en
Feedback
Tadele Tibebu - ታደለ ጥበቡ

Tadele Tibebu - ታደለ ጥበቡ

Open in Telegram

ማንኛውንም ሀሳብና አስተያየት በዚህ ሊንክ መላክ ይችላሉ @Tadeletibebut

Show more
Ethiopia510The category is not specified

📈 Analytical overview of Telegram channel Tadele Tibebu - ታደለ ጥበቡ

Channel Tadele Tibebu - ታደለ ጥበቡ (@tadeletibebu) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 52 631 subscribers, ranking in the Other category and 510 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 52 631 subscribers.

According to the latest data from 02 December, 2024, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 0 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
ማንኛውንም ሀሳብና አስተያየት በዚህ ሊንክ መላክ ይችላሉ @Tadeletibebut

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 03 December, 2024), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Other category.

52 631
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
#ሼር_ፖስት! ብልፅግና ሆቴል ውስጥ አስቀምጦ እንደ ሰንጋ በሬ የሚቀልባቸው አክቲቪስቶች ይህን ዘግናኝ አገዳደል (horrifying killing) ከማውገዝ ይልቅ ለማስተባበል የሄዱበት እርቀት ያስገርማል። እነዚህ አእምሯቸው የታጠበ አክቲቪስት ተብየዎች ሰብአዊነት ከማስቀደም ይልቅ የመሪያቸውን ገመና ለመሸፈን ሲጋጋጡ ማዬት ያሳዝናል። አንድ እውነት ግን መታወቅ ይኖርበታል እንዲህ ያለ ግድያ እየተፈፀመ ያለው በኦህዴድ ብልፅግና ዘመነ መንግሥት፣ በአብይ አሕመድ የሥልጣን ዘመን እና በብርሃኑ ጁላ ፊልድ ማርሻል ዘመን ነው። ታሪክም መዝግቦ የሚያስቀምጠው በዚህ መልኩ ነው። ሁለት ኦርቶዶክሳዊን ወጣቶችን በገመድ ለኋሊት የፍጥኝ በማሰር አነጣጥረው ተኩሰው የገደሏቸው የመከላከያ ዩኒፎርም የለበሱ ናቸው። እንዴት እንደገደሏቸውም ቪዲዮ ቀርፀዋል። ቪድዮውን ሚቀርፃቸው ሌላ ሶስተኛ ወገን ሳይሆን ደግሞ እራሳቸው ገዳዮቹ ናቸው። ከቪድዮ ቀራጩ ውጭ በቁጥር አራት ሲሆኑ፣ ሁሉንም የመከላከያ ዩኒፎርም ልብስ የለበሱ ናቸው። አብይ አሕመድ ወደሥልጣን ከመጣ ጀምሮ እንደዚህ ያሉ ግድያዎች ተራ ጉዳይ ሆነዋል። ባጠቃላይ ከ1982 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ 2015 በዐማራ ከተፈጸሙ ግድያዎች መካከል እነዚህ ይገኙበታል፣ 1. ወደ ገደል መጣል 2. ጡት መቁረጥ 3.ብልትና ምላስ መቁረጥ 4.ሥጋቸውንም ቆርጦ ማብላት 5.በድንጋይ መቀጥቀጥ 6. በሜንጫ እና በስለት ማረድ 7. በቀስት መውጋት 8. ፅንስ ማቋረጥ 9. በጅምላ መረሸን 10.በእሳት ማቃጠል...ወዘተ ይገኙበታል። እነዚህን በምሳሌ በጥቂት ምሳሌዎች ላስረዳ! ሀ. #ወደገደል_መጣል፦ የዐማራ ተወላጆች ከተገደሉባቸው ገደሎች መካከል በወልቃይት ገነሃም ግንብ እና እመን አላምንም፣ በኦሮሞ ክልል እንቁፍቱ ገደል፣ ሞሶ ጊዎርጊስ ገደል፣ ጥርሶ ገደል፣ ኩርባ ጀርቲ ገደል ይገኙበታል። የአገዳደሉ ስልት የኋሊት በማሰር፣ ዐይናቸው ሸፍኖ ወደገደሉ ጫፍ ከአስጠጓቸው በኋላ በጥይት በማርከፍከፍ እንዲወድቁ ማድረግ አንደኛው ነው። ሁለተኛው አገዳደል እጅና እግራቸውን በማሰር ፊታቸውን በመሸፈን ከነሕይወታቸው ወደጥልቁ ገደል መጣል ሲሆን፣ ሦስተኛው አንገታቸውን በሰይፍና በሜንጫ ቀልቶ መወርወር ናቸው። ሕወሓት ከደጀና ከተማ በስተሰሜን ምስራቅ በኩል ወደሚገኘው "እመን አላምንም" እየተባለ ከሚጠራው ወደ 200 ሜትር ከሚረዝመው የገደል አፋፍ ላይ የወልቃይት ጠገዴ ዐማራዎችን በመወርወር ይገድላቸው ነበር። በተመሳሳይ የዐማራው ልኳንዳ አራጅ ኦነግ ደግሞ በደኖ መግቢያ ላይ ከሚገኘው የእንቁፍቱ ገደል ዐማሮችን እጃቸው በገመድ እያሰረ ዐይናቸው በሻሽ እየሸፈነ ይጥላቸው ነበር። ለምሳሌ፣ አፈሩን ገለባ ያድርግላቸውና አቶ አበበ ምትኬ በሐረርጌ የበደኖ ከተማ ኗሪ ነበሩ፡፡ በ1984 ዓ.ም. በበደኖ ዕልቂት ሙሉ ዘጠኝ ቤተሰቦቻቸውን ከነነፍሳቸው አስረው እንቁፍቱ ገደል በመወርወር ጨረሷቸው። (ምጽአተ ዐማራ፣ 327) ለ.#ጡት_መቁረጥ፦ በጃዋር ምክንያት ዶዶላ ላይ የሁለት ህፃናት እናት የነበረችው ዘምሼ ሲሳይ የገደሏት ጡቷን ቆርጠው ነው። ኦነግ በ1984 ዓ.ም. ብቻ በሐረርጌ ክፍለሀገር፣ ደጉ መድኃኔዓለም 3፣ ከሀረር ከተማ በ7 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ፈዲስ 7፣ ከበደኖ አለፍ ብላ ከምትገኘው ቡርቃ 4 ባጠቃላይ 14 የዐማራ ሴቶችን ጡት ቆርጧል። (ምጽአተ ዐማራ፣ 329) ሐ.#ብልትና_ምላስ_መቁረጥ፦ በምሥራቅ ወለጋ ህዳር 21 ቀን 1993 ዓ.ም. በጊዳ ኪራሞ ወረዳ፣ ዲቡክ ማርያም 1100 የሚሆኑ የብሉይ ዘመን ሕይወትን የሚገፉ ሚስኪን ዐማሮችን ሕፃናት፣ አዛውንቶችና ሴቶች አልቀዋል። በወቅቱ ጦቢያ መጽሔት "የዐማራው ሕዝብ ዕልቂት በአንድ ዘር ላይ የተነጣጠረ ጥቃት" በሚል ይዞት በወጣው ልዩ ጥንቅር ከዕልቂቱ አስከፊ ገጽታ መካከል የሚከተለውን በዝርዝር ይገልጻል፣ "አባ በላይ ዋለ የተባሉትን ዓይነ ሥውር ገደሏቸው። 'ዐማራ ዐማራ ነው' ብለው ብልታቸውን ቆረጡት። መልካሙ ውባለምን አርደው ገደሉትና ምላሱን አውጥተው ወሰዱት። (ጦቢያ መጽሔት፣ ቅጽ 8፣ ቁጥር 8፣ 1993) መ.#ሥጋቸውንም_ቆርጦ_ማብላት፦ በዐማራ ላይ ከተፈፀሙ የግድያ አይነቶች ሌላኛው ልብሳቸውን እያስወለቁ ሥጋቸውን እያበሉ መግደል ነው። ለምሳሌ፣ ገቦ ሀብሩ ወረዳ አቶ ፀደቀ አውሉው የሚባል የዐማራ ተወላጅን መጀመሪያ ወርቅ ጥርሱን አውልቀው ወሰዱ። ቀጥሎ ሰውነቱን እንደ ጥሬ ሥጋ በመቆራረጥ እያበሉ ገደሉት። በገለምሶ በልበልቲ ይኖር የነበረው አቶ ገብሬ አወቀ የሚባል ሕዝብ በተሰበሰበት በሚስማር እንደ ክርስቶስ እጅና እግሩን ቸንክረው በመጀመሪያ ብልቱን ከዚያም የተለያየ የአካል ክፍሉን እየቆራረጡ እያበሉ ገድለውታል። ሠ. #ፅንስ_ማቋረጥ፦ "የዐማራ ልጅ አይወለደም" እያሉ ፅንስን መግደል በዐማራ ከተፈፀሙ ዘግናኝ ግድያዎች መካከል አንዱ ነው። በሃጫሉ ሞት ምክንያት በተነሳ አመፅ ሻሸመኔ ከተማ የዘጠኝ ወር ነፍሰ ጡር መሬት ላይ ጥለው፣ ልብሷን አስወልቀው፣ እግሯን ይዘው እየጎተቱ "የዐማራ ልጅ አይወለድም፤ የክርስቲያን ልጅ አይወለድም፤ ግደላት ሰንጥቅና አሳየኝ " እያሉ ሜጫቸውን፣ ጩቤያቸውንና መጥረቢያቸውን ወደ አንገቷ እና ሆዷ አስጠግተው እየሳሉ አሰቃይተው ከነፅንሷ እስከወዲያኛው ህይወቷ እንዲያልፍ ሆኗል። ሕወሓትም በጦርነቱ ወቅት "ተወልዶ አድጎ ይወጋናል" በሚል ከእናቱ ሆድ እያለን ፅንስ በርግጫ እና በሰደፍ እየጨፈለቀ አጨናግፏል። ሰ. #በእሳት_ማቃጠል፦ በሰኔ ወር 2014 ዓ.ም. በምዕራብ ወለጋ ግምቢ ቶሌ መንደር ከተፈጸሙ ዘግናኝ አገዳደሎች መመካከል በእሳት ማቃጠል ይገኝበታል። በዚሁ ቀበሌ ወደ 22 የሚሆኑ ዐማሮች በር ተዘግቶባቸው ከነሕይወታቸው ቤታቸው ውስጥ ተቃጥለዋል። ባጠቃላይ ከኢትዮጵያዊያን ባሕል፤ ሃይማኖት፤ ሞራል እና ሰብአዊነት ተግባር ባፈነገጠ መልኩ በዐማራ ላይ ያልተፈፀመ የግድያ አይነት የለም። እነዚህ አውሬዎች በዐማራ ላይ እንዲህ ያለውን ዘግናኝ ድርጊት ሲፈፅሙ በደስታ ነው። የዐማራ ሴቶችን ጡት ጥሬ ስጋ እንደሚበላ ሆዳም ሰው ተስገብግበው ሲቆርጡት በኩራት ነው። አይሁዶች በክርስቶስ በየተራ እንደተዘባበቱበት ሁሉ እንደ በግ ጠቦት ለመግደል ባዘጋጁት ዐማራ ላይ ሲዘባበቱ በሲቃ ነው። ምክንያቱም ይህን እያደረጉ ያሉት በዐማራው ላይ ስለሆነ!

