cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ᴇʟɪᴀꜱ ᴍᴇꜱᴇʀᴇᴛ

Journalist-at-large

Show more
Advertising posts
100 730
Subscribers
+1824 hours
+2027 days
+4 71130 days
Posting time distributions

Data loading in progress...

Find out who reads your channel

This graph will show you who besides your subscribers reads your channel and learn about other sources of traffic.
Views Sources
Publication analysis
PostsViews
Shares
Views dynamics
01
እንኳን ለትንሳኤ በዓል አደረሳችሁ፣ አደረሰን! መልካም በዓል። @EliasMeseret
27 47855Loading...
02
100,000 followers on #Telegram አመሰግናለሁ! Galatoomaa! የቐንየለይ! @EliasMeseret
73 17520Loading...
03
አስተያየት እና ጥቆማ ለምታደርሱኝ፣ አካውንቶቼ ለተወሰኑ ሳምንታት ዝግ ሆነው ይቆያሉ፣ ሁሉንም መልእክቶቻችሁን ላልመለከት ስለምችል አቆዩልኝ። መልካም ግዜ 👋👋 @EliasMeseret
99 88222Loading...
04
#Update የአለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) በድሬዳዋ ነፃ የንግድ ቀጠና ዙርያ ባቀረብኩት መረጃ ላይ ያደረሰኝ መረጃ በድሬዳዋ ነፃ የንግድ ቀጠና ውስጥ ከሚገኝ የምግብ ማከማቻ መጋዘን ውስጥ ለተራቡ ዜጎች ተብለው የሚወጡትን የምግብ አይነቶች እዛው የንግድ ቀጠና ውስጥ ፓኬጁ ላይ ባንዲራ በመጨመር እየታሸጉ እንደሆነ አንድ መረጃ አቅርቤ ነበር። በዚህ ዙርያ የአለም ምግብ ፕሮግራም ይህን መረጃ አድርሶኛል: "WFP procured 50,000 MT of wheat on behalf of the EDRMC from WFP’s Global Commodity Management Facility (GCMF) - WFP's regional storage facility for purchased commodities - for EDRMC’s humanitarian support to communities affected by drought, floods, and conflict in Ethiopia. The wheat purchased from WFP by EDRMC is being collected from WFP’s warehouses in Dire Dawa after it has been transferred from UN bags to those provided by the government, ready for distribution. WFP occasionally leverages its extensive procurement expertise and networks to provide food procurement services to partners allowing them to respond to food needs in a timely manner." ለመረጃው የአለም ምግብ ፕሮግራምን እያመሰገንኩ ከለጋሽ ድርጅቶች የሚለገሱ የምግብ አይነቶችን 'በኢትዮጵያ የተመረተ' በሚል ማሸግያ ቀይሮ ማውጣት ለምን እንዳስፈለገ የሚመለከተው የመንግስት አካል አስተያየት ቢሰጥበት መልካም ነው እላለሁ። በቅርብ ወራት የእርዳታ ምግብ ምን ሲደረግ እንደነበር የሰማን/የምናውቅ እና እርዳታው ለተጠቃሚው ህዝብ እንዲደርስ የምንፈልግ ሁሉ ይህን መጠየቅ አለብን። @EliasMeseret
94 01447Loading...
05
Media files
63 8836Loading...
06
👌👌 @EliasMeseret
70 00887Loading...
07
የትብብር ጥያቄ! ዶ/ር እደግልኝ ሀይሉ ፓስፖርታቸው ትናንት (ቅዳሜ) አዲስ አበባ ብሔራዊ አካባቢ ጠፍቶባቸዋል። ፓስፖርቱን ያገኘ ሰው ቢተባበራቸው ውለታውን ይከፍላሉ። ስልክ ቁጥራቸው: 0936454509
58 75513Loading...
