en
Feedback
Tadele Tibebu - ታደለ ጥበቡ

Tadele Tibebu - ታደለ ጥበቡ

Open in Telegram

ማንኛውንም ሀሳብና አስተያየት በዚህ ሊንክ መላክ ይችላሉ @Tadeletibebut

Show more
Ethiopia510The category is not specified

📈 Analytical overview of Telegram channel Tadele Tibebu - ታደለ ጥበቡ

Channel Tadele Tibebu - ታደለ ጥበቡ (@tadeletibebu) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 52 631 subscribers, ranking in the Other category and 510 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 52 631 subscribers.

According to the latest data from 02 December, 2024, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 0 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
ማንኛውንም ሀሳብና አስተያየት በዚህ ሊንክ መላክ ይችላሉ @Tadeletibebut

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 03 December, 2024), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Other category.

52 631
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
በዐማሮች ኤሊቶች ላይ አፈናው (abduction)፣ ያለፍርድ እስራት (Arbitrary Arrest)፣ እና ስቃዩ (torture) ቀጥሏል። ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ምሽት ሁለት ሰዓት አፍነው ወስደውታል። በነገራችን ላይ የኦሮሚያ ብልፅግና አፋኝ ቡድን አቋቁሟል። ስሙም "ORO abbichuu team" ይባላል። ሥራቸው ሁለት አይነት ነው። የመጀመሪያው የአማራ ተወላጆችን መለየት፣ ባለሥልጣን ከሆኑ እስከ ቢሮ የስለላ መረብ መዘርጋት፣ ግለሰብ ከሆኑ ስውር ክትትል ማድረግ፣ እንዲመታ የሚፈልጉትን የአማራ ተወላጅ አስቀድሞ መፈረጅ ወይንም ስም መስጠት፣ የአማራ ተወላጅ የሆኑ ንብረቶችን ሆቴሎችን መለየት፣ ከዛም ለጥቃት ዒላማ ማመቻቸት ሲሆን፣ ሁለተኛው ሥራቸው ደግሞ የመጀመሪያው ግሩፕ በሚሰጣቸው መረጃ ተመስርተው ኃይል በመላክ ማሳፈን አለበለዚያ ማስወገድ ነው። ይህ አፋኝ ቡድን በዋነኝነት የሚመራው የኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ኃላፊ ኃይሉ አዱኛ ሲሆን፣ አደረጃጀቱ ከኦሮሚያ ብልፅግና፣ ከክልሉ ፀጥታ ቢሮ፣ ከአክቲቪስቶች፣ የኦሮሞ ተወላጅ ሆነው በፌዴራል ፀጥታ ቢሮዎች የሚሰሩ የተቀናጁበት ነው። የቡድኑ ዓላማ ባጭሩ የኦሮሞ ደም (oromo genetic make up) የላቸወም በሚሏቸው የአማራ ሆነ የሌላ ነገድ ተወላጅ ኢሊቶችን ማጥቃትና ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖትን ማዳከም ነው። ሰሞኑን እንኳን ታፍነው ከጠፉት ወንድ ወንድሞቻችን መካከል፦ ➼ አወቀ ስንሻው፣ ➼አብርሃም መልካሙ፣ ➼ ኤርሚያስ መኩሪያ ➽ ኤዶሚያስ ጥሩነህ ይገኙበታል። ኤርሚያስ መኩሪያ አሁን እንዳረጋገጥሁት የታሰረው ሳር ቤት በሚገኘው የመከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ መምሪያ ቅጥር ግቢ ውስጥ ሲሆን ከሱ ጋር ከ20 በላይ ዐማራዎች ታስረዋል። በቦሩ ሜዳ ጉባኤ ቤት ጉባኤ በመዘርጋት በርካታ ሊቃውንት ያፈሩት መምህር ኃይለ ማርያም ዘውዱ ከባህርዳር ወደ አዲስ አበባ ታፍነው ከተወሰዱ በኋላ የተገኙት ፌዴራል ወንጀል ምርመራ ቢሮ ውስጥ ነው። እኒህ ሊቅ እንደሚታሰሩ ወይ እንደሚገደሉ ብልፅግና በወርሀ ግንቦት በ2014 ዓም ለከፍተኛ እና መካከለኛ ካድሬዎቹ ባዘጋጀው የሥልጠና ሰነድ ላይ ስማቸውን ጠቅሶት ነበር።

photo content
+4

ገዳመ ወንያት አቡነ ሐራ ድንግል ዓመታዊ ክብረ በዓል በዚህ መልኩ ተከብሯል። በዛሬው ቀን ግንቦት 11 ቀን የአቡነ ሐራ ፀበል ተባርኮ አገልግሎት መስጠት የጀመረበት ቀን በመሆኑ ይህንን ምክንያት በማድረግ ብዙ ህዝብ ከተለያየ አካባቢ መጥቶ በዓሉን አክብሯል። ገዳሙ ከባህር ዳር ከተማ ሰሜን ምሰራቅ አቅጣጫ 17 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምዕ/ጎጃም ዞን ባህር ዳር ዙሪያ ወረዳ ላጉና ቀበሌ አስተደደር ውስጥ የሚገኝ ሲሆን፣ የተመሰረተው በ1574 ዓ.ም በፃድቁ በአቡነ ሐራ ድንግል ነው። ስለዚህ ገዳም ፈዋሽነት፣ ራሴን እንዴት ከሳይነስ እንዳዳነኝ፣ ፀበሉ ዓይነስውር የነበረ ሰው እንዴት አይኑ እንደበራለት ከዚህ በፊት በዝርዝር የጻፍኩት በዚህ ሊንክ ታገኙታላችሁ https://www.facebook.com/112841945777908/posts/1762202944175125/?app=fbl

