መንገደኛው
Open in Telegram
የአላህ መልዕከተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል:- “ዱንያ ላይ ስትኖር እንደንግዳ አሊያም እንደ መንገደኛሆነህ ኑር።”
Show more287
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
287
اللهم افتح لنا فتحًا مُبينًا ، واهدنا صراطًا مستقيمًا ، وانصرنا نصرًا عزيزًا ، وأتِم علينا نعمتك ، وأنزِل في قلوبنا سكينتك ، وانشر علينا فضلك ورحمتك يا رب .
287
ምን ባደርግ እቃናለሁ?
***
ጌታዬን እንዳመፅኩ ሲታወሰኝ ለራሴ ማነሳው ጥያቄ ነው።
እርግጥ ጥያቄው በውስጤ የሚያሳርፈው ምት ከፈፀምኩት አመፅ ደረጃ ፣ አመፅ ውስጥ ከነበረኝ ታሪክ ከአመፁ ባህሪ ጋር በቀጥታ ይያያዛል።
አመፁ አንዴ ተፈፅሞ የሚጠፋ መሆኑ ቀርቶ እኔነቴን የሚገልፅ ድግግሞሽ መሆኑ ሲያሳስበኝ ከሰው ተለይቼ ብቻዬን ጥግ እይዛለሁ። ቁልቁል አቀርቅሬ በቁጭት
"ምን ባደረግ ? እላለሁ
በምጠብቀው እኔ እና እየሆንኩ ባለሁት እኔ መሃል የተፈጠረው ግዙፍ ቅራኔ አሳስቦኝና እፍረት ተሰምቶኝ ከሰው ብለይና ጥጌን ብይዝ "ምን ባደርግ" እያልኩም ብጠይቅ ነውሩ ምኑ ጋር ነው?
በኔ ግምት እራሴን ምጠብቀው የጌታውን ትዕዛዝ ሳያዛንፍ የሚጠብቅ ፣ እንዲጠበቅ የሚታገል ግለሰብ አድርጌ ነው። ምወክለው ኢስላምንና ኢስላም በሰው ልጆች ላይ ያለውን ጥቅም ነው። እራሴን ማስበው የጊዜ ጉዳይ ካልሆነ በቀር ከራሱ ያለፈ ማህበራዊ ትርጉም ያለው ሰው አድርጌ ነው።
ተግባር ሚያረጋግጥልኝና ራሴን የማገኘው ግን ፍፁም ባልጠበቅኩት ቦታ ነው።
አዎን ጌታዬን ለመታዘዝ ድንጋጌውን ለመፈፀም ተነስቼ የተወሰነ እሄድና ምን እንደመታኝ ሳላይ መሃል ላይ ተደናቅፌ እወድቃለሁ።
በ 1 ጉድጓድ ውስጥ 10 ጊዜ ወድቄ እራሴን ሳገኘው ፣ ከውድቀቴ መማርና መነሳት ሲሳነኝ ከሰው ተለይቼ ብቻዬን ጥጌን ብይዝ ሰማይ ምድሩን እያየሁ ምን ባደርግ ብል ችግሩ ምንድ ነው!
አዎን ምን ባደርግ ጌታዬ?
ይህን ጥያቄ መጠየቅ ከጀመርኩ አመታት ተቆጠሩ ።
በወንጀሌ ምክንያት የማንም መፈንጫ ሆኛለሁ ።
በዚህ ሁሉ ውስጥ ግን ተስፋ አልቆረጥኩም መጠየቄንም አላቆምኩም።
ልክ እንደ ትናንቱ ዛሬም ምን ባደርግ እያልኩ እየጮህኩ ነው።
አሁን ላይ ሙስሊሙ አለም ይህን ሲል በመጠየቅ ላይ ያለ ይመስለኛል። ጥያቄውም ይቀጥላል
حتى ترجعوا إلى دينِكم.
