en
Feedback
Kolfe Woreda 06 Communication - ኮልፌ ወረዳ 06 ኮሙኒኬሽን

Kolfe Woreda 06 Communication - ኮልፌ ወረዳ 06 ኮሙኒኬሽን

Open in Telegram

This is a governmental media, News organization ; based in Kolfe Keranio Subcity Woreda 6 Administration.

Show more
206
Subscribers
No data24 hours
-17 days
-230 days
Posts Archive
ያሉ ጥንካሬዎችን በማስቀጥል ውስንነቶችን በማረም መስራት እንደሚገባ ተገለፀ። 11/02/2017 ዓ.ም የኮ/ቀ/ክ/ከተማ ወረዳ 6 ኮሙኒኬሽን የኮ/ቀ/ክ/ከተማ ወረዳ 6 አጠቃላይ አመራር ባለፉት ቀናት
+7
ያሉ ጥንካሬዎችን በማስቀጥል ውስንነቶችን በማረም መስራት እንደሚገባ ተገለፀ። 11/02/2017 ዓ.ም የኮ/ቀ/ክ/ከተማ ወረዳ 6 ኮሙኒኬሽን የኮ/ቀ/ክ/ከተማ ወረዳ 6 አጠቃላይ አመራር ባለፉት ቀናት በፓርቲና በመንግስት የተሰሩ ስራዎችን የወረዳው አስተባባሪ ኮሚቴ በተገኘበት ገመገመ። በውይይቱ በ2ኛ ዙር ስልጠና ከገቡ አመራሮች ዉጪ ባሉ አመራሮች በአስተዳደሩ የተሰሩ ስራዎች ሪፖርት ቀርቦ ሀሳብ የተሰጠበት ሲሆን አመራሩ የተሰጠውን ተልዕኮ ለማሳካት ሙሉ አቅሙን መጠቀሙ ተመላክቷል። በአስተዳደሩ ስልጠና ቆይተው ለመጡ አመራሮች የእንኳን ደህና መጣችሁ መረሐግብርም ተከናውኗል።

የወረዳው ሰላም እና ጸጥታ ጽ/ቤት እና ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በጋራ የ2016 ዓ.ም ሪፖርት፣ የ2017 ዕቅድ አደረጉ፡፡ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ የኮልፌ ወረዳ 06 ኮሙኒኬሽን ጥቅምት 9/2017 ዓ.ም የ
+9
የወረዳው ሰላም እና ጸጥታ ጽ/ቤት እና ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት በጋራ የ2016 ዓ.ም ሪፖርት፣ የ2017 ዕቅድ አደረጉ፡፡ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ የኮልፌ ወረዳ 06 ኮሙኒኬሽን ጥቅምት 9/2017 ዓ.ም የወረዳው ሰላም እና ጸጥታ አስተዳደር እና ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት የ2016 ዓ.ም ሪፖርት፣የ2017 ዕቅድ ከባለ-ድርሻ አካላት ጋር ውይይት አደረጉ የኮ/ቀ/ክ/ከተማ ወርዳ 06 አስተዳደር የሰላምና ፀጥታ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ዘካሪያስ እንደተናገሩት የሰላም ሰራዊቱ ውጤታማ ስራዎች እየሰራ ነው ይህ ዉጤት የተገኘዉ የሰላም ሰራዊት፣ ደንብ ማስከበር፣ አዲስ አበባ ፖሊስ እና ፌደራል ፖሊስ እና አመራሩ በቅንጅት በመስራት ነዉ ብሎዋል፡፡ የኮ/ቀ/ክ/ከተማ ወረዳ 06 ደንብ ማስከበር ፅ/ቤት ሪፖርቱን የቀረበዉ የፅ/ቤቱ ሀላፊ ወ/ሮ ልዩወርቅ ዳኜ በሪፖርታቸዉ እንደገለፁት በ2016 በጀት አመት ከደንብ መተላለፍ ክትትልና ቁጥጥር እርምጃ አወሳሰድ እና ሰርቪላንስ ዘርፍ አንጻር የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን አቅርበዋል። ከነዚህም መካከል ፣ በተፈፀመ የመሬት ወረራ ህገ ወጥ ድርጊት ላይ፣ በተፈፀመ ህገ-ወጥ ግንባታ፣ በተፈፀመ የመሬት ማስፋፋት በተመለከተ ፣በተፈፀመ ህገ-ወጥ የጎዳና ንግድ ላይ እርምጃ መውሰድ መቻሉን ገልፅዋል፡፡ የፅ/ቤቱ ኃላፊዉ አክሎም በደንብ መተላለፍ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች ብሮሸርና በራሪ ጹሁፍ እንዲሁም በመድረክ የህብረተሰብ ክፍል ግንዛቤ መስጠት መቻሉን ገልፆዋል ፡፡ የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 ሰላምና ፀጥታ ፅ/ቤት ለወረዳዉ አስተዳደር ለህዝባዊ ሰላም ሰራዊት የእጅ ባትሪ የተሻለ አፈፃፀም ላላቸው ቀጠናዎች አበርክቷል።

