en
Feedback
seıd (official channel) 🕋🇪🇹

seıd (official channel) 🕋🇪🇹

Open in Telegram

“ዕውቀትንና ዖለሞችን ወዳጅ!፥ የ’ነርሱ አገልጋይ መሆንን የምመኝ ደካማ #የአሏሕ ባሪያ ነኝ!” ሐሳብ መስጫ - @seidmuha tiktok.com/@habeshynegn facebook.com/habeshynegn youtube.com/@habeshynegn ⊰ ♡ ⫹⫺ㅤ ⎙ㅤ ⌲ ⊱ ࿙ ᴸⁱᵏᵉ ˢᵘᵖᵖᵒʳᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳᵉ ࿚

Show more
1 304
Subscribers
-224 hours
+27 days
+430 days
Posts Archive
የሱፍዮች ፊት አውራሪ ሰዪዱ አህመዱ አር-ሪፋዕይ [ቀደሰሏሁ ሲረሁ] ከንግግራቸው መካከል እንድህ ይላሉ፤ «እራሱን አክብዶ ሰዎችን ያሳነሰ፥ የናቀ የቁርብነት ሜዳ አልገባም [ከአሏሕ ዘንድ ተወዳጅነትን አላገኘም]።» ▣ telegram t.me/habeshynegn ▣ Tiktok tiktok.com/@habeshynegn ▣ Facebook facebook.com/habeshynegn ▣ Youtube youtube.com/@habeshynegn

ርቆ እንዳልነበረ ፣ ሳያውቃቸው ጠልቶ ወዲያው ሰልሞ ገባ ፣ ፊታቸውን ዓይቶ ዛዲያ ምን ሊዐጅብ ፣ መች ሊደንቀኝ ከቶ ፣ ተገረም ካላችሁ ፣ እኔ ምገረመው ያንን ግንባር ዓይቶ፣ ባልሰለመው ሰው ነው። ፡ በባለ ብዕሩ ኡስታዝ ሰኢድ አህመድ በአድዋ ድል መታሰባያ አዳራሽ ያቀረቡትን ግጥም ሙሉውን በክፍል ➌ #በyoutube ይጠብቁን...! t.me/habeshynegn tiktok.com/@habeshynegn

እኒህ ጉምቱ ብዙ ያልተወሱ ያልተዘከሩ ከሰው ልብ ሸሪዐን ( የእስልምናን ህጎች ) ፍቅር የሚዘሩ ። እውቀትን ተምሮ ተግባር በማስከተል እንደዚሁም ለሌሎች በማስተላለፍ እድሜያቸውን ያሳለፉ የሀዲስ የዐ
እኒህ ጉምቱ ብዙ ያልተወሱ ያልተዘከሩ ከሰው ልብ ሸሪዐን ( የእስልምናን ህጎች ) ፍቅር የሚዘሩ ። እውቀትን ተምሮ ተግባር በማስከተል እንደዚሁም ለሌሎች በማስተላለፍ እድሜያቸውን ያሳለፉ የሀዲስ የዐረቢያ የፊቅህ እውቀትን ለየት ባለሁኔታ የሚያውቁ ። ራያ ላይ የሚያበሩ የቀን ፀሀይ የሌሊት ጨረቃ ሸኽ ዐብዱል ዐዚዝ ራያ በመባል ይታወቃሉ ። የዱንያን ፍቅር ከእግር ጥፍር እስከ ራስ ፀጉራ ድረስ ጋዝ አርከፍክፈው ያቃጠሉ ። ብቻ ስለሳቸው ታሪክ ለመፃፍ ብዙ ሰዓታቶች ያሸበረቁ ቃላቶችን ብንጠቀምም አንጨርሰውም ። በጥቅሉ እርዳታቸውን በዱንያ ሸፈዓቸውን በአኺራ ከሚያገት ያድርገን ብዬ ልደምድመው ።

ያ ረሱለሏሂ ያ ወርዱ ጉንጭዎ ይቅርና ላዩት በኸበር ለሰሙት ከእንቅልፍ አጋጭቶ በናፍቆት ሲያዋትት እኔ እንዴት ይግረመኝ መገረምን ገርሞት
ያ ረሱለሏሂ ያ ወርዱ ጉንጭዎ ይቅርና ላዩት በኸበር ለሰሙት ከእንቅልፍ አጋጭቶ በናፍቆት ሲያዋትት እኔ እንዴት ይግረመኝ መገረምን ገርሞት

እነሆ ክፍል ሁለት ተለቋል ሰብስክራይብ እንዳይረሳ..! https://youtu.be/Fi7ZC_Bkb4E?si=rpaz2Rcse68G8fMn

ክፍል ሁለትን እየመጣ ነው ይጠብቁን...!

