en
Feedback
ለበጉ ክብር 🙏

ለበጉ ክብር 🙏

Open in Telegram

In this channel every thing is about Jesus.We praise and worship the Lamb with gospel singers ; preach and reveal the mystery of the cross with preachers by the power of the Holy spirit. If you are a singer or a preacher contact @hallelujah2016

Show more
220
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
#ልፀልይላችሁ 🙏 ጌታችን "ሰላሜን እተውላችኋለሁ" እንዳለ ምንም መጣ ምን ተፅዕኖ የማይፈጠርበት የጌታ ሰላም ህይወታችሁን ይቆጣጠረው። 🙏 በተለያየ ሀዘን ውስጥ ላላችሁ : የእግዚአብሔር ጥልቅ ፍቅር ክንፍ ሆኖ ከሁኔታ በላይ ያበራችሁ ዘንድ የፍቅሩ መረዳት በሁለንተናችሁ ይትረፍረፍ። ዓለም ሁሉ በሰማያት ታላቅ አፍቃሪ አባት እንዳለው አውቆ ከሰይጣን ማባበያዎች እንዲሸሽ በመድሃኔአለም ስም ፀለይኩኝ። 🙏 አገልጋዮች በአገልግሎታችሁ የሚድኑ ሰዎች እየተጨመሩ : መንግስቱ እየሰፋ : የእግዚአብሔር ፈቃድ ሁሌ ይፈፀምባችሁ። 🙏 ብትገፉት ብትገፉት አልነቃነቅ ብሎ ያስጨነቃችሁ ሁሉ : አምላክ ትጠነክሩለት ዘንድ ያዘጋጀላችሁ መሆኑን በመረዳት በሃይሉ ችሎት የበረታችሁ ሁኑ ። 🙏 የተቅበዘበዙ በወንጌል እንዲያርፉ እረኛ ወዳጡ ሁሉ የሰማዩ አባት እግዚአብሔር አብ የመከሩን ሰራተኞች አብዝቶ እንዲልክ በኢየሱስ ስም ለመንኩኝ። 🙏 መፅሀፍ ቅዱስ ማንበብ : መፀለይ : ሀጥያትን እምቢ ማለት የማያልፍበት ፋሽን የሚሆንበት የትጋት እና የቅድስና ጉልበት በምድራችን ላይ ይገለጥ። 🙏 በሚያስፈልጋችሁ ጊዜ ሁሉ ሊረዳችሁ ወደ ታመነው ጌታ ፀጋ ዙፋን አብልጣችሁ የምትቀርቡበት : ፀጋና ምህረቱን በሙላት የምትቀበሉበት ዘመን ይብዛላችሁ። 🙏 አይናችሁ በሞተላችሁ ጌታ ላይ ይፍዘዝ : ከኢየሱስ ውጪ ሱስ ሁሉ ከህይወታችሁ ይወገድ ። እርሱን መምሰልን አጥብቆ መለማመድ ይሁንላችሁ። 🙏 ቶሎ ቶሎ የሚከበን ሀጥያት : ሸክምና : ድካም በልጁ ይወገድ ዘንድ ... ቶሎ የምናስወግድበትም ትኩረት እና መታመን እንዲሁም ትጋት እለት እለት በህይወታችን ይብዛ ። 🙏 Repent and Repair ( በድካማችን በንስሃ ወደ እርሱ እየተመለስን በመንፈሱ በሀይል እየተጠገንን : ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ባለን ህብረት የማንደራደርበት ዓመት ይሁንልን። በእኔም በእናንተም ላይ እንዲፈፀም በኢየሱስ ክርስቶስ ስም በእምነት ፀለይኩኝ። @Lebegu @Lebegu @Lebegu

Join for more 😍 @Lebegu                                @Lebegu

Join for more 😍 @Lebegu                                @Lebegu

Join for more 😍 @Lebegu                                @Lebegu

Join for more 😍 @Lebegu @Lebegu የቃል ጊዜ ; ርዕስ : የፀጋ ሙሉ ገፅታ 😍 በወንድም በረከት በላይ

♦️ የእግዚአብሔር ልጀ በብሉይ ኪዳን መለኮታዊው የእግዚአብሔር ልጅ በብሉይ ኪዳን እንዴት እንደተገለጠ የሚዳስስ ጽሑፍ ነው። የአይሁድ ተንታኞችም በዚህ ጉዳይ ላይ የሰጡት ትርጓሜ ተካቷል። share!