#እኔም_የአካባቢዬ_የሰላም_ዘብ_ነኝ የሰላም ሰራዊት ስምሪት ዛሬም ተጠናክሮ ቀጥሏል! ኮልፌ ወረዳ 06 ኮሚኒኬሽን ጥቅምት 8/2017 የኮልፌ ቀራኒዬ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር የሰላም ሰራዊት
+5
#እኔም_የአካባቢዬ_የሰላም_ዘብ_ነኝ የሰላም ሰራዊት ስምሪት ዛሬም ተጠናክሮ ቀጥሏል! ኮልፌ ወረዳ 06 ኮሚኒኬሽን ጥቅምት 8/2017 የኮልፌ ቀራኒዬ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር የሰላም ሰራዊት ሁልጊዜ የአካባቢያቸውን ሰላም ለመጠበቅ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ በወረዳው በመገኘት በአንድ መአከል ስምሪት በመውሰድ የአካባቢያቸውን ሰላም በማስጠበቅ ላይ ይገኛሉ።

የወረዳ 06 አስተዳደር የ2017 በጀት ዓመት ከተማ አቀፍ የገቢ ንቅናቄ መድረክ አካሄደ፡፡ ኮልፌ ወረዳ 06 ኮሚኒኬሽን ጥቅምት 8/2017 በኮልፌ ቀራንዬ ክ/ከተማ የወረዳ 06 አስተዳደር የ2017
+9
የወረዳ 06 አስተዳደር የ2017 በጀት ዓመት ከተማ አቀፍ የገቢ ንቅናቄ መድረክ አካሄደ፡፡ ኮልፌ ወረዳ 06 ኮሚኒኬሽን ጥቅምት 8/2017 በኮልፌ ቀራንዬ ክ/ከተማ የወረዳ 06 አስተዳደር የ2017 በጀት ዓመት ከተማ አቀፍ የገቢ ንቅናቄ መድረክ በዛሬዉ ዕለት አካሂዷል፡፡በመድረኩም ላይ የግ/ከ/ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሰላም የግብር ንቅናቄን በማስመልከት የተዘጋጀውን ሰነድ አቅርበዋል በዕለቱም የወረዳ 06 ዋና ስራ አስፈጻሚ ተወካይ የሆኑት አቶ ቢኒያም ዜና እንዳሉት መንግስት የተለያዩ የልማት ስራዎችን እያከናዎነ መሆኑን ገልጸው ይኸንን የልማት ስራ አጠናክሮ ለመጓዝና የከተማችንን ብሎም የሀገራችንን ብልጽግና እውን ለማድረግ ገቢን በአግባቡ መሠብሠብ ያስፈልጋል ብለዋል።በከተማዋ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ ከተማዋን የሚመጥን አስደናቂ የልማት ስራዎች እየተከናዎነ መሆኑን የገለጹት አቶ ቢኒያም በቀጣይም ይኸን አጠናክሮ ለመቀጠልና የህብረተሰቡን የመልማት ጥያቄ ለመመለስ የግብር አሰባሰብን ማጠናከር እንደሚገባ ገልጸዋል። የወረዳ 06 የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ ፅ/ቤት ፓለቲካ ዘርፍ ተወካይ አቶ ሚካኤል ፍቅሬ የሀገራችንን ብልፅግና ለማረጋገጥ የገቢ መሰብሰብ ወሳኝ ነው።የከተማችን የአጭር ጊዜ ልውጥ የመጣው በተሰበሰበው ገቢ በመሆኑ አሁንም የዜጎች ፍትሀዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ገቢ መሰብሰብ ላይ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል መሳተፍ ይኖርበታል። ለመንግስት መግባት የሚገባውን ገቢ የሚሸሽጉትን በማጋለጥ ሀገራዊ ሀላፊነታቸውን ዜጎች እንዲወጡም አሳስበዋል።

