en
Feedback
Gedeo Tube🇪🇹

Gedeo Tube🇪🇹

Open in Telegram

መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ! @Gedeotube

Show more
1 416
Subscribers
No data24 hours
+47 days
-1030 days
Posts Archive
የጌዴኦ ብሔር የዘመን መለወጫ "ዳራሮ" በዓል በገደብ እየተከበረ ነው (ዲላ ጥር 05-2017 ዓ/ም) የ2017 ዓ/ም የጌዴኦ ብሔር የዘመን መለወጫ "ዳራሮ" በዓል በተለያዩ ዝግጅቶች በገደብ ወረዳና
+5
የጌዴኦ ብሔር የዘመን መለወጫ "ዳራሮ" በዓል በገደብ እየተከበረ ነው (ዲላ ጥር 05-2017 ዓ/ም) የ2017 ዓ/ም የጌዴኦ ብሔር የዘመን መለወጫ "ዳራሮ" በዓል በተለያዩ ዝግጅቶች በገደብ ወረዳና ገደብ ከተማ እየተከበረ ይገኛል። በባዓሉ አከባበር የጌዴኦ ህዝብ የባህል አስተዳደር መሪ አባ ጋዳ ቢፎሚ ዋቆ፣ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳደሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር)፣ የገደብ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ሳሙኤል ምትኩ፣ የገደብ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ታርኩ ሮቤ፣ የመንግስት ኃላፊዎችና የተለያዩ ህብረተሰብ ክፍል ተገኝተዋል። @የጌዴኦ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን።

ለውጥ! ለውጥ ሁል ጊዜ ህመም አለው! ባሉበት መቆየትም እንዲሁ ህመም አለው! ለውጥ አሁን ለአጭር ጊዜ ያመናል፣ ነገ ግን ለረጅም ጊዜ ይከፍለናል፣ ያስደስተናል! ባሉበት መቆየት አሁን ለአጭር ጊዜ ይ
ለውጥ! ለውጥ ሁል ጊዜ ህመም አለው! ባሉበት መቆየትም እንዲሁ ህመም አለው! ለውጥ አሁን ለአጭር ጊዜ ያመናል፣ ነገ ግን ለረጅም ጊዜ ይከፍለናል፣ ያስደስተናል! ባሉበት መቆየት አሁን ለአጭር ጊዜ ይመቸናል፣ ነገ ግን ለረጅም ጊዜ ዋጋ ያስከፍለናል! በዙሪያችሁ እና በላያችሁ ላይ ነገሮች ሲከናወኑና ሲለወጡ ዝም ብላችሁ አትመልከቱ፡፡ ተነሱና አቅዱ፣ ለውጥን አነሳሱ! የነጋችሁን ዛሬ አቅዱ! መልካም አዳር ለሁላችሁ!

ድላ መምሕራን ትምህርት ኮልጅ በምስጠው የቀልብ ጥያቄ ምክንያት ትምህርት ከቆመ ሳምንት አልፎል የዲፕሎማ ተማሪ ብቻ እያስተማሩ ይገኛሉ ነግር ግን ለድግር ተማር ምንም ምላሽ እንዴለል እየተግልፃ ይግኝል

ድላ መምሕራን ትምህርት ኮልጅ በምስጠው የቀልብ ጥያቄ ምክንያት ትምህርት ከቆመ ሳምንት አልፎል የዲፕሎማ ተማሪ ብቻ እያስተማሩ ይገኛሉ ነግር ግን ለድግር ተማር ምንም ምላሽ እንዴለል እየተግልፃ ይግኝል