ዋስትናዬ ደምህ ነው || 😍 ይትባረክ ታምሩ ተባረኩበት @untothelamb @untothelamb       

#ሰው_መንፈስ_ነው_ብንል_በተዘዋዋሪም_ሆነ_በቀጥታ_የሚፈጠሩትን_የአረዳድ_ቀውሶች_ላመላክታችሁ_እሻለሁ። ሰው መንፈስ ነው ብንል... 1.የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ የመሆናችን እውነታ በፈቃዳችን እንጣረሳለን። “ወይስ #ሥጋችሁ ከእግዚአብሔር የተቀበላችሁት በእናንተ የሚኖረው የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንደ ሆነ አታውቁምን? በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ ስለዚህ በሥጋችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ።” — 1ኛ ቆሮንቶስ 6፥19-20 ወዳጆቼ "ሰው መንፈስ ነው በስጋ ውስጥ ያድራል" ስንል #መንፈስ_ቅዱስም_እኛ_ባደርንበት_ስጋ_ውስጥ_እንጂ_እኛ_ውስጥ_አላደረም እያልን መሆኑን ከላይ በጠቀስኩት የመፅሀፍ ቅዱስ ክፍል በግልፅ መረዳት እንችላለን። እኛነታችን መንፈሳችን ነው ካልን በስጋችን ውስጥ ያደረውን መንፈስቅዱስ በእኔ ውስጥ አድሯል ለማለት ምንም መሰረት የለንም። በተጨማሪም በስጋችሁ የሚያድር እና በእናንተ የሚያድር የሚለውን ሀሳብ ሐዋሪያው ጳውሎስ በተለዋዋጭነት መጠቀሙ "ሰው መንፈስ ነው" ለማለት ምንም ክፍተት የማይተው ነው። ወዳጆቼ በጥንቃቄ እና በማስተዋል ካየነው #መንፈስ_ለመሆን_በሚደረግ_ጥረት_መንፈስቅዱስን_ማጣት ወይም ደግሞ #በእኔ_አላደረም_በስጋዬ_እንጂ ብሎ ማለት ምንኛ የሚያሳዝን ነው !! 2. (ክሪስቶሎጂካል ቀውስ) በክርስቶስ ሰዋዊ ማንነት ላይ እና በዳንንበት ቤዛዊ ክንውን ላይ የማያባራ ጥያቄ የሚጭር ሀሳብ ማስነሳቱ ግልፅ ነው። ለመሆኑ ከመነሻው አምላክ ሰው ሆነ ስንል አምላክ መንፈስ ሆነ ማለታችን ሊሆን ነው። ለስም አጠራሩ ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ(መንፈስ) የነበረ ሲሆን እንደኛው በደምና በስጋ በመካፈሉ ምክንያት ሰው ሆነ እንላለን። “ቃልም ሥጋ ሆነ፤ ....።” — ዮሐንስ 1፥14 ይህም ወንጌል #በሥጋ ከዳዊት ዘር ስለ ተወለደ ስለ ልጁ ነው ብሎ መፅሀፍ እንደሚለን ከሰው በመወለዱ ራሱን የሰው ልጅ ብሎ ደጋግሞ ጠርቷል። ከዚህም ባሻገር ሰው መንፈስ ነው ማለት በሰውነቱ የተደረገው የቤዝዎት ስራ ላይ ያለንን እርግጠኝነት ዝቅ ሊያደርግና ጥያቄ ውስጥ ሊከት ይችላል። የዳንነው በደሙና በስጋው በተደረገ ቤዛነት ነውና ። ዕብራውያን 2 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁴-¹⁵ እንግዲህ ልጆቹ በሥጋና በደም ስለሚካፈሉ፥ እርሱ ደግሞ በሞት ላይ ሥልጣን ያለውን በሞት #እንዲሽር፥ ይኸውም ዲያብሎስ ነው፥ በሕይወታቸውም ሁሉ ስለ ሞት ፍርሃት በባርነት ይታሰሩ #የነበሩትን_ሁሉ ነጻ እንዲያወጣ፥ በሥጋና በደም እንዲሁ ተካፈለ። ¹⁶ የአብርሃምን ዘር ይዞአል እንጂ የያዘው የመላእክትን አይደለም። “በውድ ልጁም፥ እንደ ጸጋው ባለ ጠግነት መጠን፥ #በደሙ የተደረገ ቤዛነታችንን አገኘን እርሱም የበደላችን ስርየት።” — ኤፌሶን 1፥7 “ለኃጢአት ሞተን ለጽድቅ እንድንኖር፥ እርሱ ራሱ #በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ፤ በመገረፉ ቁስል ተፈወሳችሁ።” — 1ኛ ጴጥሮስ 2፥24 ስለዚህ ከላይ እንደጠቀስኩት አምላክ ሰው ሆነ ስንል በነገር ሁሉ እኛን መስሎ (በስጋና በደም ተካፍሎ) ነው። ስጋውን መንፈስ የሆነው ሰዋዊ ማንነቱ እንዲያድርበት ሳይሆን እኛን ሊያድንበት ነው የተካፈለው። 3.የመጨረሻው አስፈሪ ነገር የክርስቶስን ቃል መቃወም ነው። “እኔ ራሴ እንደ ሆንሁ #እጆቼንና #እግሮቼን እዩ፤ በእኔ እንደምታዩት፥ #መንፈስ_ሥጋና_አጥንት_የለውምና እኔን #ዳስሳችሁ እዩ አላቸው።” — ሉቃስ 24፥39 መንፈስ ስጋ እና አጥንት የለውም። አለቀ ። ይሄ የአምላክ ቃል ነው። ማንም መጥቶ Edit ሊያደርገው የማይችል የአምላክ ቃል። እኛ ደሞ ስጋ እና አጥንት አለን። ስለዚህ መንፈስ አይደለንም። ካላስ።ጌታችን ይሄን የተናገረው ከትንሳኤው በኋላ መሆኑ ደግሞ ይበልጥ ይደንቃል። እንኳን አሁን የትንሳኤን አካል ለብሰን እንኳን መንፈስ ነን ማለት አንችልም። ሰው ነን በቃ። ከክርስቶስ ቃል ጋር የማይስማማን አልቀበልም ማንም ይሁን ማን። 1ኛ ጢሞቴዎስ 6 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ³ እነዚህን አስተምርና ምከር። ማንም ልዩ ትምህርት የሚያስተምር ከጌታችንም #ከኢየሱስ #ክርስቶስ #በሆነው #ጤናማ #ቃልና እግዚአብሔርን ለመምሰል በሚስማማ ትምህርት የማይጠጋ ቢሆን፥ ⁴-⁵ በትዕቢት ተነፍቶአል አንዳችም አያውቅም፥ ነገር ግን ምርመራን በቃልም መዋጋትን እንደ በሽተኛ ይናፍቃል፤ ከእነዚህም ቅንዓትና ክርክር ስድብም ክፉ አሳብም እርስ በርስ መናደድም ይወጣሉ፥ አእምሮአቸውም በጠፋባቸው እውነትንም በተቀሙ፥ እግዚአብሔርን መምሰል ማትረፊያ የሚሆን በመሰላቸው ሰዎች ይገኛሉ። እንደነዚህ ካሉት #ራቅ። ታሜ ነኝ። እወዳችኋለሁ ። ተባረኩ @Lebegu @Lebegu

ሰላም የተወደዳችሁ የዚህ channel ቤተሰቦች ትናንት የነበረንን የትምህርት ጊዜ ለዛሬ ያጠፍኩት "ሰው መንፈስ ነው።" የሚለውን ኢ-መፅሀፍቅዱሳዊ የሆነ ትምህርት ስህተትነት ጋር ተያይዞ ጥያቄዎች እንድታነሱ ብጋብዝም አንዳችም ጥያቄ ባለመነሳቱ ተጨማሪ ጊዜ ለመስጠት ነበር። ሆኖም አሁንም ጥያቄዎች አልተነሱም። ስለዚህ አጥጋቢ በሆነ ሁኔታ ሰው መንፈስ ያለመሆኑን መፅሀፍ ቅዱሳዊ እውነት ማረጋገጥ ችለናል ማለት ነው ። ስለዚህም በዚህ ትምህርት ላይ ከተነሱት ነጥቦች በተጨማሪ እኔም የተወሰኑ ሀሳቦች በመጨመር የዚህን ትምህርት ሀሳብ እናጠቃልላለን። ተከታተሉት 😍 @Lebegu @Lebegu