በወረዳዉ አስተዳደር በKPI (Key Performance Indicator) በእቅድ እና ሪፖርት ዝግጅት ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ። ፨፨፨፨፨፨፨፨ ኮልፌ ወረዳ 6 ኮሙኒኬሽን ጥቅምት 8፣ 2017ዓ.ም በኮ/ቀ/
+4
በወረዳዉ አስተዳደር በKPI (Key Performance Indicator) በእቅድ እና ሪፖርት ዝግጅት ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ። ፨፨፨፨፨፨፨፨ ኮልፌ ወረዳ 6 ኮሙኒኬሽን ጥቅምት 8፣ 2017ዓ.ም በኮ/ቀ/ክ/ከተማ ወረዳ 06 ዋና አስፈጻሚ ጽ/ቤት ለጽህፈት ቤት ሀላፊዎች እና ቡድን መሪዎች KPI (Key Performance Indicator) በእቅድ ዝግጅት እና ሪፖርት ላይ ስልጠና ተሠጥቷል። በእቅድ እና ሪፖርት ስራ ወጥነት እና ተናባቢነት እንዲኖረው በፕላን እና ልማት ኮሚሽን አማካኝነት ወጥ የእቅድ እና አፈጻጸም መለኪያ ስርዓት ተዘርግቷል። ይህንም በተመለከተ የወረዳው ዋና ስራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ፕላን እና ልማት ስራ ሂደት ከክፍለ ከተማ ፕላን እና ልማት ኮሚሽን ጋር በትብብር ስልጠናውን ሰጥቷል። ስልጠናውም ለቀጣይ ወጥ የሆነ እቅድ እና ሪፖርት ስርዓት እንዲኖር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።

"ክብርና ፍቅር ለአረጋውያን" የኮ/ቀ/ክ/ከተማ ወረዳ 06 ኮሙኒኬሽን ጥቅምት 7/2017 ዓ.ም በኮ/ቀ/ክ/ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር በአለም አቀፍ ለ34ኛ በሀገራችን ደግሞ ለ33ኛ ጊዜ የሚከበረዉን
+6
"ክብርና ፍቅር ለአረጋውያን" የኮ/ቀ/ክ/ከተማ ወረዳ 06 ኮሙኒኬሽን ጥቅምት 7/2017 ዓ.ም በኮ/ቀ/ክ/ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር በአለም አቀፍ ለ34ኛ በሀገራችን ደግሞ ለ33ኛ ጊዜ የሚከበረዉን የአረጋዉያን ቀን ምክንያት በማድረግ በወረዳ 06 ሴቶችና ህፃናት ማህበራዊ ጉዳይ ፅ/ቤት አስተባባሪነት አረጋዊያን ማህበር በተገኙበት የአረጋዉያን ቀን ተከብሯል። በፕሮግራሙ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአረጋውያን ማህበር ሰብሳቢ የሆኑት አቶ መኩሪያ ሲሆኑ እንዳሉት የአረጋውያን ቀን አስባችሁ እንዲ ላዘጋጃችሁ አመራሮች እንዲሁም ባለሙያዎች ምስጋና አቀርባለሁ በመቀጠል እኛ አገጋውያን ፍቅር እና እንክብካቤ እንሻለን እንጂ ተረጂ መሆን አንፈልግም አረጋውያን ሲባል ሁሌ የሚደገፍ የሚመስለው አለ እኛ አረጋውያን ደጋፊዎችም ነን ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ የወረዳዉ ሴቶችና ህፃናት ማህበራዊ ጉዳይ ፅ/ቤት ሀላፊ ወ/ሮ ታገሰች ክባሞ አረጋዉያን በሁሉም ዘርፍ ተጠቃሚነታቸዉን በማረጋገጥና ተሳትፏቸዉን በማሳደግ የህይወት ተሞክሯቸዉን መዉሰድ ያስፈልጋል ብለዋል። በዛሬው መርሀግብር ላይ ሰነድ የቀረበ ሲሆን በሰነዱ ዙሪያም ሰፊ ውይይት ተደርጓል። "አረጋውያን ሲባል ሁሌ የሚደገፍ የሚመስለው አለ እኛ አረጋውያን ደጋፊዎችም ነን"ያሉት አረጋውያኑ "ሰነዱ በፅሁፍ የተቀመጠ ብቻ ሳይሆን በተግባር የሚታይ መሆን አለበት" የሚሉና ሌሎች ሊፈቱ የተገቡ ጥያቄዎችን ለፅ/ቤቱ ሀላፊ በማንሳት በቂ ምላሽን አግኝተዋል። በመጨረሻም አረጋውያሁ ሀገራችን ካለችበትባት ፈተና ነፃ ወጥታ፣ለዜጎቿ ተስፋን፣ተድላና ሰላም የሚገኝበት ዘምን እንዲሆን ያላቸውን ምኞት ገልፀዋል።