08
የዛሬ 50 አመት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከካናዳ፣ ከሳውዲ አረቢያ፣ ከቱርክ፣ ከአውስትራሊያ፣ ከጣልያን... ወዘተ ይበልጣል? አንዳንድ 'ተቀፅላዎች' ይህን ስክሪንሾት በስፋት ሲያጋሩ እንደነበር ጥቆማዎች ደርሰውኝ ነበር፣ እንዲጣራም የጠየቁ አሉ። ነገሩ እንዲህ ነው፣ መረጃው በ Goldman Sachs የ 2022 ሪፖርት ላይ የተመሰረተ ሲሆን የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እ.አ.አ በ 2075 ወይም የዛሬ 50 አመት 6.2 ትሪሊየን ዶላር የማደግ እድል እንዳለው ይጠቁማል። በዚህ መረጃ ላይ ታድያ እነ ከካናዳ፣ ሳውዲ አረቢያ፣ ቱርክ፣ አውስትራሊያ፣ ጣልያን ከኢትዮጵያ በታች የተቀመጡ ሲሆን ቻይና፣ ህንድ እና አሜሪካ ከ 1-3 ያለውን ቦታ ይዘዋል። እውነታው ግን ወዲህ ነው፣ እንዲህ አይነት የኢኮኖሚ እድገት ትንበያዎች በአብዛኛው የወደፊት የማደግ አቅምን የሚያሳዩ ሲሆን በርካታ አሁናዊ እና የወደፊት እድሎችን እና መሰናክሎችን አያካትትም። በተጨማሪም ይህ አሀዝ በከፍተኛ ደረጃ የሚንተራሰው የህዝብ ብዛት ቁጥር ላይ ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ ብዛት በ2075 አካባቢ 281 ሚልዮን ዶላር ይገመታል፣ ይህም ለከፍተኛ ምርታማነት እና የኢኮኖሚ እድገት መሰረት የመሆን እድል አለው። ሪፖርቱ የጠቀሰውም ይህን ነው። ይሁንና ተቀፅላዎቹ ሊያቀርቡት እንደፈለጉት ይህ ብቻውን የሀብት ወይም እድገት መለኪያ እንዳልሆነ አለም ተግባብቷል። ትክክለኛ እድገት መለኪያው ፍትሀዊ የሀብት ክፍፍል፣ የኑሮ ደረጃ መሻሻል፣ እንደ ውሀ፣ መኖርያ ቤት እና ኤሌክትሪክ ላሉ አገልግሎቶች ያለ ተደራሽነት... ወዘተ መሆናቸውን ራሱ Goldman Sachs ይጠቅሳል። - የጋሪ እና ፈረስ ትራንስፖርት እናመጣለን እየተባለ ወደ ቀደመው ክፍለ ዘመን ወደኋላ ለመሄድ እየተንደረደርን - በአለም ትላልቅ የሚባሉ ግጭቶች፣ ጦርነቶች፣ መፈናቀሎች እና ስደቶች እያስተናገድን - የህዝብ የመኖር፣ የቤት ባለቤትነት፣ የስራ እና ተንቀሳቅሶ የማምረት አቅም እየተፈተነ... ወዘተ ባለበት ወቅት ይህን ትንበያ ይዞ ከካናዳ እና አውስትራልያ ልንበልጥ ነው ማለት ማደንዘዣ እንጂ ምንም ሊሆን አይችልም። ብቻ መልካሙን ለሀገራችን እንመኛለን። @EliasMeseret
68 76856Loading...
09
Media files
62 87129Loading...
10
ለእርሻ፣ ለኮንስትራክሽን እና ተያያዥ አገልግሎቶች የሚውሉ ትራክተሮች እና ከባድ ተሽከርካሪዎችን ወደ ሀገር ውስጥ እንዳያስገቡ እንደተከለከሉ አስመጪዎች መናገራቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነበበን ይህም የሆነው ካለምንም መመርያ ሲሆን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ያለ ምንም በቂ ምክንያት "የመኪና ማስገቢያ ፈቃድ አልሰጣችሁም" እንዳላቸው ገልጸዋል። ስለጉዳዩ ዝርዝር መረጃም የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤትን ጠይቁ መባላቸውን አመልክተዋል። ከሁሉም ግር የሚለው ደግሞ በቅርቡ በከተሞች በእንስሳት የታገዘ ትራንስፖርት እንዲኖር ስራ እየሰራ እንደሆነ የጠቆመው ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከባድ ተሽከርካሪዎች በኤሌክትሪክ እንዲሰሩ መጠበቁ ነው። በኤሌክትሪክ የሚሰራ ትራክተር? ገልባጭ መኪና? ግሬደር? ቡልዶዘር? ታድያ ይህ እየሆነ ያለው በቢልዮን ዶላሮች የሚቆጠር ገንዘብ ለጫካ ፕሮጀክት እየፈሰሰ፣ ተጨማሪ በመቶ ሚልዮን ዶላሮች የሚቆጠር ደግሞ ለከተማ ማስዋብ እና ለቱሪዝም ስፍራዎች ግንባታ እየዋለ ባለበት ወቅት ነው። ነዳጅ ለማስገባት የዶላር በእጅጉ መመናመን እንዳለ እንረዳለን፣ ግን በአንድ በኩል ለወደፊት ሊቆዩ የሚችሉ የከተማ ማስዋብ ፕሮጀክቶች ላይ ገንዘብ እየፈሰሰ፣ በዚህ በኩል ደግሞ ያውም ለኢኮኖሚ እድገት ወሳኝ የሆኑትን ግብርናን እና ግንባታን የሚያከናውኑ ቅንጡ ያልሆኑ ተሽከርካሪዎችን መከልከል ምን ያህል misplaced priorities እንዳሉብን ማሳያ ነው። @EliasMeseret
51 14570Loading...