#ሰው_መንፈስ_ነው_ብንል_በተዘዋዋሪም_ሆነ_በቀጥታ_የሚፈጠሩትን_የአረዳድ_ቀውሶች_ላመላክታችሁ_እሻለሁ። ሰው መንፈስ ነው ብንል... 1.የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ የመሆናችን እውነታ በፈቃዳችን እንጣረሳለን። “ወይስ #ሥጋችሁ ከእግዚአብሔር የተቀበላችሁት በእናንተ የሚኖረው የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንደ ሆነ አታውቁምን? በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ ስለዚህ በሥጋችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ።” — 1ኛ ቆሮንቶስ 6፥19-20 ወዳጆቼ "ሰው መንፈስ ነው በስጋ ውስጥ ያድራል" ስንል #መንፈስ_ቅዱስም_እኛ_ባደርንበት_ስጋ_ውስጥ_እንጂ_እኛ_ውስጥ_አላደረም እያልን መሆኑን ከላይ በጠቀስኩት የመፅሀፍ ቅዱስ ክፍል በግልፅ መረዳት እንችላለን። እኛነታችን መንፈሳችን ነው ካልን በስጋችን ውስጥ ያደረውን መንፈስቅዱስ በእኔ ውስጥ አድሯል ለማለት ምንም መሰረት የለንም። በተጨማሪም በስጋችሁ የሚያድር እና በእናንተ የሚያድር የሚለውን ሀሳብ ሐዋሪያው ጳውሎስ በተለዋዋጭነት መጠቀሙ "ሰው መንፈስ ነው" ለማለት ምንም ክፍተት የማይተው ነው። ወዳጆቼ በጥንቃቄ እና በማስተዋል ካየነው #መንፈስ_ለመሆን_በሚደረግ_ጥረት_መንፈስቅዱስን_ማጣት ወይም ደግሞ #በእኔ_አላደረም_በስጋዬ_እንጂ ብሎ ማለት ምንኛ የሚያሳዝን ነው !! 2. (ክሪስቶሎጂካል ቀውስ) በክርስቶስ ሰዋዊ ማንነት ላይ እና በዳንንበት ቤዛዊ ክንውን ላይ የማያባራ ጥያቄ የሚጭር ሀሳብ ማስነሳቱ ግልፅ ነው። ለመሆኑ ከመነሻው አምላክ ሰው ሆነ ስንል አምላክ መንፈስ ሆነ ማለታችን ሊሆን ነው። ለስም አጠራሩ ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ(መንፈስ) የነበረ ሲሆን እንደኛው በደምና በስጋ በመካፈሉ ምክንያት ሰው ሆነ እንላለን። “ቃልም ሥጋ ሆነ፤ ....።” — ዮሐንስ 1፥14 ይህም ወንጌል #በሥጋ ከዳዊት ዘር ስለ ተወለደ ስለ ልጁ ነው ብሎ መፅሀፍ እንደሚለን ከሰው በመወለዱ ራሱን የሰው ልጅ ብሎ ደጋግሞ ጠርቷል። ከዚህም ባሻገር ሰው መንፈስ ነው ማለት በሰውነቱ የተደረገው የቤዝዎት ስራ ላይ ያለንን እርግጠኝነት ዝቅ ሊያደርግና ጥያቄ ውስጥ ሊከት ይችላል። የዳንነው በደሙና በስጋው በተደረገ ቤዛነት ነውና ። ዕብራውያን 2 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁴-¹⁵ እንግዲህ ልጆቹ በሥጋና በደም ስለሚካፈሉ፥ እርሱ ደግሞ በሞት ላይ ሥልጣን ያለውን በሞት #እንዲሽር፥ ይኸውም ዲያብሎስ ነው፥ በሕይወታቸውም ሁሉ ስለ ሞት ፍርሃት በባርነት ይታሰሩ #የነበሩትን_ሁሉ ነጻ እንዲያወጣ፥ በሥጋና በደም እንዲሁ ተካፈለ። ¹⁶ የአብርሃምን ዘር ይዞአል እንጂ የያዘው የመላእክትን አይደለም። “በውድ ልጁም፥ እንደ ጸጋው ባለ ጠግነት መጠን፥ #በደሙ የተደረገ ቤዛነታችንን አገኘን እርሱም የበደላችን ስርየት።” — ኤፌሶን 1፥7 “ለኃጢአት ሞተን ለጽድቅ እንድንኖር፥ እርሱ ራሱ #በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ፤ በመገረፉ ቁስል ተፈወሳችሁ።” — 1ኛ ጴጥሮስ 2፥24 ስለዚህ ከላይ እንደጠቀስኩት አምላክ ሰው ሆነ ስንል በነገር ሁሉ እኛን መስሎ (በስጋና በደም ተካፍሎ) ነው። ስጋውን መንፈስ የሆነው ሰዋዊ ማንነቱ እንዲያድርበት ሳይሆን እኛን ሊያድንበት ነው የተካፈለው። 3.የመጨረሻው አስፈሪ ነገር የክርስቶስን ቃል መቃወም ነው። “እኔ ራሴ እንደ ሆንሁ #እጆቼንና #እግሮቼን እዩ፤ በእኔ እንደምታዩት፥ #መንፈስ_ሥጋና_አጥንት_የለውምና እኔን #ዳስሳችሁ እዩ አላቸው።” — ሉቃስ 24፥39 መንፈስ ስጋ እና አጥንት የለውም። አለቀ ። ይሄ የአምላክ ቃል ነው። ማንም መጥቶ Edit ሊያደርገው የማይችል የአምላክ ቃል። እኛ ደሞ ስጋ እና አጥንት አለን። ስለዚህ መንፈስ አይደለንም። ካላስ።ጌታችን ይሄን የተናገረው ከትንሳኤው በኋላ መሆኑ ደግሞ ይበልጥ ይደንቃል። እንኳን አሁን የትንሳኤን አካል ለብሰን እንኳን መንፈስ ነን ማለት አንችልም። ሰው ነን በቃ። ከክርስቶስ ቃል ጋር የማይስማማን አልቀበልም ማንም ይሁን ማን። 1ኛ ጢሞቴዎስ 6 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ³ እነዚህን አስተምርና ምከር። ማንም ልዩ ትምህርት የሚያስተምር ከጌታችንም #ከኢየሱስ #ክርስቶስ #በሆነው #ጤናማ #ቃልና እግዚአብሔርን ለመምሰል በሚስማማ ትምህርት የማይጠጋ ቢሆን፥ ⁴-⁵ በትዕቢት ተነፍቶአል አንዳችም አያውቅም፥ ነገር ግን ምርመራን በቃልም መዋጋትን እንደ በሽተኛ ይናፍቃል፤ ከእነዚህም ቅንዓትና ክርክር ስድብም ክፉ አሳብም እርስ በርስ መናደድም ይወጣሉ፥ አእምሮአቸውም በጠፋባቸው እውነትንም በተቀሙ፥ እግዚአብሔርን መምሰል ማትረፊያ የሚሆን በመሰላቸው ሰዎች ይገኛሉ። እንደነዚህ ካሉት #ራቅ። ታሜ ነኝ። እወዳችኋለሁ ። ተባረኩ @Lebegu @Lebegu

ተወዳጆች : ሙሉ ፅሁፉን ተከታትላችሁ አሁንም በዚህ ሙሉ ፅሁፍ መልስ ያላገኘ ጥያቄ አለኝ ለምትሉ @Hallelujah2015 ላይ መላክ ትችላላችሁ። ትምህርቱን ስንጀምር እንዳልኩት በመተናነፅ አላማ ጥያቄዎችን በነገው እለት እመልሳለሁ። እንደ አስፈላጊነቱም ጥቂት ተጨማሪ የግል ሀሳቦቼን በኢዮብ ነጥቦች ላይ አክላለሁ። እወዳችኋለሁ ተባረኩልኝ 😍😍

መደምደሚያ.... Continued ለትምህርቱ ዋና ዋና የመከራከሪያ ነጥቦች የሰጠሁት ምላሽ ላላሰመናቸውና “ሰው መንፈስ ነው” የሚለው ትምህርት መጽሃፍ ቅዱሳዊ ነው ለሚሉም የምለው አለኝ። የመጀምሪያው “ሰው መንፈስ ነው” የሚለው ትምህርት የክርስትና መውደቂያና መነሻ ትምህርት አድርገው ከሚያስቡና ከሚያስተምሩ ወገን ከሆናችሁ በእኔ እምነት ወደ ኑፋቄ እየተንደረደራችሁ ነውና መለስ በሉ ማለት እፈልጋለሁ። አንዳንድ ሰዎች ይህን ትምህርት የማይቀበሉ ሰዎችን “ሃይማኖተኛ” ብለው ያንኳስሳሉ፤ “ያለ መንፈስ ቅዱስ ‘ኢየሱስ ጌታ ነው’ ማለት አይቻልም” የሚለውን ጥቅስ “ያለመንፈስ ቅዱስ ‘ሰው መንፈስ ነው’ ማለት አይቻልም” ብለው ሊቀይሩት ነው እንዴ በሚያስብል መልኩ ለትምህርቱ የተጋነነ ቦታ ይሰጣሉ። በእኔ መረዳት ትምህርቱ ከአከራካሪነት ወይም ተራ ስህተት ወደ ኑፋቄነት የሚሻገረው ያኔ ነው። እንዲሁም ትምህርቱን እንደልዩ መገለጥ የሚያቀርቡ ሰዎችም ትምህርቱ ነባርና ተራ እንደሆነ እንዲገነዝቡ እወዳለሁ። ይህ ትምህርት እንደሚባለው መንፈሳዊ ሰዎች ብቻ የሚረዱት ሳይሆን ከክርስትና በእጅጉ ያፈነገጡ እንደ ሳይንቶሎጂ (Scientology)8 እና ሞርሞኒዝም (Mormonism)9 ያሉ ሃይማኖቶችም በስፋት የሚያስተምሩት ነው። በግርጌ ማስታዎሻዎች የተሰጡትን ድረ-ገፆች መመልከት ይቻላል። ይህን የምለው እነዚህ ሃይማኖቶች ስላስተማሩት ትምህርቱ ስህተት ነው ለማለት ሳይሆን፣ ትምህርቱን የሚያስተምሩ ሰዎች እንደልዩ መገለጥ አድረገው ማቅረባቸውና ትምህርቱን የማይቀበሉ ሰዎችን የጌታ መንፈስ እንደጎደላቸው አድርገው ማሰባቸው ትክክል እንዳልሆነ ለትምህርቱ አዳዲስ መምህራንና ደቀመዛሙርት ለማሳየት ነው። እግዚአብሔር ይባርካችሁ። 😍

