en
Feedback
Voa Amharic

Voa Amharic

Open in Telegram

መረጃዎችን ለመላክ @Voa_News_Amharic_bot

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Voa Amharic

Channel Voa Amharic (@voa_amharic1) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 26 526 subscribers, ranking 9 050 in the News & Media category and 1 302 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 26 526 subscribers.

According to the latest data from 09 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 102 over the last 30 days and by -1 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 18.05%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 9.37% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 787 views. Within the first day, a publication typically gains 2 486 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“መረጃዎችን ለመላክ @Voa_News_Amharic_bot”

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 10 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

26 526
Subscribers
-124 hours
+137 days
+10230 days
Posts Archive
የ ሶማሊላንድ ፕሬዚዳንት ዲፕሎማሲያዊ እውቅና የማግኘት ጥረት በቀጠለበት ወቅት የመጀመሪያ ይፋዊ ጉብኝታቸውን ወደ አሜሪካ ማድረግ ጀመሩ የሶማሊላንድ ፕሬዚዳንት አብዲራህማን ሞሐመድ አብዱላሂ ኢሮ ሥል
የ ሶማሊላንድ ፕሬዚዳንት ዲፕሎማሲያዊ እውቅና የማግኘት ጥረት በቀጠለበት ወቅት የመጀመሪያ ይፋዊ ጉብኝታቸውን ወደ አሜሪካ ማድረግ ጀመሩ የሶማሊላንድ ፕሬዚዳንት አብዲራህማን ሞሐመድ አብዱላሂ ኢሮ ሥልጣን ከያዙ ወዲህ የመጀመሪያቸውን ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ለማድረግ ወደ አሜሪካ ያቀኑ ሲሆን፣ ይህም ሀርጌሳ ሰፊ ዓለም አቀፋዊ እውቅና ለማግኘት የምታደርገውን የዲፕሎማሲ እንቅስቃሴ ባጠናከረችበት ወቅት የተከናወነ ነው። የሶማሊላንድ ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት እንዳስታወቀው፣ ፕሬዚዳንት ኢሮ ወደ አሜሪካ የሚያደርጉት ጉዞ በተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች በኩል የሚደረግ ነው። ሆኖም ጽሕፈት ቤቱ የጉብኝቱን የቆይታ ጊዜም ሆነ ፕሬዚዳንቱ ከየትኞቹ ባለሥልጣናት እና ተቋማት ኃላፊዎች ጋር እንደሚገናኙ የሰጠው ዝርዝር መረጃ የለም። ጉብኝቱ በሀርጌሳ በኩል ከዋሺንግተን ጋር ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር፣ በደኅንነት እና በኢኮኖሚ ዘርፎች የሚደረጉ ትብብሮችን ለማስፋፋት ያለመ ታላቅ የዲፕሎማሲ ተልዕኮ ተደርጎ ተወስዷል። በተጨማሪም የውጭ ኢንቨስትመንትን በመሳብ ረገድ እና ሶማሊላንድ ዓለም አቀፍ እውቅና ለማግኘት ለረጅም ጊዜ የምታደርገውን ጥረት በማስቀጠል ላይ ትኩረት ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል። https://t.me/voa_amharic1 https://t.me/voa_amharic1

የ ብራዚል የንግድና ኢንቨስትመንት ማስተዋወቂያ ኤጀንሲ በ አዲስ አበባ ቋሚ ጽሕፈት ቤት ሊከፍት ነው ተባለ የብራዚል የንግድና የኢንቨስትመንት ማስተዋወቂያ ኤጀንሲ (Apex Brazil) በአዲስ አበባ
+2
የ ብራዚል የንግድና ኢንቨስትመንት ማስተዋወቂያ ኤጀንሲ በ አዲስ አበባ ቋሚ ጽሕፈት ቤት ሊከፍት ነው ተባለ የብራዚል የንግድና የኢንቨስትመንት ማስተዋወቂያ ኤጀንሲ (Apex Brazil) በአዲስ አበባ ቋሚ ጽሕፈት ቤቱን ሊከፍት መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታወቀ። በጉዳዩ ላይ በተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ፤ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽነር ዶክተር ዘለቀ ተመስገን እንደገለጹት፣ ኤጀንሲው በአዲስ አበባ ጽሕፈት ቤት መክፈቱ በኢትዮጵያና ብራዚል መካከል ያለውን የኢኮኖሚ ትብብር ወደ ተጨባጭ የንግድና የኢንቨስትመንት ዕድሎች ለመቀየር የሚያስችል ስትራቴጂያዊ ድልድይ ሆኖ ያገለግላል። ኮሚሽነሩ አክለው፣ የሁለቱ ሀገራት የብሪክስ (BRICS) አባል መሆን የንግድ፣ የቀጥታ የውጭ ኢንቨስትመንትና የጋራ ኢንዱስትሪያዊ ትብብርን ይበልጥ ለማሳደግ ተጨማሪ ዕድል የሚፈጥር ነው ብለዋል። ኢንቨስትመንት ኮሚሽኑ ከአፔክስ ብራዚል ጋር በግብርና እና ግብርና-ነክ ማቀናበር (አግሮ-ፕሮሰሲንግ)፣ በኢንዱስትሪ ማምረቻ፣ በአረንጓዴ ኢነርጂ፣ በሎጂስቲክስና በቴክኖሎጂ ሽግግር ዘርፎች ትብብርን ለማጠናከር ዝግጁ መሆኑንም ዶክተር ዘለቀ ጠቁመዋል። https://t.me/voa_amharic1 https://t.me/voa_amharic1

ኔፓል እና ቲቤት ውስጥ በደረሰው የጎርፍ አደጋ የሞቱት ሰዎች ቁጥር ከ1 ሺህ 200 አለፈ አደጋው በደረሰ በስምንተኛው ቀን ዛሬም 4875 ሰዎች ይሙቱ ይኑሩ አልታወቀም። ዛሬ በወጡ መግለጫዎች መሠረት
ኔፓል እና ቲቤት ውስጥ በደረሰው የጎርፍ አደጋ የሞቱት ሰዎች ቁጥር ከ1 ሺህ 200 አለፈ አደጋው በደረሰ በስምንተኛው ቀን ዛሬም 4875 ሰዎች ይሙቱ ይኑሩ አልታወቀም። ዛሬ በወጡ መግለጫዎች መሠረት ያሉበት ካልታወቀው መካከል ፣ 601 የውጭ ዜጎች ይገኙበታል። በአደጋው ሞተው ከተገኙት አስከሬኖች መካከል የአብዛኛዎቹ ማንነት ገና አልተለየም።  በአንዳንድ ሁኔታዎችም የሰዎች አጥንቶች ብቻ እንደተገኙም የእርዳታ ሠራተኞች ተናግረዋል። የበረዶ ክምርና የድንጋይ ናዳ የተቀላቀለበት ጎርፍ አንዳንድ መንደሮችን ሙሉ በሙሉ ጠራርጎ በመውሰዱ በቢሊዮንች ዶላር የሚቆጠር ንብረትም እንዳልነበር ሆኗል። https://t.me/voa_amharic1 https://t.me/voa_amharic1

እየተጠናከረ የመጣው ኤል ኒኖ ከባድ የአየር ሁኔታ ስጋት እያሳደረ እንደሆነ ተገለጸ የዓለም ሜትሮሎጂ ድርጅት እንደገለጸው አሁን ላይ እየተስተዋለ የሚገኘው የኤል ኒኖ ክስተት በ70 ዓመታት ውስጥ ከታ
እየተጠናከረ የመጣው ኤል ኒኖ ከባድ የአየር ሁኔታ ስጋት እያሳደረ እንደሆነ ተገለጸ የዓለም ሜትሮሎጂ ድርጅት እንደገለጸው አሁን ላይ እየተስተዋለ የሚገኘው  የኤል ኒኖ ክስተት በ70 ዓመታት ውስጥ ከታዩት በጣም ኃይለኛ ክስተቶች አንዱ ሊሆን እንደሚችል ያስታወቀ ሲሆን፥ ክስተቱም ቢያንስ እስከ የካቲት 2027 ሊቀጥል እንደሚችል ተገልጿል። የተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ዓለም ከፍተኛ የአየር ሁኔታ አደጋ ወደሚበዛበት ደረጃ እየገባች መሆኑን አንስተው፥ ኤል ኒኖ እየጠነከረ በመምጣቱ የድርቅ፣ የጎርፍ፣ የመሬት ናዳ እና የከፍተኛ ሙቀት አደጋዎች ሊባባሱ እንደሚችሉ ተናግረዋል። በፓሲፊክ ውቅያኖስ ማዕከላዊና ምሥራቃዊ ክፍል የባሕር ሙቀት በቅርብ ወራት በከፍተኛ ሁኔታ  የጨመረ ሲሆን፥በተለይም የባሕር ወለል ሙቀት ከመደበኛው በ2 ዲግሪ ሴልሺየስ በላይ መሆኑ ተዘግቧል ። የኤል ኒኖ ተጽዕኖ በሰው ልጅ ከሚመነጨው የረጅም ጊዜ የአየር ንብረት ሙቀት መጨመር ላይ ተደምሮ የከፋ የአየር ሁኔታ ሊያስከትል እንደሚችል ሳይንቲስቶች ገልጸዋል። ባለሙያዎች በበኩላቸው የኤል ኒኖ ተጽዕኖ በሰዎች ላይ የሚያደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ ቅድመ ማስጠንቀቂያ፣ የሕክምና ድጋፍና የአደጋ ዝግጅት ሥርዓቶችን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል። https://t.me/voa_amharic1 https://t.me/voa_amharic1

