cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking ÂŤAccept allÂť, you agree to the use of cookies.

avatar

Infinity Vibes🇪🇹

No trash post only reality for any questions dm @heyecani_yok7

Show more
Advertising posts
273
Subscribers
No data24 hours
+137 days
+2330 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ከአስራ አምስት ቀናት በፊት ማጨስ ሊገድልህ እንደሚችል አነበብኩ; በማግስቱ ማጨስ አቆምኩ። ከአስራ ሁለት ቀናት በፊት, በጣም ብዙ ቀይ ስጋ ሊገድልዎት እንደሚችል አነበብኩ; በማግስቱ ቀይ ስጋ መብላት አቆምኩ። ከስምንት ቀናት በፊት መጠጣት ሊገድልህ እንደሚችል አነበብኩ; በማግስቱ ማንበብ አቆምኩ!!!🙈😂 እኔን ብሎ አንባቢ😏 @Infinity_vibee
Show all...
👍 1
[ል ክ ፍ ት...] . አዉቃለሁ ጠልተሽኛል፣ አትወጂኝም ይገባኛል፣ መቼስ አንዴ ለክፈሽኛል... (መቼስ አንዴ ታምሜያለሁ...) ዛሬም አንቺን አስባለሁ። (አዎ...) ከሄድሽ በሁዋላ... (ምወዳቸዉ ሴቶች) ማደንቃቸዉ ሴቶች (ከኔ ጋር ያደሩ) ከኔ ጋር የዋሉ፣ በጥቂቱም ቢሆን... አንችን ይመስላሉ። . ተመልከቻት እሷን፣ ዉብ አረማመዷን እግር አነሳሷን፣ ያ'ነጋገር ስልቷን ደግሞ አለባበሷን። "ቁርጥ ራስሽን!" (ማለት ቢያስቸግርም፣) የሆነ ነገሯ... እንዳ`ንቺ እንደሆነ አልጠራጠርም። (እያት ደግሞ ያቺን...) ካ'ፍንጫዋ በታች| ያለዉ ከፊል ገጿ፣ ከንፈርና ጥርሷ| የንግግር ድምጿ። ደግሞ ሳቅ ስትል... የጉንጯ ስርጉዳት፣ ያንቺን በመምሰሉ ነፍሴን ሲያሻፍዳት፣ ልቤን ሲያሟሽሻት...| አየሽኝ?| አየሻት? ፥ ፥ (እናልሽ...) ከብዙ ሴቶች ላይ ጥቂት አንችነትን... እያነፈነፍኩኝ፣ ያቺንም..|ያቺንም... "ወደድኩዋት" ስላልኩኝ፣ ባ'ገር በመንደሩ| "ሴሰኛ" ተባልኩኝ። ሰማሽልኝ ስሜን? ልክፍቴን ህመሜን? ስራብሽ ስጠማሽ..| በሰዉ አፍ መክረሜን? አየሽልኝ ህልሜን..? (አንቺን ባላገኝሽ) ካ'ምሳያሽ ጋራ ነኝ| እድሜ ዘላለሜን። {} @Infinity_vibee @Infinity_vibee
Show all...
✝️✝️✝️✝️"ዮም ፍስሀ ኮነ በሰንበተ ክርስቲያን እስመ ተንሥአ ክርስቶስ እም ሙታን ቀድሳ ወአክበራ እም ኲሎን መዋዕል አልዓላ  አማን  ተንስአ እም ሙታን """""""ህያውን ከሙታን መሀል ለምን ትፈልጋላችሁ  ተነስቷል በዚህ  የለም፤  ሉቃ 24:5 እንኳን  ትንስኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ መልካም  በዓል @Infinity_vibee
Show all...
❤ 2
ግን እናቴ ትሙት ይጨንቃል ሁሉም ደስተኛ ነው ሁሉም ተፍ ተፍ እያለ ነው ለበዓል ዝግጅት ግን እኔ ውስጤ ባዶ ነው ባዶ የሞተልኝን እንኳን በቅጡ አላመሰገንኩም ይቅር በለኝ ብዬ ሰግጄ በተመለሰኩ በደቂቃዎች ውስጥ ያሳምሙኛል ሰላም ያሳጡኛል መሞት እፈልጋለሁ ግን ከዛስ .... መኖርም እፈልጋለሁ ግን ከአምላኬ ሊያጣሉኝ ነው ... ነገ የለም ዛሬ የለም ሁሌም ህመም ውስጥ ስቃይ ውስጥ ከነሐጥያቴ ቤቱ መሔድ ከበደኝ ፈጣሪ ደራሲ ነው ይሉ የለ ሲኦልን ቤቴ አድርጌ ቆጠርኩ ... አልፆምኩም አላስቀደስኩም ዳንኪራም አልመታሁም ግን ጠፋሁ ጠፋሁ በቃ ... ሁሉም በዙሪያዬ ደስተኛ ነው እንዴት ህመሜን ልደብቀው
Show all...