መደምደሚያ  በመግቢያው እንደገለጽኩት “ሰው መንፈስ ነው” የሚለው ትምህርት እንደኑፋቄ መቆጠር ያለበት ትምህርት ነው ብየ አላስብም። በዚህም ጽሁፍ ላይ ሐዋርያ ብስራት የሰጠውን ትምህርት ወጥነት ባለው መልኩና በቀላሉ ከዩቱዩብ ላይ ስላገኘሁ እንደ መንደርደሪያ ተጠቀምኩ እንጂ ትምህርቱን የሚቀበሉም ይሁኑ የሚያስተምሩ አብዛኞች ሰዎች የሚጠቀሙባቸው የመከራከሪያ ነጥቦች ተመሳሳዮች ናቸው። በዚህ ጽሁፍ ሰው መንፈስ አለመሆኑን ያሳየሁ ሲሆን ይህን ጽሁፍ ለመጻፍ ያነሳሳኝ ዋናው ምክንያት ግን ጃፒ ትምህርቱን ለመደገፍ ያቀረባቸውን ጥቅሶች ለመፍታት የተከተለው አካሄድ ላይ ትልቅ ችግር አለ ብየ ማሰቤ ነው። እንደሚታወቀው ዛሬ “ፕሮቴስታንት”፣ “ጴንጤ ቆስጤ”፣ “ወንጌላዊያን”፣ “ሐዋርያዊ”ና የመሳሰሉት እየተባሉ የሚጠሩት ቤተ እምነቶቻችን መሰረታቸው በ16ኛው ክፍለ ዘመን የተነሳው የተሃድሶ እንቅስቃሴ ነው። የዚህን እንቅስቃሴ አቋሞች የሚያንጸባርቁ “አምስቱ ብቻዎች (five solas)” ተብለው የሚጠሩ መግለጫዎች አሉ። “እምነት ብቻ”፣ “መጽሃፍ ቅዱስ ብቻ”፣ “በክርስቶስ ብቻ”፣ “በጸጋ ብቻ” እና “ክብር ለእግዚአብሔር ብቻ” ተብለው ይታወቃሉ። በእኔ መረዳት “መጽሃፍ ቅዱስ ብቻ” የሚለው አቋም ለሌሎች አቋሞች በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ እንደ መሰረት የሚያገለግል ከኢየሱስ፣ ከሐዋርያቱና ከቀደሙ የእምነት ወንድሞቻችን የተቀበልነው ትልቅና በጥንቃቄ መያዝ ያለብን ውርሳችን ነው። “መጽሃፍ ቅዱስ ብቻ” የሚለው አዳሾቹ በየትኛውም አስተምህሮ ይሁን ልማድ ላይ መጽሃፍ ቅዱስ ብቻ ባለስልጣን መሆኑን ለማሳየት የተጠቀሙበት አገላለጽ ነው። እንደሌሎች ሃይማኖቶች በትውፊትና የገድል መጻህፍት የታሰርን ባንሆንም አስተምህሯችንን ለመደገፍ ሲባል መጽሃፍ ቅዱስን ከልክ ባለፈ የመጠምዘዝ ባህል ከጊዜ ወደጊዜ እያዳበርን መምጥታችን ግልጽ ነው። በዚህም ምክንያት “መጽሃፍ ቅዱስ ብቻ” የሚለው መሰረታችን ከእኛው የተሃድሶ አራማጆች ነን ከምንለው መሸርሸር እየደረሰበት ይገኛል። እኔም አቅሜ በፈቀደ ይህን መሰረታችንን ለማስጠበቅና ከመሸርሸር ለማዳን በዚህ ጽሁፍ ጥሩ ያልሆኑ የመጽሃፍ ቅዱስ አፈታቶች ናቸው ያልኳቸውን ለማሳየት ሞክሪያለሁ። መጽሐፍ ቅዱስን ከአውዱ በተፋታ መልኩ ቃላቶቹ ላይ በመንጠልጠል ሳይሆን መልዕክቱ ላይ በማተኮር፣ የራሳችንን አስተምህሮ እንዲደግፍልን በመጠምዘዝ ሳይሆን በንፁህ አእምሮ ቃሉ ሊል የፈለገውን በማጤን፣ የተወሰኑ “ተወዳጅ” ጥቅሶችን ብቻ በመደጋገም ሳይሆን ከሌሎችም የመጽሃፍ ቅዱስ ክፍሎች ጋር የሚጣጣመውን ትርጓሜ በመመርመር ልናነበው፣ ልንፈታውና ልናስተምረው ይገባል። አንዳንድ ሰዎች “ሰው መንፈስ ነው” የሚለውን ትምህርት ከተቀበሉ በኋላ ተለማምደው የማያውቁትን ዓይነት መንፈሳዊ መነቃቃት ስለሚያገኙ፣ መንፈሳዊ መነቃቃቱና እርሱን ተክትሎ የሚመጡትን አንዳንድ በጎ ለውጦች ምንጫቸው “ሰው መንፈስ ነው” የሚለውን ትምህርት ማመናቸው እንደሆነ አድርገው ይቆጥራሉ። ከዚህም የተነሳ በትምህርቱ ላይ ችግር ቢያዩም ወይም መጽሃፍ ቅዱሳዊ መሰረቱ ደካም መሆኑን የሚያሳዩ ፍንጮች ቢያገኙም ትምህርቱን ለመፈተሽ ይሁን ለመጣል ያመነታሉ ወይም ትምህርቱን ጣሉ ማለት እያገለገሉና እየተገለገሉበት ያለውን ቤተ ክርስቲያን እንዲሁም እየተለማመዱት ያሉትን በጎ ለውጥ አብረው መጣል እንዳለባቸው ያስባሉ። “ሰው መንፈስ ነው” የሚለው ትምህርት ችግሮቹ ከላይ እንዳየነው ሆኖ የሚያስገኘው ግን አንድ ጥቅም ቢኖር፦ ሰው የራሱንና የዙሪያውን ውስንነት ከማየት ለሚመጣ የእምነት እንቅፋት ጆሮውን እንዲደፍን አይኑን እንዲጨፍን ማድረጉ ነው። ይህ ደግሞ ወደ ፅንፍ እስካልተወሰደ ድረስ ለክርስትና አስፈላጊ ነገር ነው። በእኔ እይታ በዚህ አስተምህሮ ውስጥ ያሉ ሰዎች አገኘናቸው የሚሏቸው በጎ ለውጦች ምንጫቸው “ሰው መንፈስ ነው” የሚለው ትምህርት ሳይሆን ይህ በዙሪያ ያለ ሰዋዊና ምድራዊ ተጽዕኖን አልሰማም ብሎ የእግዚአብሔርን ቃል ከራስ ጋር የሚያዋህድ እምነት ነው። ይህን ትምህርት ተቀብለው ላሉ አማኞች የምለው ነገር ቢኖር፦ አሁን ያገኛችሁት መነቃቃት ቢሆን ወይም ፈውስ ወይም የድል ህይዎት፣ ከሰውና ከተፈጥሮ ይልቅ የጌታን ቃል ለማመን ባገኛችሁት አዲስ ድፍረት የመጣ እንጂ “ሰው መንፈስ ነው” የሚለውን ትምህርት ስለተቀበላችሁ አይደለምና ለመጽሃፍ ቅዱስ ታማኝ መሆን አለመሆኑን ለመፈተሽ፣ አለመሆኑንም በተረዳችሁ ጊዜ ትምህርቱን ለመጣል አትፍሩ ነው። እንዲሁም ትምህርቱን መከተል ለማቆም በወሰናችሁ ጊዜ ጥሩ መጽሃፍ ቅዱሳዊ መሰረት ያላቸውን አዳዲስ ልምምዶቻችሁን ይሁን የምትሳተፉባቸውን መንፈሳዊ ህብረቶች አብራችሁ ከትምህርቱ ጋር መጣል እንዳለባችሁ አታስቡ ልል እወዳለሁ። @Lebegu @Lebegu