የኢትዮጵያ አየር መንገድ እስከ 10 የቦይንግ የጭነት አውሮፕላኖችን ሊገዛ ነው እንደ አሜሪካ ጆርናል ኦፍ ትራንስፖርቴሽን ዘገባ መሰረት ​የኢትዮጵያ አየር መንገድ እስከ 10 የሚደርሱ ቦይንግ የጭነት
የኢትዮጵያ አየር መንገድ እስከ 10 የቦይንግ የጭነት አውሮፕላኖችን ሊገዛ ነው እንደ አሜሪካ ጆርናል ኦፍ ትራንስፖርቴሽን ዘገባ መሰረት ​የኢትዮጵያ አየር መንገድ እስከ 10 የሚደርሱ ቦይንግ የጭነት አውሮፕላኖችን ለመግዛት የሚያስችለውን ስምምነት ለማጠናቀቅ መቃረቡን ምንጮች ገለጹ። ይህ ውል አየር መንገዱ ከአረብ ኤምሬትስ እና ቀጣናው አየር መንገድ ኩባንያዎች ጋር ያለውን ውድድር ለማጠናከር እና አዲስ የአፍሪካ የአየር ትራንስፖርት ማዕከል ለመገንባት ለያዘው እቅድ ትልቅ ማበረታቻ ነው ተብሏል። ​እንደ ዘገባው ከሆነ፣ ግዢው ሁለት የነባሩን '777F' ሞዴል እና የተቀሩትን ደግሞ አዲስ ምርት የሆኑትን '777-8F' የጭነት አውሮፕላኖች ያካተተ ነው። ቦይንግ የ '777X' አውሮፕላን ማረጋገጫ በመዘገየቱ ምክንያት ነባሩን ሞዴል የማምረት ፈቃድ ለማራዘም ከአሜሪካ አቪዬሽን ባለስልጣን ጋር እየተነጋገረ ይገኛል። ​አየር መንገዱ እና ቦይንግ በጉዳዩ ላይ እስካሁን የሰጡት ይፋዊ አስተያየት ባይኖርም፣ ውሉ አየር መንገዱ በዓለም አቀፍ የካርጎ ኤክስፖርት አገልግሎት ያለውን የበላይነት የበለጠ እንደሚያጠናክረው ተገልጿል። https://t.me/voa_amharic1 https://t.me/voa_amharic1