11
“ከጎጆ ብሪጅ ሀውሲንግ እና ከዳሽን ባንክ ጋር ያለው ግንኙነት እስካሁን አልተቋረጠም”--- የጤና ሚኒስቴር "በተያዘው በፕሮግራም መሰረት በዓመት አራት ጊዜ እጣ መውጣት እያለበት እስካሁን 2 ጊዜ ብቻ ወጥቷል"--- የጤና ባለሙያዎች ከሰሞኑ በተከታታይ ከሚደርሱኝ ጥያቄዎች አንዱ በጎጆ ብሪጅ ሀውሲንግ ተጭበረበርን የሚሉ ዜጎች ይገኙበታል። ኢትዮጵያ ቼክ የሰራውን ዘገባ ላጋራችሁ ⬇️ ከሰሞኑ “ጎጆ ብሪጅ ሀውሲንግ ከጤና ሚኒስቴር ጋር የተፈራረመውን የጤና ዘርፍ ሰራተኞች ቤት ግንባታ ስምምነት አፍርሷል፤ ቤት ለማግኘት ክፍያ የፈጸሙ የጤናው ዘርፍ ሰራተኞችም ተጭበርብረዋል” የሚሉና ኢትዮጵያ ቼክ ጉዳዩን እንዲያጣራ የሚጠይቁ መልዕክቶች ከተከታታዮቻችን ደርሰውናል። የጤና ባለሙያዎች ለኢትዮጵያ ቼክ ባደረሱት ተከታታይ መረጃ የከፈሉት ብር ይመለሳል የሚል መረጃ ሲዘዋወር እንደተመለከቱና ይህም ማለት ማህበሩ ፈርሷል ብለው እንዲያስቡ እንዳረጋቸው ጠቁመዋል። የጤና ባለሙያዎቹ አክለውም የጎጆ ዕጣ በተያዘው በፕሮግራም መሰረት በዓመት አራት ጊዜ መውጣት እያለበት እስካሁን 2 ጊዜ ብቻ ወጥቷል፣ በውል ስምምነቱ መሰረት በየ 3 ወሩ ነው ዕጣ ይወጣል ቢልም በ ውሉ መሰረት ዕጣ አልወጣም እንዲሁም ችግሮች እንኳን ቢኖሩ እነዚህ ችግሮች ሲፈጠሩ ወቅታዊ መረጃ ለተመዝጋቢዎች አልተሰጡም የሚሉ ቅሬታዎች ቀርበዋል። የጤና ሚኒስቴር የጤና ዘርፍ ሰራተኞች የጋራ መኖሪያ ቤት ግንባታ ፕሮጀክትን በተመለከተ ከጎጆ ብሪጅ ሀውሲንግ እና ዳሽን ባንክ ጋር የሶስትዮሽ ስምምነት ተፈራርሞ የመጀመሪያ ዙር እጣ ማውጣት ስነ ሰርዓት የተካሄደው ሰኔ 2015 ላይ ነበር። በስነ ሰርዓቱም 200 ጤናው ዘርፍ ሠራተኞች የመጀመርያ ዙር የዕጣ እድለኞች ሲሆኑ ዕጣ  የማውጣት ሂደቱ በየሶስት ወሩ እንደሚቀጥልና እየሰፋ እንደሚሄድም ተጠቁሞ ነበር። ይህ መረጃም በወቅቱ በሚኒስቴሩ የተረጋገጠ የፌስቡክ ገጽ ተጋርቶ ነበር፡ https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid02PnHVv2sH6DiS4B6m3H72FzPTVitoq2k2GBKEcPQyytBMPkZfZFDFctwHqBTWjB9El&id=100064567187444&mibextid=qC1gEa ይሁን እንጂ “ሁለቱ ተቋማት መካከል የተፈረመው ስምምነት ፈርሷል” የሚለውን መረጃ መነሻ በማድረግ ኢትዮጵያ ቼክ ከጤና ሚኒስቴር እና ጎጆ ብሪጅ ሀውሲንግ መረጃዎችን ለማግኘት ጥረት አድርጓል። በጤና ሚኒስቴር የጤና ዘርፍ ሰው ሀብት ልማት ማሻሻያ መሪ ስራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ አሰግድ ሳሙኤል ጉዳዩን በተመለከተ ለኢትዮጵያ ቼክ መረጃ የሰጡ ሲህን ‘በሁለቱ ተቋማት መካከል የተፈረመው ስምምነት ፈርሷል’ የሚለው መረጃ ሀሰት መሆኑን ነግረውናል። “ጤና ሚኒስቴር ከጎጆ እና ከዳሽን ባንክ ጋር ያለው ግንኙነት እስካሁን አልተቋረጠም። ያንን የሚያደርግ ከሆነ ጤና ሚኒስቴር በባለሙያው በኩል ነው የቆመው” ያሉት አቶ አሰግድ፤ “ማንኛውም በዚህ ሂደት ውስጥ የሚያልፍ ነገር ባለሙያው ላይ ማንኛውም አይነት ችግር የሚፈጥር ከሆነ (ጤና ሚኒስቴር) በፍጹም ዝም ብሎ የሚያይበት ነገር አይኖርም። ስለዚህ የመግባቢያ ስምምነቱ እስካሁን አልተቋረጠም” ብለዋል። የጤና ሚኒስቴር ከጎጆ ብሪጅ ሀውሲንግ ጋር ስምምነት ሲፈጽም የተቋሙን ህጋዊ ሰነዶችን ተመልክቶ መሆኑን የሚናገሩት ስራ አስፈጻሚው ጎጆ ብሪጅ ሀውሲንግ፤ ዳሽን ባንክና ጤና ሚኒስቴር የተፈራረሙት ስምምነት አላማ 10 ሺህ ቤቶችን በ10 አመት ገንብቶ ለመጨረስ እንደሆነም ነግረውናል። ባጠቃላይ ከ8000 በላይ ሰራተኞች የፕሮግራሙ አካል መሆናቸውን የጠቆሙት አቶ አሰግድ፤ እስካሁን በሁለት ዙሮች 400 የጤናው ዘርፍ ሰራተኞች በጋራ የማህበር ቤት እንዲገነቡ እጣ እንደወጣላቸውም ይናገራሉ። ይሁን እንጂ “እጣዎቹ ከወጡ በኋላ ችግር የሆነው ከመሬት አስተዳደር፤ ከአዲስ አበባ ማህበራት ማደራጃ ጋር ተያይዞ የተወሰኑ የአሰራር ለውጦች ተደረጉ። ከተማ ውስጥ ያለው ከመሬት ጋር ተያይዞ ያለው ችግርም የሚታወቅ ነው። ከተማ አስተዳደሩ ያንን ማኔጅ ለማድረግ በየጊዜው የሚያወጣቸው አዳዲስ ህጎች አሉ። እነሱ (ሂደቱን) አፌክት አድርገውታል” ብለዋል። ስለዚህም እጣ የወጣላቸው እድለኞች በሚፈለገው ጊዜ ግንባታ ያለመጀመራቸውን በመጥቀስ “ትልቁ እኛም የገመገምነው ችግር አሁን ባልኩት ዉስጣዊም ዉጫዊም ችግሮች፤ ጎጆም ጋር ባለው ግንባታው ዘግይቷል የሚል ነው” ብለዋል። በተጨማሪም ጤና ሚኒስቴር የጤናው ዘርፍ ሰራተኞችን ለማበርታትና ለማትጋት ከጎጆ ብሪጅ ሀውሲንግ በተጨማሪ ሌላ የመኖሪያ ቤት ማግኛ አማራጮች ላይ እየሰራ መሆኑንም አቶ አሰግድ ሳሙኤል ለኢትዮጵያ ቼክ ነግረዋል። በሌ በኩል ጉዳዩን በተመለከተ የጎጆ ብሪጅ ሀውሲንግን አስተያየት ለማግነት ለዋና ስራ አስኪያጁ አቶ አለማዉ ጋሪ ብንደዉልም ለጊዜው መረጃ ማግኘት አልቻልንም። @EliasMeseret
56 085186Loading...
12
Media files
50 1919Loading...
13
#ጥቆማ በድሬዳዋ ነፃ የንግድ ቀጠና (Dire Dawa Free Trade Zone) ውስጥ ከሚገኘው የ UN የምግብ ማከማቻ መጋዘን ውስጥ ለተራቡ ዜጎች ተብለው የሚወጡትን የምግብ አይነቶች እዛው የንግድ ቀጠና ውስጥ ፓኬጁ ላይ ባንዲራ በመጨመር ለሌላ አገልግሎት እንዲሰጡ ተደርገው ከስፍራው እየወጡ እንደሆነ ከስፍራው እየደረሱኝ ያሉ ተደጋጋሚ መረጃዎች ይጠቁማሉ። የሚመለከተው አካል ካለ በዜጎች ረሀብ የሚጫወቱትን እነዚህ አካላት ስርዐት ሊያስይዝ ይገባል። @EliasMeseret
54 06132Loading...
14
#የሚድያነፃነት የዛሬ 5 አመት ግንቦት 2011 ዓ/ም ላይ የአለም የፕሬስ ነፃነት ቀንን ኢትዮጵያ ለመጀመርያ ግዜ አዘጋጅታ ነበር፣ በፕሮግራሙ ላይ ከዓለም ዙርያ የተውጣጡ የሚድያ ባለሙያዎች ታድመው ነበር፣ እኔም ተገኝቼ ነበር። እለቱ በኢትዮጵያ እንዲከበር የተደረገው በወቅቱ በእጅጉ ተሻሽሎ የነበረውን የፕሬስ ነፃነት recognition ለመስጠት ጭምር ነበር። የተደረጉት ንግግሮች፣ ቃል የተገባባቸው ጉዳዮች እና ተስፋ ሰጪ ምልክቶች በርካቶች ነበሩ። በኢህአዴግ ስርዐት ውስጥ ለበርካታ አመታት በችግር ውስጥ ጋዜጠኝነት እንደሰራ አንድ ባለሙያ እኔም ተስፋ ታይቶኝ ነበር።  ዛሬስ? ዛሬ ላይ ያ ሁሉ ተቀይሮ ከድሮው እጅግ የባሰ የፕሬስ መብት ረገጣ ያለበት ግዜ ሆኗል። ጋዜጠኛ አይደለም ስህተት ሰርቶ ገና ለገና ለተቃዋሚ ድጋፍ ሊሰጥ ይችላል፣ ግፎችን ሊያጋልጥ ይችላል እና ሚስጥር ሊያወጣ ይችላል ተብሎ ወደ እስር ቤት ተግዟል። ከሰሞኑ እየሰማሁት እንደሆነው ደግሞ የመንግስት ሚድያዎች ውስጥ የሚሰሩ ጋዜጠኞች ጭምር ከፍተኛ ስጋት ውስጥ እየገቡ ነው። በባለስልጣናት ቀጭን ትእዛዝ ይህን ዘግብ፣ ያንን አትዘግብ እየተባሉ ማስፈራርያ ጭምር እየደረሰባቸው ነው። ሌላው ቀርቶ አንዳንድ የመንግስት መስሪያ ቤቶች በሙስናና እና ሌሎች ወንጀሎች ሰራተኞቻቸው ሲታሰሩ "የቀድሞ ሰራተኛ ብላችሁ ዘግቡ" በማለት በተለይ የመንግስት ሚድያዎችን እያስገደዱ ይገኛሉ። "በፕሮግራም ላይ ተገኝቼ ለምን ዜና አልሰራህም?" ተብሎ ከአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ከስራው የተባረረው ነፍሱን ይማረው ጋዜጠኛ በቀለ ሙለታ አንድ ምስክር ነበር። በቅርቡ ከአዲስ ዘመን፣ ከኢዜአ፣ ከኢቲቪ፣ ከፋና... ወዘተ ስራቸውን የለቀቁም አሉ። Free the media! @EliasMeseret
56 8619Loading...
15
ስርዐት የሚጎድላቸው እና ያልተገሩ መልዕክቶችን ማህበራዊ ሚድያ ላይ በስፋት ከሚያሰራጩ ግለሰቦች አንዱ አምባ. ሱሌማን ደደፎ መሆናቸውን ብዙዎች ያነሳሉ የሜቴክ (ኢትዮ ኢንጅነሪንግ ግሩፕ የሚባለው) ሀላፊው አሁን ደግሞ BYD ስለተባለ የቻይና መኪና አምራች ኩባንያ ትዊት ባደረጉበት አንድ ፅሁፍ ህፃናት እንዲያዩት የማይመከር ድረ-ገፅ ከፍተው ሲያዩ እንደነበር የሚያሳይ ምስል አብረው ትዊት አርገው ነበር (ምስሉ ተያይዟል)፣ ኋላ ላይ እሱን አጥፍተው እና ድረ-ገፁን ቆርጠው መልሰው መረጃውን አጋርተዋል። ለልጆቻችን ምን እናስተምር? Pics: Sad Engineer @EliasMeseret
61 583122Loading...
16
https://t.me/boost/eliasmeseret boost
65 9815Loading...
17
ግድያን ለመሸፋፈን መሯሯጥ?! በርካቶችን ያሳዘነውን የበቴ ኡርጌሳን የጭካኔ ግድያ "ከወንድማቸው ጋር ድብድብ ውስጥ ገብተው ነበር" እና አሟሟታቸው ከእርሻ ስራቸው ጋር በተያያዘ እንደሆነ ህዝብን ለማሳመን የሚደረገውን የማህበራዊ ሚድያ ዘመቻ አያይዤዋለሁ፣ የፕሮፋይል ፎቷቸው እንኳን የአንድ ምድብ ሰዎች እንደሆኑ ያስታውቃል። ለማንኛውን ተአማኒነት ያለው ምርመራ ተደርጎ ውጤቱ ለህዝብ ይፋ ሊደረግ ይገባል። @EliasMeseret
85 53562Loading...
18
ለበርካታ ወራት በእስር ሲሰቃዩ የነበሩት የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) አመራሩ አቶ በቴ ኡርጌሳ በትውልድ ከተማቸው መቂ ከተማ በትናንትናው እለት ተገድለው እንደተገኙ ታውቋል አርፈውበት ከነበረው ሆቴል እንዲወጡ ተደርገው የተገደሉት አቶ በቴ በንግግራቸው እና በሰከነ አስተሳሰባቸው በብዙዎች ዘንድ የሚታወሱ ናቸው። ነፍስ ይማር @EliasMeseret
80 28160Loading...
19
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታይ ወገኖቻችን፣ እንኳን ለ1445ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል አደረሳችሁ። ኢድ ሙባረክ! @EliasMeseret
71 78430Loading...
20
በአዲስ አበባ እየተከናወነ የሚገኘው አፈሳ እና የታሰሩ ሰዎችን ለማስለቀቅ በገንዘብ የሚደረግ ድርድር ካለፉት ሁለት ሳምንታት ወዲህ በከተማው 'ወቅታዊ' በሚል ምክንያት ከፍተኛ አፈሳ እየተፈፀመ እንደሆነ፣ በዚህም በርካታ ግለሰቦች ወደ እስር ቤቶች እየተጋዙ እንደሆነ የሚደርሱኝ መረጃዎች ያመለክታሉ። እስሩ በብዛት የአማራ ተወላጆች ላይ ያነጣጠረ እንደሆነ፣ ከሬስቶራንት፣ መዝናኛ ስፍራዎች እና የስራ ቦታ ጭምር አፈሳው እየተፈፀመ እንደሆነ ምንጮች የጠቆሙኝ ሲሆን ጉዳዩ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ጋር ደርሶ ምርመራ እየተደረገበት እንደሆነም ታውቋል። አፈሳውን በአብዛኛው የሚፈፅሙት ሲቪል የለበሱ 'ክትትል' የሚባሉ አካላት ሲሆን ለምሳሌ 22 አካባቢ አደይ አበባ ስታዲየም ፊት ለፊት የሚገኘው ፖሊስ ጣብያ አይነት ማቆያዎች ለዚህ ተግባር እየዋሉ እንደሆኑ እና ከሞሉ ደግሞ ኮንቴይነሮች ውስጥ እንዲታሰሩ እየተደረገ እንደሆነ ታውቋል። ታዲያ ይህን እስር ለየት የሚያደርገው አንዳንድ የፀጥታ አካላት በግልፅ የገንዘብ ድርድር በማድረግ ታሳሪዎችን በገንዘብ መልቀቃቸው ነው፣ ከ30,000 ብር እስከ 80,000 ብር ያውም በግልፅ በባንክ ትራንስፈር እንደሚደረግ ታውቋል። በርካታ ምስጉን የፀጥታ አካል እንዳሉ ብናውቅም እንዲህ አይነት በጫካ ከሚደረግ እገታ ያልተናነሰ ወንጀል መሀል ከተማ እንደሚፈፀም መንግስት መረጃው ይኖረው ይሆን? @EliasMeseret
67 977154Loading...