ከመንፈስ የተወለደ መንፈስ ነው” የሚለውም ሃሳብ “ዳግመኛ የምትወለደው ከመንፈስ ስለሆነና ከመንፈስ የሚወለድ ደግሞ መንፈስ ስለሆነ፣ ዳግመኛ የሚወለደው መንፈስህ ነው” ለማለት ነው እንጂ ሰው መንፈስ ነው ወይም ይሆናል ለማለት አይደለም። ዮሃንስ ከኢየሱስ ትምህርት “ሰው መንፈስ ነው” የሚለውን አግኝቶ ቢሆን ወንጌሉን ሲጽፍ በምዕራፍ አንድ ላይ “ቃልም ስጋ ለበሰ” እንጂ “ቃልም ስጋ ሆነ” ሊል አይገባውም ነበር። “ከስጋ የተወለደ ስጋ ነው” የሚለውም ሃሳብ ከስጋ ሁለተኛ መወለድ አይቻልም ቢቻልም እንኳ ስጋ የሚወልደው መልሶ ስጋን ስለሆነ መንፈሳዊ ለሆነው ዳግመኛ መወለድ የሚፈይደው ነገር እንደሌለ ለማሳየት እንጂ ከመንፈስ የሚወለዱ ሰዎች ስጋነታቸው ቀርቶ መንፈስ ይሆናሉ ማለት እንዳልሆነ ግልጽ ነው። የሰጠሁት ማብራሪያ አሳማኝ ሆኖ ካልተገኘ እስኪ መለስ ብለን ሌላኛውን አማራጭ ፍች ማለትም በዚህ ክፍል ላይ የሰጠውን የጃፒን ፍች መከተል የሚያመጣውን የአፈታት ቀውስ እንመልከት፦ 1. “ከስጋ የተወለደ ስጋ ነው፣ ከመንፈስ የተወለደ መንፈስ ነው” የሚለውን ወንድማችን ጃፒ በሚለው ዓይነት አረዳድ ከተረዳነው ኒቆዲሞስ ስጋ ነበረ ማለት ነው። ለምን? ከመንፈስ ስላልተወለደ፣ የተወለደው ገና ከስጋ ብቻ ስለሆነ። ኒቆዲሞስ ስጋ ከሆነና ኢየሱስ ደግሞ ሰው ሲል መንፈስን ማለቱ ከሆነ “ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር” ማለት አልነበረበትም፣ እንዲሁም ጸሃፊው በቁጥር አንድ ላይ “ኒቆዲሞስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ” ማለት አልነበረበትም። ለምን? ዳግም ያልተወለደ ሰው ከመንፈስ አልተወለደም፣ ከመንፈስ ካልተወለደ ደግሞ ስጋ እንጂ መንፈስ አይደለም፣ መንፈስ ደግሞ ካልሆነ “ሰው” ሊባል አይገባውምና። በተጨማሪም ጃፒ “ሰውየው ዳነም አልዳነም spirit being ነው”7 ካለው ጋር እንዲሁም “ሰው መንፈስ ነው” ነው ለሚለው አስተምህሮ ዋና መከራከሪያ ከሆነው፣ ሰው መንፈስ የሆነው ገና ከፍጥረቱ በእግዚአብሔር መልክ በመፈጠሩ እንጂ ዳግም በመወለዱ አይደለም ከሚለው መከራከሪያ ነጥብ ጋር የሚቃረን ነው። 2. ሰው ዳግም ባይወለድም መንፈስ ነውና “ሰው” ተብሎ ሊጠራ ይችላል የሚል ክርክር ይነሳ ይሆናል። ይህ ግን የ“ሰው መንፈስ ነው” አስተማሪዎች “ከስጋ የተወለደ ስጋ ነው፣ ከመንፈስ የተወለደ መንፈስ ነው” የሚለውን ከሚፈቱበት መንገድ ጋር በቀጥታ የሚጣረስ ነው። በተጨማሪም ሰው ዳግም ሳይወለድም መንፈስ ከሆነ ታዲያ የዳግም መወለድ ጥቅሙ ምንድን ነው ብለን እንድንጠይቅ ያደርገናል፣ ምክንያቱም በጃፒ አፈታት መሰረት ዳግም መወለድ ማለት መንፈስ መሆን ማለት ስለሆነ። 3. ኢይሱስ “ሰው” ሲል የሚያረጀውንና የሚሸብተውን ሰውነቱን የማይጨምር ከሆነ፣ “ሰው ዳግም ካልተወለደ በቀር” በሚለው ቃል ውስጥ ዳግም የሚለውን ቃል ማስገባት አልነበረበትም። ለምን? ዳግም ማለት ሁለተኛ ማለት ነው፣ ኢየሱስ እያለው ያለው መወለድ ደግሞ ሁለተኛ የሆነው የስጋው መወለድ እንደ አንደኛ መወለድ ተቆጥሮ ነው። ሰው ስንል መንፈስ ማለት ከሆነ ግን ስለስጋው መወለድ ልናወራ አንችልም፣ ስለዚህም ኢየሱስ የሚለው መወለድ የመጀመሪያ መወለድ እንጂ ሁለተኛ መወለድ ሊሆን አይችልም። እዚህ ላይ ኢየሱስ ራሱ በዚያው ዮሃንስ ምዕራፍ 3 ላይ “ከመንፈስ” የሚለውን ቃል በተጠቀመበት ቦታ ሁሉ “ዳግም” የሚለውን ቃል እንዳልተጠቀመ ልብ እንበል። በዚህ መሰረት ኢየሱስ “ሰው” የሚለውን ቃል “መንፈስ” ከሚል ቃል ጋር በተለዋዋጭነት እየተጠቀመበት ከነበረና “ከመንፈስ የተወለደ መንፈስ ነው” ለሚለው ጃፒ የሰጠውን ፍች ከተቀበልን ልክ “ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር” እንዳለው መንፈስ አንዴ እንጂ ዳግመኛ ሊወለድ አይችልምና “ዳግሞ” የሚለውን ቃል አውጥቶ  “ሰው ካልተወለደ በቀር” ሊል ይገባው ነበር። በአጭሩ ለማለት የፈለኩት፣ የ“ሰው መንፈስ ነው” አስተማሪዎች ለዮሃንስ 3 የሚሰጡትን አፈታት ከተቀበልን “ሰው ዳግም ካልተወለደ በቀር” የሚለው የኢየሱስ አባባል ራሱ “ሰው መንፈስ ነው” የሚለውን ትምህርት ያልተከተለ ነው ለማለት ነው። @Lebegu @Lebegu

“ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር” የሚለው የኢየሱስ አባባል “ሰው መንፈስ ነው” ብሎ እንደሚያምን ማሳያ ነው የሚለውን ለመመለስ እስኪ አንድ ምሳሌ እንይ። “ማራዶና ኳሷን መታት” ስንል ማራዶና ከእግር ጥፍሩ እስከ ራስ ፀጉሩ ወይም በመላ ሰውነቱ ኳሷን መታት ማለታችን እንዳልሆነ ግልጽ ነው። ወይም ደግሞ ይህንን የነገርነው ሰው ማራዶና ኳሷን በእግሩ ስለመታት “ማራዶና ማለት እግሩ ነው” የሚል ድምዳሜ ላይ አይደርስም። ማራዶና ሲነሳ መቼም አውዱ የእግር ኳስ ጨዋታ መሆኑን የሚያውቅ ሰው፣ ኳሷን በእግሩ አልያም በግንባሩ እንጂ በመላው ሰውነቱ መታት ለማለት እንዳልሆነ ይገባዋል። ልክ እንደዚያው “ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር” ሲል አውዱ የሚገባን እኛ “ሰው [በመንፈስ] ዳግሞኛ ካልተወለደ በቀር” ማለቱ እንጂ የሰው ሁለንተና ዳግመኛ ይወለዳል ወይም ማራዶና ማለት እግሩ ነው እንዳላልነው ሁሉ፣ ሰው መንፈስ ነው ለማለት እንዳልሆነ ይገባናል። ኒቆዲሞስም ኢየሱስ እያወራ ያለው ስለምን እንደሆነ ስላልገባው እንጂ “ሰው መንፈስ ነው” የሚለው ትምህርት ስላልገባው አልነበረም አለመግባባቱ የተፈጠረው። እንዲህ ያለው አለመረዳት በኒቆዲሞስ ላይ ብቻ የተፈጠረ አይደለም። ለምሳሌ ኢየሱስ ከዚያው የኒቆዲሞስ ክፍል ከፍ ብሎ በምዕራፍ 2 ላይ “ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት፥ በሦስት ቀንም አነሣዋለሁ” ሲል የሚያውራው ስለ እራሱ አካል እንደሆነ ያልገባቸው ሰዎች የሰለሞንን ቤተ መቅደስ አፍርሼ እሰራዋለሁ ብሏል ብለው ከሰውታል። የኒቆዲሞስ ችግር “ሰው” የሚለውን ያለመረዳት ሳይሆን “ዳግመኛ መወለድ” የሚለውን ያለመረዳት እንደሆነ የክፍሉ አውድ በግልጽ ያሳየናል። ራሱ ኢየሱስ በዮሃ 21፥18 “እውነት እውነት እልሃለሁ፥ አንተ ጐልማሳ ሳለህ ወገብህን በገዛ ራስህ ታጥቀህ ወደምትወደው ትሄድ ነበር፤ ነገር ግን በሸመገልህ ጊዜ እጆችህን ትዘረጋለህ፥ ሌላውም ያስታጥቅሃል ወደማትወደውም ይወስድሃል አለው።” በማለት ጴጥሮስን አንዴ ጎልማሳ ሌላ ጊዜ ደግሞ ሽማግሌ ብሎ እንደጠራው ማየቱ በኢየሱስ የ“ሰው” ትርጉም ውስጥ ስጋ የለም የሚለውን አባባል የሚያከሽፍ ነው። ኢየሱስ “ሰው” ሲል ፈጽሞ ስጋን የማያስብ ከሆነ “በስጋ ጎልማሳ ሳለህ … በስጋ በሸመገልህ ጊዜ” ሊለው ይገባ ነበር። እንዲሁም ኢየሱስ በሉቃ 24:6-7 “የሰው ልጅ በኃጢአተኞች እጅ አልፎ ሊሰጥና ሊሰቀል በሦስተኛውም ቀን ሊነሣ ግድ ነው” በማለት እንደሚሰቀልና ከሞት እንደሚነሳ፣ በሌሎች ክፍሎችም እንደሚቀበር ተናግሯል። ታዲያ እንደምናውቀው መንፈስ አይሰቀልም፣ አይቀበርም ወይም ከመቃብር አይነሳም። ኢየሱስ “ሰው” ሲል መንፈስን ብቻ ከሆነ የሚያስበው “የሰው ልጅ በኃጢአተኞች እጅ አልፎ ሊሰጥና ስጋው ሊሰቀል በሦስተኛውም ቀን ሊነሣ ግድ ነው”  ሊል ይገባው ነበር።  እዚህ ላይ ማስታዎስ ያለብን ይህ አባባሉ “ሰው ስጋ ነው” የሚለውን ትምህርትም ለማስተላለፍ የታሰበ እንዳልሆነ ነው። ጉልምስናና ሽምግልና ሲነሳ አውዱ የስጋ አውድ እንደሆነ ግልጽ ስለሆነ ኢየሱስ “በስጋህ” የሚለው ቃል መጨመር አያስፈልገውም እንዲሁም “ዳግም ካልተወለደ” ሲል የሚያወራው ስለመንፈስ እንደሆነ ግልጽ ስለሆነ “በመንፈስ” የሚለውን ቃል መጨመር አላስፈለገውም። በእርግጥ ኒቆዲሞስ አውዱ እንዳልገባው ሲያውቅ ኢየሱስ የሚያውራው ስለመንፈስ እንጂ ስለስጋ እንዳልሆነ አስረድቶታል። @Lebegu @Lebegu