ሶማሊያ የሶማሊላንድን እውቅና የማግኘት እንቅስቃሴ ለማገድ ከአረብ ሀገራት ጋር ውይይት እያደረገች ነው ሶማሊያ አረብ ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ተፅዕኖአቸውን በመጠቀም እስራኤል ለሶማሊላንድ የሰጠችው እውቅና ወደ ሰፊ ዓለም አቀፍ ድጋፍ እንዳይቀየር እንዲያግዱ ጥሪ አቀረበች። የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ áˆšáŠ’áˆľá‰ľáˆ­ አሊ ሞሃመድ ኦማር ከሳውዲው አል áˆťáˆ­á‰… አል አውሳት (-Sharq Al-Awsat) áŒ‹á‹œáŒŁ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ ሞቃዲሾ የሌሎች ሀገራትን እንቅስቃሴ በቅርበት እየተከታተለች መሆኗን ገልጸዋል። ሚኒስትሩ አክለውም፣ ሶማሊያ በእስራኤል ውሳኔ ላይ ያላትን ተቃውሞ ለማስረዳት ከፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ጋር በቀጥታ ግንኙነት ማድረጓን ተናግረዋል። እንደ አሊ ባልካድ ገለፃ፣ እስራኤል ባለፈው ታህሳስ ወር ሶማሊላንድን በይፋ በመቀበል የመጀመሪያዋ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አባል ሀገር ሆናለች። ሁለቱ ሀገራት áŠ áˆá‰Łáˆłá‹°áˆŽá‰˝áŠ• የተለዋወጡ ሲሆን፣ ሶማሊላንድ በኢየሩሳሌም ኤምባሲዋን በመክፈት ፕሬዚዳንቷም በእስራኤል ጉብኝት አድርገዋል። ሚኒስትሩ የእስራኤል ውሳኔ እስካሁን ሰፊ ዓለም አቀፍ እውቅና ባያስከትልም፣ በሶማሊላንድ የሚደረጉ የውጭ ሀገራት ወታደራዊ ወይም የደህንነት እንቅስቃሴዎች ውጥረትን ሊጨምሩና የአፍሪካ ቀንድን ለማረጋጋት አደጋ ሊፈጥሩ እንደሚችሉ አስጠንቅቀዋል። በመሆኑም የአረብ ሀገራት ከማውገዝ ባለፈ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን በመጠቀም ተጨማሪ እውቅናዎችን እንዲያግዱ ጠይቀዋል። ሶማሊላንድ እ.ኤ.አ. በ1991 ነፃነቷን ካወጀች ጀምሮ የራሷን መንግሥትና የደህንነት ኃይል አዋቅራ ብትቀሳቀስም፣ ሞቃዲሾ ሶማሊላንድን የግዛቷ አካል አድርጋ ነው የምትቆጥረው። https://t.me/voa_amharic1 https://t.me/voa_amharic1

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አዲስ የቤት ፋይናንስ ኩባንያ ይፋ አደረጉ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) ጋር በመተባበር 100 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያለው የመጀመሪያው
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አዲስ የቤት ፋይናንስ ኩባንያ ይፋ አደረጉ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) ጋር በመተባበር 100 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያለው የመጀመሪያውን የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ አቋቋመ።  በዚሁ ስምምነት መሠረት IFC የ 200 ሚሊዮን ዶላር አስተዋፅኦ የሚያደርግ ሲሆን፤ ተቋሙ በባንክ ዘርፍ ያለውን የጥሬ ገንዘብ ፍሰት አለመመጣጠን በመቅረፍ በመላ አገሪቱ ተደራሽ የሆነ የቤት ፋይናንስ ስርዓት እንደሚዘረጋ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስታውቀዋል። ይህ አጋርነት በተመጣጣኝ ዋጋ የሚገነቡና የኢትዮጵያውያንን ክብር የጠበቁ 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ቤቶችን ለማቅረብ እንዲሁም በፋይናንስ ሥርዓቱ ውስጥ የግል ዘርፉን ተሳትፎ ለማስፋት ያለውን ግብ እንደሚያሳካ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።  ኢትዮጵያ ፈጣን፣ ጠንካራ እና ሁሉንም ያካተተ ኢኮኖሚ መገንባቷን አጠናክራ እንደምትቀጥልም አጽንኦት ሰጥተዋል። https://t.me/voa_amharic1 https://t.me/voa_amharic1

የ ሕንድ ብሔራዊ መከላከያ ኮሌጅ ልዑክ ስትራቴጂካዊ ትስስርን ለማጠናከር በ ኢትዮጵያ ጉብኝት አካሄደ በሕንድ ብሔራዊ መከላከያ ኮሌጅ ከፍተኛ አመራር በሆኑት ሜጀር ጄነራል ፓዋንፓል ሲንግ የተመራና የበርካታ ሀገራት አባላትን ያካተተ ልዑክ በኢትዮጵያና ህንድ መካከል ያለውን ወታደራዊ እና ስትራቴጂካዊ ትስስር ለማጠናከር ያለመ ትምህርታዊ ጉብኝት ለማድረግ አዲስ አበባ መግባቱን የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቁ። የመከላከያ ሠራዊት ነሐሴ 25 ቀን 2018 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ፣ ልዑኩ በመከላከያ ሚኒስቴር ጽ/ቤት የተገኘ ሲሆን በመከላከያ ፋይናንስ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ማርታ ሉዊጂ አቀባበል ተደርጎለታል። ሚኒስትር ዴኤታ ማርታ ለልዑኩ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈው፣ ጉብኝቱ ህንድ በሁለቱ ሀገራት መካከል ወታደራዊ ግንኙነቶችን ለማጠናከር፣ ሙያዊ የልምድ ልውውጥን ለማሳደግ፣ የጋራ መግባባትን እና ትብብርን ለማጠናከር ያላትን ቁርጠኝነት ያሳያል ብለዋል፡፡ https://t.me/voa_amharic1 https://t.me/voa_amharic1