#ሼር_ፖስት! በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን በዳንሻ፣ በወፍ አርግፍና በሌሎች አካባቢዎች ደማቅ ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሂዷል።ይህ የወልቃይት ጠገዴ አማራ ህዝብ በአደባባይ ያሰማው ድምፅ፦ ☞ ወልቃይት ጠገዴ የከለው ልጅ የአማራ ዘር ግንድ መነሻ ነው! ☞ለእንግዶች እንጂ ለወንጀለኞች ቦታ የለንም! ☞ለነፃነታችን ዋጋ ከፍለንበታል፣ ወደኋላ ላንመለስ ነፃ ወጥተናል! ☞አማራ ነን እንጂ አማራ እንሁን አላልንም! ☞የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነት ጥያቄ ፍፁም ፍትሐዊና ህጋዊ ነው። ☞የማይገባንን አልፈን አንጠይቅም፣ የራሳችንንም አሳልፈን አንሰጥም! ☞የወልቃይት ጠገዴ እና የራያ አማራ የማንነት ጥያቄን "የርስት ማስመለስ ብሎ በመፈረጅ አማራን ማሸማቀቅ አይቻልም ! ሀገር ርስት ነው! ለርስት መሞት ክብር ነው!" ☞ የፖለቲካ ሴራ የሐሰት ፕሮፖጋንዳ ለድጋሜ እልቂት እንጂ ሰላምን አያመጣም የሚሻለው መራራውን ሀቅ መቀበል ብቻ ነው! ☞በወልቃይት ጠገዴ የአማራ ሕዝብ ላይ ለተፈጸሙ የዘር ማጥፋት ወንጀል የፍትህ ካሳ እንፈልጋለን! ☞ተበዳይ እንጂ በዳይ፤ ተጨፍጫፊ እንጂ ጨፍጫፊ፣ ተወራሪ እንጂ ወራሪ፤ ተፈናቃይ እንጂ አፈናቃይ አይደለነም! ☞ የትግራይ ህዝብ ሆይ መጣችሁብን እንጅ አልመጣንባችሁም የመጭው ዘመን የሰላም ሁኔታ በእጃችሁ ነው፣ ከተከዜ በመለስ አማራ የመሆኑን ሀቅ ተቀበሉና ጥሩ ጎረቤት እንሁን! ☞ በዳይ የተበዳይን ጩሆት ነጥቆ ተበዳይ ለመምሰል የሚደረግ አካሄድ ዓይነ ደረቅነት ነው! ☞ ወንጀለኞች ለህግ ይቀርባሉ እንጅ በተፈናቃይ መልክ እናስፍር አይባልም! ☞ አማራዊ ማንነታችን እና የወሰን አስተዳደር ግዛት በህግ አግባብ ይከበር! ☞ ከትግራይ ጋር ደንበራችን ተከዜ ነው።