🗿 1
Love don't pay the bills and money don't cheat.
Show all...
[በስቅለት ቀን ያጋጠመኝ አስገራሚ ክስተት] : መስገጃ ቦታ እንዳላጣ ብዬ በግዜ ብሄድም አልተሳካልኝም ነበር! የቤተክርስቲያኑ ቅጥር ግቢ በሰው ተሞልቶ ጠበቀኝ! ምንጣፌን ይዤ በአይኔ ክፍት ቦታ ስቃኝ ያየኝ አንድ አስተባባሪ "ና ቦታ ልስጥህ" ብሎ ወደ አንድ ቦታ መራኝና "እዚህ ጋ ተቀመጥ" ብሎ በእጁ ጠቆመኝ! ልጁን አመስግኜ ምንጣፌን አንጠፍሁና የአቅሜን ከሰገድሁ በኋላ ትንሽ ረፍት ለመውሰድ ተቀመጥሁ! ድንገት አንዲት ሴት አጠገቤ መጥታ ቆመች!ዕድሜዋ በሀያዎቹ አጋማሽ ላይ ነው!...በእጇ መስገጃ የሚሆናት ምንጣፍም ሆነ ምንም ነገር አልያዘችም!..ያደረገችውን ክፍት ጫማ አወለቀችና ጠጠሩ ላይ መስገድ ጀመረች!...የያዝኩት ምንጣፍ ሰፊ በመሆኑ ምንጣፉ ላይ ሆና እንድትሰግድ ነገርኳት!.."እሺ" ብላ አመስግናኝ ወደ ምንጣፉ ተጠጋች!...ፊቷን አየሁት!...ጉንጮቿ ደም መስለዋል..ሁለቱም አይኖቿ በዕንባ ብዛት በሚመስል መልኩ ቀልተዋል!...ደነገጥኩ!..."ምን ሆነሽ ነው?" ብዬ ልጠይቃት አልኩና "እኔ ማነኝ?" ብዬ መልሼ ተውኩት!...ተነሳሁና መስገድ ጀመርኩ!...ጎን ለጎን ሆነን መስገድ ጀመርን!...ብዙ ከሰገድኩ በኋላ ደከመኝና ተቀመጥሁ!...ልጅቷ ከገባች ጀምሮ አላረፈችም!...እየሰገደች ነው!...ድንገት ጎንበስ ስትል ዕንባዋ ምንጣፉ ላይ ጠብ ሲል ተመለከትሁ!...ድጋሚ ዝም ማለት አልቻልኩም!...እጇን ያዝ አደረኳትና "እህቴ እስቲ ትንሽ አረፍ በይ" አልኳት ዕንባዋን በነጠላዋ ጫፍ ጠራረገችና ተቀመጠች!..."ምን ሆነሽ ነው የኔ እህት...ምን ሆነሽ ነው ምታለቅሺው?" አልኳት!...ስጠይቃት ይበልጥ አለቀሰች!..."ማንም ምን ሆነሽ ነው ብሎ ጠይቆኝ አያውቅም እኮ" አለችኝ!..."እንዴት"? አልኳት...ረጅም አመት የምታውቀኝ ያህል አወራችልኝ!...ከእናቷ በቀር ምድር ላይ ማንም ዘመድ እንደ ሌላት አወራችልኝ!...እናቷ በጣም ሀብታም እንደ ነበረች አወራችልኝ!...እናቷ ከ 5 ወር በፊት እንደ ሞተች አወራችልኝ!...እናቷ ስትሞት የመኖር ትርጉም እንደ ጠፋትና ሹሾ ውስጥ እንደ ተዘፈቀች አወራችልኝ!...