ለበጉ ክብር 🙏
Open in Telegram
In this channel every thing is about Jesus.We praise and worship the Lamb with gospel singers ; preach and reveal the mystery of the cross with preachers by the power of the Holy spirit. If you are a singer or a preacher contact @hallelujah2016
Show more220
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
220
220
የዮሐንስ ራዕይ 5:1-14 ( ርዕስ : ሙሉ ቤዝዎት /Complete Redemption )
በአገልጋይ ታምራት አለማየሁ (@hallelujah2016)
አዳምጡት 🥰🥰 ታተርፉበታላችሁ።
@lebegu
@lebegu
@lebegu 👈👈 Join ለተጨማሪ
220
10 Billion ብር ዝም ብዬ ብሰጣችሁ ምን ይመስላችኋል ? ከዚያም ይሄን ብር የምትወስዱት ግን ነገ ጠዋት የማትነቁ (በህይወት የማትቀጥሉ ) ከሆነ ነው ብላችሁ?
የብዙዎቻችሁ መልስ ብሩ ጥንቅር ይበል ነው አይደል? አያችሁ ነገ መንቃት ከ 10 Billion ብር ይበልጣል ማለት ነው።
“እኔ ተኛሁ አንቀላፋሁም፤ #እግዚአብሔርም #ደግፎኛልና #ነቃሁ።”
— መዝሙር 3፥5
ሳያንቀላፋ ለሚጠብቀን : ደግፎም ለሚያነቃን ይሄም ሳያንስ በየማለዳው በአዲስ ምህረት ለሚጎበኘን ለእግዚአብሔር ክብር ይሁን።
ዛሬ ማታ ያለ ሀሳብ ለጥ ብላችሁ ስታንቀላፉ እምነታችሁ ነገን ደግፎ በሚያነቃችሁ ጌታ ላይ ከሆነ በcomment እግዚአብሔር ይመስገን በሉ።
220
አሁንም ድረስ "Thank you" ሲባሉ "አብረን Q" የሚሉ ሰዎች ሳይ ክፉኛ አዝናለሁ አለ አንዱ 🤣🤣🤣
እና ሁሉም ነገር ያልፍበታል። ሙጭጭ የሚባለው ኢየሱስ ላይ ብቻ ነው። የማያልፍበት ርዕስ : የማይሻር ህያው ቃል ነውና !!
Share አድርጉ። በ comment ስለ ኢየሱስ ፃፉ። እወዳችኋለሁ !!
✍አገልጋይ ታምራት አለማየሁ
@Lebegu
@Lebegu 👈👈 Join
@hallelujah2016 👈 ሀሳብ ለመስጠት
220
ለወሬ ያለን ጉጉት እና ፍቅር በዝቶ : ብዙ ጊዜ ሰዎች ስለሆነ ሰው ሊነግሩን ፈልገው "እከሌን ታውቀዋለህ" ሲሉን ባናውቀው እንኳን : ባየው አውቀዋለሁ ግን ወሬውን ንገረኝ ብለን እንጣደፋለን 😂😂 አቤት ያለን Excitement : ካልነገረን አንዳች ከባድ ነገር የሚደርስብን ነው ምናስመስለው። ድንቅ ስለሆነው ስለ ኢየሱስ ለመስማት ያለንስ ጉጉት ምን ያህል ይሆን?
“በመካከላችሁ ሳለሁ ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር እርሱም እንደተሰቀለ ሌላ ነገር እንዳላውቅ ቆርጬ ነበርና።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 2፥2
የህይወታችን ክበብ በጣም ሲሰፋ : የምንሯሯጥላቸው ጉዳዮች ሲበዙ : ምን ላይ ማተኮር እንዳለብን መዘንጋት ብቻ ሳይሆን : ዋና የሆነውን ነገር ጥለን ተራ በሆነው ነገር እስከመጠመድ እንደርሳለን።
ለምን ተፈጠርኩኝ ብሎ ብዙ ሰው ይጠይቃል? ከተለያዩ ሰዎችም እጅግ የተለያዩ መልሶች ይሰነዘራሉ። ለመሆኑ ለምን ተፈጠርክ/ሽ? የዚህን ጥያቄ መልስ ትክክለኛነት ለማረጋገጥ ሰውን ከፈጠረው ፈጣሪ አካል መስማቱ የማያጠያይቅ ነው።
“ምናልባትም #እየመረመሩ_ያገኙት_እንደ_ሆነ፥ #እግዚአብሔርን_ይፈልጉ_ዘንድ በምድር ሁሉ ላይ እንዲኖሩ የሰውን ወገኖች ሁሉ ከአንድ ፈጠረ፥
— ሐዋርያት 17፥26
“እግዚአብሔር ስለ ገለጠላቸው፥ ስለ እግዚአብሔር ሊታወቅ የሚቻለው በእነርሱ ዘንድ ግልጥ ነውና።”
— ሮሜ 1፥19
ሰው እግዚአብሔርን እንዲያውቅ እና እንዲፈልግ ተፈጥሯል። ይህ ከመታወቅ የሚያልፈውም አምላክ በመልካም ፈቃዱ እርሱን ለማወቅ የሚያስችሉትን መንገዶች ገልጧል።
ይኸውም አስተርዕዮ እየሰፋ የሄደ ሲሆን እርሱ የፈጠረውን ፍጥረት ተመልክተው እንዲያውቁት በማድረግ ይጀምርና : በህጉ ራሱን መግለጡን ቀጥሎ : ከዚያም በነቢያት : በመጨረሻም የማይታይ አምላክ ምሳሌ እና የክብሩ ነፀብራቅ(Reflection) በሆነው በኢየሱስ ክርስቶስ ራሱን በሙሉ ፍፅምና ገልጧል።
ዕብራውያን 1
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ከጥንት ጀምሮ እግዚአብሔር በብዙ ዓይነትና በብዙ ጎዳና ለአባቶቻችን በነቢያት ተናግሮ፥
² ሁሉን ወራሽ ባደረገው ደግሞም ዓለማትን በፈጠረበት በልጁ በዚህ ዘመን መጨረሻ ለእኛ ተናገረን፤
ታዲያ ኢየሱስን ለማወቅ እንደምን አንጓጓም። የተፈጠርንበትን አላማ በሙላት መገናኛው መንገድ እኮ እርሱ ነው። የነፍስን ብዙ ቀዳዶች የሚሞላው እርሱ ብቻ ነው።
ሁልጊዜ ኢየሱስን የምታወሩን አገልጋዮች እግዚአብሔር ከዚህ በላይ ብዙ ፀጋ እና የመንፈስ ቅዱስ ሀይል ይብዛላችሁ። ትኩረታችሁ ከኢየሱስ የተወሰደ : ተራው ነገር ላይ የተጠመዳችሁ ደግሞ በኢየሱስ ስም የጥበብ መዝገብ ሁሉ በእርሱ ዘንድ ወደሆነው ጌታ መመለስ ይሁንላችሁ።
Share አድርጉ። በ comment ስለ ኢየሱስ ፃፉ። እወዳችኋለሁ !!
✍አገልጋይ ታምራት አለማየሁ
@Lebegu
@Lebegu 👈👈 Join
@hallelujah2016 👈 ሀሳብ ለመስጠት
