ለበጉ ክብር 🙏
Open in Telegram
In this channel every thing is about Jesus.We praise and worship the Lamb with gospel singers ; preach and reveal the mystery of the cross with preachers by the power of the Holy spirit. If you are a singer or a preacher contact @hallelujah2016
Show more220
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
220
ቀኑ እጅግ ቢከፋ የሚወዱን ፍቅራቸው ቢያልቅም
የዚህ አለም ኑሮ ቢያስመርረን ብንጨነቅም
ብርሃንን ለብሰን ሰማያትን እንወርሳለን
ሁሉን እናልፍና ከጌታ ጋር እንነግሳለን
220
ትንቢተ_ዮናስ : ክፍል 2 : የእግዚአብሔር ምህረት 😍
ምዕራፍ ፩
በህዝብዋ መካከል አመፅ ስለፀና
በጣም ተቆጥቼ አዝኛለሁና
ይህን ለነነዌ ንገራት በአዋጅ
አለና ለዮናስ ለእሚታይ ልጅ
እግዚአብሔር አዘዘው እንዲሄድ በቶሎ
ዮናስ እምቢተኛው አሰበ ኮብልሎ
ከአምላክ ተደብቆ አምልጦ ሊጠፋ
ወደ ተርሴስ ሊጓዝ ሄደ ወደ ያፋ
ዋጋ ከፈለና በመርከብ ተሳፍሮ
እያጉረመረመ ባህሩን ተሻግሮ
ዮናስ ተደብቆ ሲሄድ በግስገሳ
ከእግዚአብሔር ተልኮ ማዕበል ተነሳ
ታላቅ ሞገድ ሆነ ባህሩም ተቆጣ
መርከበኞች ፈሩ ትልቅ ሽብር ወጣ
መርከቡ እንዲቀለው እናድርግ እያሉ
አንስተው ብዙ እቃ ወደ ባህር ጣሉ
ባህሩ ባሰቡት በጣም ተናወጠ
መርከቡ መሰለ የተገለበጠ
ሠው ሁሉ ተነሳ ፀሎት ለማድረስ
ይህ ሁሉ ሲሆን ተኝቷል ዮናስ
ወደ ዮናስ ሄዶ የመርከቡ አለቃ
ቀሰቀሰውና ከእንቅልፍ እንዲነቃ
እግዜር እንዲያድነን ከዚ ክፉ ጥፋት
ተነስ ፀልይ አለው ይብቃ ማንቀላፋት
በመርከብ ውስጥ ያሉ ሰዎች ተሰብስበው
ተመካከሩና በነገሩ አስበው
አለ ኃጢአት ሰርቶ ከእኛ ጋር የመጣ
ለይተን ለማወቅ እንጣጣል እጣ
ካለዚያ አንድንም ስለተባባሉ
ተሰበሰቡና እጣ ቢጣጣሉ
እውነትም እንዳሉት አጥፊው ሰው ታወቀ
በእምቢተኛው ነብይ ዮናስ ላይ ወደቀ
ዮናስ ተረዳና እጁ እንደተያዘ
ያጠፋውን ጥፋት ገልጦ ተናዘዘ
ምነው ብትመጣ ተጣልተህ ከጌታ
እየው መርከባችን እንደሚንገላታ
ቁጣው እንዲታገስ ለማግኘት ፀጥታ
በል አንተው ፍረደን ምን ይበጃል ቢሉ
ዮናስ መለሰና እንዲህ ያለ ሁሉ
ስለምን ይጠፋል ከእኔ የተነሳ
ወደ ባህር ጣሉኝ አለብኝ አበሳ
ተመልከቱ እነሆ ስራውን አወቀ
ጥፋቱን ገለጠ ይኸው መች ደበቀ
እርሱ ከፈረደ መልሶ በራሱ
ምን እናድርግ ብለው ሊጥሉት ተነሱ
ከደሙ አንፃን ሲሉ ለእግዜር አመልክተው