አሁን አርበኛ ዘመነ ካሴ ተፈቷል። እግዚአብሔር ይመስገን። ሁሉም ነገር በእግዚአብሔር መልካም ፈቃድ ሆነ።

የአብይ አሕመድ አገዛዝ ጃል መሮን ቤተመንግሥት እራት እየጋበዘ፣ ለኦነግ ሸኔዎች ታክቲካል ድጋፍ እያደረገ የሰብዓዊ መብት ታጋዩን እስክንድርን ግን እያሳደደው ይገኛል። ልብ አድርጉ እንግዲህ በጃል መሮ የሚመራው ኦነግ፣ -ጥቅምት 22 ቀን 2013 ዓ.ም በምዕራብ ወለጋ ዞን፣ ጉሊሶ ወረዳ፣ ጋዋ ቀናቲ ቀበሌ ከ200 በላይ ዐማሮችን ገድሏል። -በጥር 2014 ዓ.ም. ቄለም ወለጋ ጊዳሚ ወረዳ ወደ 160 የሚሆኑ ዐማሮች ተጨፍጭፈዋል። -ሰኔ 11ቀን 2014 ዓ.ም በምዕራብ ወለጋ ግምቢ በምትገኘው ቶሌ ቀበሌ እስካሁን በተገኘው መረጃ ከ600 በላይ የሚሆኑ ዐማሮች ተገድለዋል። - የቶሌ እልቂት ከተፈጸመ ከሁለት ሳምንት በኋላ ሰኞ ሰኔ 27 ቀን 2014 ዓ.ም. በቄለም ወለጋ ዞን ውስጥ ሃዋ ገላን ወረዳ፣ ለምለም ቀበሌ፣ መንደር 20 እና 21 ውስጥ በተፈጸመ ጥቃት ከ350 በላይ ዐማሮች በመደዳ ተጨፍጭፈዋል። -በምዕራብ ወለጋ፣ ባቦ ገንቤል ወረዳ፣ ቦኔ ቀበሌ መጋቢት 21 ቀን 2013 ዓ.ም. ከ50 በላይ ዐማሮች ከየቤታቸው በማውጣት አንድ ቦታ በመሰብሰብ በጥይት አርከፍክፈው ገድለዋቸዋል። -ምሥራቅ ወለጋ ዞን ኪራሙ ወረዳ ነሐሴ 12 ቀን 2013 ዓ.ም.ማንም የተረፈ የለም። ከ300 በላይ ዐማሮች የጀምላ ግድያ (mass execution) ተፈጽሞባቸዋል። ወቅቱ ክረምት በመሆኑ በየወንዙ የወዳደቀ አስክሬን ተፈልጎ በአንድ ግዜ 150 አስክሬን ተቀብሯል። ብዙዎቹ የቤተሰቦቻቸውን አስክሬን አላገኙም። ጭፍጨፋውን ተከትሎ (following the massacre) በሺህ የሚቆጠሩት ተፈናቅለዋል። -መስከረም 12 ቀን 2015 በዚሁ ሆሮ ጉድሩ ወለጋ ዞን ጃረዴጋ ጃርቴ፣ ሆሮ ቡልቅ እና አሙሩ ወረዳዎች የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ኦነግ ከቄሮዎች ጋር በመተባበር በፈፀሙት በዘር ላይ የተመሰረተ መጠነ ሰፊ እልቂት (large-scale ethnic-based massacre) ከ500 ያላነሱ የዐማራ ተወላጆች ተገድለዋል። ልብ አድርጉ እንግዲህ ጋዋ ቀናቲ፣ ጊዳሚ፣ ቶሌ፣ ለምለም፣ ቦኔ፣ ኪራሙ እና አሙሩ ብቻ በተፈጸመ ጥቃት በትንሹ ከ2,160 በላይ ዐማሮች ተጨፍጭፈዋል። ነገርግን "መለኞቹ" አንዴ "ንሥሮቹ" እየተባሉ የሚንቆለጳጰሱት የፀጥታ፣ የደኅንነትና የፖሊስ መዋቅር የጃል መሮን ጄኖሳይድ ማስቆም አልቻሉም። ጃል መሮንም መያዝ አልቻሉም። ምክንያቱም ኦነግ ሸኔ ዐማሮችን ከኦሮሚያ የሚያጠፋ የኦህዴድ ብልፅግና ሌላኛው የጫካ ክንፍ ስለሆነ ነው። ኦህዴድ ብልፅግና ቤተመንግሥት ውስጥ፣ ኦነግ ሸኔ ጫካ ሆነው ነው በዐማራ ላይ ጅምላ ግድያ (mass killing)፣ ዘግናኝ አገዳደል (horrifying killing)፣ አካል ጉዳት (physical harm)፣ የአእምሮ ጉዳት (mental harm)፣ በግዳጅ ማፈናቀል(forced displacement)፣ የንብረት ውድመትና ዘረፋ (Destruction of Property and Looting) እየፈፀሙበት ያለው። እናም ጃል መሮን ጫፍ እንዲነካ አይፈለግም። እንዲያውም ኦነግ ሸኔና ጃል መሮ ታክቲካል ድጋፍ ሲደረግለት ቆይቷል። ለምሳሌ፦ 1.ከ600 በላይ ዐማሮች በቶሌ ቀበሌ ሲገደሉ የቶሌ መንደር አስተዳዳሪ አቶ ንጋቱ ኡመታ እና የጊምቢ ወረዳ አስትዳዳሪ አቶ ባጫ የወረዳው ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት እንዲተባበሩ ትእዛዛት ሰጥተዋል። ከጭፍጨፋው አስቀድመው ከኦነግ ጋር ዕቅድ ከያዙ በኋላ የአካባቢው ፖሊሶችንና የሚኒሻ አባላትን ከቶሌ መንደር እንዲወጡ አድርገዋል። 2. መጋቢት 21 ቀን 2013 ዓ.ም. በምዕራብ ወለጋ ዞን በሚገኘው ባቦ ገንቤል ወረዳ፣ ቦኔ ቀበሌ ከምሽቱ አንድ ሰአት ጀምሮ ኦነግ ዐማሮች ወደሚኖሩበት ቀየ ዘልቆ በመግባት ከ50 በላይ የሚሆኑ ዐማራዎችን ሲጨፈጭፍ፣ የኦሮሚያ ልዩ ኃይል "እርምጃ እንድንወስድ አልታዘዝንም" በማለት በሩቅ ሆነው ይመለከቱ ነበር። 3. በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን፣ ኡሙሩ ወረዳ በምትገኘው አጋምሳ ከተማ ነሐሴ 23 ቀን ኦነግ በከተማዋ ውስጥ በመዘዋወር የዐማራ ሰላማዊ ብሄር ተወላጆችን በመለየት በፈጸመው ጭካኔ ከ61 በላይ ንጹሀን ዐማራዎች የተገደሉት የኦሮሞ ልዩ ሃይሎች እሁድ ነሀሴ 22 ቀን ከምሽቱ 1 ሰአት አካባቢ ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ ድንገት ከተማዋን ለቀው ከወጡ በኋላ ነበር። 4. በተመሳሳይ በምሥራቅ ወለጋ በኪራሙ ወረዳ፣ 2014 ዓ.ም. መስከረም 30 ቀን ከ60 በላይ ዐማሮች የተገደሉት በኪራሙ ወረዳ ሀሮ አዲስ አለም ከተማ ውስጥ ጥበቃ ሲያደርጉ የነበሩ የኦሮሚያ ክልል ልዩ ኃይሎች መስከረም 26 ቀን አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ ከተደረገ በኋላ ነው። 5. ጥቅምት 22 ቀን 2013 ዓ.ም በምዕራብ ወለጋ ዞን ጉሊሶ ወረዳ ጋዋ ቀናቲ በጨካኝነቱ ተወዳዳሪ የማይገኝለት፣ በመልኩም ፍፁም አስቀያሚ ጭፍጨፋ የተፈፀመው ጥቅምት 21 ቀን ቅዳሜ ጠዋት የመከላከያ ሠራዊት አካባቢውን ለቆ እንዲወጣ ከተደረገ በኋላ ነበር። በወቅቱ መከላከያ ቦታውን ለቆ ሲወጣ ዐማሮች "ገላችሁን ሒዱ ወይም ይዛችሁን ሒዱ" ብለው የመከላከያ ተሽከርካሪ (ኦራል) አግደው ቢለምኑም፣ መከላከያም "ታዘን ነው የወጣነው" የሚል አጭር መልስ ሰጥቶ ጥሎ ወጥቷል። መከላከያ ሥፍራውን ለቆ በወጣ በሰዓታት ኦነግ አከባቢውን ተቆጣጠረ። ከዚያ ጋዋ ቀናቲ በዐማሮች ደም ተጥለቀለቀች። በዐማሮች ደም ታጠበች። ሌሊቱ ወደ ንጋት፣ ንጋቱ ወደረፋዱ ቀን ሲደርስ የዐማሮች ሬሳ በቦንብ ተቦጫጭቆ፣ ሰውነታቸው ተቦዳድሶ፣ አናታቸው ተፈረካክሶ፣ ታፋቸው ተገነጣጥሉ በየቦታው ወድቋል። በየቦታው የወደቀው እስክሬን ተሰብስቦ ሲቆጠር ከ200 በላይ አለፈ። እንግዲህ ኦነግ እና ጃል መሮን ያህል አሸባሪዎች በጉያቸው ታቅፈው ነው ሌላውን ለማጥፋት ቆርጠው የተነሱት። እንዲህ ያለውን አረመኔ ጃል መሮን ደብቀው ነው የሰብዓዊ መብት ታጋዩን እስክንድር ነጋን እንገድላለን ብለው ጦር ያዘመቱበት። ለአምስት ተከታታይ ዓመታት የማያባራ የዘር ተኮር ጭፍጨፋ ሲካሄድ በመደመር ቲያትር፣ በአረንጓዴ አሻራ ቲያትር፣ በገበታ ለሀገር ቲያትር ላይ ተጠምዶ የነበረው አብይ አሕመድ እና ብርሃኑ ጁላ ጦራቸውን ወደ ጎጃም የላኩት።