የመጀመሪያው ክፍል በአድዋ ድል መታሰቢያ አዳራሽ የመውሊድ ዝግጅት https://youtu.be/dMLHSuwfn9Q?si=dk7IWke-lxbRHBUj

ዛሬ #በአድዋ_ድል_መታሰቢያ የተደረገውን ደማቅ የመውሊድ ፕሮግራም በቅርቡ በYOUTUBE እና በTIKTOK ይጠብቁን.....!

ቀድርዎን አይስትም ፤ ካልሆነ በቀር ጅል ፤ ወስፍዎ ሲወሳ ፤ በተውራት በኢንጂል ፤ እንዴት ያለ ሰው ነው ? ፤ ከእርስዎ ማይከጅል ፤ ✍️ 👌 👌 ስንኖር ስንሞት ፣ ስጠን ኢማን አማን ፤ እንኳን
ቀድርዎን አይስትም ፤ ካልሆነ በቀር ጅል ፤ ወስፍዎ ሲወሳ ፤ በተውራት በኢንጂል ፤ እንዴት ያለ ሰው ነው ? ፤ ከእርስዎ ማይከጅል ፤ ✍️ 👌 👌 ስንኖር ስንሞት ፣ ስጠን ኢማን አማን ፤ እንኳን እሳት መግባት ፣ ሽታውም አይግማን ፤ ያ ሐዩ ያ ቀዩም ፤ ያ ረሂይም ያ ረህማን ፤ ✍️ 👌 👌 ነውራችንን አርገው ፣ የወዳጅ ጥፋት ፤ ኸይሩን አታርግብን ፣ ተጠልቶ ልፋት ፤ ከፊታችን አንሳው ፤ ክፉን እንቅፋት ፤ ✍️ 👌 👌 ከጥጋብ ጠብቀን ፣ ከሚያመጣ በላ ፤ ለአንተ አሽከር እንሁን ፤ አታርገን ለሌላ ፤ እደጃፍህ ስንቆም ፤ የሌለው ክልከላ ፤ ✍️ 👌 👌 ብቻውን አያስብም ፣ በሬ ካለ ቀንጃ ፤ ዱዓ አድራጊ ወንድም ፣ ስጠን አውጪ ሐጃ ፤ ሲጠይቁት እኛን ፣ እማይለን እንጃ ፤ ✍️ 👌 👌 📖 "ሐበለና" ከተሰኘው የሸይኽ ምስለይ ኪታብ የተወሰደ ✍️🥰 ነገ የፈጅር ሶላትን ከሰገዱ በኋላ ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ አዳራሽ ጎራ ይበሉ ፤ ትኬት መያዝዎን አይዘንጉ !

#አንድ_ቀን_ቀረው
#አንድ_ቀን_ቀረው

#አይቀርም_መቅረት_ያስቆጫል ታላቅ የመውሊድ ዝግጅት የፊታችን እሁድ ዻጉሜ 1 በአድዋ ድል መታሰቢያ አዳራሽ 📍 ትኬት online ለመቁረጥ 👉 https://t.me/EiTAmewlidbot
+2
#አይቀርም_መቅረት_ያስቆጫል ታላቅ የመውሊድ ዝግጅት የፊታችን እሁድ ዻጉሜ 1 በአድዋ ድል መታሰቢያ አዳራሽ 📍 ትኬት online ለመቁረጥ 👉 https://t.me/EiTAmewlidbot

የኪስራ ታላቅ ቤተ-መንግሥት በተርገፈገፈ ጊዜ ... ምን ተከሰተ? የዚህስ ማሳያና ምስጢር ምንድን ነው? አስ-ሱና ቲቪ / As-Sunnah TV
+3
የኪስራ ታላቅ ቤተ-መንግሥት በተርገፈገፈ ጊዜ ... ምን ተከሰተ? የዚህስ ማሳያና ምስጢር ምንድን ነው? አስ-ሱና ቲቪ / As-Sunnah TV