ወደ ባህር ጣሉት ዮናስን አውጥተው
በዮናስ ላይ ኖሮ የመጣው ይህ መአት
ባህሩ ፀጥ አለ ልክ በዚያው ሰአት።
ምዕራፍ፪
ዮናስን እንዲውጥ ህይወቱን ሳይጎዳ
አንድ ትልቅ አሳ እግዜሐር አሰናዳ
ዮናስም ተውጦ በእግዚአብሔር ፈቃድ
3ቀን 3ለሊት ሲያድር በአሳ ሆድ
ተቀይመህ ኖሮ ከላይ ብትቆጣ
ይህን ያህል መአት በራሴ ላይ መጣ
የባህሩ ሞገድ እኔን አዋከበኝ
ውሃና ጨለማ ሲኦልም ከበበኝ
እያለ በአሳ ሆድ ዮናስ ሲቀመጥ
አምላኩን ለመነው በመለማመጥ
የታዛዥነትን ፀባይ እያሳየ
አዝኖ ተፀፅቶ ከልቡ ፀለየ
ምን ጊዜም ቢቆጣ ነውና መሃሪ
ፊቱን መልሶለት ታረቀው ፈጣሪ
አሳውም ዮናስን ውጦ ሳያስቀረው
ከባህር ተፋና ከየብስ ወረወረው
ምዕራፍ ፫
ይህን የእኔን ቃል ስማና በቶሎ
ሄደህ ለነነዌ እንድትነግራት ብሎ
ደገመና እግዚአብሔር ዮናስን አዘዘ
ነነዌ ሊገባ ዮናስም ተጓዘ
ድምፁን ከፍ አድርጎ ነብዩ ዮናስ
ከዛሬ ጀምሮ አርባ ቀን ድረስ
ነነዌ ጠፊ ነች ከስር ተገልብጣ
አለና ነገረ የእግዚአብሔርን ቁጣ
ሳያንገራግሩ ሁሉም ስላመኑ
የነነዌ ሰዎች ተጨንቀው አዘኑ
ከትልቅ ጀምሮ ህፃኑ ድረስ
ህይወቱ የቆመች በስጋ በነፍስ
ሰው ሆነ እንስሳ ይቀበል ንስሃ
ፍጡር ሁሉ ይፁም ይለይ ከእህል ውሃ
ሁሉም ከልብ አዝኖ ማቅ እየለበሰ
ከክፉ ወደ ደግ እየተመለሰ
መቼም ወሰን የለው እግዚአብሔር ምህረቱ
ይፀልይ አለና ይለምን በብርቱ
ንጉሱ አሳወጀ ከነመኳንንቱ
የነነዌ ሰዎች በእውነት ልቦና
መፀፀታቸውን እግዚአብሔር አየና
ፍጡር ቢለምነው እምባ እያፈሰሰ
ምህረቱን አውርዶ መአቱን መለሰ።
ምዕራፍ ፬
የተናገረው ቃል ስላልተፈፀመ
ዮናስ ተቆጥቶ እያጉረመረመ
እንደዚህ እያለ ፀለየ ወደ አምላክ
እኔን መጀመሪያ ነነዌ ለመላክ
አስበህ ብታዘኝ ይህንኑ አውቄ
ወደ ተርሴስ ልሄድ ጠፋው ተደብቄ
ምህረትህ የበዛ መሃሪና ታጋሽ
በደል የምትረሳ ከቁጣ ተመላሽ
የቁጣህን ያህል ምህረትህ የጠና
መሆንህን ከጥንት እኔ አውቃለውና
እኔን ግን ግደለኝ ልሙት ልቀበር
ሀሰት ተናግሬ የማይሆን ነገር
አልፈልግምና ቆሜ ለመኖር
ከከተማ ወጥቶ በስተ ምስራቅ በኩል
ወደ ዳር ሆኖ ነነዌን ሲያስተውል
ምን እንደሚያገኛት ለማየት ዮናስ
ሠርቶ ተቀመጠ አንዲት ትንሽ ዳስ
እግዜር በጥበቡ አንዲት ቅል አብቅሎ
ቅሉም አደገና ከፍ ከፍ ብሎ
የዮናስ ራሱ እንዲያገኝ ጥላ
ለፀሐዮ ንዳድ ሆነለት ከለላ
በዚህ በቀል ነገር ዮናስን ደስ አለው
እንዲህ ቶሎ ደርሶ ስለገላገለው
እግዜሐር በማግስቱ ጠዋት በማለዳ
ቅል የሚበላ ትል ፈጠረ አሰናዳ
ትሉ ቅሉን በልቶ በፍጥነት ደረቀ
ፀሐይ ወጣችና ጊዜው በጣም ሞቀ
እግዜሩ አዘዘና ትልቅ ንፋስ መጣ