21
የስፖርት ውርርድ (ቤቲንግ) የተባለ እንቅስቃሴ እንዲቆም መደረጉ መልካም ነው፣ ብዙ ማህበረሰባዊ ቀውሶች ፈጥሯል እሱ እንዳለ ሆኖ የቤቲንግ ድርጅቶች አከራዮች ላይ እየተፈፀመ ያለው መረን የለቀቀ የህግ ጥሰት እና እንግልት ሀይ ሊባል ይገባል። ንግድና ኢንድስትሪ ቢሮ በብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር ድርጅት በኩል ንግድ ፈቃድ ሰጥቶ፣ ከአከራዮች የኪራይ ግብር ሲሰበስብ ቆይቶ፣ ገቢዎች ካሽ ሬጅስተር ሰጥቶ ቫት እና ተያያዥ ግብሮችን እየሰበሰበ ቆይቶ አሁን ላይ ቤቲንግ እንዲቆም ሲደረግ እነሱን ኢላማ ማድረጉ አግራሞትን ያጭራል። እንደምትመለከቱት አሁን ላይ በየአካባቢው በተዋቀሩ የሰላም እና ፀጥታ ግብረ ኃይሎች ይሄን ማህተም፣ ፊርማ ወይም ከመዝገብ ቤት ወጪ የሆነበት ቁጥር እንኳን የሌለውን ወረቀት በማስፈረም ላይ ይገኛሉ። በኋላ ተመልሰው መጥተው በገንዘብ ለመደራደር በር ከፋች ነው። ቀድመው ህግ ጥሰው አከራይተው ቢሆን ባልከፋ፣ ፈቃድ ሰጥቶ እና ግብር ሲሰበስብ ቆይቶ ይህ መሆኑ ከንብረት እና ተያያዥ ህግጋት አንፃር አያስኬድም። በዚህ አካሄድ የተጎዱ በርካታ ዜጎች እየጠየቁ ያሉት: - ወደፊትስ በሌሎች ዘርፎች ላሉ ብናከራይ እና እነሱም ህገወጥ ቢባሉ ተጠያቂ የማይኮንበት ዋስትና አለን ወይ? - ካልሆነ ህጋዊ የሚባሉትን ዘርፎች ዝርዝር መንግስት ይስጠን @EliasMeseret
55 65380Loading...
22
#Update በቦሌ አየር ማረፊያ አንድ ተጓዥን በማጉላላት እና በማስፈራራት 'የያዝሽውን ጌጣ ጌጥ እና ዶላር አካፍዪኝ' በማለቷ ተይዛ የነበረችው ተጠርጣሪ ግለሰብ በዋስ መለቀቋን የደረሰኝ መረጃ ይጠቁማል የጉምሩክ ሰራተኛዋ ድርጊት በዚህ ቻናል ላይ ከተጋለጠ በኋላ መረጃው በካሜራ እገዛ በተደረገ ክትትል መታየት ችሎ ነበር። ይህን ተከትሎም በቁጥጥር ስር ውላ ቆይታለች። ዛሬ የደረሰኝ መረጃ እንደሚጠቁመው ደግሞ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ለምርመራ ማጣሪያ በቂ ጊዜ መሰጠቱን ገልጾ ግለሰቧ በ50 ሺህ ብር ዋስ ከስር እንድትፈታ ትዕዛዝ ሰጥቶ መለቀቋን ታውቋል፣ በወቅቱም ፖሊስ ይግባኝ አልጠየቀም። @EliasMeseret
55 66829Loading...
23
#FactCheck ይህን ቪድዮ በርካታ ሰዎች እያጋሩት ይገኛል ቪድዮው መሬት ላይ የሌለ እና ሀሰተኛ ሲሆን ከአምስት አመት በፊት በአዲስ አበባ ከተማ ተከስቶ የነበረን ግጭትና አለመረጋጋት የሚያሳይ ነው። ማረጋገጫ: https://youtu.be/2hNFWUmTTyw?si=-xiDFNtAnM-DZuBw ጊዜያቸውን ባልጠበቀና ከአውድ ውጭ በሆነ መልኩ የሚጋሩ ቪዲዮዎች ለሀሰተኛና አሳሳች መረጃዎች ሊያጋልጡን ስለሚችሉ ከማመናችን እና መልሰን ከማጋራታችን በፊት ተገቢዉን ጥንቃቄና ማጣራት እናድርግ። Courtesy: Ethiopia Check @EliasMeseret
65 78812Loading...