በ ኬንያ አየር መንገድ ሠራተኞች የሥራ ማቆም አድማ ምክንያት በሺዎች የሚቆጠሩ መንገደኞች ለእንግልት ተዳረጉ በኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ የሚገኘው የጆሞ ኬንያታ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሠራተኞ
በ ኬንያ አየር መንገድ ሠራተኞች የሥራ ማቆም አድማ ምክንያት በሺዎች የሚቆጠሩ መንገደኞች ለእንግልት ተዳረጉ በኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ የሚገኘው የጆሞ ኬንያታ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሠራተኞች የጀመሩት የተቀናጀ የሥራ ማቆም አድማ ሁለተኛ ቀኑን በመያዙ ምክንያት ሰኞ ዕለት በሺዎች የሚቆጠሩ የዓለም አቀፍ መንገደኞች በበረራ መዘግየት ለከፍተኛ እንግልት ተዳረጉ። የኬንያ የአቪዬሽን ሠራተኞች ማኅበር (KAWU) በጆሞ ኬንያታ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የተካሄደው የሥራ ማቆም አድማ የተቀሰቀሰው በርካታ ቅሬታዎች በመደራረባቸው መሆኑን ገልጿል። ከእነነዚህም መካከል ከኬንያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን ጋር ስምምነት ላይ መድረስ አለመቻሉ፣ እንዲሁም ከኬንያ አውሮፕላን ማረፊያዎች ባለሥልጣን (KAA) እና ከኬንያ ኤርዌይስ እህት ኩባንያ ከሆነው ጃምቦጄት (Jambojet) በኩል የታየው የትብብር እጥረት ዋነኞቹ መሆናቸውን ማኅበሩ አስታውቋል። የኬንያ አየር መንገድ ባለሥልጣን እሁድ ዕለት ባወጣው መግለጫ ምክንያቱን ሳይገልጽ አንዳንዶች በረራዎች መዘግየታቸውን ተናግሮ የነበረ ቢሆንም፣ ሰኞ ዕለት በጉዳዩ ላይ አስተያየት እንዲሰጥ ለቀረበለት ጥያቄ ምላሽ ሳይሰጥ ቀርቷል። የኬንያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን እና ጃምቦጄት በበኩላቸው አስተያየት ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆኑም። የ ሩዋንዳ አየር መንገድ እሁድ ዕለት በኤክስ ማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባሰራጨው መረጃ፣ በናይሮቢ አውሮፕላን ማረፊያ ባጋጠመ የአየር ትራፊክ ቁጥጥር ችግር ምክንያት ሁለት በረራዎችን ለመሰረዝ መገደዱን አስታውቋል። https://t.me/voa_amharic1 https://t.me/voa_amharic1