የሚዳኙት በአፋን ኦሮሞ ነው። በቋንቋቸው አይማሩም። የሚማሩት በአፋን ኦሮሞ ነው። በፍርድ ቤት በአስተርጓሚ ነው የሚናገሩት። በቋንቋው የራሳቸው ልዩ አስተዳደር የላቸውም። በቋንቋቸው ባህላቸውን እንዲያሳድጉ አልተፈቀደላቸውም። የዐማራ ባህል፣ ስነቃል፣ ትውፊት፣ ታሪክ ወዘተ... ህገመንግስታዊ ዕውቅና የለውም። በኦሮምያ ክልል የሚኖረው ዐማራ በቋንቋ የመፃፍ፣ የመናገር፣ የመቃወም፣ በነፃ የመደራጀት ወዘተ...መብቶች ህገ መንግስታዊ ዕውቅና የለውም። ከሳሽም ተከሳሽም በነፃነት በፍርድ ቤት ፊት በቋንቋቸው አይከራከሩም። በአማራ ክልል፣ ኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን ግን የአገሪቱም ሆነ የክልሉ የስራ ቋንቋ አማርኛ ሆኖ እያለ የስራ ቋንቋ ኦሮምኛ ነው። ይህም ማለት ዐማራው በራሱ በክልሉ እንኳን በአማርኛ መንግስታዊ አገልግሎት ማግኘት አይችልም። በከሚሴ፣ በባቲ፣ በሰንበቴ፣ በጨፋ ሮቢት … ወዘተ የሚኖሩ ዐማሮች በአማርኛ አገልግሎት አያገኙም። በአማራ ክልል ባለው የኦሮሚያ ልዩ ዞን ዐማሮች እያስተረጎሙ ነው አገልግሎት የሚያገኙት። የክልሉን ሆነ የአገሪቱን ህገመንግስት በሚጻረር መልኩ ኦሮምኛ ቋንቋ ለስራ ቋንቋ ሲፈቅድ አማርኛ ቋንቋ ቢያንስ እኩል የሥራ ቋንቋ እንዲሆን አልተደረገም። እንግዲህ በጅማት ላይ የሚቃኙት የትግራይና የኦሮሞ ብሔርተኞች (competing ethnic nationalists) በእኩልነትና ፍትሐዊነት ስም ይማላሉ፣ እንደ ቅዱስ መና የሚያዩት ሕገ መንግሥት መከበርና ስለ ፌደራላዊ ሥርዓት አስፈላጊነት አበክረው ይሰብካሉ። ሥራቸው በተግባር ሲታይ ግን እንደነሱ አግላይ (exclusionary)፣ ፌዴራሊዝም የሚሰጠውን መብት ገፋፊ እና አሕዳዊ ሥራዓት አራማጅ ተፈልጎ አይገኝም። በነሱ ትርጉምና መስፈርት ፌዴራሊዝም ማለት ለማንነት እውቅና መስጠትና ራስን በራስ ማስተዳደር ነው። በክልላቸው ለሚኖሩት ብሔር ብሔረሰቦች ግን ለማንነታቸው እውቅና እንዲሰጣቸው፣ ራሳቸውን በራስ እንዲያስተዳድሩ አልፈቀዱም። ከኦሮሞ ውጪ በክልሉ የሚኖረው የዐማራ፣ የዛይ፣ የጨቦ፣ የገባቶ፣ የውርጂ፣ የባንቱና ሌሎችም አውራ የሆነው የኦሮሞ ባሕል፣ ቋንቋ፣ ግዛትና አሰራር ተጭኖባቸው፣ ተጨፍልቀው በጭቆና እንደነሱ አባባል በአሃዳዊነት እንደሚኖሩ ይረሱታል። ነገርግን እንደ መጽሐፍ ቅዱስና እንደ ቅዱስ ቁርዓን መነካት የለበትም የሚሉት ህገ-መንግስት እንዳይሻሻል የማይፈልጉበት ዋነኛው ምክንያት ዐማራን በጠላትነት ፈርጆ እንዲገደል ስለመቻቸላቸው ነው። ህገ መንግቱ የክልል ሐብት ለክልሉ ብሔር ብቻ የሚል ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ቀውስ አመንጭቶ ዐማራው ተረጋግቶ ቋሚ ንብረት እንዳያፈራ ስላደረገላቸው ነው። በኦሮሚያ ክልል የሚኖሩት ብሔር ብሔረሰቦች ለማንነታቸው እውቅና እንዳይሰጣቸው ይልቁንስ፣ በኢትዮጵያ ደም የታጠበች፣ በኢትዮጵያ እንባ የጠቆረች "ንፁህ ኦሮሚያን" ለመፍጠር ለያዙት ፕሮጀክት እነዚህ ብሔረሰቦች "መጤ" እያሉ "ከአገረ-ኦሮሚያ" ነቅሎ ለማጥፋት (Intensive De-Amharization Programme) ነው። ሌላ ዓላማ የለውም!