እስክንድር ነጋ አንድ ብቻ አይደለም፤ አሁን ሺህ እስክንድሮች እና ሺህ ዘመነዎች ተፈጥረዋል። ትግል የዱላ ቅብብሎሽ ነው። አንዱ ሲደክም ሌላው ይዞት ይቀጥላል። ኦህዴድ ብልፅግና የተሳተው ነገር ቢኖር በእስክንድር ነጋ ምክንያት የሚቆም ትግል አልተጀመረም። እሳት የላሱ፣ እሳት የጎረሱ፣ በአእምሮ የነቁ፣ በአካል የዳበሩ የዐማራ ልጆች ተፈጥረዋል። ይሄው ነው።

photo content
+2

እነዚህ ዐማሮች ኃጢአት ሳይኖርባቸው የተገደሉት የኦሮሞው ሻለቃ መንግሥቱ በከፈተው የሞት ባሕር መዝገብ ዝርዝር መሰረት ነው። የገደላቸው በዐማራነታቸው ብቻ ነው። ከሞት ለይቶ ያስቀራቸው ባለሥልጣኖች ኦሮሞዎች በመሆናቸው እንጂ ከተረሸኙት ዐማሮች ያነሰ ሥልጣን ኑሮአቸው አይደለም። የኦሮሞ ተወላጅ የሆነው መንግሥቱ በኦሮሞና በደቡብ ክልል የነበሩትን ዐማራዎች ትጥቃቸውን እያስፈታ ለኦሮሞዎች እያስታጠቀ ዐማራው እንዲገደል ማድረጉ በታሪክ ተመዝግቧል።(በሪሁን፣ 1278) ሌላው ቢቀር መንግሥቱ ኃይለማርያም የሶሻሊዝም ጉዟችን ችግር አለው ብሎ ሐቁን የተናገረውንና ምክትሉ የነበረውን፤ የጎጃሙን ኮሎኔል አጥናፉ አባተን ከመግደል ያልተመለሰ ደ*ን*ቆ*ሮ ደፋር ነው። በዚህ መልኩ ደርግ የተማሩ የዐማራ ልጆችን ከኢትዮጵያ የፖለቲካ መድረክ አጥፍቷቸዋል። አገራቸውን በአርበኝነትና በዲፕሎማሲ ያስጠሩትን እነ ራስ መስፍን ስለሺ፣ ጸሐፊ ትእዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድንና ሌሎችንም የዐማራ ሊቃውንት ያለ ርህራሄ ጨፍጭፎ ዐማራውን ሕወሓት ለሚባል ጅብ አሳልፎ ሰጥቶታል። እነዚህ አገር ወዳድ መሪዎችና የጦር መሃንዲሶች በደርግ ቢላዋ መታረዳቸው የተፈጠረው ብሄራዊ ክፍተት እንዳለ ሆኖ፣ ዐማራውን ለማጥፋት ለተነሱት ሻቢያ፣ ህወሓትና ኦነግ ተዋግተው የማያገኙትን ድል አጎናጽፏቸዋል። ፀረ-ዐማራ ጎሳ-ተኮር ፌደራሊዝም መሰረት ሊይዝ የቻለው ከዚህ ጭፍጨፋ በኋላ ነው። በእብሪት፣ በድንቁርናና ስካር ናላቸው የዞረው የደርግ አለቆች አገር ወዳድ ዐማሮችን በጂምላ ጨፍጭፈው ሲጨርሷቸው የዐማራ ታሪካዊ ጠላቶች ምዕራባውያን ክፍተቱን ተጠቅመው ሐህወሓት አስፈላጊውን ድጋፍ (Critical Support) በማድረግ የሚፈልጉትን አገልጋይ መንግሥት ምኒልክ ቤተመንግሥት አስገብተዋል። ስለሆነም መንግሥቱን የሚያደንቁ ሰዎች የድ*ቁ*ር*ና አድናቆት ካልሆነ በስተቀር የሚደነቅበት አንዳች ምክንያት የለም። መንግሥቱን ማድነቅ ማለት ያሁኑን አብይ አሕመድ እንደማድነቅ ይቆጠራል።