የአፍሪካ ሕብረት በሱዳን የሚካሄደውን የውይይት ጥረት መደገፉ በሲቪል ተቃዋሚዎች ዘንድ ብርቱ ተቃውሞ አስነሳ የአፍሪካ ሕብረት ሰኞ ዕለት በሱዳን የተጀመረውን እና ሀገሪቱን ከእርስ በርስ ጦርነት ለማ
የአፍሪካ ሕብረት በሱዳን የሚካሄደውን የውይይት ጥረት መደገፉ በሲቪል ተቃዋሚዎች ዘንድ ብርቱ ተቃውሞ አስነሳ የአፍሪካ ሕብረት ሰኞ ዕለት በሱዳን የተጀመረውን እና ሀገሪቱን ከእርስ በርስ ጦርነት ለማውጣት ያለመውን አዲስ የውይይት ጥረት እንደሚደግፍ አስታወቀ። ይሁን እንጃ የህብረቱ ውሳኔ በሲቪል እና በፖለቲካ ቡድኖች ዘንድ ወዲያውኑ ውድቅ ተደርጓል። ቡድኖቹ ጥረቱን በወታደራዊ ኃይሉ የሚመራ እና ግጭቱን ቅቡል ለማድረግ የተደረገ ሙከራ ነው ሲሉ ኮንነውታል። በካርቱም የሚገኙ እና በታዋቂ ግለሰቦች የተዋቀረው አዘጋጅ ኮሚቴ፣ በሠራዊቱ ከሚመራው መንግሥት በተሰጠ የደኅንነት ዋስትና መሠረት ከፖለቲካ እና ከሲቪል ማኅበራት አካላት ጋር ውይይቶችን ለማስተባበር እሑድ ዕለት ምክክር ጀምሯል። የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን «በገለልተኛ የሱዳን የሀገር ሽማግሌዎች ኮሚቴ» የሚመራውን ውይይት እንደሚደግፍ ገልጾ፣ እርምጃው በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት፣ በአውሮፓ ሕብረት፣ በኢጋድ እና በአረብ ሊግ በተዋቀረው የሕብረቱ የአምስትዮሽ አሠራር ሥር ያሉትን የዲፕሎማሲ ጥረቶች የሚያጠናክር ነው ብሏል። ኅብረቱ ማንኛውም የፖለቲካ ሂደት፤ ሁሉንም ወገኖች ያካተተ መሆን እንዳለበት እና ቅቡልነት ባለቸው የሲቪል ተቋማት የምትመራ አንድነቷ እና ልዑላዊነቷ የተጠበቀ ሱዳንን ለመፍጠር ያለመ ሊሆን እንደሚገባው በድጋሚ አስታውቋል። https://t.me/voa_amharic1 https://t.me/voa_amharic1

በኔፓል በጭቃ በተሞሉ ዋሻዎች የሚገኙት ከ6መቶ በላይ ሠራተኞችን ለማዳን አደገኛ የፍለጋ ሥራ እየተከናወነ ነው በኔፓል ትሪሹሊ ወንዝ ዳርቻ በተቆፈሩ እና በጭቃ በተሞሉ ረጅም ዋሻዎች ውስጥ ተቀርቅረዋ
+1
በኔፓል በጭቃ በተሞሉ ዋሻዎች የሚገኙት ከ6መቶ በላይ ሠራተኞችን ለማዳን አደገኛ የፍለጋ ሥራ እየተከናወነ ነው በኔፓል ትሪሹሊ ወንዝ ዳርቻ በተቆፈሩ እና በጭቃ በተሞሉ ረጅም ዋሻዎች ውስጥ ተቀርቅረዋል ተብለው የሚገመቱ ከ600 በላይ ሠራተኞች፤ ቤተሰቦች እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው በሕይወት ይገኛሉ የሚል ተስፋ ሰንቀዋል። የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች የተረፉ ሰዎችን ለማዳን ያለው ወሳኝ ጊዜ እያለቀ ነው ከሚል ስጋት በመነሳት ወደ ትሪሹሊ-3ኤ ፕሮጀክት ቦታ አዉሮፕላን ለማስገባትና መንገድ ለመክፈት ኮረብታውን በፈንጂ በማፈንዳት የሕይወት አድን ጥረታቸውን ቀጥለዋል። በኔፓል እና ቲቤት ድንበር ላይ በደረሰው የጎርፍ አደጋ የሞቱት ሰዎች ቁጥር 9 መቶ 39 መድረሱን የሀገሪቱ የአደጋ ስጋት አመራር ባለስልጣን አስታውቋል። መሥሪያ ቤቱ የጠፉ ሰዎች ቁጥር 3ሺ9መቶ25 መድረሱን የገለጸ ሲሆን፤ከነዚህም መካከል 5 መቶ 92 ያህሉ የውጭ ሀገር ዜጎች እንደሆኑ አሳውቋል። የኔፓል ጠቅላይ ሚኒስትር ባሌንድራ ሻህ እንደተናገሩት፤ በሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫዎች ውስጥ ይሠሩ ከነበሩ ሠራተኞች መካከል 2 መቶ 79 ሰዎች መዳናቸውን ገልጸዋል። የማዳን ሥራው በቻይና እና ኔፓል ወታደራዊ አባላት በተቋቋመ ዓለም አቀፍ ቡድን እየተመራ የሚገኝ ሲሆን፤ በተጨማሪም የሕንድ፣ የኮሪያ እና የአውስትራሊያ ባለሙያዎች በሥራው ላይ በመሳተፍ ላይ ናቸው። https://t.me/voa_amharic1 https://t.me/voa_amharic1