የባለጉዳይ ቀን በኮልፌ ቀራንዬ ወረዳ 06! የኮልፌ ቀራንዬ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር የባለጉዳይ ቀን ተብለው በተለዩት ቀናቶች አመራሩና ሰራተኛው በቢሮው ተገኝቶ አገልግሎት እንዲሰጥ አቅጣጫ
+8
የባለጉዳይ ቀን በኮልፌ ቀራንዬ ወረዳ 06! የኮልፌ ቀራንዬ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር የባለጉዳይ ቀን ተብለው በተለዩት ቀናቶች አመራሩና ሰራተኛው በቢሮው ተገኝቶ አገልግሎት እንዲሰጥ አቅጣጫ መቀመጡን ተከትሎ በዛሬው እለት ምልከታ ተካሂዷል። ምልከታውን የወረዳው ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ፣ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ጽ/ቤት እና ምክር ቤት በጋራ ያካሄዱ ሲሆን አመራሮችና ባለሙያዎች እሮብና አርብ በፅ/ቤታቸው ተቀምጠው ተገልጋዩን በአካል በማግኘት የመልካም አስተዳደር ችግሮችን የሚፈቱበትና የተሟላ አገልግሎት የሚሰጡበትን ሂደት የሚያጠናክር መሆኑ መመልከት ተችሏል፡፡ ጥቅምት 06/01/2017

የ2016 እቅድ አፈፃፀም እና የ2017 በጀት አመት እቅድ ዙሪያ የተለያዩ ፅ/ቤቶች እና ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይትአካሄዱ፡፡ ፡ ኮልፌ ወረዳ 06 ኮሙኒኬሽን ጥቅምት 05/2017 ዓ.ም የኮ/ቀ/ክ
+9
የ2016 እቅድ አፈፃፀም እና የ2017 በጀት አመት እቅድ ዙሪያ የተለያዩ ፅ/ቤቶች እና ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይትአካሄዱ፡፡ ፡ ኮልፌ ወረዳ 06 ኮሙኒኬሽን ጥቅምት 05/2017 ዓ.ም የኮ/ቀ/ክ/ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር የሴቶች ህፃናት ማ/ ጉዳይ ፅ/ቤት እና ወጣቶችና የስፖርት ፅ/ቤት በጋራ በመሆን የ2016 በጀት አመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እና የ2017 በጀት አመት እቅድ ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሄዷል። በውይይቱ የ2016 በጀት አመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት የቀረበ ሲሆን ፅ/ቤቶቹ ያከናወኑዋቸው ተግባራት እንዲሁም የህብረተሰቡን ጥያቄ ለመፍታት የተኬደበት ርቀት በስፋት ተነስቷል። የወጣቶችና ስፖርት ፅ/ቤት ለወጣቶች የስራ ዕድልና ነፃ የትምህርት ዕድል መፍጠር የቻለበት፣ሴቶች፣ህፃናትና ማህበራዋ ጉዳዮች ፅ/ቤት የሴቶች፣ህፃናትና አረጋውያን ተጠቃሚነት ላይ በተለያዩ ዘርፎች ውጤታማ ስራ ማከናወኑ በሪፖርቱ ከተገለፁት ተጠቃሽ ነው። በ2016 ዓ.ም ውስጥ ያጋጠመው ተግዳሮቶችና ስኬቶች በስፋት ቀርበውም ውይይት ተደርጓል። በውይይቱም ከባለድርሻ አካላትና ከተሳታፊዎች የሴቶችና ወጣቶች ተጠቃሚነት፣የወጣቶች የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ዕድሳትና ጥገና፣የስራ ዕድል ፈጠራ፣የህብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ለመፍታት ሊሰሩ ስለሚገቡ ስራዎችና ለወጣቶች ሊሰጡ ስለሚገባ ስልጠናዎችና ሌሎች ጉዳዮች ላይ በየፅ/ቤቶቹ ክፍተት መኖሩ በውይይቱ ከተሳታፊዎች ተነስቷል። የፅ/ቤቶቹ ሀላፊዎች የተነሱቱን ጉዳዮች በቀጣይ በዕቅድ ሊካተቱ የተገቡ እንዲሁም ሊፈቱ በሚገባቸው ጉዳዮችና አፋጣኝ ምላሽ በሚሹት ዙሪያ መፍትሔ ለመስጠት መግባባት ላይ በመድረስ ውይይቱ ተጠናቋል።