ሰሞኑን መንግሥቱ ኃይለማርያም የተባለን የምድራችን ጨካኝና አረመኔ ሰው ብዙዎች እንደ ሀገር ወዳድና እንደ ጀግና ቆጥረው እያሞካሹ ሲጽፉ ተመልክቻለሁ። የእነዚህ ሰዎች ትልቁ ችግር ታሪክን በሚገባ አለማወቅ በመሆኑ አድናቆታቸውም ከአለማወቁ ነው። መንግሥቱ ኃይለማርያም ማለት ዐማራውን በሕይወቱ እያለ በቁመናው ቁርበቱን የገፈፈ፣ የዐማራውን ዐይን በጋለ ብረት እየወጋ ያፈሰሰ፣ የወንዶችን ብልት ውኃ እየሞላ ፊያሽኮ እያንጠለጠለ ያንኮላሸ፣ በሰው ጆሮ የፈላ ውኃ እያፈሰሰ ያሰቃየ፣ ሠላማዊ ሠልፈኞችን በጥይት ገድሎ የተገደሉበትን የጥይት ዋጋ ካልከፈላችሁ ሬሣቸውን አልሰጥም እያለ ሬሳቸውን በገንዘብ የቸበቸበ፣ በቀይ ሽብር ስም በመንገድ ላይ የሚሄደውን በአደባባይ የቆመውን ዐማራ ያለፍትሕ በጭካኔ በመደዳ የጨፈጨፈ፣ እድሜ ልኩን ጥሮ ግሮ ያፈራውን ንብረቱን ቀምቶ ለረሃብ የዳረገ የዘመናችን አብይ አሕመድ እንጂ ፈጽሞ የሀገር ፍቅር የነበረው ሰው አይደለም። በኮሎኔል አብይ አሕመድና በኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም መካከል ምንም ልዩነት የለም። አብይ የበሻሻ ኦሮሞ ተወላጅ ሲሆን፣ መንግሥቱም የፉሪ ኦሮሞ ተወላጅ ነው። ሁለቱም አሻጋሪ ነን ብለው ሥልጣን ያዙ። ህዝቡ አሜን አለ። መንግሥቱ "ኢትዮጵያ ትቅደም" ብሎ እንደተነሳው ሁሉ አብይ አሕመድ "አዲሲቲን ኢትዮጵያ እፈጥራለሁ" አለ። ኢትዮጵያዊያን አማን አሉ። የሀገሪቱን ስር መሰረት የሚሆኑ ተቋማትን እፈጥራለሁ አሉ። ኢትዮጵያዊን አሜን አሉ፡፡ ዲሞክራሲያዊ ነፃ ምርጫ እናደርጋለን አሉ። ኢትዮጵያዊን አሜን አሉ፡፡ እየዋለ እያደረ ግን በአሸብራቂና አደንዛዥ ቋንቋ የተደበቁት አብይ አሕመድና መንግሥቱ ድብቅ አውሬአዊ ባህሪ ተገለጠ። መንጌ ለ17 ዓመት፣ አሁን ደግሞ አብይ አሕመድ ለአምስት ዓመት የመቃብር መሬት እስኪጠብ ዐማሮችን ጨፈጨፉ። መንግሥቱ ኃይለማርያም በ1966 ዓ.ም. የብቸና አርሶአደሮች ለጠየቁት ጥያቄ የተሰጣቸው ምላሽ በሻለቃ እንዳለ ተሰማ የሚመራ የደርግ ወታደር ልኮ ከአንድ ሺህ የበለጡ የጎጃም አርሶአደሮች መጨፍጨፍ ነበር። የጎጃም ዐማራ አርሶአደሮችን ለማንበርከክ ደርግ ሄሊኮፕተሮችና ሞርታሮችን ከመጠቀሙም በላይ ለወታደሮቹ የተሰጠው ትዕዛዝ የተገኘውን ዐማራ ሁሉ ግደል የሚል ነበር። ከተገደሉት ውስጥ በጣም ወጣቶቹ ወንድማማቾቹ ምኒልክና ግርማ ገሠሠ፣ አካለ ስንኩላን የነበሩት አቶ ወበት፣ አቶ አደም፣ በጣም የሸመገሉት የዘጠና ዓመቱ አባ ዑመር የሚታሰቡ ናቸው። አንዲት ሴትዮም ከሰባት ልጆችዋ ጋር ጎጆዋ ውስጥ እንዳለች ተቃጥላ ሞታለች። ከዚህ ጊዜ ጀምሮ የደርጉ ሻለቃ እንዳለ "የብቸናው አራጅ" ተብሎ ይታወቃል። (ባቢሌ ቶላ፣ ቀዩ ሽብር በኢትዮጵያ፣ ገጽ, 40) መንግሥቱ ኃይለማርያም "ነጭ ሽብርን በቀይ ሽብር እናሸንፋለን" (We shall beat back White Terror with Red Terror) በሚል ሁለት ደም የተሞላበት ጠርሙስ በማውጣት መሬት ላይ ከደፋ በኋላ፣ በቀይ ሽብር ስም በመቀሌ፣ በጅማና በአርባምንጭ ካፈሰሰው ደም ይልቅ በጎንደር፣ በጎጃም፣ በወሎና በሸዋ በክላስተር ቦምብ፣ በታንክ፣ በመድፍ እና በጥይት ያፈሰሰው የደም ጎርፍ ይልቃል። ደብረ ማርቆስ በ1969 ዓ.ም. በጥቅምት፣ በየካቲት፣ በሰኔና ነሐሴ፣ ውስጥ የጅምላ ርሸናዎች ተካሂደዋል። ከደሴና ከኮምቦልቻ ገረንገብ ውስጥ በ1969 እና እንደገናም ነሐሴ 1970 ዓ.ም. ውስጥ እሥረኞች በቋርጥ በቋርጥ እየተወሰዱ ተረሽነዋል። ከሚያዝያ 23 እስከ ግንቦት 7 ቀን 1969 ዓ.ም. ብቻ ደርግ ራሱ 1,713 ሰዎችን በጎንደር፣ ሲዳሞ፣ ሐረርጌ፣ ባሌ...