24
በባህር ዳር ከተማ ቀበሌ 14 ትላንት መጋቢት 29 የመግሪብ ሰላት ሰግደው ሲመለሱ የነበሩ አባት ከ3 ልጆቹ እንዲሁም አንድ ጎረቤታቸውን ጨምሮ አጠቃላይ 5 ሰዎች በተከፈተባቸው የጥይት እሩምታ መገደላቸው ተነግሯል። ትላንትና ምሽት በግፍ የተገደሉት አቶ ሙሄ ፣ልጃቸው አበባዉ ሙሄ፣ ሽኩር ሙሄ፣ ሙላት ሙሄ እና ጎረቤታቸው አቶ እንድሪስ የተባሉ ሲሆኑ ስርዓት ቀብራቸው በዛሬው ዕለት ተፈፅሟል። እስካሁን ገዳዮች ስለመያዛቸው የተባለ ነገር የለም። በከተማዋ ከተገደሉት ሰዎች ባሻገር ባህርዳር ከተማ አባይ ማዶ የሚገኘው መስጂድ ከፍተኛ የመሳሪያ ድብደባ እንደተፈፀመበት ተገልጿል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ ዛሬ የባህር ዳር ሙስሊሞች በክልሉ በሙስሊሞች ላይ አነጣጥረዋል ያሉትን ግድያ እና እገታ በመቃወም ሰልፍ ማድረጋቸውን "ሀሩን ሚዲያ" ዘግቧል። እስካሁን በአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤትም ሆነ በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የተሰጠ አስተያየት የለም። Via Tikvah Ethiopia @EliasMeseret
62 15434Loading...
Photo unavailableShow in Telegram
እንኳን ለትንሳኤ በዓል አደረሳችሁ፣ አደረሰን! መልካም በዓል። @EliasMeseret
Show all...
976🙏 383👍 159🕊 22😁 16🤔 7
Photo unavailableShow in Telegram
100,000 followers on #Telegram አመሰግናለሁ! Galatoomaa! የቐንየለይ! @EliasMeseret
Show all...
1820👍 939🙏 108😁 82🕊 46🤔 20😱 17😢 2
አስተያየት እና ጥቆማ ለምታደርሱኝ፣ አካውንቶቼ ለተወሰኑ ሳምንታት ዝግ ሆነው ይቆያሉ፣ ሁሉንም መልእክቶቻችሁን ላልመለከት ስለምችል አቆዩልኝ። መልካም ግዜ 👋👋 @EliasMeseret
Show all...
👍 792😢 138 71😁 52🤔 26😱 18🙏 15
#Update የአለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) በድሬዳዋ ነፃ የንግድ ቀጠና ዙርያ ባቀረብኩት መረጃ ላይ ያደረሰኝ መረጃ በድሬዳዋ ነፃ የንግድ ቀጠና ውስጥ ከሚገኝ የምግብ ማከማቻ መጋዘን ውስጥ ለተራቡ ዜጎች ተብለው የሚወጡትን የምግብ አይነቶች እዛው የንግድ ቀጠና ውስጥ ፓኬጁ ላይ ባንዲራ በመጨመር እየታሸጉ እንደሆነ አንድ መረጃ አቅርቤ ነበር። በዚህ ዙርያ የአለም ምግብ ፕሮግራም ይህን መረጃ አድርሶኛል: "WFP procured 50,000 MT of wheat on behalf of the EDRMC from WFP’s Global Commodity Management Facility (GCMF) - WFP's regional storage facility for purchased commodities - for EDRMC’s humanitarian support to communities affected by drought, floods, and conflict in Ethiopia. The wheat purchased from WFP by EDRMC is being collected from WFP’s warehouses in Dire Dawa after it has been transferred from UN bags to those provided by the government, ready for distribution. WFP occasionally leverages its extensive procurement expertise and networks to provide food procurement services to partners allowing them to respond to food needs in a timely manner." ለመረጃው የአለም ምግብ ፕሮግራምን እያመሰገንኩ ከለጋሽ ድርጅቶች የሚለገሱ የምግብ አይነቶችን 'በኢትዮጵያ የተመረተ' በሚል ማሸግያ ቀይሮ ማውጣት ለምን እንዳስፈለገ የሚመለከተው የመንግስት አካል አስተያየት ቢሰጥበት መልካም ነው እላለሁ። በቅርብ ወራት የእርዳታ ምግብ ምን ሲደረግ እንደነበር የሰማን/የምናውቅ እና እርዳታው ለተጠቃሚው ህዝብ እንዲደርስ የምንፈልግ ሁሉ ይህን መጠየቅ አለብን። @EliasMeseret
Show all...
👍 628 69😢 60😁 15🕊 14🤔 10😱 3
Photo unavailableShow in Telegram
👍 35 5
Photo unavailableShow in Telegram
👌👌 @EliasMeseret
Show all...
👍 1330 385🙏 42🕊 19😁 15🤔 7😱 5😢 2
Photo unavailableShow in Telegram
የትብብር ጥያቄ! ዶ/ር እደግልኝ ሀይሉ ፓስፖርታቸው ትናንት (ቅዳሜ) አዲስ አበባ ብሔራዊ አካባቢ ጠፍቶባቸዋል። ፓስፖርቱን ያገኘ ሰው ቢተባበራቸው ውለታውን ይከፍላሉ። ስልክ ቁጥራቸው: 0936454509
Show all...