ከመንፈስ የተወለደ መንፈስ ነው ከዚህ ሶስተኛው ነጥቡ ጋር አያይዞ ጃፒ የሚያነሳው የመጽሃፍ ቅዱስ ክፍል በዮሃንስ ወንጌል 3፥1-8 ያለውን በኒቆዲሞስንና በኢየሱስ መካከል ያለውን ውይይት ነው። ኢየሱስ “ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር” ማለቱ የሰውን መንፈስነት የሚያሳይ አባባል ነው ባይ ነው። ምክንያቱሳ ካላችሁ፦ ስጋ ዳግመኛ ሊወለድ አይችልም፣ የሚወለደው መንፈስ ነው፣ ስለዚህ ኢየሱስ “ሰው” እና “መንፈስ”ን በተለዋዋጭነት እየተጠቀመ ነው፣ በተለዋዋጭነት ከተጠቀማቸው ደግሞ ሰው ማለት መንፈስ ነው ይሆናል የጃፒ ምላሽ። ከዚያም “ከመንፈስ የተወለደ መንፈስ ነው” ስለሚል በኢየሱስ ያመንን እኛ መንፈስ ነን በማለት ሃሳቡን ያጠናክራል። ኒቆዲሞስም “ሰው ከሸመገለ በኋላ” ሲል ከኢየሱስ በተቃረነ መልኩ “ሰው ብሎ define ያደረገው ሽማግሌ፣ ሽበታም ሰውየ ነው” ይለንና “በኢየሱስ ስም … እንዲህ ዓይነት የኒቆዲሞስን እይታ ከምድሪቱ ላይ አንስቻለሁ” ብሎ ያውጃል። የዚህ ዓይነቱ አፈታት ከላይ ለማሳየት እንደሞከርኩት የተውላጠ ስምን አጠቃቀም ካለመረዳት ወይም “ሰው” የሚለውን ቃል ከመንፈስ ጋር በተለዋዋጭነት መዋሉን “ሰው መንፈስ ለመሆኑ ማሳያ ነው” ከሚለው የተሳሳተ ግንዛቤ የሚነሳ ነው። (በነገራችን ላይ ይህ የዮሃንስ ወንጌል ክፍል ሰውና መንፈስን በተለዋዋጭነት እየተጠቀመ አይደለም፣ እንዴት እንዳልሆነም ወደኋላ አሳያለሁ።)  “ሰው” የሚለው ቃል ከመንፈስ ጋር ብቻ ሳይሆን ከስጋም ጋር በተለዋዋጭነት በብዙ የመጽሃፍ ቅዱስ ክፍሎች ላይ ዉሏል፣ ነገር ግን እነዚህኛዎቹ ክፍሎች “ሰው ስጋ ነው” ሊያስብሉን እንደማይችሉ ሁሉ እነዚያኛዎቹ ክፍሎች ደግሞ “ሰው መንፈስ ነው” አያስብሉንም። ለምሳሌ 1ቆሮ 2፥11 “በእርሱ ውስጥ ካለው ከሰው መንፈስ በቀር ለሰው ያለውን የሚያውቅ ሰው ማን ነው?” በማለት  ከመንፈሱ-ውጭ-ያለውን-የሰው-ክፍል ራሱን አስችሎ “ሰው” በማለቱ መንፈስ ለሰው ተጨማሪ ነገር እንጂ ሰውን ሰው የሚያስብለው መንፈሱ አይደለም ልንል ነው ማለት። ይህ ከሰው ቋንቋ ውስንነት የመጣ አገላለጽ ነው እንጂ “ሰው” የሚለውን ጽንሰ ሃሳብ ከመንፈሱ ነጥሎ እያየው አይደለም። እንደዛ ከሆነ “በልሳን ብጸልይ መንፈሴ ይጸልያል አእምሮዬ ግን ያለ ፍሬ ነው። እንግዲህ ምንድር ነው? በመንፈስ እጸልያለሁ በአእምሮም ደግሞ እጸልያለሁ፤ በመንፈስ እዘምራለሁ በአእምሮም ደግሞ እዘምራለሁ።” የሚለውን ጥቅስ ሰው ከመንፈሱም ከአእምሮውም ውጭ የሆነ ሌላ “ሰው” የሚባል ክፍል አለው ልንል ነው ማለት ነው። ነገሩን ደግሞ የበለጠ ግልጽ ለማድረግ 1ተሰ 5፥ 23ን ልንጠቅስ እንችላለን፦ “መንፈሳችሁም ነፍሳችሁም ሥጋችሁም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመጣ ጊዜ ያለ ነቀፋ ፈጽመው ይጠበቁ” ከዚህ ጥቅስ ተነስተን “[የእናንተ] መንፈስ፣ [የእናንተ] ነፍስ፣ [የእናንተ] ስጋ” ስላለ፣ “እናንተ” እያለ የሚጠራው ከመንፈስ፣ ከነፍስና ከስጋ ውጭ የሆነ ክፍል አለ ልንል ነው ማለት ነው። ምክንያቱም እንደ ጃፒ አፈታት ከሆነና ሰው መንፈስ ከሆነ “እናንተም፣ ነፍሳችሁም፣ ስጋችሁም” ሊባል ይገባው ነበር፣ እንደ ጃፒ አፈታት ከሆነና ሰው ደግሞ ነፍስ ከሆነ “መንፈሳችሁም፣ እናንተም፣ ስጋችሁም” ሊባል ይገባው ነበር፣ እንዲሁም እንደ ጃፒ አፈታት ከሆነና ሰው ስጋ ከሆነ ደግሞ “መንፈሳችሁም፣ ነፍሳችሁም፣ እናንተም” ሊባል ይገባው ነበርና ነው። ጳውሎስ ግን ማለት የፈለገው “[እናንተን ይቀድስ፣ እናንተን ስልም መንፈሳችሁን፣ ነፍሳችሁንና ስጋችሁን ማለቴ ነው]” ነው። @Lebegu @Lebegu

እስኪ የዚህ ዓይነት አጠቃቀም በዘፍጥረት ዘገባ ውስጥ እንመልከት። ዘፍ 2፥22 “ከአዳም የወሰዳትን አጥንት ሴት አድርጎ ሠራት” በማለት ሴት የተገኘችው ከአዳም አጥንት እንደሆነ ይነግረንና መልሶ ግን በቁጥር 23 ላይ “እርስዋ ከወንድ ተገኝታለችና ሴት ትባል” በማለት ሴት ከወንድ አጥንት ሳይሆን ከወንድ ተገኝታለች ይለናል። ይህን ስናይ የወንድን አጥንት በ“ወንድ” ስለተካው ለመጽሃፍ ቅዱስ ወይም ለእግዚአብሔር ወንድ ማለት አጥንት ነው አንልም። “ከወንድ” ሲል አጥንትን ለይቶ ወንድ እያለው እንዳልሆነ ግልጽ ነው፣ “ከወንድ” ሲል “ከወንድ አጥንት” እንደሆነ ከአውዱ እንረዳለን። ወደ ጃፒ አፈታት ስንመለስ የእሱ መከራከሪያ “ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህ” የሚለው አነጋገር ወይ “ከእርሱ በበላህ ቀን መንፈስህ ሞትን ይሞታል” ማለት ነበረበት ወይ መጽሃፍ ቅዱስ “አንተ” እያለ የሚጠራው መንፈስን ነው ባይ ነው። እኔ ደግሞ ከላይ በሰጠሁት ማብራሪያ መሰረት ይህ አፈታት አያስኬድም ባይ ነኝ። በዚህ አካሄድ ከሆነ ጃፒ “አዳም በስጋው ሞቷል እንዴ?” የሚል መከራከሪያ እንዳቀረበ ሌላም ሰው በቀላሉ “አዳም በመንፈሱ በልቷል እንዴ?” የሚል መከራከሪያ ሊያነሳና “[አንተ] በበላህ” በሚለው ንግግር ውስጥ ያለው “አንተ” የሚያመለክተው ስጋውን ስለሆነ እግዚአብሔር “አንተ” ወይም “ሰው” የሚለው ስጋን ነው ሊል ይችላል። እንዲህ ያለ የጸጉር ስንጠቃ አፈታት እንደማያስኬድ እስኪ ጃፒ በሚለው መንገድ ተጨማሪ የዘፍጥረት ምዕራፍ 2 ክፍሎችን እየተረጎምን እንያቸው፦ ዘፍ 2፥21 “እግዚአብሔር አምላክም በአዳም ከባድ እንቅልፍን ጣለበት፥ አንቀላፋም፤ ከጎኑም አንዲት አጥንትን ወስዶ ስፍራውን በሥጋ ዘጋው።” እዚህ ላይ “መንፈስ ያንቀላፋል እንዴ?” ብለን ብንጠይቅ “አይ የለም የሚያንቀላፋው ስጋ ነው” የሚል መልስ እናገኛለን። ከዚያም በመነሳት “[እርሱ] አንቀላፋም” ስለሚል እግዚአብሔር “እርሱ” የሚለው ስጋን ነው ስለዚህም “ሰው” የሚለው ስጋን ነው ልንል እንችላለን። ዘፍ 2፥22 “እግዚአብሔር አምላክም ከአዳም የወሰዳትን አጥንት ሴት አድርጎ ሠራት” በተመሳሳይም “መንፈስ አጥንት አለው እንዴ?” በማለት እግዚአብሔር “አዳም” እያለ የሚጠራው ስጋን ነው ልንል እንችላለን፣ ስጋ እንጂ መንፈስ አጥንት የለውምና። ዘፍ 2፥25 “አዳምና ሚስቱ ሁለቱም ዕራቁታቸውን ነበሩ፥ አይተፋፈሩም ነበር።” እንዲሁም “መንፈስ ራቁቱን ነው ይባላል እንዴ?” በማለት “[እነርሱ] ዕራቁታቸውን ነበሩ” ስለሚል፣ እግዚአብሔር “አዳምና ሔዋን” ወይም “እነርሱ” ወይም “ሰው” እያለ የሚጠራው ስጋን ነው ልንል እንችላለን። የዚህ ዓይነት በመቶዎችና በሽዎች  የሚቆጠሩ ጥቅሶችን እያወጣን ልናይ እንችላለን፣ ቁም ነገሩ ግን – ተውላጠ ስሞች ከሆነ የሰው ክፍል ጋር በተለዋዋጭነት ስለዋሉ፣ ያ የሰው ክፍል ብቻ ነው “ሰው” ማለት አያስኬድም የሚለው እውነታ ነው። @Lebegu @Lebegu