#ሼር_ፖሽት ይሁን! *ስሞኑን የሀገርና የማኅበረሰብ የክፋት ጭንቅላት የሆኑት ወያኔና ኦነግ "ሰናፌ" ላይ አርቅቀው በ1987 ዓ.ም. ያጸደቁት ህገ መንግስት "ይሻሻላል" መባሉን ተከትሎ ጥላቻን፣ ልዩነትን፣ አክራሪ ብሔርተኝነትን፣ ማንአህሎኝነትን፣ እብሪትን፣ ግጭትን፣ በመለፈፍ፣ በመስበክ፣ በመቀስቀስ የሚታወቀው የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትዎርክ (OMN) የሚባለው የዘር ማጥፋት ሚዲያ (genocidal Media) በዐማራ ህዝብ ላይ ያነጣጠረ እስከዛሬ በዐማራ ሕዝብ ላይ ያነጣጠረ አሳሳች (misleading)፣ የተፈበረኩ (fabricated)፣ ለምድ ለባሽ (Imposter)፣ አላግባብ የተተረጎሙ (manipulated) ይዘቶችና ፕሮፖጋንዳዎች በማስተላለፍ ላይ ይገኛል። ዘመቻውን የከፈተው "አሃዳዊ" የሚል ስያሜ በመስጠት ነው። በህገመንግስቱ መሻሻል ዙሪያ ምሁራን ተብየዎችን በመጋበዝ በሚያደርገው የዶንቆሮዎች ውይይት (dialogue of the deafs) "አሃዳዊ" የሚለውን ቃል ሲደጋግሙት ይሰማል። ኧረ ለመሆኑ ማን ነው አሃዳዊ? እውነታውን እንመርምረው እስቲ.... 1ኛ. በ1987 ዓ.ም.ህገ መንግስቱን ከማርቀቁ ጀምሮ እስከ ማፅደቁ በነበረው ሂደት ዐማራውን በማግለል (excluding the Amhara) ነበር። የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት (self determination) እስከ መገንጠል የሚል ኮሚኒስታዊ መርህ አርቅቀው ሲያፀድቁ ዐማራ አልነበረም። "ተጨቆኑ" የሚሏቸውን ብሔሮች "ነጻ የሚያወጣ" ያልተገደበ መብት የሚሰጥ ሕገመንግሥት ሲቀርፁ ዐማራ አልነበረም። ስለሆነም ህገመንግስቱ የሕወሓትና ኦነግ የጋራ ሰነድ እንጂ ዐማራ የወሰነበት አይደለም። ሁለቱ አሸባሪዎች የጋራ ዓላማዎቻቸውና እምነቶቻቸው ማስፈፀሚያ ይሆናል ብለው ቃል ኪዳናቸውን ያፀኑበት ደም ያዘለ ሰነድ ነው። ሁለቱ የዐማራ ጅቦች ሕወሓት እና ኦነግ በጋራ ዐማራውን ለማጥፋት የወሰኑ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የሥታሊን ዶግማ ነው። ሁለቱ አፍሪካ ለቅርጫ መሥዋዕት እንደቀረበችበት የበርሊን ጉባኤ ስምምነት (General Act of the Berlin Conference) በደመኛ ጠላትነት የፈረጁትን ዐማራን ለመበታተን፣ ለማዋረድ (humiliation) ለማዳከምና ወደ አናሳነት ለመቀየር የተስማሙበት የጋራ ውል ነው። 2ኛ .ዐማራን በማግለል የተደነገገውን ህገ መንግስታዊ በመንተራስ የተነደፉ የክልሎች ሕገመንግሥት ብንመለከት በዐማራ ላይ ያነጣጠሩ ናቸው። ሁሉም ሕወሓት "አማራ ክልል" ብሎ ከፈጠረው ክልል ውጪ ለሚኖሩት በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ዐማሮች ሕገ መንግስት ተብየው ካስቀመጠው መርሆ በተቃራኒ ለዐማሮች በቂ ሕጋዊ፣ አስታደራዊና ፖለቲካዊ መብት አይሰጡም። ለምሳሌ፦ የኦሮሚያ ህገ መንግስት በቅድሚያ የበቀል ጡንቻው ታርጌት ያደረገው በክልሉ የሚኖሩ ዐማሮችን ነው። ምዕራፍ 2. አንቀጽ 8. እንዲህ ይላል፣ "የኦሮሞ ህዝብ የክልሉ የበላይ ሥልጣን ባለቤት ሲሆን፣ የህዝቡ የበላይነትም የሚገለጸው በሚመርጣቸው ተወካዮችና ራሱ በቀጥታ በሚያደርገው ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎ ነው" ይህም ማለት በአዲሱ "ኦሮምያ" ክልል ውስጥ የበላይ ሥልጣን ባለቤትነቱ ለኦሮሞ ብቻ ነው። በ1987 ዓ.ም. የሕዝብና የቤቶች ቆጠራ ውጤት መሠረት በኦሮሚያ ክልል ከሚኖረው 18, 732, 525 ሕዝብ መካከል 9 ከመቶ የሚሆነው የዐማራ ነገድ መሆኑን እና ይህም በክልሉ ከሚኖሩት ነገዶች መካከል ከኦሮሞው ቀጥሎ በሕዝብ ብዛት በሁለተኛ ደረጃ እንደሆነ ያሣያል። በዚህ ሠላሳ ዓመት ውስጥ የህዝቡ ቁጥር ከ15-20 ሚሊዬን በላይ ያድጋል ተብሎ ይጠበቃል። እንግዲህ ይህን ያህል የዐማራ ማኅበረሰብ በክልሉ እየኖረ በ1994 ዓ.ም. የተሻሻለው የኦሮሞ ክልል ሕገ-መንግሥት ግን ኦሮሞን ብሔር ከማለት ውጭ ዐማሮችን እንደሌሉ ቆጥሮ ምንም ዓይነት እውቅና አይሰጣቸውም። ህልውናቸው በኦሮሞ ፖለቲከኞች መልካም ፈቃድ ላይ ብቻ የተመሠረተ ነው። እኩል የመኖር፣ የመመረጥና የመምረጥ መብት የላቸውም። በኦሮሚያ ከልል ምክር ቤት ውስጥ ውክልና የላቸውም። ራስን በራስ ማስተዳደር (self-Rule) አይችሉም። እንደሌለ ተቆጥረው የዐማራ ብሔረሰብ ልዩ ዞን አልተቋቋመላቸውም። ሀገር አልባ ናቸው። መብት አልባ ናቸው። ነፃነት አልባ ናቸው። ሰብአዊ ክብር አልባ ናቸው። ተወካይ አልባ ናቸው። የህግ ከለላ የላቸውም። 3ኛ. በአንጻሩ፣ አማራ ክልል ባላጸደቀው ህገመንግስት ተመሥርቶ በክልሉ ለሚኖሩ ጎሣዎች ራሳቸውን በራሳቸው እንዲያስተዳድ የልዩ ዞንና ልዩ ወረዳ መብቶችን አጎናጽፏል። በንፅፅር እንመልከተው። በኦሮምያ ክልል ከ20 ሚሊዮን ያላነሰ ዐማራ ይኖራል። የልዩ ዞንና ወረዳ መብት ግን አልሰጣቸውም። ደራ 85% ፍፁም ዐማራ ነው። በልዩ ወረዳ ወይንም በልዩ ዞን ግን አልተቋቋመም። በአንጻሩ፣ በአማራ ክልል ውስጥ የኦሮሞ ብሔረሰብ ድርሻ ከክልሉ ሕዝብ 2 ከመቶ በታች ቢሆንም፤ "የኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን" የሚል አጥር ግን ተፈጥሯል። ዐማራው ህገ-መንግሥቱን አርቅቆ ሳያፀድቅ አንቀጽ 39 "ማንኛውም ብሔረሰብ ራሱን ያስተዳድራል" የሚለውን ግን ተግባራዊ አድርጓል። ዐማራው ግን በያለበት ራስ ገዝ እንዲሆን፣ በዘጠኙም ክልሎች ሆነ በፌዴሬሽን ምክር ቤት መንግሥታዊ ውክልና እንዲኖረው፣ በዞን እና በልዩ ወረዳ እንዲደራጅ፣ በቋንቋውና በባህሉ እንዲጠቀም አልተፈቀደለትም። በአሃዳዊነት የሚከሰሰው ዐማራ ደግሞ በተግባር ሲታይ ፌዴራሊዝምን በተግባር አረጋግጧል። በ1994 የተሻሻለው የአማራ ክልል ህገ-መንግሥት "እኛ የአማራ ብሔራዊ ክልል ሕዝቦች" ብሎ ነው የሚጀምረው፣ የኦሮሚያ ክልል ህገ-መንግሥት ግን "እኛ የኦሮሞ ሕዝብ" ብሎ ይጀምራል። ልዑላዊ ሥልጣን ለሁሉም የክልሉ ነዋሪዎች አድርጎ የሚደነግገው የአማራ ክልል ህገ-መንግሥት ብቻ ነው። በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ በተከለለው የኦሮሞ ብሄረሰብ አባላት ባህላቸው፣ ወጋቸው፣ ቋንቋቸውና ማንነታቸው ተጠብቆ እየኖሩ ናቸው። በኦሮምኛም ትምህርት በተለየ መልኩ ይሰጣል። ፌደራሊዝም በሚደነግገው መሠረት በኦሮምያ ሆነ በሌሎች ክልሎች የሚኖሩ ዐማሮች ደግሞ ባሉበት አካባቢ የራሳቸውን ዕድል በራሱ እንዳይወስኑ፣ ማንነታቸው ተጠብቆ፣ ባህላቸውንና ቋንቋቸውን እንዳያሳድጉ፣ በቋንቋቸው እንዳይዳኙ ተጨፍልቀው ይገኛሉ። የኦሮሚያ ክልል ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 5 ላይ፣ "ኦሮምኛ የስራ ቋንቋ ይሆናል" በማለት በክልሉ ውስጥ በሚሊዮኖች የሚናገሩትን የአማርኛ ቋንቋ እውቅና አይሰጥም። ይህም ማለት በኦሮሚያ የሚኖሩ የዐማራ ተወላጅ ነዋሪዎች ከሚደርስባቸው አስተዳደራዊና ፖለቲካዊ ጫና (acculturation and forced assimilation) ጥቃቶች አንዱ የቋንቋ ተፅዕኖ ነው። ለምሳሌ፣ በ1987 ቆጠራ መሠረት የአዳማ ወረዳ ነዋሪዎች ከተሞቹንና ገጠሮቹን ጨምረን 55% ነዋሪዎች የአፍ መፍቻ ቋንቋቸው አማርኛ ነው፡፡ የአፍ መፍቻ ቋንቋቸው ኦሮምኛ የሆኑት 35% ብቻ ናቸው፡፡ እንደዚሁም የፈንታሌ ወረዳ ኦሮሞኛ የአፍ መፋቻ ቋንቋቸው የሆኑ 39% ብቻ ናቸው፡፡ 61% የሚሆነው ኦሮምኛ ተናጋሪ አይደለም፡፡ በሰላሌ ፍቼ ጎሃ ጽዮን፣ ዋሻ ሚካኤል፣ ግንደበረት፣ በደራና በግራር ጃሮስ ነዋሪው አማርኛ የአፍ መፍቻ ቋንቋው ነው፡፡ ነገርግን በቋንቋቸው አይዳኙም።