በዕንባ ብዙ ብዙ ነገር አወራችልኝ!...ላቋርጣት አልፈለግሁም!...ዝም ብዬ ሰማኋት!...መጨረሻ ላይ ዕንባዋን ጠራረገችና ፈገግ ብላ..."ታውቃለህ" አለችኝ..."ታውቃለህ እናቴ ከሞተች በኋላ መጀመሪያ ግዜዬ ነው ቤተክርስቲያን ስመጣ!...በእርግጥ የመጨረሻዬም ነው!...የመጨረሻዬ ስግደትም ስለሆነ ነው  ያለማቋረጥ ስሰግድ የነበረው ምን አልባት ቢምረኝ ብዬ!"...ብላ ትንሽ ዝም አለችና!..."ይቅርታ በማያገባህ ብዙ ጨቀጨኩህ!...አመሰግናለሁ ቻው በቃ" ብላኝ ተነስታ ሄደች!...ከሄደች በኋላ ስታወራቸው የነበረችው ነገሮች አይምሮዬ ላይ ማቃጨል ጀመሩ... "ታውቃለህ እናቴ ከሞተች በኋላ መጀመሪያ ግዜዬ ነው ቤተክርስቲያን ስመጣ!...በእርግጥ የመጨረሻዬም ነው" "የመጨረሻዬ ስግደትም ስለሆነ ነው  ያለማቋረጥ ስሰግድ የነበረው.... ምን አልባት ቢምረኝ ብዬ!" በድንጋጤ ከተቀመጥሁበት ተነሳሁ!...ከህዝብ መሀል በአይኔ ፈለኳት...በሩ አከባቢ ስትወጣ ተመለከትኩ...ጫማዬን እንኳ ሳላደርግ በፍጥነት ሄድኩ! : : የመኪናዋን በር ከፍታ ልትገባ ስትል ደረስኩባት!...እጇን ይዤ አስቆምኳት...ወደ ኋላ ዞራ አየችኝ... "እራስሽን ልታጠፊ ነው አይደል?" አልኳት! ምንም ሳትናገር እጇን አስለቀቀችና መኪናዋ ውስጥ ገባች...ምንም ብናገር...ምንም ባወራ በዚህ ስሜት ሆና ማድረግ ከፈለገችው ነገር እንደማትመለስ አውቃለሁ...ብቻ ግን እግዚአብሔር አንደበቴ ላይ ቃላቶችን አስቀመጠ.. "እግዚአብሔር ከ እናትም ከ አባትም በላይ እንደ ሆነ አታውቂም?...ተስፋን የሰጠን የታመነ እንደሆነ አታውቂም?....ክርስቶስ ተሰቅሎ አለምን ባዳነበት ዕለት አንቺ ትሞቻለሽ?"...አልኳት!....ተንሰቅስቃ አለቀሰች! : : መርሀ ግብሩ ካለቀ በኋላ ከማውቃቸው ደግ እማሆይ ጋ አገናኘኋት!...ፀለዩላት!...አረጋጓት!...እንደ እናት አቀፏት!...አባበሏት!..አይዞሽ አሏት!...  ዲያቢሎስ አስቦባት የነበረውን የሞትን ደብዳቤ ክርስቶስ ኢየሱስ በስቅለቱ ዕለት ሰቀለው!....ስሟን ጠየኳት!...ሩት አለችኝ.... : ሩት!....በእግዚአብሔር ምህረት ከሞት እና ከዘላለማዊ እሳት ያመለጠች ነፍስ! [እዮብ ዘ ማርያም] @Infinity_vibee
Show all...