287
ዐብዱላህ ኢብኑ ዐባስ እንዲህ ይላሉ
« የአላህ መልክተኛ አንድ ቀን ከባድ ህመም ላይ ነበሩ ሁለት መልአክቶች መጥተው አንደኛው ከራሳቸው በኩል አንደኛው ደግሞ ከእግራቸው በኩል ተቀመጠ በእግራቸው በኩል የተቀመጠውም መላኢካ በራስ በኩል ላለው እንዲህ አለ « ሙሃመድ ታሟል እና ምን ትመለከታለህ ምን ሁኖ ነው (ምን ትላለህ ) ? » አለ
ሌላኛው መላኢካም «በረሱሉ ላይ ተደግሞባቸዋል»
ሌላኛው መላኢካም « ማነው ታዲያ የደገመባቸው» ብሎ ጠየቀ « የደገመባቸው የሁዲዮ ለቢድ ኢብኑል አዕሶም ነው! »
« ታዲያ እሺ የተደገመባቸው ድግምቱ የት ነው » ሲል ጥያቄውን ደገመው
መላኢካውም « የነ እገሌ ቤተሰብ ጋር አንድ የጉድጓድ ውሃ አለ በውስጡ ቋጥኝ አለ ከቋጥኙ ስር ነው ድግምቱ የተቀበረው አለ»
መላኢካዎቹም ወደዚያች ጉድጓድ ሄዱና ጉድጓዱ ውሃው እንዲደርቅና ከቋጥኙ ስር ጥቅልል ያለ ነገር እንዲወጣ አድርገው አቃጠሉ!
ከዛ የተድበለበለ ነገር ውስጥ ጥቅልል ገመድ ክሮች አሉ በክሮቹም ላይ 11 የሚሆን ቋጠሮዎች ተቋጥረው ነበር!
በዚህም ግዜ ሙዐወዘተይኖች ሱረቱል ፈለቅ እና ሱረቱንናስ ወደ መልክተኛው ተወረዱ!
ረሱል ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እያንዳንዱን አንቀፅ ባነበቡ ቁጥር እያንዳንዱ ቋጠሮ ተራ በተራ ተፈታ ¹
አነስ ኢብኑ ማሊክም እንዲህ አለ «
የሁዶች ለመልክተኛው ዐለይሂሰላም ትንሽ ምግብ ሰርገው በንግድነት ጋበዟቸው በተመገቡት ምግብም ምክንያት ለከባድ ህመም ተጋለጡ ሶሃቦችም መልክተኛው ወደነበሩበት ክፍል ገብተው ነበር ጅብሪል ሙዐወዘተይኖችን ይዞ መጥቶ አነበበባቸው ከዚያም ቡሃላ ረሱሉ ጤነኛ ሁነው ወደ ሶሃቦቻቸው ተቀላቀሉ! »②
①አስባበ ኑዙል ሊልዋሂዲይ ገፅ 410
② ጠበራኒይ «ዱዓእ» በሚለው ኪታባቸው 335
287
ጭንቀቱን ላወያየህ ሰው የምታደርግለት የመጀመሪያ እርዳታ ልቡ እንዲረጋጋና ሰላም እንዲሰማው ማድረግ ነው።
ነቢ ሙሳ ለዚያ ሷሊሕ ሰው ታሪኩን ካጫወተው በኋላ
لا تخف نجوت من القوم الظالمين"
ሲለው እንዴት አይነት ሰላም ተሰምቶት ይሆን?