photo content
+9

#ሼር_ፖስት! አማርኛ ቋንቋ እንደሆነ የራሡ የሆነ ሥርዓተ ድህፈት (Orthography) ያለው፣ ከፍተኛ የሆነ የሰዋሠው (Grammar) እና የሥነ-ልሣን (Linguistics) ጥናትና ምርምር የተደረገበት፣ በአፍሪካ ምድር በስነ ጽሁፍ ሀብት የበለጸገ ብቸኛውና ነባር ዓለምአቀፍ ቋንቋ ነው። 👉 ከትግራይ ሥርዓተ ትምህርት ብታስወግደው በ2007 ዓ.ም.የአፕል የቴክኖሎጂ ማዕከል አማርኛን ከዓለም ግዙፍ ቋንቋዎች ተርታ መድቦ የቴክኖሎጂ ቋንቋ አድርጎታል። 👉 አማርኛን ከትግራይ ብትፍቀው በ2008 ዓ.ም. የጎግል የቴክኖሎጂ ማዕከል የመተርጎሚያ ቋንቋ አድርጎታል። 👉እንዲያው አዲስ የጫጉላ ሽርሽር ሆናባችሁ እንጂ አማርኛ በUS አሜሪካ የመንግስት ቋንቋም ነው። በአሜሪካዋ ቨርጂኒያ ግዛት አሌክሳንድሪያ ዳሽ የሚባለው የከተማ አውቶቢስ ላይ "እንኳን ወደ #WESTEND በደህና መጣችሁ!" የሚል ጽሁፍ ማየትም የተለመደ ነው። 👉Dstv'ም የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና፣ የኦሊምፒክ ውድድሮችን ጨምሮ የእንግሊዝ ኘሪሚየር ሊግ ፣ የስፔን ላሊጋ ፣ የጣሊያን ሴ ሪ ኤ እንዲሁም ቻምፒየንስ ሊግ ጨዋታዎችን በአማርኛ ቋንቋ እንዲተላለፉ ከወሰነ አመት አስቆጥሯል። 👉ከጀርመን ታዋቂ ከሆኑት ዩኒቨርስቲዎች አንዱ የሆነው ሀምቡርግ ዩንበርሲቲ የአማርኛ ት/ ት ማስተማር ከጀመረ መቶ ዓመት አልፎታል። 👉ቻይና አማርኛ ቋንቋን በመጀመሪያ ዲግሪ እያስተማረች ነው። ትምህርቱ እየተሰጠ ያለው በቤጂንግ የውጭ ጥናት ዩኒቨርስቲ (BFSU) ነው። 👉በቅርቡ ደግሞ የፑቲን ሀገር ሩሲያ የአማርኛን ቋንቋ በሩሲያ ትምህርት ቤቶች ማስተማር ልትጀምር መሆኗን ይፋ እንዳደረገች የምናስታውሰው ነው። እነዚህ የግንጠላ አራማጅ ዘውጌዎች ተፈራረሙ አልተፈራረሙ የሚመጣ ለውጥ የለም። ከትግራይ ሥርዓተ ትምህርት ተወገደ አልተወገደ የሚጎዳቸው እራሳቸውን እንጂ ማንንም አይጎዱም። አማርኛ እንደሆነ እንደ ሰሜን አሜሪካ የመሣሠሉ ታላላቅ ሀገሮች ውስጥ በኦፊሻል ቋንቋነት መንግሥታት እየተቀበሉት የመጣ ቋንቋ ነው።አሜሪካ ከ500 ሺህ በላይ ተናጋሪ ላለው ለተጨማሪ የሥራ ቋንቋነት በማጨት ከ10 ዓመት በፊት ነበር አማርኛ በተለያዩ የአሜሪካ ግዛቶች የሥራ ቋንቋ እንዲሆን ያደረገችው። እነዚህ ስብስቦች ግን ከኢትዮጵያ ለመሸሽ የግእዝ/አማርኛን ፊደል በመጤ የላቲን ፊደል የተኩ የማ*ህ*ይ*ም መጨረሻዎች ናቸው። የኦሮምኛ ቋንቋ አህጉር ተሻግሮ በመጣ የላቲን ፊደል እንዲተካ የተደረገው በ1984 ዓ.ም. ነው። ይህን ያደረጉት የግዕዝ/አማርኛ ፊደል የዐማራ ብቻ ስለመሰላቸውና በዐማራ፣ በአማርኛና በግዕዝም ላይ በነበራቸው ጥላቻ የተነሣ ነው። ዛሬ በአለም ላይ የራሳቸው የሆነ የጽህፈት ስርዓት ወይም ፊደላት አላቸው ከሚባሉት ቻይና፣ ሕንድ፣ ፋርስ፣ ግሪክ፣ ሮም፣ እስራኤል፣ ባቢሎን እና ግብፅ መካከል ኢትዮጵያ አንዷ የሆነችው ግእዝ ከሚናገሩ አግዓዝያን እና አማርኛ ከሚናገሩ ዐማራዎች የተገኘ ነው። የግዕዝ ፊደል የሚባሉት 24ቱ' ፥ሀ፥ ለ፥ ሐ፥ መ፥ ሠ፥ ረ፥ ሰ፥ ቀ፥ በ፥ ተ፥ ኀ፥ ነ፥ አ፥ ከ፥ ወ፥ ዐ፥ ዘ፥ የ፥ ደ፥ ገ፥ ጠ፥ ጸ፥ ፀ፥ ፈ፥ ናቸው። እነዚህ የግዕዝ ፊደል ኆኅያት ለአማርኛ ቋንቋ በቂ ሆኖ ስላልተገኘ የዐማራ የትምህርቱ ኀላፊዎች ከግእዝ ፊደል ተጨማሪ ምልክትና ተጨማሪ ኆኄያትን መፍጠር ስላስፈለጋቸው፣ የኆኄዎች ምንጮች የቶቹ የግዕዝ ኆኄዎች እንደሆኑ አጥንተው ፦ ግዕዝ አማርኛ ከ “ደ” “ጀ”ን ከ“ጠ” “ጨ”ን ከ“ሰ” "ሸ”ን ከ"ነ" ”ኘ”ን ከ “ተ” “ቸ” ን ከ"ከ" "ኸ"ን ከ"ዘ" "ዠ"ን አስወለዱ። እነዚህ ሰባት ግንደ ፊደላት ከእንዚሮቻቸው ጋር ሲደመሩ 49 ይሆናሉ። የኢትዮጵያ የፊደላት ቁጥር ከግዕዝ ኆኄዎች 24'ቱ ከግሪኮች ኆኄዎች 2'ቱ ፊደላት ከአማርኛ ኆኄዎች 7' ቱ ፊደላት ተደምረው ወደ 33 ኆኄዎች ሊያድግ ችሏል። ኢትዮጵያ በነዚህ ፊደላት አማካኝነት ልጆቿን አስተምራለች፣ ለወግ ለማዕረግ አብቅታለች፣ ታሪኳንና ማንነቷን ፅፋበታለች፣ ነገሥታቶቿ እና ደራሲዎቿ አያሌ ጉዳዮችን ፅፈውባቸዋል። የኢትዮጵያ የማንነት ሐውልት የተገነባውና የቆመው በእነዚህ ፊደላት ነው። እንደ አኩስም፣ እንደ ላሊበላ፣ እንደ ጎንደር ኪነ-ሕንፃዎች አባቶቻችን ያወረሱን ድንቅዬ ቅርሶች፣ የማንነታችን መገለጫ ሀብቶች ናቸው።