የሚከለልበት መጠጊያ ስላጣ
ቅሉ ደረቀና ንዳድ ቢያቃጥለው
ዮናስ ተበሳጭቶ ለአምላክ እንዲ አለው
እንደዚስ ሆኜ ቆሜ ከመኖር
እባክህ ግደለኝ ልሙት ልቀበር
ደረቀብኝ ብለህ ይህን ቅል በማጣት
እውን ይገባል ወይ የአንተ አሁን መቆጣት
ብሎ እግዜሐር ቢጠይቅ መለሰ ዮናስ
በንዴት ብዛት እስክሞት ድረስ
አዎ ይገባኛል መናደድ መጤስ
እግዜርም መለሰ ለምን ጠፋ ስትል
ይህ ያለፋህበት ያልደከምክበት ቅል
አንተ ስትናደድ ፈጥሬያት እኔማ
ሳጠፋ ሳፈርሳት ነነዌን ከተማ
120 ሺህ ነው የህዝቧም ብዛት
ለምን ትቆጣለህ እኔ ባዝንላት
ብሎ በምሳሌ ሲያስተምር ይቅርታ
ለዮናስ ነገረው የምህረቱ ጌታ
ለእግዚአብሔር ቸርነት ምስጋና ይድረስ
በዚህ ተፈፀመ ትንቢተ ዮናስ!!!!
#እንደተባረካችሁ_ቆዩ
#ብዕረኛዋ M.T
@Lebegu
@Lebegu
@Lebegu 👈👈join
220
#ልባቸው_ተነካ
ወንጌል የሰዎችን አዕምሮ ማሳበጫ ወይንም መነቋቆሪያ ሳይሆን የሰዎችን ልብ የምንነካበት የእግዚአብሔር ኃይል ነው። ልብ የማይነካበት ወንጌል እሱ ወንጌል ሊሆን አይችልም።ሰው ሰራሽ ወንጌል እንጂ.... የሰው ልጅ ሰው በሰራው ወንጌል ልቡ ሊነካ አይችልም አዕምሮው ግን በጥቅስ ሊያብጥ ይችላል።
የሰዎች ወንጌል የሰዎች ብልሃትና ፈጠራ ነው ምንም እንኳን መግቢያና መውጫ ጥቅስ ቢኖረውም ሰዎችን ወደ ክርስቶስ የሚያሳድግ ሊሆን አይችልም። መንፈሳዊ ዕድገት በተብላላ አስተሳሰብ ሳይሆን ከዋናው ማዕድ በመቋደስ ነውና።
(1ኛ ቆሮ 2:13)
ወንጌል የሰዎች ልብ የሚነካና በመንካቱም የሰዎችን መንገድ የሚቀይር ሰዎች ምን እናድርግ እስኪሉ የሚያደርስ የሰዎችን ጠማማነት የሚያቀና የእግዚአብሔር እውነት ነው።
ወንጌል ነው ብለህ ተምረህ ምን ላድርግ ወደሚል ውሳኔ ላይ እስካላመጣህ ድረስ ወንጌል አይደለም። እሱ ሰዎች ክሽን አድርገው የሰሩት የአዕምሮ ትምህርት ነው። እውነተኛ ወንጌል በመጀመሪያ ልብ ይነካል ሰዎችን ወደ ንስሃ ይመራል። እንግዲህ በኃዋሪያቱ የተሰበከው ክርሰቶስ ይህ ነው።
(ሐዋ 2:37-38)
#ተባረኩልኝ
✍ M.T
@Lebegu
@Lebegu
220
Dear Customer, you have received Unlimited eternal life from Jesus Christ which doesn't expire. Now enjoy this unlimited package. Buy additional iternal life for your besties by preaching what you gained. Let visit our channel
@lebegu
@lebegu
220
ለመዳን፣ የእኔ ድርሻ ምንድን ነው?