فَلَمَّا جَاءَهُ وَقَصَّ عَلَيْهِ الْقَصَصَ قَالَ لَا تَخَفْ ۖ نَجَوْتَ مِنَ الْقَوْمِ الظَّالِمِينَ
ወደእርሱ በመጣና ወሬውን በእርሱ ላይ በተረከለትም ጊዜ «አትፍራ ከበደለኞቹ ሕዝቦች ድነሃል» አለው፡፡
287
የድሮ ሴቶች ወንዶች የሚያማልሉ ሳይሆኑ
ወንዶች የሚሰሩ ነበሩ‼️
አላህ ይህንን ዲን ይጠበቅ ዘንዳ ሰበብ ካደረጋቸው ሰዎች በግንባር ቀደምትነት ከሚጠቀሱት ውስጥ አንዱ የሆኑት; ታላቁ የአህለል ሱና ወል_ጀምዓ ኢማም
አቡ ዐብደላህ አሕመድ ቢን ኸንበል
እንዲህ ይላሉ፦
«የአስር ዓመት ልጅ ሳለሁ እናቴ ቁርኣን አስሃፍዛኛለች። ከፈጅር ሰላት በፊት ቀስቅሳኝ ብርዳማ በነበሩ የበግዳድ ሌሊቶች እንዳልቸገር የውዱእ ውሃ ታሞቅልኛለች። ልብሴን አልብሳኝ እሷም ለባብሳ; መስጂዱ ከቤታችን ራቅ ያለ ቦታ ስለ ነበርና ሌሊቱም ጨለማ ስለ ነበር አብራኝ ወደ መስጂዱ ትወስደኛለች።»
👌የዚህ ትውልድ ታሪክ እንዲታደስ
እኛን የሚያማልሉን ሳይሆን
ልጆቻችንን የሚሰሩልን እህቶች ያስፈልጉናል‼️
287
ሀሰን አልበስሪ ረሂመሁላህ እንዲህ ይላሉ፦
" አላህ ቁርዓን ውስጥ ዘጠና ቦታዎች ላይ ሪዝቅን በአጠቃላይ ለፍጡራኖች መወሰኑንና ማስተማመኑን አንብቢያለሁ ። አንድ ቦታ ላይ ብቻ ይህን አንብቢያለሁ ፡
{ ٱلشَّيْطَٰنُ يَعِدُكُمُ ٱلْفَقْرَ وَيَأْمُرُكُم بِٱلْفَحْشَاء}
«ሰይጣን (እንዳትለግሱ) ድኽነትን ያስፈራራችኋል። በመጥፎም ያዛችኃል »
እኛ ግን እውነተኛውን በዘጠና ቦታዎች ላይ አላምን ብለን ውሸታሙን አንድ ቦታ ላይ ብቻ አመንን !! "
『📚قمع الحرص بالزهد والقناعة /للقرطبي
ص60 』
287
ወንድም ከእህቱ ጋር በብዛት ሀያ አመታትን አብሮ ያሳልፋል። ይሄን ሁሉ አመታት ይወዳታል። ያዝንላታል። ማንም አዛ እንዳያደርጋት ይታገልላታል፣ ይጋደልላታል። እሷም ወንድማለም፣ ወንድም ጋሻዬ፣ መከታዬ፣ ኩራቴ እያለችው፣ ሲያመሽ እየተጨነቀችለት፣ ጩኸት ስትሰማ ወንድሜ ምን ሆኖ ይሆን እያለች እየሰጋችለት፣ እያከበረቺው፣ እያሰበችለት ይሄን ሁሉ አመታት ከሱ ጋር ታሳልፋለች።
ይህ በሥስት አይን የምታየው ወንድሟ አሏህ ብሎለት በሀያዎቹ የእድሜው አጋማሽ ላይ የሆነችን ልጅ ያገባል። ሚስት ተብዬዋ ደግሞ ገና በመጣች በወሯ ወይም ጥሩ ከሆነች ባመቷ ያችን የእድሜ ልክ ወዳጁን፣ ሚስጥረኛውን እና አክባሪውን እህቱን ማጣጣልና ክፋቷን መጠቃቀስ ትጀማምራለች። በአንድ ማህጸን ላይ የኖሩን አጣጥላ፣ ከማዶ መጥታ የእህትን ቦታ ላትተካ ነገር ከእህቱ ጋር ልታቀያይመው ብዙ አይነት ምክንያቶችን ትደረድራለች። በዚህም በእህቱ ላይ የአጭር ጊዜ ቂም ይይዝ ይሆናል። ሚስት ግን ባሏ ለቀናት እህቱን ተወት ሲያደርጋት ጊዜ የምርም እኔ የምለውን ይሰማል በሚል ትቀጥልበታለች። ወይም ከመነሻውም የሚስትን ወቀሳ ከቁብ ካልቆጠረው ደግሞ ለኔ አታስብ፣ የኔ ነገር ግድ አይሰጥህ እያለች ትነዘንዘዋለች። ይህን ተከትሎ እህቱን ከመውቀስ ይልቅ ይች ጨቅጫቃና ነገረኛ ሚስት ማለት ይጀምራል። የሆነ ጊዜ ሚስቱን ያርቅና ስለእህቱ መልካምነትና ስለሚስቱ ክፋት በአደባባይ ሲያወራ ይሰማል።
እቴ እህቱ እህቱ ነች። የተጋሩት ደምና ስጋ አላቸው። 9 ወራትን አንድ ማህጸንን ተጋርተዋል። የእድሜያቸውን ግማሽ ወይም ሲሶ ያክል በአንድት ጣሪያ ስር በፍቅር ኖረዋል። እህቱ ነገሩ ሁሉ ነች።ቭምናልባት ትኩስ ፍቅር ላይ ማሚዬ፣ ማማዬ፣ እህቴ እያለ ቢያንቆለጳጵስሽ አንቺ የእህትም ይሁን የእናት ምትክ የሆንሽ ያክል አይሰማሽ። ውሸት ነው!ዉሸት ነው። የእህቱን ልክ ካላወቅሺ ያንችን ክብር ታጫለሽ። የትዳር አጋርን ቤተሰብ (በተለይም የባልን ብዬ ብጽፍ ባል ምን ስለሆነ ትላላችሁ አይደል) አይደለም በቋሚነት መጥላትና በአጋጣሚ ማነወር የሚያስከትለው ጦስ ከሚገመተው በላይ ከባድ ነው። ዘመድ ከዘመዱ አህያ ከአመዱ የሚባለውም አባባል ትክክል ነው።
እወቁበት።
287
.
