠናቀቅና ለሀገራቸው አለኝታ እንዲሆኑ የሚያስችል እንደሆነና ሀገራቸውንና ከተማቸውን ብሎም ወረዳቸውን በመጠበቅ ትልቅ ሀላፊነት እንዳለባቸው በስምሪቱ ላይ ተገልፆል። ኮልፌ ወረዳ 06 ኮሙኒኬሽን መስከረም 24/2017ዓ.ም

"እንኳን ለ 2017 ዓ.ም የኢሬቻ በዓል አደረሳቹ/አደረሰን"። የኮልፌ ቀራንዬ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ማስተባበሪያ ፅ/ቤት ሀላፊ ወ/ሮ አልማዝ ፍሮምሳ ለኢሬቻ በዓል የእን
"እንኳን ለ 2017 ዓ.ም የኢሬቻ በዓል አደረሳቹ/አደረሰን"። የኮልፌ ቀራንዬ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 የዴሞክራሲ ስርአት ግንባታ ማስተባበሪያ ፅ/ቤት ሀላፊ ወ/ሮ አልማዝ ፍሮምሳ ለኢሬቻ በዓል የእንኳን አደረሳቹ መልዕክት አስተላልፈዋል። የእርቅ፣ የሰላምና የወንድማማችነት መገለጫ የሆነው ኢሬቻ ባህላዊ ትውፊቱንና ዕሴቱን ለመጪው ትውልድ ከማቆየት ባለፈ አለማቀፋዊ ይዘት ያለው እንደመሆኑ በአሉ በጎ እድሎችን የሚፈጥር የሀገራችን ድንቅ ባህልና የአለም ቅርስ ነው። መላው ኢትዮጵያዊያን በፍቅርና በአብሮነት አሸብርቀን ከምናከብረው የኢሬቻ በዓል የሚገኙ ትሩፋቶችን ለሀገራዊ አንድነት ለማዋል ሁላችንም የድርሻችንን መወጣት ይጠበቅብናል። ኢሬቻ ለህዳሴያችን!

#ኢሬቻ_የሰላምና_የወንድማማችነት_እህተማማችነት_ተምሳሌት እንኳን ለኢሬቻ በዓል በሰላም አደረሰን/አደረሳችሁ ! አቶ አሸናፊ ይርጋ የኮልፌ ቀራንዬ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 ዋና ስራ አስፈፃሚ #ኢሬቻ የ
#ኢሬቻ_የሰላምና_የወንድማማችነት_እህተማማችነት_ተምሳሌት እንኳን ለኢሬቻ በዓል በሰላም አደረሰን/አደረሳችሁ ! አቶ አሸናፊ ይርጋ የኮልፌ ቀራንዬ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 ዋና ስራ አስፈፃሚ #ኢሬቻ የወንድማማችነት የእህትማማችነት የፍቅር የመቻቻል ፈጣሪን የምንለምንበት በዓል እንዲሁም ከጨለማ ወደ ብርሃን ላሸጋገረን አምላክ ምስጋና የምናቀርብበት የኢትዮጵያ ውበት የሆነ የኦሮሞ ህዝብ ድንቅ በዓል ነው! እንዲሁም ሀገራችንን በዓለም አደባባይ በድንቅ ውበቱ ያስተዋወቀ የሀገራችን ቅርስ ነው! #ኢሬቻን ስናከብር በወንድማማችነት በእህትማማችነትተጋምደን በፍፁም ፍቅር ኃላፊነታችንን በመወጣት ሰላምና ፀጥታ በማስጠበቅ መስራት አለብን። በማለት ገልፀው በድጋሚ እንኳን አደረሳቹ አደረሰን ብለዋል! መልካም በዓል!