የሰው ዘር ከውድቀት በኋላ በእግዚአብሔር ፊት ጻድቅ ሆኖ መቅረብ ባለመቻሉ፣ ክርስቶስ ለዚህ ተስፋ ቢስ
የሰው ዘር ወኪል በመሆንና በመታዘዝ ጻድቅ ሕይወቱን በሰው ልጅ ፈንታ ለእግዚአብሔር አቀረበ፡፡ የሰው ልጅ
ሊሸከማት ያልቻለውን የኃጢአት ቅጣት በእርሱ ፈንታ በመሸከም የኃጢአት ስርየትን አስገኘለት፡፡ ከዚህም
የተነሳ ሰው በእግዚአብሔር ፊት እንደ ጻድቅ ተቆጠረ፤ ክርስቶስ ግን እንደ ኃጢአተኛ ተቆጠረ፡፡ ሐዋሪያው
ይህን ታላቅና አስደናቂ ልውውጥ «እኛ በእርሱ (በክርስቶስ) ሆነን የእግዚአብሔር ጽድቅ እንሆን ዘንድ
ኃጢአት ያላወቀውን እርሱን (ክርስቶስን) ስለ እኛ ኃጢአት አደረገው›› በማለት ገልጦታል (2ቆሮንቶስ
5፡21)፡፡ በአንድ በኩል ክርስቲያን ከእግዚአብሔር ጋር እርቅና ሰላም የሚኖረው ክርስቶስ በእርሱ ስፍራ የሕግን
ቅጣትና እርግማን በመሸከሙ ሲሆን (ገላቲያ 3፡13) በሌላ በኩል ደግሞ በክርስቶስ ጽድቅ ውስጥ በመቆሙ
ነው (1ቆሮንቶስ 1፡30-31)፡፡
የክርስቶስ ሞት የእኛ ምትክ መሆኑ የሚያስገነዝበን ነገር ቢኖር እርሱ በእኛ ምትክ መሞቱን፣ የእኛን ህማም
መታመሙን፣ የእኛን በደል መሸከሙን (ኢሳይያስ 53) ነው፡፡ ኢየሱስ ስለ እኛ ቆሰለ፣ ስለ እኛ ተዋደረ
የማይገባውን ያውም የመስቀል ሞት ለመሞት የታዘዘ ሆነ (ፊሊ. 2፡8)፡፡ ጤነኛ የሆነ አእምሮ ሁሉ ይህን
ካነበበ በኋላ «ግን ለምን?›› ብሎ ሊጠይቅ ይገባዋል፡፡ መልሱም ሊያድነን፣ ከፈጣሪያችን ጋር ሊያስታርቀን፣
ቅዱስ ሕዝብ ሊያደርገን፣ ቀድሞ ወደ ነበርንበቱ ክብር መልሶ ሊያመጣን የሚል ይሆናል፡፡ ይህ የመዳን መንገድ
ብቸኛው የመዳን መንገድ ነው (ዮሐንስ 14፡ 6)፣ ከዚህ የተሻለ የመዳን መንገድ ለመፈለግ ማሰብም ሆነ
ማድረግ ከእግዚአብሔር ይልቅ ጥበበኛ ነኝ ከሚል ትእቢተኛ ልብ የሚመነጭ ከመሆኑ ባሻገር የኢየሱስን ሞት
ከንቱ ማድረግ ይሆናል (ገላቲያ 2፡21) ደሙንም ማክፋፋት ይሆናል (ዕብራዊያን 10፡29)፡፡
ኢየሱስ ይህን ሁሉ ከፈጸመልኝ የእኔ ድርሻ ምንድር ነው?