👏 1
🤣የበዓል ገጠመኝ! ኮንዶሚኒየም ውስጥ መኖር ችግር ነው! ሁሉም ዶሮና በጉን በሩ ላይ አስሮ ብሎካችንን ኤልፎራ አስመስሎታል። እኔም ትናንት ሚስቴ በግ ካልገዛህ እያለች ስትነተርከኝ ጥቂት ብር ይዤ በግ ልገዛ ብወጣ አንድ ቀውላላ በግ ነጋዴ ሁለት ፊታቸው ላይ ከባድ ድብርት የሚታይባቸውን ከሲታ በጎች ይዞ ቆሞ አገኘሁና ጠጋ ብዬ «ልትሸጣቸው ነው?» አልኩት «እና ሐገር ላስጎበኛቸው ነው ካገሬ ይዣቸው የወጣሁት?»አለኝ «እንደው ኩነኔ አይሆንም እነዚህን መግደል?» ስለው ፈጠን ብሎ «አንቀህ ነው እንዴ ምትገድላቸው?» አለኝ «አይ ያው በቢላም ቢሆን ...» ብዬ ሳልጨርስ «ወንድሜ ካሳዘኑህ ውሰድና በጉዲፈቻ አሳድጋቸው» አለኝ «እሺ ስንት ነች እቺ?» አልኩት ወደአንዷ እየጠ ቆምኩ «በግ ታውቃለህ ማለት ነው። በጣም አስተዋይ በግ ነች እሷ» ብሎ ጀርባዋን መታ መታ ሲያደርጋት ወደጎን ፍንግል አለችና አቧራ ዋን አራግፋ ተነሳች። «እኔ አስተውሎቷ ምን ይሰራልኛል ላስተምራት አይደለም እኮ ምወስዳት» ስለው «ስምንት ሺህ ብር ክፈል» አለኝ «ስምንት ሺህ ብርማ አታወጣም» «በርግጥ ላታወጣ ትችላለች ነገር ግን እኔ 8 ሺህ ብር ነው የሚያስፈልገኝ» «ቀንስና ልውሰድልህ» አልኩት «አይ ወዳጄ በጓን ግን አይተሃታል? ውስጠ ወይ ራ እኮ ነች። መፍዘዟን አትይ። በዚያ ላይ በእንክብካቤ ነው ያደለብኳት» «ጭራሽ ደልባ ነው እንዲህ የከሳችው?» «አዎና! በርግጥ እኔ ስብእናዋ ላይ ነው የሰራሁት። በጥሩ ስነምግባር ነው ያሳደግኋት» አለኝ ቆፍጠን ብሎ። ሳቄን ለመቆጣጠር እየሞ ከርኩ «5ሺህ ብር ትሸጥልኛለ ...?» ብዬ ሳልጨርስ«ውሰዳት!» አለኝ በደስታ ተሞልቶ። ምነው ዝም ባልኩ ብዬ በይሉኝታ 5 ሺህ ብር ሰጥቼው በጓን ይዤ ልሄድ ስል መራመድ አቅቷት በቀስታ ስታዘግም «ቃሬዛ ቢኖርኮ ደግ ነበር» አለኝ ሰውዬው በጉን በሃዘን እየሸኘ። ተበሳጭቼ ዝም ብዬው ስሄድ «ወንድሜ እንደው ለነፍስ ትሆንሃለች መጀመሪያ የህክምና እርዳታ አርግላት» አለኝ መንገድ ላይ በጓን ያየ ሁሉ ከንፈሩን እየመጠጠ ያልፋል። አንዳንዱ እኔን እያየ አንገቱን በሃዘን ይነቀንቃል። በግ ላርድ ሳይሆን እንደአብርሃም ልጄን ልሰዋ ይዤ እየሄድኩ ነው ያስመሰሉት ። ሽምቅቅ እንዳልኩ ቤት ደረስኩ። ሚስቴ በጓን እንዳየቻት «ምንድነው ይዘህብኝ የመጣኸው?» ብላ ጮኸች። በጩኸቷ ከኔ ይልቅ የደነገጠችው በጓ ነች። አይኗን አስለምልማ መሬት ወደቀች! የመጀመሪያ ደረጃ እርዳታ ላደርግላት ሞከርኩ። አልነቃ ስትለኝ በአፌ ትንፋሽ ልሰጣት ሳጎነብስ ሚስቴ «በዚህ አፍህ እኔ ከንፈር ጋር ድርሽ እንደማትል እወቀው!»ስትለኝ ቀና ብዬ መጨረሻዋን ማየት ጀመርኩ ..