የህዝባዊ የሰላም ሰራዊት እንቅስቃሴ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው ሰላም ለሁሉም፣ ሁሉም ለሰላም! ኮልፌ ወረዳ 06 ኮሚኒኬሽን መስከረም 4/2017 በወረዳው አስተዳደር ክላስተር 4 ቆይታውን ያደረገው የሰ
+4
የህዝባዊ የሰላም ሰራዊት እንቅስቃሴ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው ሰላም ለሁሉም፣ ሁሉም ለሰላም! ኮልፌ ወረዳ 06 ኮሚኒኬሽን መስከረም 4/2017 በወረዳው አስተዳደር ክላስተር 4 ቆይታውን ያደረገው የሰላም ሰራዊት ዋንጫ ወደ ክላስተር 2 አቅንትዋል። በወረዳው አስተዳደር ክላስተር 4 ቆይታውን ያደረገው የሰላም ሰራዊት ዋንጫ ወደ ክላስተር 2 በነበራቸው የሰላም ሰራዊት ስምሪትና አፈፃፀም በክብር ተረክበዋል የወረዳው ሰላምና ፀጥታ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ሳሙኤል ዘካሪያስ እንዳሉት ይህ የዋንጫ ርክክብ የተሻለ መነቃቃትን የፈጠረ ነበር ብለዋል ።

በመንግስትና በፓርቲ ትኩረት ተሰጥቷቸው እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ተገመገመ። ጥቅምት 4/2017ዓ.ም ኮልፌ ወረዳ 06 ኮሙኒኬሽን በኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር በመንግስትና በፓርቲ
+5
በመንግስትና በፓርቲ ትኩረት ተሰጥቷቸው እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ተገመገመ። ጥቅምት 4/2017ዓ.ም ኮልፌ ወረዳ 06 ኮሙኒኬሽን በኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር በመንግስትና በፓርቲ ትኩረት ተሰጥቷቸው እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት የወረዳው አመራሮች በተገኙበት በዛሬው ዕለት ተገምግሟል። በግምገማው ወቅት የውስጠ ፓርቲን ለማጠናከር እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት በቀጣይ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች እና በመንግስት ስራዎች ትኩረት ተሰጥቶ በአስተዳደሩ ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል አንዱ የዜጎችንን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የውጭ ሀገር የስራ ስምሪት በተመለከተ፣ ስራ እድል ፈጠራ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት በዝርዝር ቀርቦ ተገምግሟል። ከዚህም ጋር በተያያዘ የወረዳ 06 ዋ/ስራ አስፈፃሚ ተወካይ የሆኑት አቶ ቢኒያም ዜና በፓርቲ እና በመንግስት የሚከናወኑ ሥራዎች ጥራታቸውን በጠበቀ መልኩ ማከናወን እንደሚገባ በስራ እድል የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በየብሎኩ ደጋፊ አመራሮች አጠናክረው ማስቀጠል እንደሚገባቸውና ስራዎችን አስተሳስሮ መስራት በቀጣይ ቀናት ትኩረት ተሰጥቶባቸው የሚከናወኑ ተግባራት ላይ የስራ ስምሪት ሰጥተዋል።

#ሰንደቅ_ዓላማችን_ለብሄራዊ_አንድነታችን_ለሉዕላዊነታችንና_ለኢትዮጲያ_ከፍታ 17ኛው የሰንደቅ ዓላማ ቀን በኮልፌ ወረዳ 6 አስተዳደር እና ት/ቤቶች በድምቀት ተከበረ። ኮልፌ ወረዳ 6 ኮሙንኬሽን መስከ
+9
#ሰንደቅ_ዓላማችን_ለብሄራዊ_አንድነታችን_ለሉዕላዊነታችንና_ለኢትዮጲያ_ከፍታ 17ኛው የሰንደቅ ዓላማ ቀን በኮልፌ ወረዳ 6 አስተዳደር እና ት/ቤቶች በድምቀት ተከበረ። ኮልፌ ወረዳ 6 ኮሙንኬሽን መስከረም 4/2017ዓ.ም በኮልፌ ቀራንዬ ክ/ከተማ ወረዳ 6 አስተዳደር 17ኛው የሰንደቅ አላማ ቀን ''ሰንደቅ አላማችን ለብሄራዊ አንድነታችን፣ ለሉአላዊነታችንና ለኢትዮጵየ ከፍታ!" በሚል መርህ በወረዳው ምክር ቤት አስተባባሪነት በድምቀት ተከብሯል። በአከባበር ስነ ስርአቱ ላይ ላይ የወረዳው አመራሮች፣ ሰራተኞች፣ የፀጥታ አካላት፣ የወጣት ማህበር አደረጃጀቶች ፣ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች እና የአካባቢው ነዋሪዎች የተገኙ ሲሆን የኮልፌ ቀራንዬ ክ/ከተማ ወረዳ 06 ምክር ቤት ፀሀፊ የተከበሩ አቶ ኢሳያስ ፈቀደ ስለ በአሉ አከባበር በተለይም የሰንደቅ አላማ ምንነት፣ በአሉ ሊከበር ስለሚገባው አስተምህሮት እና አጠቃላይ ስለ ሰንደቅ አላማ ተያያዥ ጉዳዮች ለበአሉ አክባሪዎች ገለፃ አድርገዋል፡፡ የኮልፌ ቀራንዬ ክ/ከተማ ወረዳ 06 የማነብርሀን ት/ት ቤት ለተማሪዎች ግንዛቤ በማስጨበጥ እንዲሁም በጥያቄና መልስ ውድድር ተከብርዋል። እንደ ሀገር ጥቅምት 04፡ 2017ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡30 የተከበረው የአንድ ሀገር ሉዓላዊነትና ብሩህ ተስፋ መገለጫ የሆነው ሰንደቅ አላማ በሀገራችን በየአመቱ ጥቅምት ወር በገባ የመጀመሪያው ሰኞ ይከበራል፡፡