#የጤናባለሙያዎችድምጽ " ቸግሮናልጠምቶናል፣ ርቦናል፣ ሰልችቶናል፣ ከኑሮ ውድነቱ ጋር ተያይዞ የዱቲ ሳይከፈለን ለ17 ወራት ስንሰራ ከመንግስት አካል ማንም ያሰበን የለም " - ጤና ባለሞያዎች 🔴 " ምንም ምላሽ የለንም። ቢሮ መጥተው ይጠይቁን " - ወናጎ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት በጌዴኦ ዞን ወናጎ ወረዳ ያሉ ጤና ባለሙያዎች የወራት ያልተከፈለ የዱቲ ክፍያ እንዲፈጸምላቸው በመጠየቃቸው ከደመወዛቸው እንዲቆረጥባቸው መወሰኑን በመግለጽ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ቅሬታቸውን አሰምተዋል። " ዱቲ ስላልከፈሉን የሰራነውን ገንዘብ ስለጠየቅን ብቻ ከሦስት ወራት በላይ ደሞዛችን ከ960 ብር ጀምሮ በስኬል  እየተቆረጠ ይገኛል " ብለው፣ ደመወዛቸው እንዲቆረጥ የተወሰነው የዱቲ ሥራ በማቆማቸው መሆኑን ገልጸዋል። የዱቲ ሥራ በመቆሙ ህዝቡም ችግር ላይ ስለሆነ አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጣቸው ጠይቀው፣ " ካልሆነ ለሚፈጠር ችግር ተጠያቂ አንሆንም " ሲሉ አስጠይቅቀዋል። በዞኑ ዲላ ዙሪያ ወረዳ ጪጩ ጤና ጣቢያ ያሉ ባለሙያዎቹ በበኩላቸው፣ የ17 ወራት የዱቲ ክፍያ እንዳልተፈጸመላቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል። ያማረራቸውን ቅሬታ በተመለከተ በዝርዝር ምን አሉ ? " በጌዴኦ ዞን በዲላ ዙሪያ ወረዳ የ17 ወራት የዱቲ ክፍያ ባለመከፈሉ የጪጩ ጤና ጣቢያ ከመስከረም 1 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ የዱቲ ሥራ በማቆም ሕዝቡ ከፍተኛ ችግር ላይ ወድቋል። በተደጋጋሚ ለዞኑና ለወረዳው ቅሬታ ብናቀርብም ምላሽ በመስጠት ፈንታ ባለሞያዎችን ለእስር ሲዳርግ ቆይቷል። ለሦስት ዓመት ያክል በዱቲ ክፍያ እየተከራተተ የሚገኝ የዲላ ዙሪያ ወረዳ ጤና ባለሞያ እስከ ዛሬ ተገቢ ምላሽ አላገኘም። በጌዴኦ ዞን በወናጎ ወረዳ የሚገኙ ጤና ባለሞያዎች የዱቲ ጥያቄ አቅርበው ተገቢ ምላሽ ባለማግኘታቸው መብታቸው ለማስከበር የዱቲ ሥራ በማቆማቸው በየወሩ ከደሞዛዝ እንዲቆረጥ ተወስኗል። ዱቲ ስላልከፈሉን የሰራነውን ገንዘብ ስለጠየቅን ብቻ ከሦስት ወር በላይ ደሞዛችን ከ960 ብር ጀምሮ በየወሩ እየተቆረጠ ይገኛል። መንግስት አፋጣኝ ምላሽ ይስጠን። ቸግሮናል፣ ጠምቶናል፣ ርቦናል ሰልችቶናል ሞራላችን ተነክቷል መውጫ ቀዳዳ አሳጥቶናል ከኑሮ ውድነት ጋር የዱቲ ሳይከፈለን ለ17 ወራት ስንሰራ ከመንግስት አካል ማንም ያሰበን የለም " ብለዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ምላሽ የጠየቀው የወናጎ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ቀጥተኛ ማብራሪያ በመስጠት ፋንታ፣ " ምንም ምላሽ የለንም። ቢሮ መጥተው ይጠይቁን " ብሏል። ሰሞኑን በተደጋጋሚ ስልክ ለማሳት ፈቃደኛ ባይሆኑም የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ አንዱዓለም ማሞ ከዚህ ቀደም ጉዳዩን በተመለከተ በሰጡትን ምላሽ ችግሩን ለመቅረፍ እየተሰራ መሆኑን ገልጸውልን ነበር። "ጉዳዩ በእርግጥ ያለ ነው። መሠረታዊ ችግሩ የበጀት ችግር ነው፤ የካሽ እጥረት ነው ያለው። ያን ለመፍታት በጋራ እየሰራን ነው" የሚል ቃል ነበር የሰጡን።