ምስጋና ሁሉ ዓለምን በነቢያችን ﷺ መላክ ላደመቀው ፣ የዘመናትን ጨለማ በሙስጠፋ ﷺ ብርሃን ላበራው ፣ ለልቦች ህይወትን ፣ ለነፍሳት መዳንን ፣ ለዓለማትም እዝነትንና መሪነትን ነብያችንን ﷺ ለመረጠው ጌታችን አሏህ እልፍ ምስጋና ይገባው። ፡ የአሏህ ረህመትና ደህንነት የነቢያት መደምደሚያ በሆኑት አይነታችን ሙሐመድ ﷺ በቤተሰቦቻቸው እንዲሁም በባልደረቦቻቸው ላይ ይዘውትር። ለቀናት ቀናት ፤ ለወራትም ወራት እንዳላቸው እሙን ነው። በፍቅር ከተሞሉ ልቦች ውስጥ ዘውታሪ የሆኑት ነቢያችን ﷺ የተወለዱበት የረብዑልአወል 12ኛው ቀን ከምርጥ ቀናቶች አንዱ ነው። ፡ በዚህ የዓለም ጥግን በሚያበራው ፣ የፍቅር ጠረን በሚያዳርሰውና የወዳጆች ልብ በናፍቆት በሚያናውጠው በተከበረው ወር የሙስጠፋን ﷺ ፍቅር የተራቡትን በማብላት ፣ የታረዙትን በማልበስ እንዲሁም የተቸገሩትን በማገዝ ድርብርብ አድርገን ልናሳይ ይገባል። አሏህ በዕውቀታችንና በዕድሜያችን ላይ በረከቱን እንዲጨምርልን ፤ እኛንም እናንተንም በቂያማ ቀን በሙስጠፋ ﷺ ሰንደቅ ስር ፣ ከሐውዳቸው ዘንድ እንዲሁም  ፊርደውስ ውስጥ ከነቢያት ፣ ከእውነተኞች ፣ ከሸሂዶችና ከደጋጎች ጋር አብሮ እንዲሰበስበን እየተመኘሁኝ  እንኳን ❶❹❹❽ ኛው የመውሊድ በዓል በሰላም ፣ በጤና እና በፍቅር አደረሳችሁ ለማለት እወዳለሁ። መልካም የመውሊድ በዓል! #copy @habeshynegn