በኔፓል የሞቱት ሰዎች ቁጥር ከ1,000 በላይ መድረሱ ተገለጸ በኔፓል በተከሰተው ከባድ የጎርፍ አደጋ የሟቾች ቁጥር 1,003 መድረሱን የአገሪቱ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ባለስልጣን አስታወቀዋል። ባ
በኔፓል የሞቱት ሰዎች ቁጥር ከ1,000 በላይ መድረሱ ተገለጸ በኔፓል በተከሰተው ከባድ የጎርፍ አደጋ የሟቾች ቁጥር 1,003 መድረሱን የአገሪቱ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ባለስልጣን አስታወቀዋል። ባለስልጣኑ ዛሬ ባወጣው መግለጫ እንዳመለከተው፣ከሟቾቹ በተጨማሪ በርካታ ሰዎች የደረሱበት ያልታወቀ ሲሆን፣ በመቶዎች የሚቆጠሩ ደግሞ ጉዳት ደርሶባቸዋል። የነፍስ አድን ሰራተኞች አሁንም አስከሬኖችን ፍለጋ እና በጎርፍ የተከበቡ ሰዎችን የማውጣት ስራቸውን አጠናክረው ቀጥለዋል። በጎርፉ ምክንያት በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ከመኖሪያ ቀያቸው የተፈናቀሉ ሲሆን፣ በመሰረተ ልማቶችና በመኖሪያ ቤቶች ላይም ከፍተኛ ውድመት መድረሱ ተገልጿል። የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ባለስልጣኑ የሟቾች ቁጥር አሁንም ሊጨምር እንደሚችል ስጋቱን ገልጿል። https://t.me/voa_amharic1 https://t.me/voa_amharic1

የአሜሪካ እና ኢራን አዲስ ውጥረት‼️ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ያለው ውጥረት በማገረሹ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ አሳየ‼️ ከሳምንታት አንጻራዊ ሰላም በኋላ፣ በዩናይትድ ስቴትስ እና በኢራን መካከል የተ
የአሜሪካ እና ኢራን አዲስ ውጥረት‼️ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ያለው ውጥረት በማገረሹ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ አሳየ‼️ ከሳምንታት አንጻራዊ ሰላም በኋላ፣ በዩናይትድ ስቴትስ እና በኢራን መካከል የተጀመረው አዲስ ወታደራዊ ፍጥጫ በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ስጋት ዳግም ቀስቅሶታል። ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ ኢራን በድርጊቷ የምትቀጥል ከሆነ "በከባድ ሁኔታ" እንደሚያጠቋት መዛታቸውን ተከትሎ፣ በዛሬው ዕለት በዓለም አቀፍ ገበያ የነዳጅ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል። ይህ በሁለቱ ሀገራት መካከል የተቀሰቀሰው ወታደራዊ ፍጥጫ እና የቃላት ምልልስ፣ ሁኔታው ወደ ሰፊ ቀጠናዊ ጦርነት ሊያመራ ይችላል የሚል ስጋት በኢንቨስተሮች ዘንድ እንዲፈጠር አድርጓል። በዚህም ምክንያት የነዳጅ ዋጋ ማክሰኞ ዕለትም ጭማሪውን ቀጥሎ ውሏል። የነዳጅ ገበያ ተንታኞች እንደሚሉት ከሆነ፣ በመካከለኛው ምስራቅ ያለው አለመረጋጋት በቀጠለ ቁጥር የነዳጅ አቅርቦት ላይ መስተጓጎል ሊፈጠር ይችላል የሚለው ስጋት የዋጋ ግሽበትን ሊያባብሰው ይችላል። https://t.me/voa_amharic1 https://t.me/voa_amharic1