"ወሬህ ይፃፋል ንግግርህም ይመረመራል አንተ ሰው ሆይ አዎ ተፈላጊ ነህ ወንጀል አለብህ አቶብትም የህይወት ፀሀይ መግባቷን ይዛለች በልቦች መሀል ልብህ ምንኛ አደረቀው።".
- ابن الجوزي👉
287
የቀዝቃዛ ውሀ ፀጋ !!!
አብደላህ ኢብኑ ኡመር ረዲየላሁ አንሁ ቀዝቃዛ ውሀን ጠጥቶ ሲያበቃ በጣም ምርር ብሎ አለቀሰ ። ከዚያም ምንድን ነው የሚያስለቅስህ ተበሎ ሲጠየቅ እንዲህ አለ ፦
" ይህን የአላህን ንግግር አስታውሼ ነው
{ وَحِيلَ بَيْنَهُمْ وَبَيْنَ مَا يَشْتَهُونَ }
«በእነርሱና በሚፈልጉት መካከል ተጋረደ»
ከዚህም የጀሀነም ሰዎች ቀዝቃዛ ዉሀን ከመጠጣት ዉጭ ሌላ ነገር እንደማያምራቸው ተረዳሁኝ … አላህም እንዲህ ይላል ፦
{ وَنَادَىٰٓ أَصْحَٰبُ ٱلنَّارِ أَصْحَٰبَ ٱلْجَنَّةِ أَنْ أَفِيضُوا۟ عَلَيْنَا مِنَ ٱلْمَآءِ أَوْ مِمَّا رَزَقَكُمُ ٱللَّهُ ۚ قَالُوٓا۟ إِنَّ ٱللَّهَ حَرَّمَهُمَا عَلَى ٱلْكَٰفِرِينَ }
« የእሳትም ሰዎች የገነትን ሰዎች «በእኛ ላይ ከውሃ አፍስሱብን ወይም አላህ ከሰጣችሁ ሲሳይ (ጣሉልን)» ብለው ጠሩዋቸዋል፡፡ እነርሱም «አላህ በከሓዲዎች ላይ እርም አድርጓቸዋል» ይሏቸዋል፡፡ » "
【አል አዕራፍ 50】
الزهد للإمام أحمد : 1055
287
ለፈገግታ ያህል
አንድ ሰው አራት ሚስቶች ነበሩት ። ሊካሰሱ ፍርድ ቤት ቀረቡ ። በጣም ሲንጫጩ ዳኛው " ከመካከላችሁ ታላቋ ትናገር " ሲል ፀጥታ ሰፈነ። እስካሁን የጉዳዩ ፋይል ተዘግቷል !
አንድ ሰውዬ ሙሉ ነዋሪዎቿ ሴት በሆኑባት ደሴት ላይ አረፈ ይባላል ። ከዛም ሴቶቹ ሊገድሉት ወሰኑ ። "የመጨረሻ ኑዛዜህ ምንድን ነው? " ሲሉት " ከእናንተ መካከል አስቀያሚ የምትባሏ ሴት ትግደለኝ " ይላል ።
. ይህ ሰውዬ በሕይወት ቆይቶ ከእነሱም አራት ሴቶችን አግብቶ በሰላም ኖረ !