3. የተውላጠ ስሞች አጠቃቀም  በዚህ የመካራከሪያ ነጥቡ ጃፒ የሚለው ይህን ነው፦ እግዚአብሔር ወይም መጽሃፍ ቅዱስ መንፈስንና ሰውን በተለዋዋጭነት (interchangeably) ስለሚጠቀምባቸው እግዚአብሔር ወይም መጽሃፍ ቅዱስ “ሰው” የሚለው መንፈስን ነው። ወይም መጽሃፍ ቅዱስ መንፈስንና ሰው-አመልካች-ተውላጠ-ስሞችን (እኔ፣ አንተ፣ አንቺ፣ እሷ፣ እሱ፣ እናንተ) በተለዋዋጭነት ስለሚጠቀምባቸው መጽሃፍ ቅዱስ “ሰው” ሲል መንፈስን ማለቱ ነው። ለዚህ መከራከሪያ መልስ ለመስጠት በመቶዎችችና በሺዎች የሚቆጠሩ ሰው-አመልካች-ተውላጠ-ስሞችን ከሰው መንፈስ ጋር ሳይሆን ከሰው ስጋ ጋር በተለዋዋጭነት የሚጠቀሙ ጥቅሶችን ማቅረብ ይቻላል። በሁለተኛው ነጥብ በአጭሩ እንዳብራራሁት አማርኛው “ስጋ ለባሽ” ወይም “ስጋ የለበሰ” እያለ የተርጎማቸው በዕብራይስጡና በግሪኩ “ስጋ” ተብለው የተቀመጡ ሲሆን እነዚህንም ጥቅሶች ወስድን እግዚአብሔር “ሰው” እና “ስጋ”ን በተለዋዋጭነት ስለተጠቀመባቸው ሰው ስጋ ብቻ ነው ልንል እንችላለን። በነገራችን ላይ ይህንኑ ዓይነት መከራከሪያ “ሰው ስጋ ብቻ ነው” ለማለት የሚጠቀሙ ብዙ ሃይማኖቶችና አስተማሪዎች አሉ። ጃፒ የጠቀሳቸውን ጥቅሶች ከማየታችን በፊት እስኪ ስለ ተውላጠ ስም አጠቃቀም ጥቂት ማብራሪያ ከምሳሌ ጋር ልስጥ። “እሱ እሷን በቦክስ ሲመታት ደም በደም ሆነች” ብሎ አንድ ሰው ስለ አንድ አጋጣሚ ነገረን እንበል። ያንኑ ሁኔታ ያየ ሌላ ሰው “እሱ አፍንጫዋን በቦክስ ሲመታት አፍንጫዋ ደም በደም ሆነ” ብሎ ሲናገር ደግሞ ሰማን እንበል። ሁለተኛው አገላለጽ ከመጀመሪያ የሚለየው አፍንጫ የሚል ቃል መጨመሩ ሲሆን የሚያስተላልፉት ሃሳብ ግን አንድ አይነት ነው። የመጀመሪያው ተናጋሪ “አፍንጫዋን” የሚለውን ቃል “እሷ” ብሎ ስለተካውና አፍንጫዋንና እሷን በተለዋዋጭነት ስለተጠቀመ እሷ ማለት አፍንጫዋ ናት አንልም። ወይም አንድ ሰው መጀመሪያ “አመመኝ” ብሎን ቀጥሎ “ራሴን አመመኝ” ቢለን “የእኔን ራስ” እና “እኔን” የሚሉትን ቃላት በተለዋዋጭነት ስለተጠቀመ ሰውየው ራስ ነው አንልም። እንዲህ ዓይነት የተውላጠ ስም አጠቃቀም ያለምንም ችግር በስፋት በዕለት-ተዕለት ኑሯችን እንጠቀማለን፣ መጽሃፍ ቅዱስም ይጠቀማል። የወሬው አውድ ስለሚገባን “እሷ” የሚለው የሚያመለክተው “አፍንጫዋን” እንደሆነ እንገነዘባለን እንጂ “እሷ ማለት አፍንጫዋ ናት” አንልም፣ እንዲሁም “እኔን” የሚለውን ቃል “ራሴን” ከሚለው ጋር በተለዋዋጭነት ስለተጠቀምንበት ሰውየው “እኔ” ብሎ የሚጠራው ወይም “ሰው” ብሎ የሚጠራው ራስን (head) ነው አንልም። ይህ እንግዲህ ተውላጠ ስም እንደ አውዱ አንዳንዴ ሙሉ ሰውን ሲያመለክት ሌላ ጊዜ ደግሞ የሰውን አንድ ነገሩን ወይም ክፍሉን ያመለክታል ለማለት ነው።

ሰላም ተወዳጆች : የጌታ ፀጋ እና ሰላም ይብዛላችሁ። "ሰው መንፈስ ነውን?" በሚል የጀመርነውን ትምህርት ክፍል 3 ዛሬ እናያለን። የተሳሳቱ የተውላጠ ስም አጠቃቀሞችን "ሰው መንፈስ ነው።" ለሚለው ትምህርት ከመጠቀማቸው ጋር የተያያዘውን ሀሳብ ከመፅሀፍ ቅዱስ አንፃር በዝርዝር እንመለከታለን። ተከታተሉት 😍😍😍😍 @Lebegu @Lebegu