በተባበረ ክንድ የአካባቢያችንን ሰላም ለማስጠበቅ በትጋት እንሰራለን ኮልፌ ወረዳ 06 ኮሚኒኬሽን መስከረም 24/2017 በኮልፌ ቀራንዬ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር የሰላም ሰራዊት ስምሪት በአን
+9
በተባበረ ክንድ የአካባቢያችንን ሰላም ለማስጠበቅ በትጋት እንሰራለን ኮልፌ ወረዳ 06 ኮሚኒኬሽን መስከረም 24/2017 በኮልፌ ቀራንዬ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር የሰላም ሰራዊት ስምሪት በአንድ ማእከል ተሰጥቷል ። በወረዳ አስተዳደሩ የሰላም ሰራዊት ስምሪት የዘወትር ተግባር ቢሆንም ነገ የሚከበረውን የኢሬቻ በዓል ጋር በተያያዘ ከወትሮው የተለየና የተጠናከረ የአንድ ማዕከል ስምሪት መስጠት ተችልዋል ። የኮልፌ ቀራንዬ ክፍለ ከተማ ስራ አስኪያጅ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ዳኛቸው አበበ በስምሪቱ ባሰ‍እተላለፊት መልክታቸውን የሰላም ሰራዊቱ ከፀጥታ ሀይሉና ከማህበረሰቡ ጋር በመቀናጀት የአከባቢውን ሰላምና ደህንነት በንቃት ይህንን ታላቅ በዓል በሰላም እንዲጠናቀቅ በትኩረት መስራት እንዳለባቸው ተገልጿል ። በዓሉ ሰላማዊ ሆኖ እንዳይከበር የሚፈልጉ ፀረ ሰላም ሀይሎች እኩይ ዓላማና ፍላጎት እንዳይሳካ የፀጥታ ሀይሉ አጋዥና ተጨማሪ አቅም በመሆን መስራት እንዳለባቸው የኮልፌ ቀራንዬ ክፍለ ከተማ ዲሞክራሲ ስርአት ግንባታ ማስተባበሪያ ፅ/ቤት ሀላፊ ወ/ሮ አልማዝ ፍሮምሳ መልዕክት አስተላልፈዋል።

#ኮልፌ_ኢሬቻ_2017 #Irreecha_Keenya_Haaromsa_Aadaa_Keenyaaf #እሬቻ_ለባህላችን_ህዳሴ! #Irreechaa_for_Our_Cultural_Renaissance! ኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከ
+6
#ኮልፌ_ኢሬቻ_2017 #Irreecha_Keenya_Haaromsa_Aadaa_Keenyaaf #እሬቻ_ለባህላችን_ህዳሴ! #Irreechaa_for_Our_Cultural_Renaissance! ኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር ለኢሬቻ በዓል ተሳታፊ እንግዶቿን ለመቀበል እንዲህ ቅድመ ዝግጅት ተጠናቋል። "ኢሬቻ በዓልን በወንድማማችነት እሴት ከኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ጋር በጋራ በአብሮነት ማጠናከር ይገባል "

ኢሬቻ - የምስጋና፣ የዕርቅ እና የሰላም ፣የፍቅር፣ የይቅርታ እና የአንድነት በዓልን በማስመልከት የፅዳት ዘመቻ ተካሄደ ኮልፌ ወረዳ 06 ኮሚኒኬሽን መስከረም 24/2017 መስከረም 25 በአዲስ አበባ
+8
ኢሬቻ - የምስጋና፣ የዕርቅ እና የሰላም ፣የፍቅር፣ የይቅርታ እና የአንድነት በዓልን በማስመልከት የፅዳት ዘመቻ ተካሄደ ኮልፌ ወረዳ 06 ኮሚኒኬሽን መስከረም 24/2017 መስከረም 25 በአዲስ አበባ የሚከበረውን የሆራ ፊንፊኔ ኢሬቻ በዓልን በማስመልከት በፅዳት አስተዳደር ጽ/ቤት አስተባባሪነት በኮልፌ ቀራንዬ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 እንግዶች በምንቀበልበት ቦታዎች ላይ ፅዳት ዘመቻ ተካሄዷል። “ኢሬቻ የሠላም ወንድማማችነት እህትማማችነት ተምሳሌት ነው” በሚል መሪ ሀሳብ ዘንድሮ የሚከበረውን ኢሬቻ በማስመልከት የወረዳው ነዋሪዎች፣ወጣቶች እንዲሁም አመራሮች በጋራ በመሆን የፅዳት ዘመቻ አካሂደዋል።