ወዘተ ፀረ አብዮተኞችና አድኀርያን በሚል እንደረሸነ ገልጿል። ከታኅሣሥ 7 ቀደም ብሎ ከአዲስአበባ 385 እሥረኞች፣ ከወሎ 74፣ ከጎንደር 56 ተገድለዋል።(ባቢሌ ቶላ፣ ቀዩ ሽብር፣ 163) በደርግ ዘመን በባሕርዳር ከተማ ብርሃኔ ኪዳኔ የተባለ ዕድሜው 25 ዓመት የነበረ ጠቅላላ ልብሱን እንዲያወልቅ ከተደረገ በኋላ ዕርቃነ ሥጋው ላይ ቤንዚን እንዲርከፈከፍበት ተደርጎ በእሳት ተቃጥሏል። ሀሰኑ አልቃሲም ጎንደር እሥርቤት ቤት ግብረ ሰይል ሲፈፀምበት ሙቶ የተዘነጣጠለ ሬሳው ለትትርዒት እንዲታይ አውራ ጎዳና ላይ ተወርውሯል። ዕድሜዋ 25 መኖርያዋ ዳባት የነበሩ እታገኝ ብርሃኑ የአምስት ወር ነፍሰጡር ግብረ ሰይል ተፈጽሞባት ተገድላ አውራ ጎዳና ላይ ተጥላለች። ከሷ ሬሳ ጋር ፈንቱ ገላው የተባለ የሌላ እሥረኛ የተቆራረጠ እሬሳ አብሮ ለትርዒት ቀርቧል። ጎንደር ውስጥ መምህር የነበረው የ34 ዓመቱ ዮናስ አዲሱ "የኢሕአፓ ከፍተኛ አመራር ነህ" በሚል ተይዞ ግብረ ሰይል ሲፈፀመበት ከቆዬ በኋላ፣ ጥቅምት 1969 ዓ.ም. ከሆስፒታል በቃሬዛ እንዲወጣ ተደርጎ ከነሕይወቱ ወደመቃብር ውስጥ ተወርውሯል። (ባቢሌ ቶላ፣ ቀዩ ሽብር፣ 176-177) በመንግሥቱ ጭካኔና አውሬነት በዚህ መልኩ እልፍ የዐማራ ልጆች አሥር ቤት ውስጥ እንዳሉ ሞተዋል፣ ግብረ ሰይል ሲፈጸምባቸው ሞተዋል፣ በነጻ እርምጃ ሞተዋል፣ በደም የተበከሉና ዝንጥልጥላቸው የወጣ እሬሳዎች በመስቀለኛ መንገዶች ላይ፣ በዋና አውራ ጎጃናዎች ላይ፣ እቤቶች አጠገብ ይጣሉና ለአንድ ቀን ትርዒት ሆነው ታይተዋል። በዚህ አሰቃቂ እልቂት ከሁሉም በላይ የዐማራው ሕዝብ ለብዙ ጊዜያት በአንገት መድፋት ቆፈን (trauma) ውስጥ እንዲገባ ሆኗል። ከሁሉም በላይ ቀይ ሽብር በዐማራ ምሁራን ላይ ያነጣጠረ ነበር። አንዳርጋቸው ፅጌ የሚለውን እንስማ፣ "በአስከፊ የቀይ ሽብር ጭፍጨፋ በሺዎች የሚቆጠሩ ታጋይ ዐማራ ምሁራን አለቁ። ከአንድ ዓመት በፊት በተደረሰበት ቆጠራ በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ በቀይ ሽብር ያለቀው የሕዝብ ቁጥር 54 ሺህ ደርሷል። ከዚህ ውስጥ የከተማውን የዐማራ ሕዝብ ብዛትና የአማራውን ምሁር ሠፊ የፖለቲካ ተሳትፎ ግምት ውስጥ በማስገባት ጭፍጨፋው ክፉኛ የዐማራውን ሕዝብ እንደጎዳ ማየት ይቻላል። በጎጃም፣ በወሎ፣ በጎንደር በተለያዩ ከተሞችም ቁጥሩ በጣም ብዛት ያለው ወጣትና ምሁር በቀይ ሽብር ረግፏል።" (የአማራው ሕዝብ ከዬት ወዴት፣ 51) ኅዳር 14 ቀን 1967 ዓ.ም. ደርግ ከወሀኒ ቤትና ከሆስፒታል እያወጣ በውድቅት ሌሊት ከፈጃቸው 59 ባለሥልጣኖች መሀከል ከኤርትራ ሌ/ጀ ኢሳያስ ገብረ ሥላሴ፣ ሌ/ጀ አማን ሚካኤል አምዶም፣ ዶ/ር ተስፋዬ ገብረ እግዚእ፣ ሻምበል በላይ ፀጋዬ፣ ከኦሮሞ ሌ/ጀ አበበ ገመዳ፣ ሻለቃ ብርሃኔ ሜጫ፣ ቄስ ጉዲና ቱምሳ ከእነዚህ ከ7ቱ ሰዎች በቀር የቀሩት ዐማራዎች ናቸው። (በሪሁን ከበደ፣ 806) ደጃዝማች ፀሐዩ ዕንቆ ሥላሴ በመንግሥቱ ኃይለማርያም ጭካኔ ከተረሸኑት 59'ኙ ሰዎች መካከል አንዱ ናቸው። ታናሽ ወንድሞቻቸው ክፍሌዕንቆ ሥላሴ፣ ደጃዝማች ወርቁ ዕንቆ ሥላሴ እና ፊታውራሪ ታደሰ ዕንቆ ሥላሴ በመንግሥቱ ቀጥተኛ ትእዛዝ ተረሽነዋል። አራቱም ዐማሮች የአንድ አባትና ልጅ ናቸው። ከአባታቸው ጀምሮ ሁሉም ቆራጥ፣ ቆፍጣና፣ አልበገር ባይ በሰሜን ሸዋ ቆላማ ሥፍራዎች እየተዘዋወሩ ከጥሊያን ጋር የተፋለሙ አርበኞች ነበሩ። የጥሊያን ጥይት ያልገደላቸውን እነዚህን የመርሐቤቴ ጀግኖች የመንግሥቱ ሰይፍ ግን ቀላቸው። ምን ይሄ ብቻ የእናታቸው የአጎት ልጅ ደጃዝማች አእምሮ ሥላሴን ከተገደሉት 59 ከፍተኛ ባለሥልጣናት መካከል አንዱ ናቸው።