ፌስቡክ የቴክኒክ ችግር እንዳጋጠመው አስታወቀ‼️ ኢትዮጵያን ጨምሮ በዓለም ዙሪያ የፌስቡክ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ተጠቃሚዎች ችግር እንዳጋጠማቸው በተለያየ ሁኔታ ሲገልፁ ተስተውሏል። በሜታ ኩባንያ ስር
ፌስቡክ የቴክኒክ ችግር እንዳጋጠመው አስታወቀ‼️ ኢትዮጵያን ጨምሮ በዓለም ዙሪያ የፌስቡክ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ተጠቃሚዎች ችግር እንዳጋጠማቸው በተለያየ ሁኔታ ሲገልፁ ተስተውሏል። በሜታ ኩባንያ ስር የሚንቀሳቀሰው የፌስቡክ መተግበሪያም የቴክኒክ ችግር እንዳጋጠመው በራሱ ገፅ ላይ ለተጠቃሚዎቹ ይፋ አድርጓል። ያጋጠመውን የቴክኒክ ችግር በአፋጣኝ ለመፍታት ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የገለፀው ተቋሙ፤ ለተፈጠረው ችግር ተጠቃሚዎቹን ይቅርታም ጠይቋል። @Gedeotube

ፌስቡክ የቴክኒክ ችግር እንዳጋጠመው አስታወቀ‼️ ኢትዮጵያን ጨምሮ በዓለም ዙሪያ የፌስቡክ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ተጠቃሚዎች ችግር እንዳጋጠማቸው በተለያየ ሁኔታ ሲገልፁ ተስተውሏል። በሜታ ኩባንያ ስር
ፌስቡክ የቴክኒክ ችግር እንዳጋጠመው አስታወቀ‼️ ኢትዮጵያን ጨምሮ በዓለም ዙሪያ የፌስቡክ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ተጠቃሚዎች ችግር እንዳጋጠማቸው በተለያየ ሁኔታ ሲገልፁ ተስተውሏል። በሜታ ኩባንያ ስር የሚንቀሳቀሰው የፌስቡክ መተግበሪያም የቴክኒክ ችግር እንዳጋጠመው በራሱ ገፅ ላይ ለተጠቃሚዎቹ ይፋ አድርጓል። ያጋጠመውን የቴክኒክ ችግር በአፋጣኝ ለመፍታት ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የገለፀው ተቋሙ፤ ለተፈጠረው ችግር ተጠቃሚዎቹን ይቅርታም ጠይቋል። @Gedeotube