photo content
+9

photo content
+9

ዐማራ ሆይ! ይህቺ ከንቱ ምድር ለበጎዎች ተመችታ አታውቅም፡፡ ይህቺ ምድር እንደ ፈሪሳውያን ላሉ ቀጣፊዎች፣ እንደ ይሁዳ ላሉ ከሃዲዎች፣ እንደ በርባን ላሉ ቀማኛዎችና እንደ ጲላጦስ ላሉ አፈ ጮሌዎች ናት፡፡ በእነዚህ ዓይነት ከሀዲዎች፣ ቀማኛዎችና አፈ ጮሌዎች ቅዱስ እስጢፋኖስ እንደ እባብ ተቀጥቅጦ እንደሞተ፣ ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ ጴጥሮስም አንገቶቻቸውን እንደ አገዳ እንደተቀሉ ላንተ አልነግርህም፡፡ ይህቺ ምድር እንደ ኡጋንዳው ኢዲ አሚን ዳዳ፣ እንደ ቺሌው ፒኖቼ፣ እንደ ካምቦዲያው ፖልፖት፣ እንደ ኢትዮጵያዊኖቹ መንግሥቱ ኃይለማርያም፣ መለስ ዜናዊ እና አብይ አሕመድ ላሉ ገዳይና አረመኔዎች ናት። ያለምንም ደም (With out blood) በሚል መፎክ የተጀመረው የደርግ አብዮት ዐማሮችን በመረፍረፍ እደተጠናቀቀ አታውቅም? አሚን ዳዳ "አዲሲቱን ኡጋንዳ እፈጥራለሁ" ብሎ እንደተነሳው ሁሉ አብይ አሕመድ "አዲሲቲን ኢትዮጵያ እፈጥራለሁ" ብሎ በአምስት ዓመት የሥልጣን ዘመኑ የመቃብር መሬት እስኪጠብ ዐማሮችን እንዳስጨፈጨፈ አታውቅም? በሦስቱ ኢትዮጵያዊያን መሪዎች መንግሥቱ ኃይለማርያም፣ መለስ ዜናዊ እና አብይ አሕመድ ስንቱን ዐማራ ነው ያለቀው? በእነዚህ አረመኔያዊ የደርግ፣ የኢሕአዴግ እና የብልጽግና አገዛዝ በዐማራ ላይ የደረሰው እልቂት ስንቱ ስንቱ ነው? ዋ!....እናም ይህቺ ዓለም እንኳን ለሌላው የሰው ሥጋ ለብሶ ለመጣው መለኮት ለክርስቶስም አልሆነችም፡፡ ክርስቶስና ሐዋርያቱን የሰዋቸውን የከሀዲዎች፣ የቀማኛዎችና የጮሌዎች ጭካኔ በጠላትነት የተፈረጅከው አንተ ዐማራው በምን የትዕግስት ጫንቃ እንደቻልከው አላውቅም፡፡ ማርያምን አላውቅም! ዐማራ ሆይ! በጨቋኝነት ፈርጀው የሚያሳድዱህ አውሬዎች እኮ እጅግ የከፉ ጭራቆች ናቸው፡፡ ፍቅርን፣ የአንድነትን፣ የኢትዮጵያዊነትን አስኳል ከውስጣቸው አውጥተው የጣሉ ከሰውነት በታች ወርደው የክፉ ክፉ የሆኑ አውሬዎች ናቸው። እነዚህን ስለኢትዮጵያዊነት በመስበክ፣ በሰልፍ፣ ኮሚቴ በማቋቋም፣ በአድማ፣ በመግለጫ ብቻ ማስቆም አይቻልም። እነዚህን ማስቆም የሚቻለው ወይንም እንደ እሥራኤሎች ከፈጽሞ መጥፋት መዳን የሚቻለው እንዳመጣጣቸው በመደራጀት፣ እንደ እስራኤላዊያን ባንድነት በመቆም ብቻ ነው። ዐማራ ሆይ! የተረሳ ይደገማልና በዋግኽምራ ዞን በሰቆጣ ወረዳ ጭላ ቀበሌ ከተወለደ አስር ቀን ያልሞላውን ልጇን ወርውረው ገድለው እናቱን እንደደፈሯት አትርሳ እንጂ። ሻሸመኔ ከተማ የዘጠኝ ወር ነፍሰ ጡር መሬት ላይ ጥለው፣ ልብሷን አስወልቀው፣ እግሯን ይዘው እየጎተቱ "የዐማራ ልጅ አይወለድም፤ ግደላት ሰንጥቅና አሳየኝ " እያሉ ሜጫቸውን፣ ጩቤያቸውንና መጥረቢያቸውን ወደ አንገቷ እና ሆዷ አስጠግተው እየሳሉ አሰቃይተው ከነፅንሷ እስከወዲያኛው ህይወቷ እንዲያልፍ እንዳደረጉ አትርሳ። በምዕራብ ወለጋ ግምቢ ወረዳ ቶሌ ቀበሌ ነዋሪ የነበረችው አንሻ ሰይድ ገና የ15 ቀን እርጥብ አራስ ነበረች። ያማጠችበት ወገቧ ገና አልጠናም። እግሮቿም ቢሆን ለማምለጥ ብርታት አልነበራቸውም። ጡቶቿ እንዳጋቱ ነበር። ሰኔ 11 ቀን 2014 ቶሌ ቀበሌ በኦሮሞ ታጣቂዎች ተከበበች። አንሻን ከተኛችበት ይዘዋት ሲሄዱ ገና ደሟ ያልደረቀ ጨቅላ ልጇን በእቅፏ ይዛለች። "ጨፌ" ወደሚባል ጫካ ይዘዋት ሄዱ። ከዚያም ረሸኗት። አራሷ አንሻ ጀርባዋ ላይ በጥይት ተመትታ ጨቅላ ልጇን እንዳቀፈች እዚያው አሸለበች። ሦስት ልጆቿን ሜዳ ላይ በትና በዐማራነቷ በሰቀቀን የምትኖርባትን ጊምቢንና ይህችን ዓለም ተሰናብታለች። አንሻ ይህችን ዓለም