👍 233 14😢 12😁 10🕊 3
የዛሬ 50 አመት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከካናዳ፣ ከሳውዲ አረቢያ፣ ከቱርክ፣ ከአውስትራሊያ፣ ከጣልያን... ወዘተ ይበልጣል? አንዳንድ 'ተቀፅላዎች' ይህን ስክሪንሾት በስፋት ሲያጋሩ እንደነበር ጥቆማዎች ደርሰውኝ ነበር፣ እንዲጣራም የጠየቁ አሉ። ነገሩ እንዲህ ነው፣ መረጃው በ Goldman Sachs የ 2022 ሪፖርት ላይ የተመሰረተ ሲሆን የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እ.አ.አ በ 2075 ወይም የዛሬ 50 አመት 6.2 ትሪሊየን ዶላር የማደግ እድል እንዳለው ይጠቁማል። በዚህ መረጃ ላይ ታድያ እነ ከካናዳ፣ ሳውዲ አረቢያ፣ ቱርክ፣ አውስትራሊያ፣ ጣልያን ከኢትዮጵያ በታች የተቀመጡ ሲሆን ቻይና፣ ህንድ እና አሜሪካ ከ 1-3 ያለውን ቦታ ይዘዋል። እውነታው ግን ወዲህ ነው፣ እንዲህ አይነት የኢኮኖሚ እድገት ትንበያዎች በአብዛኛው የወደፊት የማደግ አቅምን የሚያሳዩ ሲሆን በርካታ አሁናዊ እና የወደፊት እድሎችን እና መሰናክሎችን አያካትትም። በተጨማሪም ይህ አሀዝ በከፍተኛ ደረጃ የሚንተራሰው የህዝብ ብዛት ቁጥር ላይ ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ ብዛት በ2075 አካባቢ 281 ሚልዮን ዶላር ይገመታል፣ ይህም ለከፍተኛ ምርታማነት እና የኢኮኖሚ እድገት መሰረት የመሆን እድል አለው። ሪፖርቱ የጠቀሰውም ይህን ነው። ይሁንና ተቀፅላዎቹ ሊያቀርቡት እንደፈለጉት ይህ ብቻውን የሀብት ወይም እድገት መለኪያ እንዳልሆነ አለም ተግባብቷል። ትክክለኛ እድገት መለኪያው ፍትሀዊ የሀብት ክፍፍል፣ የኑሮ ደረጃ መሻሻል፣ እንደ ውሀ፣ መኖርያ ቤት እና ኤሌክትሪክ ላሉ አገልግሎቶች ያለ ተደራሽነት... ወዘተ መሆናቸውን ራሱ Goldman Sachs ይጠቅሳል። - የጋሪ እና ፈረስ ትራንስፖርት እናመጣለን እየተባለ ወደ ቀደመው ክፍለ ዘመን ወደኋላ ለመሄድ እየተንደረደርን - በአለም ትላልቅ የሚባሉ ግጭቶች፣ ጦርነቶች፣ መፈናቀሎች እና ስደቶች እያስተናገድን - የህዝብ የመኖር፣ የቤት ባለቤትነት፣ የስራ እና ተንቀሳቅሶ የማምረት አቅም እየተፈተነ... ወዘተ ባለበት ወቅት ይህን ትንበያ ይዞ ከካናዳ እና አውስትራልያ ልንበልጥ ነው ማለት ማደንዘዣ እንጂ ምንም ሊሆን አይችልም። ብቻ መልካሙን ለሀገራችን እንመኛለን። @EliasMeseret
Show all...
👍 872😁 195 81🙏 12🤔 9🕊 9😱 8😢 2
Photo unavailableShow in Telegram
😁 158👍 35 13🤔 8😱 5🙏 4
Photo unavailableShow in Telegram
ለእርሻ፣ ለኮንስትራክሽን እና ተያያዥ አገልግሎቶች የሚውሉ ትራክተሮች እና ከባድ ተሽከርካሪዎችን ወደ ሀገር ውስጥ እንዳያስገቡ እንደተከለከሉ አስመጪዎች መናገራቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነበበን ይህም የሆነው ካለምንም መመርያ ሲሆን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ያለ ምንም በቂ ምክንያት "የመኪና ማስገቢያ ፈቃድ አልሰጣችሁም" እንዳላቸው ገልጸዋል። ስለጉዳዩ ዝርዝር መረጃም የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤትን ጠይቁ መባላቸውን አመልክተዋል። ከሁሉም ግር የሚለው ደግሞ በቅርቡ በከተሞች በእንስሳት የታገዘ ትራንስፖርት እንዲኖር ስራ እየሰራ እንደሆነ የጠቆመው ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከባድ ተሽከርካሪዎች በኤሌክትሪክ እንዲሰሩ መጠበቁ ነው። በኤሌክትሪክ የሚሰራ ትራክተር? ገልባጭ መኪና? ግሬደር? ቡልዶዘር? ታድያ ይህ እየሆነ ያለው በቢልዮን ዶላሮች የሚቆጠር ገንዘብ ለጫካ ፕሮጀክት እየፈሰሰ፣ ተጨማሪ በመቶ ሚልዮን ዶላሮች የሚቆጠር ደግሞ ለከተማ ማስዋብ እና ለቱሪዝም ስፍራዎች ግንባታ እየዋለ ባለበት ወቅት ነው። ነዳጅ ለማስገባት የዶላር በእጅጉ መመናመን እንዳለ እንረዳለን፣ ግን በአንድ በኩል ለወደፊት ሊቆዩ የሚችሉ የከተማ ማስዋብ ፕሮጀክቶች ላይ ገንዘብ እየፈሰሰ፣ በዚህ በኩል ደግሞ ያውም ለኢኮኖሚ እድገት ወሳኝ የሆኑትን ግብርናን እና ግንባታን የሚያከናውኑ ቅንጡ ያልሆኑ ተሽከርካሪዎችን መከልከል ምን ያህል misplaced priorities እንዳሉብን ማሳያ ነው። @EliasMeseret
Show all...
👍 584😢 90 47🤔 30😁 8😱 4🙏 4