ውይይ! አረፈች! በጣም የሚያሳዝን ሁኔታ ነው የገጠመኝ ጎበዝ። «ቆይ ግን ...የግድ ስጋዋን ለመብላት እኛ ልንገድላት ይገባል እንዴ? ያው ሞት ሞት ነው። በቢላም ሞተች በድንጋጤ ያው መሞቷ አይቀርም!» ስል ሚስቴ ሶስት ግዜ አማትባ «በል አውጥተህ ጣል» አለች። እኔ ግን ተስፋ አልቆ ረጥኩም! እቺን በግ እኮ ስጋዋን ፈልጌ ሳይሆን እንደበግ እንድትተውን ነው የገዛኋት። አክተር ደሞ አይሞትም ኦህኦህኦህኦህህ! ተመስገን! ነቅታለች ጎዶች «እልልልል ...» (አሉ እትዬ ዘርፌ የቤት እቃ (ማማሰያ ሳይቀር) እየሰረቀ ያሰለቻቸው ልጃቸው ሲታሰር) እንዲህ ነው እንጂ በግ! ዝም ብሎ መሞት አለንዴ? እኛ ሳንፈቅድላትማ አትሞታትም! አልኩ ለሚስቴ (አንዳንዴኮ እንደ አፍሪካ መሪዎች ሚያደርገኝ ነገር አለ)ሚስቴ መንቃቷን ስታይ «በል ቶሎ እረድልኝ» ብላ የአሉላ አባነጋን ሻሞላ የሚያህል ቢላ ይዛ መጣች። «አሁን ለዚች በግ ይሄን የሚያህል ቢላ መጠቀም ተመጣጣኝ እርምጃ ነው ብለሽ ታስቢያለሽ?» አልኳት «ወሬውን ተወውና ሳትሞት እረዳት» የሚል ቀጭን ትዛዝ ሰጠችኝ! ሻሞላውን ተቀብዬ ወደበጓ ስጠጋ አይኗን ከፈት አርጋ ቢላውን አየት አረገችና እንደሰው እንባዋ ባይኗ ሞልቶ ፀጥ አለችላችሁ! በቃ ሞተች!ብቻ በጣም የሚያሳዝን ጉዳይ ነው የገጠመን ወገን! ከሚስቴ ጋር ያደርኩትን አዳር አዳር አትበሉት። ለሊት ላይ ጠጋ ብዬ እያቀፍኩ «አይዞን እኛ ጤና የሚቀጥለው በዓል ምን የመሰለ ሙክት ነው ምናርደው» ስላት እንደ አለቃ ገብርሃና ገፍትራ ከግድግዳጋር አጋጨችኝ! ኤጭ አሁንስ መረረኝ! ጌታ ሆይ ትመጣለህ ወይስ እኔ ልምጣ? መልካም በዓል ✍️ዘውዳለም
Show all...
ታማኙ ይሁዳ ከሙት ባህር እየተነሳ የሚነፍሰው ንፋስ ፤ ሙቀት ያዘለ ነው። አንድ ጊዜ ኃይሉን አሰባስቦ ሲመጣ ጨርቅ ያስጥላል። ልጃገረዶች ቀሚሳቸውን ወደታች እየጎተቱ ከነፋሱ ጋር እየታገሉ ወደ አንዱ ጥግ እፍረት በወለደው ሳቅ እያሽካኩ ይፈተለካሉ። ገርበብ ተደርጎ በተከፈተው መስኮት በኩል የሚገባው ንፋስ መጋረጃውን እንደ ሰንደቅ እያነሳ ሲያርገበግበው ነበር የቆየው። ኃይል ጨምሮ ሲመጣ ግን መስኮቱን እንደ ልጃገረዶቹ ቀሚስ ጎትቶ የሚያስጥለው አላገኘም። ወስዶ ከግርጊዳው ጋር አላተመው። ጓ !! ተመስጠው በነበሩ ሰዎች መሃል ይሄ ድምፁ ከፍተኛ ነው። ዘኪዮስ ለንግግሩ ጆሮውን ጣል እንዳደረገ ተነስቶ መስኮቱን ሸጎረው። "መንገድም ፤ ህይወትም እኔ ነኝ" ይላል ድምፁ የቤቱ ማዕዘናት ላይ ፋኖሶች ተንጠልጥለዋል። ቤቱ የኖራ ድንጋይ ከሚባለው ነው የተሰራው። መሬቱ ሰሌን ለብሶ ጥግጥጉ ላይ የሀር አልጋ ልብስ የለበሱ ፍራሾች ተዘርግተዋል። በዚህ ፍራሽ ላይ ዛሬ ብዙ እንግዶች ተቀምጠዋል። ከገሊላ ወገን የሆኑ ፤ የሳምራዊያን ዘሮች ፤ አይሁዶች ፤ የተለያየን ነን የሚሉ በአንድ ላይ ተቀምጠዋል። አንድ ላይ ስለመሆናቸው ምክንያት የሆነው ደግሞ ዛሬ በመካከላቸው ቁጭ ያለው። ኢየሱስ ነው። ኢየሱስ የማሪያም ልጅ!! ማነው የውቅያኖስን ውሃ ጭልጥ አድርጎ ጠጥቶ 'እፎይ' ብሎ ጥሙን የቆረጠ ? ማነው ሀሳብን ሁሉ ጥሎ ራሱን ባዶ አድርጎ ከደመና በላይ ወቶ የተደላደለ ? ማነው ? ማንም !! ኢየሱስን ለቅስፈት መመልከት ግን ከዚህ ሁሉ በላይ ፍፁም እርካታ ፤ ፍፁም ሰላም ነው። ለዚህም ነው ሀገር ምድሩ ሁሉ "ጌታ ሆይ " እያለ የሚከተለው። ከሚከተሉት ውስጥ የተመረጡት ዛሬ በዘኪዮስ ቤት አብረውት አሉ። ከእነሱ ውስጥ የአስቆረጦሱ ይሁዳ አንዱ ነው። ይሁዳ ወደዚህች ከተማ ከሶስት አመት በኃላ መመለሱ ነው። አሁን በቤቴ እረፉ ብሎ ካስተናገዳቸው ሰውዬ በቅርብ ርቀት ባለች መንደር ነበር የሚኖረው። በዛ መንደር ውስጥ ሰንበት ሲሆን 'የጥቅምት አበባ' መስላ መታ ወደ ከተማው ዳርቻ ወዳለ ኮረብታማ ቦታ ይዛው ሄዳ 'በሚፍነከነክ ሳቋ ፤ በሚደንሰው ሰውነቷ ፤ በሚንዛለፈው ፀጉሯ ፤ 'ዘራፍ' በሚለው ደረቷ " አለሙን አሳይታ ፤ ፍሳውን አስዳስሳ የምትመልሰው 'ሴፔራ' አለች። ይሁዳ ወደዚህ ቤት ከገባ ጀምሮ የሚያስበው ስለ እርሷ ነው። "በህይውት ትኖር ይሁን ? አግብታስ ቢሆን ? ያን ፀጉሯን ተቆርጣው እንዳይሆን ብቻ " ይሁዳ ከዚህ ውጪ ሌላ ነገር ሊያስብ አልቻለም። ይሁዳ በሀሳብ እንደተዋጠ ኢየሱስ "እንካቹሁ ተቃመሱ" ብሎ ለደቀመዛሙርቱ የሳጣቸው ቂጣ እርሱ ጋር ደረሰ ከላዩ ላይ ቆንጠር አርጎ አሳልፎ ለጴጥሮስ ሰጠው። ተከትሎ በዋንጫ የሆነ ነገር መጣ። ተቀብሎ አየው። ወይን ነው። ከሶስት አመት በፊት የተውው ነገር። ወይን ስትቀምስ ሙዚቃ የሚመስል ሳቅ የምትስቀው ሴፔራ መጣችበትና አፉ በሳቅ ተሞላ። ወንጫውን ከፍ አድርጎ ከንፈሩን አስነክቶ ሽራፊ ሳቁን ዋጫው ውስጥ ሳቀ። በቤቱ ፀሎት ሆነ። ሁሉም በአንድ ላይ ተጉ። ይሁዳ ግን ሆዴን አመመኝ ብሎ ጥጉን ይዞ ቁጭ አለ። ትንሽ ቆይቶ በሩን ከፍቶ ወጣ። ከቤቱ ልክ እንደወጣ ጉልበቱ አገጩን እስኪነካ ድረስ እያነሳ ሮጦ ወደነ ሴፔራ መንደር ገባ ! የተቀየረ ነገር የለም። መንደሩ ያው በፊት እንደሚያውቀው ነው። በቀጥታ ወደ ሴፔራ ቤት ሄዶ በቀስታ ቆረቆረ። ሴፔራ ነበር የከፈተችው። "ማን ልበል" አለችው ፤ ሳይነግራት በድንገት የጠፋባት ይሁዳ መሆኑን አለየችውም። ይሁዳ ግን አዘነ ! ሴፔራ ተጎሳቁላለች። ግንባሯ ላይ ያለችው ፀሀይ ጠልቃለች። እንደፈራው ፀጉሯንም ተቆርጠዋለች። የጎደጎደው አይኗ ከህይወት አርቋታል። ሴፔራ በጎረምሳ እጅ ላይ እንዳለች ሎሚ ሟምታለች። በይሁዳ ጉንጭ ላይ የሚፋጅ እንባ ወረደ ! ፈጥኖ አቅፉ ወደ ጉያው ሸጎጣትና ስቅስቅ ብሎ ማልቀስ ጀመረ። ጥሎት በመሄዱ ራሱን እየወቀሰ ይሁዳ አለቀሰ !! ይሁዳ ከሴፔራ ተለይቶ ሲመለስ መንገድ ላይ የተባባሉትን መልሶ እያሰበ ነበር። ከንፈሩን ስማ " ድጋሚ ጥለህኝ አትሂድ" ስትለው 'እሺ' ብሏታል። "ትንሽ ሳንቲም ብናገኝ ፤ የመኮመሪያ ቤት ከፍተን ኑሯችን ይደላደላል" ስትለውም አምኗት "ልክ ነሽ" ብሏታል። ነገር ግን ሳንቲሙን ከየት እንደሚያመጣው ሊገባው አልቻለም፤ ብቻ "መላ አላጣም" እያለ ነው ወደ ዘኪዮስ ቤት የተመለሰው። በአንድ ማለዳ በጌቴሰማኔ እያሉ ሴፔራ በስትክክል ያለበሰችውን ሻርፕ ወደ ግራ ወደ ቀኝ እያማታች መጣች። የተጣደፈች ትመስላለች። እንደ ደረሰች ከህዝብ ማሃል እጇን ከፍ አድርጋ ለይሁዳ አውለብልባ ምልክት ሰጠችው። ይሁዳ እንዳያት ሰዎችን ይቅርታ እየጠየቀ አቆራርጦ መጣ። ሴፔራ የይሁዳን ክንድ ለቀም አድርጋ ወደ ጥግ ወሰደችውና "እንኳን ደስ አለህ " አለችው "ለምኑ" አላት " ብዙ ብር ሊኖርህ ነው " "እንዴት ሆኖ " "ቄሳሮች ሲፈልጉህ ነበር " "እኔን? ለምን? " "ኢየሱስ ወንጀለኛ ነው' ነው የሚሉት ፤ ሊቀጡት ፈልገዋል መሰለኝ" "እና" "ሊይዙት ብለው የትኛው እንደሆነ አለዩትም" "ልክ ነው " አለ ይሁዳ " አይለዩትም ፤ ኢየሱስና ዮሀንስ አንድ ነው መልካቸው። ከአፉ ላይ ቀበል አርጋ "እኮ" አለች ሴፔራ "እነሱም የፈለጉኹ ለዚህ ነው። አንዳቸውን በምልክት አሳልፈህ እንድትሰጣቸው ይፈልጋሉ። ለዚህም '30 የወርቅ ዲናር አለህ" አለችው። ድምፆ ውስጥ የኔ ጌታ ፤ የሚል ማባበል ነበረው። በመሸም ጊዜ ትምህርቱ አብቅቶ ስለነበር ደቀመዛሙርቱ ሰውን ሁሉ በአቅራቢያው ወዳለ መንደር ሸኝተው እነርሱ ኢየሱስን ይዘው ወደ ተራራው ወጡ። ይሁዳ ቀን ላይ ወደ ቄሳሮቹ ጋር ሄዶ ተስማምቶ 30 ዲናሩን ተቀብሎ ነው የመጣው። "ስንመጣ ኢየሱስ የሆነውን ስመህ ምልክት ስትሰጠን እንይዘዋለን" ሲሉት እሺ ብሏል። አሁን ከተራራው ላይ ፈንጠር ብሎ ለብቻው ተቀምጦ በሀሳብ ተጠምዶል።ዕቅዱ ዮሀንስን "ኢየሱስ ነው " ብሎ ስሞ አሳልፎ መስጠት ነው። 'ያበላኝ ፤ያጠጣኝ' ኢየሱስ ላይ ከምጨክን ምንም የማልግባባው ዝምተኛው ዩሀንስ ቢሆን ይሻላል ብሎ ደምድሟል። ሚጠብቀው መምጣታቸውን ነው። ብዙም ሳይቆዩ ቄሳሮች መጡ ! ይሁዳ ፈንጠር ብሎ ተነሳ። ከፊት ላለው ቄሳር ሰላምታ ሰቶ እየመራ ወደ ተሰበሰቡበት ቦታ ይዟቸው ሄደ። አጋጣሚ ሆኖ ኢየሱስና ዩሃንስ ጎን ለጎን ቆመው ነበር። ይሁዳ ፈንጠር ብሎ ተራምዶ ኢየሱስና ዩሀንስ ፊት ቆመ። ዩሀንስን ተመለከተው ፤ ደሞም በተራ ኢየሱስን አየው። አሁን በሁለት ምርጫዎች መሀል ነው የቆመው ። የመምረጥ ግዴታ ደግሞ አለበት። ቄሳሮች ከኃላ ተላልፎ የሚሰጣቸውን ሰው ለመሸለት ሻሞላቸውን ስለው እየጠበቁት ነው። እንደ ቃሉ ኢየሱስን አሳልፎ መስጠት ፣ ወይም ዋሽቶ ገራገሩን ዮሀንስን ስሞ ወደ እርድ መላክ - - - ይሁዳ ይሄን ሀሳብ በፍጥነት እያመነዥገ ወደ ዩሃንስ ተጠጋና እጁን ትከሻው ላይ አድርጎ መታ መታ አድርጎ ተወውና ኢየሱስን አቅፎ ስሞት ፊቱን አዙሮ ሄደ- - - ✍️ Henok Mengistu @Infinity_vibee @Infinity_vibee @Infinity_vibee
Show all...
You can earn up to 50,000 ETB per month online just by using your phone or computer at home. When you invite 1 person to Mela Events bot using the Mela Events Bot invite link, 30 Birr will be added to your Mela bot account. When you invite 95 users to Mela Events bot  you can withdraw  2700 birr. Your invitation link https://t.me/MelaEvents_Bot?start=r05953287570
Show all...
ማርች 8 አስመልክቶ እኔ ስቂያለሁ እናንተም ሳቁና ሼር አርጋቹ ለጉዋደኞቻቹ አጋሩት! በጣም የምትመቸኝ ወግ...“በጥሩ የፍቅር ግንኙነት እንዴት መኖር ትችላላችሁ” በሚል ሴሚናር ላይ በርከት ያሉ ባለ ትዳር ሴቶች ተገኝተው ነበር።ሴቶቹም እንዲህ የሚል ጥያቄ ቀረበላቸው ፦ “ምን ያህሎቻችሁ ባላችሁን ታፈቅራላችሁ?” ሁሉም እጃቸውን አወጡ።ተከታዩም ጥያቄ ፦ “ለመጨረሻ ጊዜ ለባሎቻችሁ እንደምታፈቅሯቸው የገለፃችሁት መቼ ነው?”አንዳንዶቹ “ዛሬ”፣ የተወሰኑት “ትላንት” ፣ ቀሪዎቹ እንደማያስታውሱት ተናገሩ።ከዛም ሴቶቹ በስልካቸው ሜሴጅ የሚከተለውን መልእክት ለባሎቻቸው እንዲልኩ ተጠየቁ ፦“ የኔ ጣፋጭ ፣ በጣም አፈቅርሃለሁ"ከባሎቻቸው ከተመለሱት መልሶች በከፊል፦ .1— ደግሞ ዛሬ ምን ተፈጠረ? መኪናውን ዛሬም አጋጨሽው? 2— እህ ፣ የልጆቼ እናት ፣ ዛሬ በጤናሽ ነው? 3— አልገባኝም ! ምንድነው ማለት የፈለግሽው? 4— አሁን ምን አያደረግሽ ነው? ዛሬ እንኳ በጭራሽ አንላቀቅም። 5— ??!!?? 6— በይ አሁን ዙሪያ ጥምጥም አትሂጂ ፣ ዝም ብለሽ ምን ያህል እንደምትፈልጊ ብቻ ንገሪኝ! 7— ምንድነው? በህልሜ ነው? 8— ይሄን ሜሴጅ ለማን ልትልኪው እንደነበር ካልነገርሽኝ ዛሬ ገደልኩሽ!!!!!!! 9— በቀን እንዳትጠጪ ተነጋግረን አልነበር? እባክሽ አሁንም ከዚህ በላይ አትጠጪ!!ምርጡ መልስ ፦ ..10— ይቅርታ ፣ ማን ልበል????? @Infinity_vibee
Show all...
😁 5