የተሰናበተችው ብቻዋን አይደለም። የ14 ዓመት እህቷን አስከትላ ነው። እሁድ ዕለት ከጥቃቱ የተረፉት ነዋሪዎች፣ በየቤቱና በየመንገዱ የወደቁ የሕጻናት፣ የሴቶችና የሽማግሌዎች አስክሬን እየሰበሰቡ መቅበር ያዙ። እረፋድ ላይ ያገኙትን ሲቀብሩ ከዋሉ በኋላ በዚያው ዕለት ከቀኑ 7፡00 ገደማ ሌላ መርዶ ተሰማ። ታግተው ጨፌ የሚባል ጫካ ውስጥ የተገደሉ አሉ ተባለ። የአንሻ ዘመዶችና ሌላው የዘመዱን አስክሬን ፍለጋ በመከላከያ ኃይል ታጅበው ወደዚያው አመሩ። በቦታው ሲደርሱ ጨፌ ጫካ በዐማሮች አስክሬን ተሞልቷል። ሁሉም ሰው የራሱን ዘመድ አስክሬን ፍለጋ እያገላበጠ በማየት ማንሳት ጀመረ። የአንሻ ዘመድም ዐይኑ ከዘመናት ጎረቤቱ እና ዘመዱ አስክሬን ላይ አረፈ። አንሻ አራስ ልጇን በፊቷ አድርጋ፣ የ15 ቀን ጨቅላ ልጇን ደገፍ ብላ አሸልባለች። አንሻን ሲያነሷት ልጅቷ በሕይወት ትተርፋለች የሚል ሃሳብ አልነበራቸውም። የ15 ቀኗ ጨቅላ' ትንሿ አንሻ' ግን ትንፋሽ ነበራት። ትንሿን አንሻ፣ ጨቅላዋን አንሻ አግቻት ነበር። ገና አንድ ዓመት አልሞላትም። አፏን አልፈታችም። እናቷ እንደሞተችም አታውቅም። ይህ ግፍ እንዴት ይዘነጋል ዐማራ? ዐማራ ሆይ! ግፉ በአደባባይ የዋለውን የማይካድራን፣ የቶሌን፣ የጭናን ጅምላ ጭፍጨፋን አትዘንጋ፡፡ በዐማራነታቸው ግድግዳ እየገፉ ራቁታቸውን በሴት ታጣቂ የተገረፉትን መነኩሴ አባ ጡመልሳን አትርሳ። ዛሬም በመላ አገሪቱ በተለይም በወለጋ የሚደርስብን አላባራ ያለ የዘር ፍጅትና የሕዝብን ሰቆቃ ልብ በለው፡፡ ወደፊት ልትሰማ የምትችለውን አደባባይ ያልወጣ ሰቆቃም ግምት ውስጥ አስገባው፡፡ የገዥዎችህ ራዲዮና ቴሌቪዥን ለፍትህ እታገላለሁ የሚለው የውጩ ድህረ-ገጥ ሳይቀር የተጨናነቀው አውሬ በበላቸው ልጆችህ ሳይሆን በማይፀድቅ ችግኝ ተከላ፣ በማይጠና የነፍሰ ገዳይ ሌቦች እርቅ፣ የደላው በሚጫወተው የእግር ጓዝ ወሬ ነው፡፡ በአንተ ደም ስልጣናቸውን የሚያስጠብቁት ወሮበላ ገዥዎችህም የፈሰሰውን ደምህን ከመጤፍ ሳይቆጥሩ ደምህ የፈሰሰበትን እርስትህን ሊያስነጥቁ እያቆበቆቡ ነው፡፡ ዐማራ ሆይ! ብዙ አውሬዎች ተከፋፍለው ስለዋጡህ ወደ አምስት ሚሊዮን ጎለሃል፡፡ ተራ በተራ ሊውጡህ የተሰልፉትን አውሬዎች ካልተከላከልክ የመጥፋት እድልም ይገጥምሃል፡፡ እንደምታውቀው የደን ጭፍጨፋ ከአንድ ዛፍ ይጀምራል፡፡ የአንተ ጭፍጨፋ ግን በፍጥነት አምስት ሚሊዮን ደርሷል፡፡ ዛሬም እንደበፊቱ አውሬዎችን በትምህትና በፍቅር ወደ ሰውነት እቀይራለሁ በሚለው ቀጥለህ ከሆነ የመጥፊያህን ጊዜ አሳጥረሃል፡፡ ግዜ እየጠበቀና እያደባ የሚበላህ አውሬ የትምህርት ሐተታና የፍቅር ስብከት እንደማይገባው ተሞክሮህ ሊያስገነዝብህ ይገባል፡፡ ትምህርትና ፍቅር ለአውሬ እንደማይገባው ስለ አንድነትና ፍቅር ያስተማርከው ከአለት የተዘራ ስንዴ ሆኖ መቅረቱ በመረጃነት ሊያሳምንህ ይገባል፡፡ ዐማራ ሆይ! ማንኛውም ፍጥረት ዘሩ እንዳይጠፋ የተቻለውን ያደርጋል፡፡ እንኳን ሰው እንስሳትም እንኳ በደመ ነፍሳዊት ባሕርያቸው ራሳቸውን ይከላከላሉ። አጋም ፍሬውን ላለማስነካት በእሾሁ ይዋጋል፡፡ ንብ ማሩን ላለመስጠት በሰንኮፉ ይናደፋል፡፡ አነር ከጠላት ለመከላከል በጥፍሩ ይፏጭራል፡፡ ጎሽ ልጁን ለማዳን በቀንዱ ይዋጋል፡፡ አንተም ይህ መብት አለህ። ዘርህን ለማትረፍ የተቻለህን ሁሉ ማድረግ ይጠበቅብሃል፡፡ ራስህን አድነህ ዘርህን ከመጥፋት ስታድንና ክንድህን ስታፈረጥም ጉልበተኛን ብቻ የሚያከብረው ይህ ምድር ክብር ይሰጥሃል፡፡ የፈጠረውን ዘር ከመጥፋት ያዳንክለት መለኮትም በተመቻቸ የሰማይ ቤት ያኖርሃል፡፡ ማንኛውንም ሀሳብና አስተያየት በዚህ ሊንክ መላክ ይችላሉ @Tadeletibebut