" እኔ ኢየሱስ ክርስቶስን እወደዋለሁ !! " በሀገራችን ኢትዮጵያ ጨምሮ በመላው ዓለም ላይ በቢሊዮኖች ተመልካች ያለው የእንግሊዝ ፕሪሜየርሊግ ግብረሰዶማውያንን ለመደገፍ በሚል በየአመቱ ዘመቻ ያደርጋል። ይህንን ዘመቻ የሚያደርገውም በእያንዳንዱ ክለብ አምበል ክንዶች ላይ ግብረሰዶማውያንን የሚገልጸውን ባዲራ / እንዲያደርጉ በማድረግ ነው። ይህን የሊጉን ተግባር እጅግ በርካታ ሃይማኖተኛ ደጋፊዎች እና ተጫዋቾች ነው የሚያወግዙት። በዘንድሮው ዓመት የሊጉ ፍልሚያ ኢፒስዊች ታውን የተባለው ክለብ አምበል እና የእስልምና እምነት ተከታዩ ሳም ሞርሲ " እኔ ሃይማኖቴ አይፈቅድልኝም " በማለት የግብረሰዶማውያንን ምልክት ሳያደርግ ቀርቷል። ከዚህ ባለፈ ግን አንድ የሌላ ክለብ ተጫዋችና አምበል የክርስትና እምነት ተከታይ ክንዱ ላይ ምልክቱን ቢያደርግም ከላይ " እኔ ኢየሱስ ክርስቶስን እወደዋለሁ !! " የሚል ፅሁፍ ፅፎ በመግባቱ የሊጉን አስተዳደሮች እንዳስቆጣ በዚህም ቅጣት ሊጣልበት እንደሚችል ተሰምቷል። ተጫዋቹ ማርክ ጉሂ ይባላል ፤ እድሜው 24 ሲሆን የአይቮሪኮስት ዝርያ ያለበት የእንግሊዝ ዜጋ ነው። የሚጫወትለት ክለብ ክርስታል ፓላስ የሚባል ነው። ይኸው ተጫዋች ነው ባለፈው ቅዳሜ ኒውካስትል ከተባለው ሌላኛው የሊጉ ክለብ ጋር ጨዋታቸውን ሲያደርጉ ግብረሰዶማውያንን የሚደግፈውን ምልክት ክንዱ ላይ ቢያጠልቅም ከላዩ " እኔ ኢየሱስ ክርስቶስን እወደዋለሁ ! " የሚል ፅሁፍ ፅፎበት በመግባት ጨዋታውን አድርጓል። በዚህም የሊጉን አስታዳዳሪዎች አስቆጥቶ ቅጣት ሊጥሉበት እንደሆነ ተነግሯል። የእንግሊዝ ፕሪሜየርሊግ ግብረሰዶማውያንን ለመደገፍ በየዓመቱ አምበሎች የግብረሰዶማውያን ምልክት የሆነውን የተለያየ ቀለም ያለው ምልክት በክንዳቸው አጥልቀው እንዲጫወቱ ያደርጋል። Proud me❤🙏

photo content
+2

photo content
+7

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በጌዴኦ ዞን የቡና ምርት አሰባሰብና ዝግጅት ስራን የመስክ ምልከታ በማድረግ ላይ ይገኛሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በጌዴኦ ዞን በዲላ ዙሪያ፣ ወናጎ እና ይርጋጨፌ ወረዳ ተዘዋውረው የቡና ምርት አሰባሰብና ዝግጅት ያለበትን ደረጃ ምልከታ በማድረግ ላይ ይገኛሉ። በዞኑ የ2017 ምርት ዘመን የቡና አሰባሰብና ዝግጅት በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ እንደሚገኝ የተገለፀ ሲሆን በተያዘው ምርት ዘመን 34 ሺ ቶን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝም ተጠቁሟል።

photo content
+5

photo content
+19

በጌዴኦ ዞን ጮርሶ ወረዳ ቂሻ ቀበሌ የአስፓልት ቱቦ በመናዱ ምክንያት በንብረት ላይ ጉዳት ያስከተለው ስሆን የአካባቢው ነዋሪዎችንም አፈናቅሏል ጉዳቱ የደረሰው ከአድስ አበባ ወደ ኬኒያ በሚወስደው ዋና ሀገር አቋራጭ መንገድ ላይ ስሆን በጌዴኦ ዞን ጮርሶ ወረዳ ቂሻ ተብለው በሚጠራበት አከባቢ ነው። ከዚህ ቀደም የምንጭ ውሀዎች ከአስፓልቱ ስር በተሰራው ቱቦ ውስጥ ያልፍ የነበረው ሲሆን አሁን በአስፓልት ናዳ ምክንያት የውሀ መተላለፊያ ቱቦዎች ተዘግተው ውሀው መተላለፊያ መንገድ በማጣቱ በአቅራቢያው በሚገኙ ማበረሰብ ንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱ ተገልጿል። በጉዳቱም 7 አባወራና 45 የቤተሰቡ አባላት ከአከባቢ ተፈናቅለው ቀበሌ ተጠልለው እንደሚኖሩ ተገልፃል።