photo content
+3

#ሼር_ፖስት! በኢትዮጵያ ታሪክ ገዳማትን የደፈሩት ጥሊያንና ሕወሓት ነበሩ። አሁን የኦህዴድ መራሹ የብልፅግና መንግሥት ታሪካቸውን ተጋርቷል። በአምስቱ የጥልያን ወረራ ወቅት ጥሊያን በመርዝ ጋዝ፣ ቦምብ፣ መድፍና መትረየስ በፈጸመችው ጥቀት በድምሩ 2,000 በላይ ቤተ ክርስቲያኖችን አቃጥላለች። ጎጃም የደብረ ጽሞና ቤተክርስቲያን በጥሊያን አውሮፕላን ቦምብ ነዷል። ዲማ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ጣራ ላይ ሁለት የአውሮፕላን ቦምቦች ጥለዋል። መተማ የማኅበረ ሥላሴን ገዳም መነኮሳት እና የደብረ ሊባኖስ መነኮሳት በግፍ ረሽነው አውሬ እንዲበላቸውም የትም ተወርውረዋል። በ1928 ዓ.ም. ማኅበረ ሥላሴን በከባድ መሳሪያና በአውሮፕላን አቃጥለውታል። ከዚህ ድፍረት ከተሞላበት የፋሽት ጥቃት ቀጥሎ ሕወሓት አማራ ክልልን በወረረ ግዜ በታሪካዊና ሃይማኖታዊ ቅርሶችን ዘርፏል፤ ካህናትና መነኮሳትን ገድሏል። ጠለምት ውስጥ ወይቀል ኪዳነምህረት ቤተክርስቲያንን አፈራርሶታል። በኤፍራታና ግድም ወረዳ የቆሬ ሜዳ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያንን ኢላማ በማድረጋቸው ቤተ ክርስቲያኑ ከአገልግሎት ውጪ ሆኗል። በዚህ ሰይጣናዊ ቡድን ሰሜን ጎንደር ዞን ዳባት ወረዳ ጭና ቀበሌ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን በቤተ-መቅደስ ውስጥ ካህናትን የፍጥኝ አስሮ እያሰቃየ (tortured) ረሽኗል። ቤተ መቅደስ ውስጥ በግዳጅ አዘፍኗቸዋል። ይባስ ብሎ እዛው ቤተ መቅደስ ውስጥ ማብሰያ ምድጃ ሰርተው በግ አርደው በምጣድ ጠብሰው ተመግበዋል። ከዚህ ዘግናኝ ግፍና በደል (horrifying atrocities) በኋላ ደግሞ ተረኛው የኦህዴድ ብልፅግና እንደ ደርግ እና ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ጦር አዝምቶ ጎጃምን እያመሰው ይገኛል። በተለይም በምስራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ኤሊያስ ወረዳ ደገሎ ቀበሌ፣ ብሔረ ብፁዓን ሥላሴ መልከአ አንድነት ገዳም በሞርተር፣ በተለያዩ ከባድና የቡድን መሳሪያዎች ጥቃት ተፈጽሞበታል። በሩዋንዳ የፖሊስ አባል የነበረው ፉልጌንሴ ካይሼማ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተሸሸጉ 2 ሺህ ቱትሲዎች እንዲገደሉ ትዕዛዝ ሰጥቶ እንዳስገደላቸው ሁሉ የኦህዴድ ብልፅግናው ኮሎኔል አብይ አሕመድ በሥላሴ ገዳም የሚኖሩትን መነኮሳት በሞርተር እንዲጨፈጨፉ አድርጓል። እስካሁን ባለው መረጃ ለለተከታታይ አምስት ቀናት በተፈጸመ ጥቃት በገዳሙ ይኖሩ ከነበሩት ከ600 በላይ ሰዎች ብዙዎች ተገድለዋል፣ ቆስለዋል ሌሎች ደግሞ ተበትነዋል።