መካ ለዓለማት ብርሀን በተሰናዳች ጊዜ
+3
መካ ለዓለማት ብርሀን በተሰናዳች ጊዜ

ለዓለማት እዝነት ተደርገው የተላኩት የእዝነቱ ነብይ የኛ ሙሐመድ ﷺ በርካታ ስሞች አሏቸው ከነርሱም ውስጥ #ቡኻሪና_ሙስሊም በዘገቡት ሐዲስ ነብያችን ተከታዩን ብለዋል፦ عن جبير بن مطعم قال: سمعت رسول الله ﷺ يقول: «إن لي أسماء: أنا محمد، وأنا أحمد، وأنا الماحي الذي يمحو الله بي الكفر، وأنا الحاشر الذي يحشر الناس على قدمي، وأنا العاقب».متفق عليه. #ጁበይር_ኢብኑ_ሙጥዒም እንዳስተላለፉት የአሏህ መልዕክተኛ እንዲህ ማለታቸው ተዘግቧል "ለእኔ ስሞች አሉኝ ፦ እኔ ሙሐመድ ነኝ እኔ አሕመድ ነኝ ፤ አሏህ በእኔ ክህደትን ያስወገደብኝ የሆንኩት ማሒ እኔ ነኝ ፤ እኔ ሓሽር ነኝ አሏህ ሰዎችን ለእኔ የሚሰበስብልኝ ፤ ዓቂብም እኔ ነኝ " ቡኻሪና ሙስሊም። #ሙሐመድ እጂግ ምስጉን የሆኑ በርካታ ባሕሪያቶች ባለቤት በመሆናቸው የተሰጣቸው ስም ሲሆን ከኛ ነብይ በፊት በጣት የሚቆጠሩ ሰዎች ብቻ የተሰየሙበት ስም ነው ይህም ሰዎች ልጆቻቸውን የመጨረሻው ነብይ ቢሆንል በማለት በመልካም ምኞት የሰየሙት ነው። مُّحَمَّدٌ رَّسُولُ اللَّهِ ۚ وَالَّذِينَ مَعَهُ أَشِدَّاءُ عَلَى الْكُفَّارِ رُحَمَاءُ بَيْنَهُمْ ۖ "የአሏህ መልዕክተኛ ሙሐመድ እነዚያም ከርሱ ጋር ያሉት ወዳጆቹ በከሓዲዎች ላይ ብርቱዎች በመካከላቸው አዛኞች ናቸው፤" አል ፈትሕ 29 #አሕመድ አመሰጋኝ የሚል ትርጉም ያለው ሲሆን በቀደምት ጊዜያት ከመላካቸውና ከመወለዳቸው በፊት በዚህ ስያሜ ይታወቁ ነበር እንጂልና ተውራትም ላይ በዚሁ ስም እንደተወሱ ዑለማዎች ያስረዳሉ። የኛ ሙሐመድ ﷺ ከሰዎች ሁሉ አሏህን አብዝተው የሚያመሰግኑ እንዲሁም የሰዎችን ውለታ የማይረሱ የሚደረግላቸው ነገር ሁሉ አመስጋኝ የነበሩ ሰው ናቸው። ﴿ وَإِذْ قَالَ عِيسَى ابْنُ مَرْيَمَ يَا بَنِي إِسْرَائِيلَ إِنِّي رَسُولُ اللَّهِ إِلَيْكُم مُّصَدِّقًا لِّمَا بَيْنَ يَدَيَّ مِنَ التَّوْرَاةِ وَمُبَشِّرًا بِرَسُولٍ يَأْتِي مِن بَعْدِي اسْمُهُ أَحْمَدُ ۖ فَلَمَّا جَاءَهُم بِالْبَيِّنَاتِ قَالُوا هَٰذَا سِحْرٌ مُّبِينٌ﴾ [ الصف: 6] "የመርየም ልጅ ዒሳም የእስራኤል ልጆች ሆይ እኔ ከተውራት በፊት ያለውንም የማረጋግጥና ከኔ በኋላ በሚመጣው መልዕክተኛ ስሙ አሕመድ በሆነው የማብስር ስኾን ወደናንተ (የተላክሁ) የአሏህ መልዕክተኛ ነኝ ባለ ጊዜ (አስታውስ) በግልጽ ታምራቶች በመጣቸውም ጊዜ ይህ ግልጽ ድግምት ነው አሉ።" አል-ሶፍ 6 #ማሒ አሏህ በርሳቸው ምክንያት ክህደት (ኩፍር) ያስወገዳል ማለት ሲሆን ዑለማዎች ከርሳቸው መላክ ጀምሮ ሰዎች ከባዕድ አምልኮት ቀስ በቀስ እየተላቀቁ ተውሂድ ይነግሳል ማለት ነው በማለት አብራርተዋል። #ሐሽር እኔ የመጨረሻው እና መደምደሚያው ነብይ በመሆኔና ከኔ በኋላ አዲስ ሸሪዓን ይዞ የሚመጣ ነበይ ባለመኖሩ ከኔ መላክ በመሆኑ ከኔ በኋላ የሚኖረው የሰዎች መቀስቀስና መሰብሰብ ነው ወይንም ከሰዎች ሁሉ ቀድመው ምድር የምትሰነጠቅላቸው ቀድመው የሚቀሰቀሱ ሰው ናችው በማለት ዑለማዎች አብራርተዋል። #ዓቂብ የነብያት ሁሉ መደምደሚያና መጨረሻው ነብይ እኔ ነኝ ማለት ነው። اللّهُمَّ صلِّ صلاةً كاملةً وسَلِّمْ سلامًا تامًّا على سيّدِنا مُحمّدٍ الّذي تَنْحَلُّ بهِ الْعُقَدُ وتَنْفَرِجُ بهِ الْكُـرَبُ وتُقْضى بهِ الْـحوائجُ وتُنالُ بهِ الرَّغائبُ وحُسْنُ الْخواتِـيمِ ويُسْتَسْقَى الْغَمَامُ بِوَجهِهِ الْكريمِ وعلى ءالِهِ وصَحبِهِ وسلم. ሸይኽ ዑመር ኢማም - Sheikh Umar Imam

#ኸሚስ_ረቢዕ_መውሊድ #አሕመድ_ነብዬ...

ዓለምን ያበሩ ታላላቅ የመስርቾች አስ-ሱና ቲቪ / As-Sunnah TV
+3
ዓለምን ያበሩ ታላላቅ የመስርቾች አስ-ሱና ቲቪ / As-Sunnah TV