በጌዴኦ ዞን ጮርሶ ወረዳ ቂሻ ቀበሌ የአስፓልት ቱቦ በመናዱ ምክንያት በንብረት ላይ ጉዳት ያስከተለው ስሆን የአካባቢው ነዋሪዎችንም አፈናቅሏል ጉዳቱ የደረሰው ከአድስ አበባ ወደ ኬኒያ በሚወስደው ዋና ሀገር አቋራጭ መንገድ ላይ ስሆን በጌዴኦ ዞን ጮርሶ ወረዳ ቂሻ ተብለው በሚጠራበት አከባቢ ነው። ከዚህ ቀደም የምንጭ ውሀዎች ከአስፓልቱ ስር በተሰራው ቱቦ ውስጥ ያልፍ የነበረው ሲሆን አሁን በአስፓልት ናዳ ምክንያት የውሀ መተላለፊያ ቱቦዎች ተዘግተው ውሀው መተላለፊያ መንገድ በማጣቱ በአቅራቢያው በሚገኙ ማበረሰብ ንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱ ተገልጿል። በጉዳቱም 7 አባወራና 45 የቤተሰቡ አባላት ከአከባቢ ተፈናቅለው ቀበሌ ተጠልለው እንደሚኖሩ ተገልፃል።

የዲላ መካከለኛ አግሮ ኢንዲስትሪ ፓርክ ለመጀመሪያ ጊዜ 22 ሺህ ሊትር የአቮካዶ ዘይት ለውጭ ገበያ አቀረበ አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 16፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የዲላ መካከለኛ አግሮ ኢንዲስትሪ ፓርክ ለመጀመሪያ ጊዜ ያመረተውን 22 ሺህ ሊትር የአቮካዶ ዘይት ምርት ለውጭ ገበያ ማቅረቡን ገለጸ። በኢንዱስትሪ ፓርኩ የሲይዝ አግሮ ኢንዱስትሪ ማህበር ሥራ አስኪያጅ አቶ ሰለሞን ጌቱ ፥ በአንድ ፈረቃ የተመረተ 22 ሺህ ሊትር የአቮካዶ ዘይት ለመጀመሪያ ጊዜ ለውጭ ገበያ መቅረቡን ገልጸዋል፡፡ በቀጣይ…