photo content
+4

#ሼር_ፖስት! በኢትዮጵያ "የሥራ ቋንቋ" በሚል እንዲጠፋ የተፈረደበት የአማርኛ ቋንቋ በቻይና ዩኒቨርሲቲዎች ለማስተማሪያ አገልግሎት የሚውሉ የአማርኛ መጻሕፍት ተመርቀው መነበብ ጀምረዋል። አማርኛ ቋንቋን በመጀመሪያ ዲግሪ ስታስተምር የቆየችው ቻይና አሁን ደግሞ ለማስተማሪያነት የሚውል የአማርኛ መማሪያ መፅሐፍት አሳትማለች። መጽሐፉ ሲመረቅ ቻይናዊያን ተማሪዎች በአማርኛ ግጥምና መነባንብ አቅርበዋል። ወዳጄ ...አማርኛ ቋንቋ እንደሆነ ከዛሬ 1700 በፊት ከአኩስም ሰሜን ምሥራቅ በአሕፈሮም ወረዳ መዝብር ቀበሌ ከዕዳጋ ረቡዕ በቅርብ ርቀት ከሚገኝ ቦታ በድንጋይ ተጽፎ የተገኘ ቋንቋ ነው። ኢትዮጵያን ከ1307 እስከ 1551 ዓ.ም. ያስተዳደሩት 6 ነገሥታቶች ማለትም የዐፄ ዓምደ ጽዮን፣ ቀዳማዊ ዳዊት፣ ዐፄ ይሥሐቅ፣ ዐፄ ዘርዓያዕቆብ፣ ዐፄ በእደ ማርያም እና ዐፄ ገላውዴዎስ ወታደሮቻቸው ጀግንነታቸውን ለማድነቅ በግጥም መልኩ በሰደድ እሳት፣ ፍሪዳ በሚሰብር አንበሳ፣ ጫካውን በቀንዱ እየገለጠ፣ መሬትን እየፎገረ በሚታይ ጎሽ፣ በተወርዋሪ እያነፃፀሩ የተራቀቁበት ቋንቋ ነው። ለምሳሌ፣ አረብ አስፈሪ” የሚባል ቄንጠኛ ፈረስ የነበራቸው ዐፄ ዓምደ ጽዮን የዛሬ 700 ዓመት፣ "አምደፅዮን ስም የዘራ በወጅ እስከ በጥር አሞራ ቃራ ይነስነስ ቃራ እንደጭራ በወንዶች ገራገራ በሃድያ እስከጉዴላ በባህር እስከኤርትራ አምደፅዮን ስም የዘራ" ተብሎ ተገጥሞላቸዋል። (Ignasio Guidi, "Le canzoni geez-amgariña in onore di Re Abissini," p.63) በ16ኛው ምዕተ ዓመት የመጀመሪያ አጋማሽ ከፖርቹጋል ወታደሮች ጋር አብረው የገቡት ኢየሱሳውያን (Jesuites) አቀላጥፈው ይናገሩት የነበረ ቋንቋ ነው። በተለይም ኢትዮጵያ ውስጥ ለሃያ ዓመታት ያህል የቆዬው ፔድሮ ፓኤዝ አማርኛን ቋንቋ አቀላጥፎ ይናገር ነበር። ለስብከት ከአንዱ የኢትዮጵያ ክፍል ወደሌላ የኢትዮጵያን ክፍል እየተዘዋወረ የካቶሊክን ሃይማኖት ለማስፋፋት የሞከረው በአማርኛ ቋንቋ ነበር። ብዙ የካቶሊክን እምነት የሚገልጡ መጻሕፍት ወደ አማርኛ እንዲተረጎሙ አድርጓል። ከእነዚህ ሥራዎች መካከል፦ 1. ጴጥሮስ ፖኤዝ ካርቲላ የተሰኘውን በጥያቄና መልስ መልክ የተዘጋጀውን መጽሐፍ ወደ ግእዝ ተርጉሞታል። በ1612 ዓ.ም. ደግሞ አካለ ክርስቶስ ወደ አማርኛ ተርጓሟል። 2. አልፎንዞ ሜንዴዝ 'Light of Faith' የሚል የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንን የሚነቅፍ መጽሐፍ ወደ አማርኛ ተርጉሞ ነበር። 3. አባ አንቶንዮ ፈርናንዴዝ 'Life of the Holiest Vergin Mary' እና 'Magseph Assetat, contra Llbellum Aethiopicum' የተባሉ ጽሑፎችን ወደ አማርኛ ተርጉሟል። 4. የሪቤራን የዕብራውያን ትርጓሜ ወደ አማርኛ መልሰዋል። 5.ቶሌዶ የጻፈውን የሮሜ ትርጓሜ ወደ አማርኛ መልሰዋል። 6. ብራስ ቪጋ ስለ ራእየ ዮሐንስ የጻፈውን ወደ አማርኛ ተርጉመዋል። 7. ማልዶናዶ የጻፈው የአርባዕቱ ወንጌል ትርጓሜ ወደ አማርኛ ተተርጉሟል። 8.በ1617 ዓ.ም. ሉዎስ ካርዲያ የአማርኛ/ግእዝ የሰዋስው መጽሐፍ አዘጋጅቶ ነበር። ጀርመናዊ የኢትዮጵያ ባህልና ቋንቋ ተመራማሪ ሒዮብ ሉዶልፍ የአማርኛ ሰዋሰውን በ1690 ዓ.ም. አሳትሟል። ሉዶልፍ ባሳተመው የአማርኛ ሰዋሰው “ዘአባ ጎርጎሪዮስ ድርሰት በአምኃርኛ” የተባለው አጭር ግጥም ተካቷል። የግጥሙ ይዘት ለእመቤታችን ለቅድስት ማርያም የቀረበ ውዳሴ ነው። በዚህም አማርኛም ወደ ላቲን የተተረጎመ የመጀመሪያው የአፍሪካ ቋንቋ ያደርገዋል። ወዳጄ፣ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ጋዜጣ አእምሮ መታተም የጀመረው በአማርኛ ነው። ከጣልያን ወረራ በፊት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው የሰሩት ህሩይ ወልደሥላሴ "ወዳጄ ልቤ፣ የልቅሶ ዜማ፣ አዲስ ዓለም፣ መጽሐፈ ቅኔ፣ የልብ ሐሳብ፣ የቡንያንን የመናኞች ጉዞ" የሚሉ መጽሐፎቹን ያዘጋጁት በአማርኛ ነው። በ1885 ዓ.ም. በጎጃም ክፍለሀገር በደብረኤልያስ የተወለዱት ዮፍታሄ ንጉሴ "አጥንቱን ልልቀመው"፣ "ወላድ ኢትዮጵያ" እና "ድንግል ሃገሬ ሆይ" እያሉ ለአርበኞች ወኔን የሚቀሰቅሱና የሚያጽናኑ ቀስቃሽ ጽሑፎችን ያዘጋጁ የነበሩት በአማርኛ ነው። በአፍሪካ ምድር በስነ ጽሁፍ ሀብት የበለጸገ ብቸኛውና ነባር የሆነው የአማርኛ ቋንቋ በ1981 ዓ.ም. በዶክተር አበራ ሞላ አማካኝነት አማርኛ የኮምፒውተር ፊደል ተዘጋጅቶለታል። በ2007 ዓ.ም.የአፕል የቴክኖሎጂ ማዕከል አማርኛን ከዓለምም ግዙፍ ቋንቋዎች ተርታ መድቦ የቴክኖሎጂ ቋንቋ አድርጎታል። በ2008 ዓ.ም. የጎግል የመተርጎሚያ ቋንቋ ለመሆን ችሏል። አማርኛ ከሴማዊ ቋንቋዎች መካከል ከአረብኛ ቋንቋ ቀጥሎ በአለም ላይ በሁለተኛ ደረጃ የሚነገር ቋንቋ ነው። አማርኛ ቋንቋ በኢትዮጵያ "የሥራ ቋንቋ" በሚል ቢገለልም ዓለምአቀፍ ግስጋሴውን ግን ቀጥሏል። ባለፈው በዝርዝር እንደጻፍነው የፑቲን ሀገር ራሽያም ከመጪው መስከረም ጀምሮ ልጆቿን የአማርኛ ቋንቋ ለማስተማር ከወዲሁ ቅድመ ዝግጅት እያደረገች ነው።

photo content
+7