እርስዎን ከእግዚአብሔር ጋር ለማስታረቅ የሚቀር ሌላ መሥዋዕት እንደሌለ ይወቁ፣ የኢየሱስ መሥዋዕት
ፍጹም፣ ንጹህ፣ ቅዱስ፣ በቂ በመሆኑ እርስዎን ለማዳን የሚችል እንደሆነ ይመኑ፡፡ ይህንን የማዳን መንገድ
ሙሉ ለማድረግ ከእምነት ውጪ ከእርስዎ ምንም እንደማይጠበቅ ይመኑ፡፡ ከዚህ ውጪ ምንም ነገርለማድረግ በሚንቀሳቀሱበት ቅስበት የኢየሱስ የመስቀል ሥራ ጎዶሎና ያለእኔ እርዳታ በራሱ ሊቆም
የማይችል ደካማ ሥራ ነው እያሉ እንደሆነ አይዘንጉ፡፡ «ለመዳን (ከእግዚአብሔር ጋር ለመታረቅ) ከማመን
ውጪ ከኔ የሚጠበቅ እኔ የማዋጣው ነገር የለም ነው የምትለኝ)´ የሚሉኝ ከሆነ፣ እኔ ደግሞ በተራዬ አንድ
ጥያቄ እንድጠይቆ ይፍቀዱልኝ፡- «ከእግዚአብሔር ጋር ለመታረቅ እርሶ ሊያደርጉት የሚችሉት አንዳች ነገር
ቢኖር ኖሮ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን ለዚህ ሥቃይ አሳልፎ የሚሰጠው ይምስሎታል?
ኢየሱስ በመሥቀሉ ሥራ ሞትዎን እንደሞተልዎ ሥቃዮን እንደ ተሰቃየልዎ፣ ቢያምኑ ለነፍስዎም ቤዛ አድርጎ
ሕይወቱን ስለ እርስዎ አሳልፎ እንደ ሰጠልዎ ቢያምኑ፣ እግዚአብሔር በእርስዎ ላይ የተቆጣውን ቁጣ በእርስዎ
ምትክ ሆኖ ሁለት እጆቹን ዘርግቶ እርቃኑ በቀራንዮ ኮረብታ ላይ በተገኘልዎ አዳኝ ላይ ማሳረፉና እርስዎም
በዚህ ምክኒያት ከዚያ አስፈሪ ቁጣ ማምለጥዎን ቢያምኑ፣ ከተጣልዎ ፈጣሪ ጋር እርቅ ፈጥረዋልና በእርግጥ
የዘላላም ሕይወት አለዎት!!
@lebegu
@lebegu
✍ Tsion birhanu
220
አንድ ዝሆን እና አንድ ውሻ በእኩል ቀን እርግዝና ጀመሩ።
ውሻዋ በ3 ወሯ ላይ በአንድ ጊዜ 6 ቡችሎችን ወለደች።አሁንም ደግማ 4 ቡችላ ወለደች።
እኩል ቀን አርግዘው ውሻዋ ሶስተኛ ዙር ወለደች ።ከዚያም ውሻዋ ዘወር ብላ የምር ግን አርግዘሻል እርግጠኛ ነሽ አለቻት።
እኩል ቀን አረገዝን እኔ 3 ዙር ወለድኩ አንቺ ግን አንዴም አልደወልሽም አለቻት።
በዚህ ጊዜ ዝሆኗ እንዲህ አለቻት
እኔ እንደ አንቺ ቡችላ አይደለም ያረገዝኩት ዝሆን ነው ያረገዝኩት
አንድ እለት የተውለደ ጊዜ ገና ማደግ እንደጀመረ የብዙዎችን ቀልብ የሚስብ የሚጎበኝ እና ድንቅ ፍጥረት ነው የሚሆነው አለቻት።
ዛሬም ቢሆን የጸሎት መልሶቻችን ስለዘገዩ እውነተኛ የማንመስላቸው ቢኖሩም የዘገየው ነገራችን መልስ ባገኘ ጊዜ የሚያስደንቅ እና ትኩረት የምንስብ መሆናችን አይቀርም።
ሁሉን ግን በትዕግስት እንጠብቀው።
መልካም ምሽት ተመኘሁላችሁ።
✍ beki belay
@Lebegu
@Lebegu
@Lebegu
220
#አልፈረደብኝም_ምህረቱ_አይሎበት
የሆነ ጊዜ ምን ገጠመኝ መሰላችሁ - ATM ረጅም ሰልፍ ተሰልፌ ... ከሰልፉ ፊት ያሉት ሁለት ተረኛ ልጆች ገትረውን ይነጋገገራሉ። እና Offended ሆንኩኝ። ምንድነው ሚዝናኑት ሰው አስቁመው : ሲያስጠሉ ፋራዎች ሚያወሩበት አጡ ? ምናምን Stuff እያልኩ ስበሰጫጭ ልጁ ጨርሶ ወጣ። ታምኑኛላችሁ ወዳጆቼ ዓይነ ስውር ነበር ልጁ 😔 እያገዘው ነበር ከኋላው ያለው ልጅም ። ተሸማቀኩ አይገልፀውም። መፍረድም በጣም ፈራሁ ።
በዚህ ምድር ባለን መንፈሳዊ ህይወትም የቱንም ያህል ጥሩና መልካም እንደሆንን ብናስብ : ጌታችን ኢየሱስ ጥቂት ያህል እንኳን ያልተወልን Ground የመፍረድ ነው። ቢፈርድ የሚያምርበት እንከን አልባው ሳይፈርድ እኛ በብዙ ድካም የተከበብን ለመፍረድ ምን ያንቀዠቅዠናል??
“እርስዋም፦ ጌታ ሆይ፥ አንድ ስንኳ አለች። ኢየሱስም፦ #እኔም_አልፈርድብሽም፤ ሂጂ ከአሁንም ጀምሮ ደግመሽ ኃጢአት አትሥሪ አላት።”
— ዮሐንስ 8፥11
የኢየሱስን ርህራሄ በዘመናት ከፋፍላችሁ በህጉ ዘመን ውስጥ በህጉ Mentality የሚሰራ ብቻ አድርጋችሁ ለምትሰብኩም አንድ ነገር ልጨምር። የእርሱ ርህራሄ ከራሱ ማንነት የሚቀዳ እንጂ በምክንያት ላይ የተመሰረተ አይደለም።
“እርሱ ራሱም ደግሞ #ድካምን_ስለሚለብስ፥ ላልተማሩትና ለሚስቱት ሊራራላቸው ይችላል፤”
— ዕብራውያን 5፥2
ይኸውላችሁ የትኛውም ሊቀካህናት ለሀጥያተኞች የሚራራው ራሱ ድካም ስላለበት ብቻ ነው። ማለትም ሀጥያት ባይሰራ ኖሮ አንድም ሀጢያተኛ በርህራሄ አይስተናገድም : ያልቅለት ነበር። ሀጥያት የተባለ የሌለበት ፍፁም ቅዱስ ሲሆን ለሀጥያተኞች የሚራራ የአዲስኪዳን ሊቀ_ካህናት አንድ መድሃኔዓለም ብቻ ነው። ርህራሄው ከራሱና ከማንነቱ የሚፈልቅ ነው።
ደግሞኮ ላልተማሩትና ለሚስቱት(በስህተት ለሚሰሩት ) ብቻ ነው ሊቀ-ካህናት ይራራ የነበረው ። የኛ ጌታ ስንት ድፍረት ትዕቢታችንን ይቅር እንዳለን የሚችል ይቁጠረው
ፍቅሩ ያለአንዳች አስገኚ ምክንያት : ቸርነቱ ያለምክንያት : ርህራሄው ያለምክንያት : ላይጠላን በምክኒያት ላይለቀን ይዞናል : ምስጋና ይገባዋል
Ohhh Sweet Jesus 😍 በድካም ያላችሁ : በሀጥያትም ያላችሁ እባካችሁ ሳያሸማቅቅ ወደሚያቀርባችሁ : ነገር ግን በምህረት ወደሚፈርድላችሁ ጌታ ተጠጉ ቅረቡት ። መልካም ፍሬ እውነተኛውን ግንድ ከመጣበቅ የሚመጣ ነው።
ታሜ ነኝ 😍 እወዳችኋለሁ
Share the post
@Lebegu
@Lebegu
220
ግዴታ ይነበብ በጣም_ወሳኝ_ጥቆማ
#ክርስትያን የሆነ ሁሉ ይህ መረጃ ይመለከተዋል
የተወደዳችሁ ወንድሞቼ እና እህቶቼ