ፕሬስ ሪሊዝ 17ተኛው የሰንደቅ አላማ ቀን "ሰንደቅ አላማችን ለብሔራዊ አንድነታችን፣ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ከፍታ"በሚል መሪ ቃል በነገው እለት ጥቅምት 4-2017 ይከበራል። ኮልፌ ወረዳ 06 ኮ
ፕሬስ ሪሊዝ 17ተኛው የሰንደቅ አላማ ቀን "ሰንደቅ አላማችን ለብሔራዊ አንድነታችን፣ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ከፍታ"በሚል መሪ ቃል በነገው እለት ጥቅምት 4-2017 ይከበራል። ኮልፌ ወረዳ 06 ኮሚኒኬሽን ጥቅምት 3/2017 በኮልፌ ቀራንዬ ክፍለ ከተማ የወረዳ 6 አስተዳደር 17ተኛው የሰንደቅ አላማ ቀን "ሰንደቅ አላማችን ለብሔራዊ አንድነታችን፣ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ከፍታ"በሚል መሪ ቃል በነገው እለት በተለያዩ ዝግጅቶችና በተለያዩ ቦታዎች እንደሚከበር አስታወቀ። የወረዳው ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ኢሳያስ ፈቀደ ሰንደቅ አላማችን በተለያዩ ጊዜያት ፈተናዎች ገጥመውት ጀግኖች አባቶቻችና እናቶቻችን ደማቸው አፍስሰው አጥንታቸው ከስክሰው በክብር ለዛሬው ትውልድ ከነሙሉ ክብሩ አስረክበዋል ብለዋል።የዛሬ ትውልድ በተሰማራንበት የስራ መስክ ሁሉ ጠንክረን በመስራት ሰንደቅ ዓላማችንን ከፍ የማድረግ ሀላፊነት ተጥሎብናል ብለዋል። በነገው እለት ረፋድ 4:30 የወረዳው አመራሮች የፀጥታ አካላት የመንግስት ሰራተኞችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በአስተዳደሩ ቅጥር ግቢ ውስጥ ሰንደቅ አላማ የመስቀል ስነ-ስርዓት ይከወናል ብለዋል።

መደበኛ የመንግስት እና የፓርቲ ተግባራት ተገመገሙ:: ኮልፌ ወረዳ 06 ኮሙኬሽን መስከረም 30/2017 የኮልፌ ቀራንዬ ክፍለ ከተማ የወረዳ 06 አስተዳደር የፓርቲና የመንግስት ወቅታዊና መደበኛ ተግባ
+6
መደበኛ የመንግስት እና የፓርቲ ተግባራት ተገመገሙ:: ኮልፌ ወረዳ 06 ኮሙኬሽን መስከረም 30/2017 የኮልፌ ቀራንዬ ክፍለ ከተማ የወረዳ 06 አስተዳደር የፓርቲና የመንግስት ወቅታዊና መደበኛ ተግባራት የወረዳ ተወካይ አስተባባሪ እና አመራሩ በተገኙበት የስራ ዕድል ፈጠራ፤ የፓርቲ መደበኛ ተግባራት ሌሎች ወቅታዊና መደበኛ የፓርቲና የመንግስት ተግባራት አጀንዳ ተደርገው በስፋት ተገምግሟል። ከመድረኩ አመራሩ በተሻለ አቅምና ተነሳሽነት በጊዜ የለኝም መንፈስ ተግባራትን በፍጥነትና በጥራት በመፈጸም የህብረተሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ በመግለፅ የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫም ተቀምጧል።