📒 كن حكيما مع النساء
አንድ በእድሜ የገፉ ሽማግሌ ተጠየቁ " እርሶ 80 አመቶት ነው። ግን እስካሁን ድረስ ባለቤቶትን " ውዴ ፣ ህይወቴ …" እያሉ ነው የሚጠሩት ። ሚስጥሩ ምንድን ነው? "
ይህ ሽማግሌ ምን ቢሉ ጥሩ ነው
. " ስሟን ረስቼው መጠየቅ ፈርቼ ነው !! "
287
الكذاب
ሙሰይለማህ በረሱል ﷺ ለመመሳሰል ይሞክር ነበረና ረሱል ﷺ ደረቅ ጉድጓድ ላይ ተፍተው ውሀ እንደፈለቀ ሲሰማ እሱም የውሀ ጉድጓድ ላይ ሲተፋ ውሀው ጨው ጨው አለ
አይኑን ለታመመ ሰው ዱዓ አደርጋለው ብሎ አይኑን ሲያብሰው ሰውዬው አይኑን ታውሮ እርፍ !!
📒 البداية والنهاية 7/37 مقتل مسيلمة الكذاب
287
ያንተ ሪዝቅ ምናልባት ከምንም አይነት በሽታ ነፃ ሁነህ ጤነኛ መሆንህ ሊሆን ይችላል…
ወይም ለምትሰራቸው ጥፋቶችና ወንጀሎች የአላህ ሲትር ሊሆን ይችላል…
ወይም ባሮቹ ዘንድ ተቀባይነት እንዲኖርህ ሊያደርግ ይችላል…
ወይም በፍቅር የተሞላ ቤተሰብ የሰጠህ ሊሆን ይችላል…
ወይም ጠቃሚ የሆነ እውቀትን ሰጥቶህ ሊሆን ይችላል…
የአላህ ሲሳዮች ብዙ ናቸው … በገንዘብና በቁሳዊ ነገሮች ብቻ የሚገደቡ አይደሉም ።
አላህ በውሳኔዎቹ ላይ መደሰትን ከለገሰህ …ሁሉም ነገር ጥሩ ሪዝቅ ሁኖ ይታይሀል ።
በአላህ ውሳኔ መደሰትን ያጣህ እንደሆነ… ዱንያን በአጠቃላይ ብትይዝ እንኳ አትደሰትም።
ለአንተ የተወሰነ ነገር ከሆነ በሁለት ተራሮች መካከልም ቢሆንም ይመጣልሀል…
ለአንተ ያልተወሰነ ነገር ከሆነ ደግሞ በእጆችህ መካከል ቢሆንም እንኳ አይሆንህም …
ለአንተ የተፃፈ ነገር ከሆነ በእርግጥም ደካማ ብትሆንም እንኳ ታገኘዋለህ …
ሲጀመርም ለአንተ ያልሆነ ነገር ደግሞ ጠንካራ ብትሆንም እንኳ አታገኘውም…
አላህ ለአንተ የከፈተውን በር የሰው ልጆችም አጋንንትም ቢተባበሩ አንኳ ሊዘጉብህ እንደማይችሉ አውቀህ ህይወትህን ተረጋግተህና በአላህ ተማምነህ ኑር !!!