photo content
+6

በዚህ አምስት ዓመት ውስጥ በዐማራ ላይ ምን ያልሆነ ነገር አለ? ዐማራን በማግለል የሰኔ ወር ጉባዔ ተደርጎ የሽግግር መንግሥት ሲመሠረት ቀንደኞቹ የኦነግ አመራሮች አቶ ዲማ ነገዎ የማስታወቂያ ሚኒስትር፣ አቶ ኢብሳ ጉተማ የትምህርት ሚኒስትር፣ አቶ አሕመድ ሑሴን የንግድ ሚኒስትር፣ አቶ ዘገየ አስፉው የግብርና ሚኒስትር ሆነው ሲሾሙ የተሳሉ ሜንጫዎች የዐማሮችን አንገት ይቆርጡ እንደነበረው ሁሉ፣ በአብይ አሕመድ የማሳመን (convince) እና የማወናበድ (confuse) የሥልጣን ዘመን በኦሮሚያ ክልል ዐማሮች ፍፁም አረመኔአዊ በሆነ ሁኔታ በቢላዋ እና በገጀራ ተቆራርጠው፣ እንደ ቄራ ታርደው፣ በጥይት ተደብድበው፣ በጦር ተጨቅጭቀው ተገድለዋል። በአንካሴ ተወግተው ወደ ገደል ተጥለዋል። በቤታቸው ተዘግተው ተቃጥለዋል። የቀንድ ከብቶቻቸው ተዘርፈዋል። የእህል ክምር ወድሟል። የዐማራ አባወራዎች ከነቤተሰብ አባሎቻቸው ጋር አውራ እንደሌለው ንብ አድራሻቸው ሳይታወቅ ወደ አራቱ የኢትዮጵያ መዓዝኖች ተዘርተዋል። የኦነጉ ቀደኛ አመራሮች በ1983 ሚኒስትር ሲሆኑ ዐማሮች እጅ እግራቸው ታስሮ ከነሕይወታቸው ወደ ጅሌቻ፣ እንቅፍቱ እና ጥርሶ ገደል ይጣሉ ነበር። የአብይ አሕመድ የሥልጣን ጉዞ 'ሀ' ብሎ የጀመረው በዐማሮች የደም ጎርፍ ነው። ገና በ "ለውጡ" ማለዳ ሐምሌ 28 እስከ 30 ቀን በሶማሌ ክልል በጅግጅጋ፣ ዋርዴር፣ ጎዴ፣ ደጋሀቡር፣ ፊቅ እና ቀላፎ ዐማሮችንና ሌሎችን ነገዶች ኢላማ ባደረገው ጭፍጨፋ ከ50 በላይ ሰዎች አለቁ። የዋርዴር ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን፣ ደጋሐቡር መካነ ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን፣ ቀብሪደኃር ደብረመድኃኒት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን በጅጅጋ የምሥራቀ ፀሐይ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ካቴድራል እና የደብረ ሰዋስው ገዳም ተቃጠሉ። አባ ገብረ ማርያም አስፋው፣ መ/ር አብርሃም ጽጋቡ ተገድለው አስከሬናቸው ተቃጠለ። በአዲሱ 2011 ዓ.ም. መባቻ ኦነግ አንድ ቀበሌ መቆጣጠር አቅቶት ፍየል ጠባቂ ሆኖ ከኖረበት የኤርትራ በረሃ በአብይ አሕመድ ጥሪ በመቀሌና በቦሌ መግባቱን ተከትሎ ለመቀበል ከተለያዩ ሥፍራዎች በመነሣት በቡራዩ በኩል ወደ አዲስ አበባ የመጡ "ቄሮ" በተባለ ሥያሜ የሚጠራው ቡድን "ዶርዜ ይውጣ" የሚል መፈክር (slogan) በማስተጋባት በስለት፣ በገጀራ፣ በፌሮ፣ ሚስማር ባለው ዱላ፣ በፈፀሙት ጥቃት ከ70 በላይ ሰዎችን በመሰዋት፣ ሺዎችን በማፈናቀል አቀባበል አደረጉለት። በአማራ ክልል "ኦሮሞ ብሔረሰብ" በሚል በተቋቋመው ልዩ ዞን በሚገኙ ቦራ፣ ፉርሲና ጀውሃ በሚባሉ ቀበሌዎች ለሁለት ዓመት ያህል ሥልጠና ይወስዱ የነበረ የኦነግ ታጣቂዎች የልዩ ኃይልና የመከላከያ ደንብ ልብስ ለብሰው መጋቢት 29 እና 29 ቀን 2011 ዓ.ም. በማጀቴ፣ በቀጨማ፣ በአጣዬ እና በካራቆሪ በሁለት ቀን ብቻ 64 ዐማሮች ገደሉ። ኮሎኔል አብይ ድርጊቱን "ጁንታ"፣ "የቀን ጅብ"፣ "ለውጡን የማይፈልጉ"፣ "ሸኔ" የሚል ተወካይ ስያሜ በመስጠት ለማደናገርና ለማታለል ቢሞክርም እልቂቱ ግን ማስቆም አልቻለም። በ2012 ዓ.ም ጥቅምት ወር አቶ ጃዋር መሐመድ በይፋዊ የፌስቡክ ገጹ "ጠባቂዎቼን በማንሳት እኔን ለመያዝ ሙከራ እየተደረገ ነው" በሚል ያሰፈረውን መልዕክት ተከትሎ ወዲያውኑ በኦሮሚያ ክልል የሚኖሩ ዐማሮች፣ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ቤተ-አምልኮዎች እና ተከታዮቻቸው "ቄሮ" በተባለው ቡድን ተጨፈጨፉ። ሰኔ 23 ቀን በሃጫሉ ምክንያት ሜጫና ሚስማር የተመታበት አጣና የያዙ ቄሮዎች “ዐማራ ውጣ"፣ "ነ*ፍ*ጠ*ኛ ውጣ"፣ “ክርስቲያን ውጣ”፣ “ይህ የኦሮሞ ነው አትንካ”፤ “እሱ/እሷ ዐማራ ነው/ናት”፣ “ክርስቲያንን አጥፉ”፣ “እናንተ የሚኒሊክ ርዝራዦች ከዚህ ትወጣላችሁ”...በሚል መፈክር ከ200 በላይ ሰዎች ገደሉ። በ2013 ዓ.ም. በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ በመተከል ዞን፣ መስከረም 15፣ ኅዳር 5፣ ታህሣሥ 13 እና ጥር 14 ቀን በተፈፀመው ጭፍጨፋ ቢያንስ ከ500 በላይ ዐማሮች ተገድለዋል። ቡለን በተባለው ወረዳ በኩጂ ቀበሌ ውስጥ ታኅሣሥ 13 ቀን ንጋት ላይ በተፈፀመ ጥቃት ከ220 በላይ ዐማሮች ተገድለዋል። በምዕራብ ወለጋ ግምቢ ወረዳ በቶሌ ቀበሌ ሰኔ 11 ቀን 2014 ዓ.ም. በኦሮሞ ታጣቂዎች በተፈፀመ ጥቃት ከ600 በላይ ዐማሮች ተገድለዋል። ሬሳውንም አሞራ እየጎተተ በልቶታል። የሰኔ 11ዱ የቶሌ እልቂት ከተፈጸመ ከሁለት ሳምንት በኋላ ሰኞ ሰኔ 27 ቀን በቄለም ወለጋ ዞን ውስጥ ሃዋ ገላን ወረዳ፣ ለምለም ቀበሌ፣ መንደር 20 እና 21 ውስጥ በተመሳሳይ ሥፍራ ተመሳሳይ ጭፍጨፋ ተፈጽሟል። በዚህ ጥቃት ሴቶች እና ሕፃናትን ጨምሮ ከ300 በላይ ዐማሮች በመደዳ ተጨፍጭፈዋል። በሰኔ 11ዱ በቶሌ ቀበሌ እና በሰኔ 27ቱ ለምለም ቀበሌ በሰው ልጅ ላይ በተፈፀመ ጭካኔ ከ1000 በላይ ዐማሮች አልቀዋል። ኢንጂነር ስመኘው በቀለ፣ ዶክተር አምባቸው መኮንን፣ አቶ ምግባሩ ከበደ፣ አቶ እዘዝ ዋሴ፣ ብርጋድየር ጄነራል አሳምነው ጽጌ፣ ኮሚሽነር አበረ አዳሙ፣ አቶ ግርማ የሺጥላ እና ሌሎችም የተገደሉት በኦህዴድ መራሹ የብልፅግና ዘመነ መንግሥት ነው። ዛሬ ላይ ተቃቅፈው እንዲህ ልናያቸው በሕወሓት እና አብይ አሕመድ መካከል በተካሄደው ጦርነት ብቻ 7,003 (ሰባት ሺህ ሦስት) የሚሆኑ ዐማሮች ተገድለዋል። እነዚህ ሟቾች ከጦርነቱ ጋር ምንም ግንኑነት የሌላቸ ሰላማዊ (civilian) ዐማሮች ናቸው። 18,496 አካል ጉዳተኛ ሆነዋል። 1968 ተደፍረዋል። 1 ሚሊዮን 411 ሺህ 313 ዐማሮች ተፈናቅለዋል። 7,460 ዐማሮች አድራሻቸው አይታወቅም። 594,943 የዐማሮች ቤት ፈርሷል። 1156 የትምህርት ተቋማት ወድመዋል። 653 የተለያዩ የጤና ተቋማት ወድመዋል። ይህ ሁሉ የሆነው አብይ አሕመድ በሚመራው በኦህዴድ መራሹ የብልፅግና ዘመነ መንግሥት ነው። ባጠቃላይ የኦህዴድ የብልፅግና መንግሥት ታሪክ እና ቅርስ ጠል፣ አድሎአዊ፣ ጠባብ ብሔርተኛ፣ የሰብአዊና የዲሞክራሲያዊ መብቶች ረጋጭ፣ ጨፍጫፊ፣ … አምባገነን ሥርዓት መሆኑን ያሳለፍናቸው አምስት ዓመታት ምስክሮች ናቸው፡፡ በሩዋንዳ የተፈፀመው እልቂት አክራሪ የሁቱ ጎሳ አመራሮች በስልጣን ላይ እያሉ ነበር። ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ ባለፉት አምስት ዓመታት በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶና ተሰምቶ የማይታወቅ የዘር ማጥፋት ወንጀል የተፈፀመው የህወኃት ርዕዮት ዓለም ወራሽ በሆነው በኦህዴድ መራሹ የብልፅግና የሥልጣን ዘመን ነው። መገለጫዎችም፦ -ጅምላ ግድያ፣ -አካል ጉዳት፣ -አስገድዶ መሰወር፣ -ማፈናቀል (displacement)፣ -ያለፍርድ እስራት (Arbitrary Arrest) -ነፃነት ማሳጣት፣ - ዐማራን ለይቶ ማሳዳድ፣ -የዘር መድሎ ስርዓት፣ -አስገድዶ መድፈር፣ -አስገድዶ ማስረገዝ፣ -ዘረፋ፣ -ቤታቸውን ማፍረስ (House Demolition)፣ -ቤታቸውን ማቃጠል (House burning) ናቸው። ከዚህ ውጪ በኦህዴድ የብልፅግና መንግሥት ለውጥ የለም። እናም ዛሬ ዐማራ እያለ ያለው አትግደሉኝ፣ አታፈናቅሉኝ ነው። እንደሌላው በእኩልነት፣ በሠላም ልኑር ነው እያለ ነው። አለበለዚያ በኔ ሞት፣ ደምና አጥንት የምትበልፅግ ኢትዮጵያ የለችም ነው እያለ ያለው። ይህን ጥያቄውን ጠምዝዞ "ፅንፈኛ" እያሉ ወካይ ስም በመስጠት አድበስብሶ ማለፍ አይቻልም።