new International version (NIV) አብዛኞቻችሁ እንደምታውቁት ገምታለው ለማታውቁ ደግሞ #NIV መፅሀፍ ቅዱስን በአለም አቀፍ ደረጃ በHard copyና በsoft copy የሚያሳትም እና የሚያከፋፍል እንደሁም መፅሐፍ ቅዱስን በተለያዩ ቋንቋዎች translate የሚያደርግ company ነው
NIVን published ያደረገው ዞንደርቫን የሚባል ሰው አሁን ደግሞ ሀፐር ኮሊንስ የተባለ ሰው ተረክቦታል
በጣም የሚያስገርመው ይህ ኮሊንስ የተባለው ሰው homosexual(gay) ሲሆን የሰይጣንን #መፅሐፍ ቅዱስ አሳትሟል
በአሁን ሰዓትም የNIV ዋና publisher ነው
በአሁን ሰዓት #NIV እና #የኢንግሊዘኛው ESV በአዲሱ እትማቸው ከመፅሐፍ ቅዱስ #45 ቃላትን አስወግደዋል😭😭😭😭
ለአብነትም #Jehovah, #calvary, #omnipotent አና #holy ghost ጥቂቶቹ ናቸው
የተወገዱት ቃላት ወሳኝ የሆኑ #ቁልፍ ቁልፍ ቃላቶች ናቸው
አብዛኞቻችን #soft copy መፅሐፍ ቅዱስን በcomputer ,tablet እና mobile ነው የምንጠቀመው
እስኪ እነዚህን ጥቅሶች በስልካችሁ NIV እና ESV published ባረጉት የመፅሐፍ ቅዱስ app ፈልገው ይሞክሩ
ማቴዎስ 17:21, 18:11, 23:14; ማር 7:16, 9:44,9:46; ሉቃስ 17:36, 23:17;
ዮሐንስ 5: 4; የሐዋርያት ሥራ 8:37
በተጨማሪም NIV እና ESV ከመፅሐፍ ቅዱስ 45 ሙሉ ቁጥር አስወግደዋል
ሰለዚህ ምን #እናድርግ?
#እርምጃ አንድ
#hard copy bible ብቻ መጠቀም
#እርምጃ ሁለት
#soft copy bible የምትጠቀሙ ከሆነ ደግሞ የድሮውን app ማለትም #update #ያልተደረገውን app ይጫኑ
bibleአችሁን #በጭራሽ update እንዳታደርጉ
የጫናችሁት app update የተደረገው ከሆነ አሁኑኑ ከስልካችሁ አጥፉት
ወይንም በሌላ #publisher የተሰሩ የbible አፕዎችን ተጠቀሙ
don't forget #ያወራነው NIVና ESV ስለሚያሳትሙት bible ነው ወዳጆቼ የዘመን ፍፃሜ ጫፍ ላይ እንደቆምን አትዘንጉ
ሰይጣን ጥቂት ጊዜ እንደቀረው አውቆ በታላቅ ቁጣ ጠንክሮ አየሰራ ነው ተጨማሪ #ጊዜ የለንም
ያለንን ጊዜ እንጠቀም #ይህንመልዕክትለ15ሰውበመላክ #የሰይጣንን #ዕቅድ_እናፈራርስ
የዚህ ዓለም ገዢ አላማው hard copy bibleን በማጥፋት soft copy bible ላይ ያሉትን የመዳናችን ምክንያት የሆኑ ቁልፍ ቁልፍ ቃላቶችን ማስወገድ ነው ስለዚህ ለhard copy bible ትኩረት
እንስጥ በእያንዳዳችን እጅ ላይ must መኖር አለበት ኢየሱስ ሊመጣ በደጅ ነው፡፡
የጌታ ፀጋ ይብዛላችሁ!!