የወረዳው ተቋማት በጋራ በመሆን የ2016 በጀት አመት የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርትእና የ2017 በጀት አመት እቅድ ከባለድርሻ ጋር ዉይይት አደረጉ ኮልፌ ወረዳ 06 ኮሙኒኬሽን መስከረም 29/2017ዓ.ም
+9
የወረዳው ተቋማት በጋራ በመሆን የ2016 በጀት አመት የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርትእና የ2017 በጀት አመት እቅድ ከባለድርሻ ጋር ዉይይት አደረጉ ኮልፌ ወረዳ 06 ኮሙኒኬሽን መስከረም 29/2017ዓ.ም የኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ የወረዳ 06 ፋይናንስ ጽ/ቤት፣እና ኮሚኒኬሽን ጽ/ቤት በጋራ በመሆን የ2016 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እና የ2017 በጀት ዓመት እቅድ በማቅረብ ከባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት መድረክ አድርጓል። በሪፖርቱም በ2016 በጀት ዓመት በተሰሩ ስራዎች አጠቃላይ በሁለቱም ተቋማት አፈፃፀም ዉጤት ሲታይ በጣም የተሸለ አፈጻጸምና ያላቸው ሲሆን እንደዚሁም የነበሩ ደካማ ጎኖችን በመቅረፍ ጥንካሬዎችን አጠናክሮ በማስቀጠል በ2017 በጀት ዓመት የታቀዱ ዘርፈ ብዙ ተግባራቶችን ወደ መሬት በማዉረድ እና በመስራት እና ለሚቀርቡ ጥያቄዎችና አገልግሎቶች ፈጣን ምላሽ በመስጠት ወደ ተሻለ አፈፃፀም ማስመዝገብ እንደሚገባ ተገልጿል፡፡ የወረዳዉ የፋይናንስ ጽ/ቤት በ2016 ዓ.ም በዉስጥ ገቢን በማሳደግና የመንግስት በጀት ለታለመለት ዓላማ እንዲዉል በማድረግ ረገድ የፋይናነንስ ግልጸኝነትና ተጠያቂነት ስራዎችን ከማጠናከርም ባለፈ የተጠናከረ የኦዲት አሰራርን በማከናዎን በትኩረት መሰራቱንም ነዉ የገለጹት፡፡ በተመሳሳይም የኮሚኒኬሽን ፅ/ቤት በእቅዳቸው የአገልግሎት አሰጣጡ በመሻሻልና ግልፀኝነት ለመፍጠር እየተሰራ እነደሆነ ተነስቷል። በመጨረሻም በቀረቡት ሪፖርት እና እቅድ ዙሪያ ከቤቱ የተነሱ ጥያቄዎች ከመድረክ መሪዎቹ ሰፊ ማብራሪያና ምላሽ በመስጠት የፋይናንስ ፅ/ቤት በ2016 በጀት አመት ጥሩ አፈፃፀም ላላቸው ቡድን እና ባለሞያዎች እውቅና በመስጠት መድረኩ ተጠናቋል፡፡

የባለ ጉዳይ ቀንን አስመልክቶ በኮልፌ ወረዳ 6 አስተዳደር! ምልከታ ተካሔደ። ኮልፌ ወረዳ 06 የኮሚኒኬሽን መስከረም 29 /2017 ዓ.ም የባለ ጉዳይ ቀንን አስመልክቶ በኮልፌ ወረዳ 6 አስተዳደር!
+8
የባለ ጉዳይ ቀንን አስመልክቶ በኮልፌ ወረዳ 6 አስተዳደር! ምልከታ ተካሔደ። ኮልፌ ወረዳ 06 የኮሚኒኬሽን መስከረም 29 /2017 ዓ.ም የባለ ጉዳይ ቀንን አስመልክቶ በኮልፌ ወረዳ 6 አስተዳደር! ምልከታ ተካሔደ። በከተማ አስተዳደሩ እሮብና አርብ የባለጉዳይ ቀን ሆኖ ከተሰየመ አመታት ተቆጥረዋል:: በዚህ አሰራርም በርካታ ችግሮች እንደተፈቱና በአንፃራዊነት የዜጎች እንግልት እንደቀነሰ ይታወቃል:: በኮ/ቀ/ክ/ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ ና ኮሚቴው አሁንም ይህ ቀን አመራሩና ባለጉዳይ ፊትለፊት በመገናኘት የመልካም አስተዳደር ክፍተቶችን በማረም የተገልጋይ እርካታን ለመፍጠር ያለመ ተመራጭ ቀን ሆኖ ቀጥሏል:: የባለ ጉዳይ ቀንን አስመልክቶ በኮልፌ ወረዳ 6 አስተዳደር! ምልከታ ተካሔደ። ኮልፌ ወረዳ 06 የኮሚኒኬሽን መስከረም 29 /2017 ዓ.ም የባለ ጉዳይ ቀንን አስመልክቶ በኮልፌ ወረዳ 6 አስተዳደር! ምልከታ ተካሔደ። በከተማ አስተዳደሩ እሮብና አርብ የባለጉዳይ ቀን ሆኖ ከተሰየመ አመታት ተቆጥረዋል:: በዚህ አሰራርም በርካታ ችግሮች እንደተፈቱና በአንፃራዊነት የዜጎች እንግልት እንደቀነሰ ይታወቃል:: በኮ/ቀ/ክ/ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ ና ኮሚቴው አሁንም ይህ ቀን አመራሩና ባለጉዳይ ፊትለፊት በመገናኘት የመልካም አስተዳደር ክፍተቶችን በማረም የተገልጋይ እርካታን ለመፍጠር ያለመ ተመራጭ ቀን ሆኖ ቀጥሏል::

በነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ ዋጋ ላይ ማስተካከያ የተደረገበትን ምክንያት በተመለከተ የተሰጠ መግለጫ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከመስከረም 28 ቀን 2017 ዓ.ም ምሽት 12 ሰዓት ጀምሮ የሚተገበ
+1
በነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ ዋጋ ላይ ማስተካከያ የተደረገበትን ምክንያት በተመለከተ የተሰጠ መግለጫ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከመስከረም 28 ቀን 2017 ዓ.ም ምሽት 12 ሰዓት ጀምሮ የሚተገበር በሁሉም የነዳጅ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ማስተካከያ ማድረጉን ገልጿል፡፡ በዚሁ መሰረት ፡- ቤንዚን በሊትር 82 ብር ከ60 ሳንቲም የነበረው 91 ብር ከ14 ሳንቲም ፣ነጭ ናፍጣ በሊትር 83 ከ74 የነበረው 90 ብር ከ28 ሳንቲም፣ ኬሮሲን 83 ብር ከ74 የነበረው 90 ብር ከ28 ሳንቲም፣ ቀላል ጥቁር ናፍጣ 65 ብር ከ48 የነበረው 100 ብር ከ2 ሳንቲም ፣ከባድ ጥቁር ናፍጣ 64 ብር ከ22 ሳንቲም የነበረው 97 ብር ከ67 ሳንቲም፣ የአውሮፕላን ነዳጅ በሊትር 70 ብር ከ 83 ሳንቲም የነበረው 77 ብር ከ 76 ሳንቲም መሆኑን ሚኒስቴሩ ለመገናኛ ብዙሀን በላከው መግለጫ አመልክቷል፡፡

#እንኳን ደስ አለን! #እንኳን ደስ አላችሁ! የኮልፌ ቀራንዬ ክፍለ ከተማ ንግድ ጽ/ቤት ባካሄደው የእውቅና ፕሮግራም የ2016 ዓ.ም እቅድ አፈጻጸም ውጤት የወረዳ 6 ንግድ ፅ/ቤት ከ11ሩም ወረዳ 2
#እንኳን ደስ አለን! #እንኳን ደስ አላችሁ! የኮልፌ ቀራንዬ ክፍለ ከተማ ንግድ ጽ/ቤት ባካሄደው የእውቅና ፕሮግራም የ2016 ዓ.ም እቅድ አፈጻጸም ውጤት የወረዳ 6 ንግድ ፅ/ቤት ከ11ሩም ወረዳ 2ኛ ደረጃ በመውጣት የዋንጫና ሰርተፍኬት ሽልማት አግኝቷል ። በተቋሙ የተሻሉ ዘርፈ ብዙ ስራዎች በተለይ የኑሮ ማረጋጋት እና ህገወጥ ንግድን ከመከላከል አንጻር በበጀት ዓመቱ የተከናወኑበት እንደነበር እና ይህ ውጤት እንዲመጣ አስተዋፅኦ ላበረከቱ የፅ/ቤቱ ሰራተኞች፣ ለወረዳው አመራሮች፣ ለም/ቤት ዘርፍ ቋሚ ኮሚቴ፣ ለንግድ ተቋማት፣ ለፀጥታ አካላት እና ለባለድርሻ አካላት ምስጋና ቀርብዋል።