የድንጋዩ ግዝፈት፣ የመቃብሩ ጥልቀትና የመቃብር ዘበኞች የክርስቶስን ትንሳዔ እንዳላስቀሩት ሁሉ፤ የዐማራን ትንሣኤ እንደ ዔሳው ብርኩናቸውን የሸጡ የይሁዳ ፍየሎች (The Judas goat) ሆኑ፣ የሀገሪቱ ፊልድ ማርሻሎች አያስቀሩትም። እስራኤላውያን ከፈርዖን ባርነት ነፃ ለመውጣት የፈጀውን ያህል ግዜ ይወስድ እንደሆነ እንጂ እንደ ኡጋንዳው ኢዲ አሚን ዳዳ ያሉ አምባገነኖች የዐማራ ትንሣኤን አያስቀሩትም። እንደ ፕሮፌሰር አሥራት ያሉ ተቆርቋሪ ዐማሮችን ልክ እንደ "ቀያፋ" እንዲያዙ ምክር የሚሰጡ ተላላኪዎች ትንሳኤውን አያስቀሩትም። በኢየሩሳሌም ሊቀ ካህናት የነበረው ቀያፋ እየሱስን ለማስያዝና ፍርድ እንዲፈረድበት፣ "ሕዝብ ሁሉ ከሚጠፋ አንድ ሰው ቢሞት ይሻላል" ብሎ የመከረ ሰው ነው። ምክሩ ግን የክርስቶስን ትንሳኤ አላስቀረውም። በአንጻሩ፣ ዛሬ ትንሳኤ ላይ ያሉ የሚመስላቸው መጨረሻቸው እንደ አሚን ዳዳ ስደተኛና ፍርደኛ እንደሚሆኑ ምንም ጥርጥር የለም። "ያለምንም ደም፤ ያለምንም ደም" (With out blood, without blood) በሚል መፎክር የተጀመረው የደርግ አብዮት ኢትዮጵያውያንን በመረፍረፍ ከተጠናቀቀ በኋላ፣ ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም የሞት ጠረን ሸተተኝ ብሎ ፈርጥጦ ዝምባዋብዌ ገብቷል። የደርግን ሥርዓት በቀይ ሽብር በመደዳ ጭፍጨፋ ገድሎ የሸጠው ሬሳ የብረት ዓምድ ሆኖ አላስቆመውም። የዘረፈው ንብረት መሰላል ሆኖ አላቆየውም። ይልቁንስ እንደ በግ እየነዳ ያረደው የደም ጎርፍ ጠራርጎ ወሰደው። በነ ማርክስ ቴዎሪ የረገጠው ሃይማኖት እንጦሮጦስ አወረደው። ዛሬ ትንሣኤ ላይ ያሉ የሚመስላቸው አምባገነኖች የዐማራን ህዝብ እንደ ሂትለር፣ ሙሶሎኒ፣ ስታሊን፣ ፓል ፖት እያሰቃዩ፣ እየጨፈጨፉና እያፈናቀሉ መሠረትነው የሚሉት የ"ብልፅግና" ርዕዮተዓለም እንደ ናዚ ፓርቲ መንኮታኮቱ አይቀርም። ወለጋ ውስጥ አንዲት የ6 ዓመት ህፃን "ወላሂ ሁለተኛ ዐማራ አልሆነም" እያለች በጉንጮቿ ያፈሰሰች ዕንባ፣ እየተሳለቁ ለማየት በሚያሣሣ ገላዋ ላይ እሽቅድምድም በሚመስል መልኩ ባዘነቡት የጥይት አረር ያፈሰሱት ደሟ የእንጦሮጦስን ጎዳና መጥረጉ አይቀርም። ይህ ታሪክ ከሩዋንዳዋ ህፃን ጋር የሚመሳሰል ነው። ሩዋንዳ ውስጥ በነበረው ፍጅት ወቅት አንዲት የ7 ዓመት ህፃን በሁቱ ገዳዮች ተከባ "እባካችሁ አትግደሉኝ። ከእንግዲህ ቱትሲ አልሆነም" (Please don't kill me, I will never be a Tutsi again) እያለች መማፀኗን ተከትሎ የዓለምን ልብ ሰብረው ነበር። ይህ የሁቱዎች ጭካኔ የተቱሲዎችን ትንሣኤ አላስቀረውም። ቱትሲዎች ሥልጣን ይዘው በደም የታጠበችውን ሩዋንዳን ውብና ፅዱ፣ የቱሪስቶች መዳረሻ፣ ለኢንቨስትመንት ተመራጭ አደረጓት። ከትንሣኤው በኋላ የሩዋንዳ ህፃናቶች በውቧ ኪጋሊ ከተማ መናፈሻዎች ሲቦርቁ ታዩ። ዛሬም በአዳነች አበቤ የከንቲባነት ዘመን በአዲስአበባ ከተማ ቤታቸው ፈርሶ መጠጊያ አጥተው የሚያለቅሱ፣ በፈረስ ጋሪ ከቤት እቃ ጋር ተጭነው የሚሰደዱ ህፃናቶች ግፍ በዮዲት ጉዲት የወረደውን አይነት መቅሰፍት ማምጣቱ አይቀርም። ግፈኞች ወደ ከርሠ መቃብርና ወህኒ ሲወርዱ፣ የአዲስአበባ ህፃናቶች፣ የወለጋ ህፃናቶች፣ ተፈናቀለው በመጠለያ ካምፕ የሚገኙ ህፃናቶች የሩዋንዳን አይነት የትንሣኤ ዘመን ይመጣላቸዋል። የግፈኞች መጨረሻ ግን እንደ መንጌ መፈርጠጥ፤ እንደ ዣን ፖል እስርቤት መሆኑ አይቀርም። የሩዋንዳዋ ታባ ከተማ ከንቲባ የነበረው "ዣን ፖል አካይሱ" በፈፀመው የዘር ጭፍጨፋና ሰብዓዊ መብት ጥሰት ከፍርድ እንዳላመለጠው ሁሉ፣ አዲስአበባ ላይ እንደ ዣን ፖል ግፍ እየፈጸሙ ያሉ ሰዎች ዕጣ ፈንታ እንደ ዣን ፖል ይሆናል። በወቅቱ ባንኩና ታንኩ በእጃችን ነው ብለው በጥጋባቸው ቦሲኒያን የጨፈጨፉት ጄነራል ራዲስላቭ ክርስቲች እና ኮማንደር ራትኮ ምላዲች ከፍርድ አላመለጡም። ግፈኞች ሲዋረዱ እንጂ ትንሳኤን አስቀርተው አያውቁም። ናዚዎች በኑምበርግ ፍርድቤት የዕድሜ ልክና የስቅላት ቅጣታቸውን አገኙ እንጂ፣ የእስራኤላውያንን ትንሳኤ አላስቀሩትም። ሁቱዎች በወረንጦ እየተለቀሙ ፍርዳቸውን አገኙ እንጂ የቱትሲዎችን ትንሣኤ አላስቀሩትም። ኢትዮጵያ ላይ ይህ ዘመን አይርቅም። ከስቅለት በኋሏ ትንሳኤ፤ ከጨለማ በኋላም ብርሀን አለና!

እንኳን ለጽሎተ ሐሙስ በሰላም አደረሳችሁ! ጸሎተ ሐሙስ ጌታችን ምሥጢረ ቊርባንን ከምሥጢረ ጸሎት ጋር አዋሕዶ የገለጠበት ዕለት ነው። ትህትና!