photo content
+1

#UpdateNews ትምህርት ሚኒስቴር የ2017 የሬሚዲያል መግቢያ ውጤትን ይፋ አደረገ፡፡ ሚኒስቴሩ እንዳስታወቀው በ2016 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች እና በተለያዩ አማራጮች የአቅም ማሻሻያ ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል የመቁረጫ ነጥብ ውሳኔን ፋ አድርጓል፡፡ የሬሚዲያል ፕሮግራም በ2016 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው 50 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ያመጡትን አነስተኛ የተማሪዎች ቁጥር ከግምት ውስጥ በማስገባት፤ ውጤት መቀነስ በትምህርት ዘርፉ እና በአጠቃላይ በሀገር ላይ ሊያስከትል የሚችለውን ማህበራዊ፣ ስነ ልቦናዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ እንዲሁም ተዛማጅ ችግሮችን ከግምት ውስጥ በማስገባት የተዘረጋ አሰራር መሆኑንም ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡ በዚህ መሰረት የ2017 የትምህርት ዘመን የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎችን በተፈጥሮ ሳይንስና ማህበራዊ ሳይንስ የትምህርት መስኮች ያላቸዉን የቅበላ አቅምን ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት የአቅም ማሻሻያ ፕሮግራም ተጠቃሚዎች በሁሉም አማራጮች (በግል እና በመንግስት ተቋማት) የሬሚዲያል ፕሮግራም ለመከታተል ተማሪዎች እንደተፈተኑት የትምህርት አይነት ብዛት 31% ከመቶ እና ከዚያ የተቆረጠ መሆኑን አስታውቋል። የተየፈጥሮ እና የማሀበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ከ600 የተፈተኑት 204 እና ከዛ በላይ ማምጣት እንዲሁም ለሴት ተማሪዎች ደግሞ 600 እና ከዛ በላይ 192 ማምጣት ይጠበቅባቸዋል ተብሏል፡፡ የታዳጊ ክልልና አርብቶ አደር አካባቢ የተፈጥሮና ማሀበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ከ600 የተፈተኑ ከሆነ 192 እና ከዛ በላይ ማምጣት ሲጠበቅባቸው ሴቶች ደግሞ ከ600ው 186 እና ከዛ በላይ ማምጣት አለባቸው ተብሏል፡፡ ማሀበራዊ ሳይንስ ዓይነስውራን ወንድ ተማሪዎች ከ500ው 160 እና ከዛ በላይ፣ እንዲሁም ሴቶች ደግሞ 155 እና ከዛ በላይ ሆኖ ተቆርጧል፡፡ በፕሪፓራቶሪ ፕሮግራም የተየፈጥሮ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች ከ700ው 238 እና ከዛ በላይ በተመሳሳይ በሴቶች ደግሞ 224 እና ከዛ በላይ ማምጣት አለባቸው ተብሏል፡፡

photo content
+1

በቤሩት እስራኤል በፈጸመችው የአየር ጥቃት የሟቾች ቁጥር 31 ደረሰ በሊባኖስ ቤሩት ደቡባዊ ክፍል እስራኤል ባደረሰችው የአየር ጥቃት የሟቾች ቁጥር 31 ደርሷል። የሊባኖስ ጤና ሚኒስትር ፊራስ አቢያድ
በቤሩት እስራኤል በፈጸመችው የአየር ጥቃት የሟቾች ቁጥር 31 ደረሰ በሊባኖስ ቤሩት ደቡባዊ ክፍል እስራኤል ባደረሰችው የአየር ጥቃት የሟቾች ቁጥር 31 ደርሷል። የሊባኖስ ጤና ሚኒስትር ፊራስ አቢያድ እንደገለጹት ከሟቾች ውስጥ ሦስት ህጻናትና ሰባት ሴቶች ይገኙበታል፡፡ የእስራኤል የአየር ጥቃት በሊባኖስ መዲና ሁለት ሕንጻዎችን ያፈራረሰ ሲሆን 68 ሰዎች ላይ ጉዳት ማድረሱንም ሚኒስትሩ አክለዋል። የከተማዋ ትራንስፖርት ሚኒስትር አሊ ሃሜህ እስራኤል በመኖርያ ሕንጸዎች ላይ ያደረሰችው ፍንዳታ የጦር ወንጀል መሆኑን እና ቀጣናውን ወደለየለት ጦርነት የሚገፋ መሆኑን ተናግረዋል። እስካሁን 23 ሰዎች በፍርስራሹ ውስጥ ጠፍተዋል ማለታቸውን አልጄዚራ ዘግቧል፡፡ የእስራኤል ጦር ግን ጥቃቱ የሄዝቦላህ ከፍተኛ አመሮችን ኢላማ ያደረገ ነበር ብሏል፡፡ ሄዝቦላህም ኢብራሂም አቂል እና አህመድ መሀመድ ዋሀቢ የተባሉ የጦር አዛዥ ኮማንደሮቹ በጥቃቱ እንደሞቱበት አረጋግጧል።