https://t.me/mengdengaw
287
አንድ ባል ሚስቱን ይዞ አዲስ መኖሪያ ቤት ይቀይራሉ ። ወደ አዲሱ ቤት በገቡ በንጋታው ቁርስ እየበሉ ሚስት ወደ ቤታቸው መስኮት እያመላከተች ለባሏ እንዲህ ትለዋለች ፦
" የጎረቤታችን የልብስ አስተጣጠብ ተመልከት ! ምንም'ኮ አልፀዳም! ይሄኔ ርካሽ ማጠቢያዎችን እየተጠቀመች ይሆናል !!! " ትላለች
ታድያ ይች ሴት ጎረቤቷ ልብስ ባጠበች ቁጥር ይህንን ትችት ሁሌ ትደጋግም ነበር ።
ከእለታት አንድ ቀን የጎረቤቷ ልብስ ፀድቶ ሲሰጣ ተመለከተች ። በጣም በመገረምም ለባሏ ለመጀመሪያ ጊዜ የጎረቤቷ ልብስ በጥሩ ሁኔታ ታጥቦና ፀድቶ እንዳየች ስትነግረው ባሏ እንዲህ ሲል መለሰላት፦
" ዛሬ እኔ በጠዋት ተነስቼ የምትመለከችበትን የቤታችንን መስኮት አፅድቼው እኮ ነው !!! " አላት
ጭብጡ…
እኛ ብዙ ጊዜ ነገራቶችን የምንመለከተው በእውነታው ሳይሆን እኛ መመልከት በምንፈልገው መልኩ ብቻ ነው።
የሰዎች ነውር በመከታተል የተጠመደ የራሱን ነውር ይዘነጋል ። የራሱን ክፍተት በመሙሏት የተወጠረ የሰዎችን ክፍተት ለመከታተል ጊዜ አይኖረውም ። ስለዚህ ቀድመህ የራስህን ክፍተት በመሙላት ተጠመድ !!!
#አድ እያደረጋቹ አህባብ
ሁላችንም አላህ ለኸይር ነገር ከፋች ያድርገን
287
ኢብነልጀውዚ ረሒመሁሏህ እንዲህ አሉ:–
𒊹︎︎︎« ሰያር ረሒመሁላህ ሪያህ ረሒመሁላህ እንዲህ ማለቱን ዘገበልኝ: –
ሪያህ:– “ አንዲት እንስት ተጠቆምኩኝ እናም አገባህዋት።
☞︎︎︎ሁሌም ኢሻን ሰግዳ እንደጨረሰች ሽቶ ላይዋ ላይ ትነሰንስና፤ ራሷን በእጣን አጥና (ተቆነጃጅታ) ምርጥ ልብሷን ትለብስና ወደኔ በመቅረብ ...
“አንዳች ፍላጎት አለህን?” ብላ ትጠይቀኛለች። መልሴ “አዎን” ከሆነ አብራኝ ትቆያለች “አይ” ከሆነም ምርጡን ልብሷን ትቀይርና እስከ ንጋት ድረስ በሰላት ታሳልፋለች።»
𒊹︎︎︎ሪያህ እንዲህ ሲል ይጨምራል :–
« በአላህ ይሁንብኝ! በጣም ነው ያስደሰተችኝ!»
[ሲፈቱ ሰፍዋህ ገፅ:116]
287
ኢብኑል ቀይም ረሂመሁሏህ የብዙ ሰዎችን ሁኔታ ሲገልፅ እንዲህ ይላል
የሚገርመው ነገር አንድን ግለሰብ ሰዎች የዲን ሰው ዛሂድ እና ዓቢድ ነው ብለው እስከሚጠቋቆሙበት ድረስ
ራሱን ሀራም የሆነን ነገር ከመብላት መጠበቅን፣ ሰዎችን ከመበደል መራቅን ከስርቆት እና ከኸምር መጠጥ ራስን ማቀብን፣ መጥፎን ከመመልከት እና ሌሎችን ወንጀሎችን ከመዳፈር ራሱን ከዚህ ዓይነት ነገር በቀላሉ ሲጠብቅ ነገርግን የምላሱን እንቅስቃሴን መጠበቅ ላይ በጣም ይከብደዋል
አላህን የሚያስቆጡ ነገራቶችን ምንም ቦታ ሳይሰጣቸው ሲናገር ይስተዋላል
በአንዲት ንግግር ምክንያት ከምስራቅ እስከ ምዕራብ ርቀት ያህል ወደታች ይምዘገዘጋል
ስንትና ስንት ሰው ታያለህ ራሱን ከአስቀያሚ ወንጀሎች እና በደሎች አርቆ ግርማ-ሞገስን የተላበሰ ምላሱ ግን በህይወት ያለውንም የሞተውንም ሰው ክብር ላይ የሚረማመድ ለንግግሩ ቦታ የማይሰጥ!
الداء والدواء (366 - 367)]
አላህ ሆይ አንተን የምታወሳን እውነተኛ የሆነች ምላስን፣የፀዳች ልብን፣የተስተካከለች ስነ-ምግባርን በእዝነትህ እንድለግሰን እንማፀንሃለን!🤲