በተለይ በእንግሊዝኛ ያለውን ትርጉም አይጠቀሙት
አደራ!!😭😭😭😭
@Lebegu
@Lebegu
220
#አንዳንዴም_ለፈገግታ
አይ የጴንጤ ወንድ መከራ😂 የምታመናፍስ ሴት ስታጋጥመው 😂😂 (ለፈገግታ)
Me - ሀይ
Her - ሰላም
Me - ሰላም ነሽ?
Her - ሰላሜ እየሱስ ነው!
Me - እውነት ነው። ጠፍተሻል ሰሞኑን ደግሞ
Her - አልጠፋሁም፤ ከማይጠፋ ዘር ነኝ!
Me - ልክ ነው እሱስ። እና ምን አዲስ ነገር አለ?
Her - ከፀሐይ በታች አዲስ ነገር የለም!
Me - ሃሃ...እኔ የምልሽ ቁርስ በልተሻል?
Her - ሰው በእንጀራ ብቻ አይኖርም!
Me - ደግሞ የፖሰትሽውን ፎቶ አየሁት። በጣም ውብ ነሽ።
Her - ውበት ሐሰት ነው፣ ደምግባትም ከንቱ ነው!
Me - አይደል? የት ሰፈር ነሽ ግን? አድራሻሽን እኮ አልነገርሺኝም? 😂
Her - አድራሻዬ መስቀሉ ስር ነው!
Me - ሃሃ...ኧረ የመኖሪያ አድራሻሽን ነው ያልኩሽ!
Her - "መኖሪያዬ ጌታ ነው" የሚለውን መዝሙር ጋብዤሀለሁ
Me - ስለመጋበዝ ካነሳሽ አይቀር ለምን አንድ ቀን አልጋብዝሽም ተገናኝተን?
Her - ውይ በጣም አመሰግናለሁ! ጌታ ይባርክህ! ግን መጀመሪያ እኔ ነኝ የምጋብዝህ!
Me - እውነትሽን ነው? በጣምም በደስታ ነዋ!
Her - ከፊታችን እሮብ ከስራ መውጫ ሰአት ላይ ይመችሀል?
Me - አዎን በደምብ [የትም ይመቸኛል! 😂]
Her - ጥሩ! "ኤልዛቤል ትፈጥፈጥ ኢንተርናሽናል ቸርች" የነፃ መውጣት ፕሮግራም አለ እዛ ጋብዤሀለሁ!
Me - ተባረኪ 😑! እና ከዛ ስንወጣ እራት አብረን እንበላለን በቃ እንደውም!
Her- ውይ አልችልም! ከዛ ስወጣ የአዳር ፕሮግራም አለኝ። ባይሆን እራት በምትጋብዘኝ ብር "እጮኝነት እና ትዳር" የሚለውን መፅሐፍ ግዛልኝ።
Me - በደስታ! ነገውኑ ገዝቼ አቀብልሻለሁ!
Her - ውይ ነገ አልችልም!
Me - እና መቼ ተገናኝተን ላቀብልሽ?
Her - ኧረ አትቸገር ቸርች ዘበኛው ጋር አስቀምጥልኝ። ሲመቸኝ ሄጄ እወስደዋለሁ።
Me - እሺ ካልሽ ምን ይደረጋል!
Her - በቃ አሁን ከSocial media online ወጥቼ ወደመንፈሳዊው አለም online ልገባ ነው!
Me - እሺ ውዴ ደህና እደሪ! ከእኔ ጋር ትንሽ ብትሆኚ ደስ ይለኝ ነበር።
Here - የጌታ ፀጋ ከአንተ ጋር ይሁን። ደህና ሁን በጌታ የተወደድክ ወንድሜ!
አስበው ከዚህ ሁሉ ጥረት በኋላ "ወንድሜ" ስትልህ የሚሰማህን የስሜት breakdown! ከ Fb
@Lebegu
@Lebegu
@Lebegu