ቴህራን በቂ የውጭ ምንዛሬ አላት ሲሉ የኢራን ማዕከላዊ ባንክ ገዢ ፡፡ የአሜሪካ ማዕቀብ እና የኢኮኖሚ ጫና ቢበረታም፤ ኢራን በቂ የውጭ ምንዛሬ እንዳላት የማዕከላዊ ባንክ ገዢ አብዱልናስር ሄማቲ ተና
ቴህራን በቂ የውጭ ምንዛሬ አላት ሲሉ የኢራን ማዕከላዊ ባንክ ገዢ ፡፡ የአሜሪካ ማዕቀብ እና የኢኮኖሚ ጫና ቢበረታም፤ ኢራን በቂ የውጭ ምንዛሬ እንዳላት የማዕከላዊ ባንክ ገዢ አብዱልናስር ሄማቲ ተናግረዋል። ተስኒም የዜና ወኪል እንደዘገበው፤ ማዕከላዊ ባንኩ 2 ቢሊየን ዶላር ወደ ውጭ ምንዛሬ ገበያው ለማስገባት ዝግጁ ነው። የአሜሪካን የኢኮኖሚ ውድቀት ክስ ውድቅ ያደረጉት ሄማቲ፤ ኢራን የውጭ ምንዛሬ ገቢዎችን እና ተከፋይ ሂሳቦችን መሰብሰቧን እንደቀጠለች ገልጸው፤ዝርዝራቸው ሊገለጽ የማይችል የአገር ውስጥ ክምችትና ሌሎች ሀብቶች እንዳሏትም ተናግረዋል። የአገሪቱ የኢኮኖሚ ሥርዓት በአዲሱ ማዕቀብ ውስጥም መስራቱን እንደቀጠለ የገለጹት ሄማቲ፤ የሪያል ዋጋ በቅርቡ መውረድ በአብዛኛው ከሥነ-ልቦናዊ ሁኔታዎች ጋር የተያያዘ መሆኑን ጠቁመዋል። ኢራን ወደ ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት ውስጥ ገብታለች የሚለውን ሀሳብ ውድቅ በማድረግ፤ ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት እና ሰፊ የኢኮኖሚ ጫና ቢኖርም ይህ የመከሰቱ ዕድል አነስተኛ መሆኑን ተናግረዋል። ዋሽንግተን በቅርቡ በቴህራን ላይ የምታደርገውን የኢኮኖሚ ጫና ዘመቻ ያሰፋች ሲሆን፤ ዋና ዋና የኢራን ገቢ ምንጮችን እና ዓለም አቀፍ ንግድን ኢላማ አድርጋለች። ኢራን እና አሜሪካ በሰኔ ወር ጦርነቱን ለማቆም ያለመ ባለ 14 ነጥብ የመግባቢያ ስምምነት ቢፈራረሙም፤ ጊዜያዊ ስምምነቱ ግን በፍጥነት መፍረሱ ይታወሳል። https://t.me/voa_amharic1 https://t.me/voa_amharic1

ዓለም አቀፍ ማኅበረሰቡ የሰላም ጥሪ አቀረበ‼ በፌዴራል መንግሥት እና በህወሓት አመራሮች መካከል እየባባሰ የመጣውን ውጥረት ተከትሎ፣ በአፍሪካ ኅብረት መሪነት እየተደረገ ያለውን የማሸማገል ጥረት የአ
ዓለም አቀፍ ማኅበረሰቡ የሰላም ጥሪ አቀረበ‼ በፌዴራል መንግሥት እና በህወሓት አመራሮች መካከል እየባባሰ የመጣውን ውጥረት ተከትሎ፣ በአፍሪካ ኅብረት መሪነት እየተደረገ ያለውን የማሸማገል ጥረት የአውሮፓ ኅብረት አባል የሆኑ 22 አገራት፣ ዩናይትድ ኪንግደም፣ ኖርዌይ፣ ካናዳ እና አሜሪካ በአንድ ድምፅ ደገፉ።  በድሮን ጥቃቶችና በወታደራዊ እንቅስቃሴዎች ሳቢያ በድርቅ ለተጎዳው የትግራይ ሕዝብ ዳግም ጦርነት መቀስቀስ "አስከፊ" እንደሚሆን አገራቱ አፅንኦት ሰጥተው አስጠንቅቀዋል። ከፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት አደራዳሪዎች አንዱ የሆኑት የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ አዲስ አበባና መቀለ በመገኘት ዳግም ምክክሮችን ማስጀመራቸው አብዛኛዎቹ አካላት የተቀበሉት ሲሆን፤ በሌላ በኩል ህወሓት የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲነሳ፣ ወታደራዊ ከበባ እንዲቆም እና የትግራይ ሉዓላዊ ግዛት ወደነበረበት እንዲመለስ ቅድመ ሁኔታዎችን ማስቀመጡ ተነግሯል።  በሁለቱ ወገኖች መካከል የሚስተዋለው አለመግባባት ሕዝቡን በከፍተኛ ስጋት ውስጥ ከቷል። https://t.me/voa_amharic1 https://t.me/voa_amharic1

የአፍሪካ ህብረትና ኢጋድ ለቀጣናው ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ ትብብራቸውን ለማጠናከር ተስማሙ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሞሐመድ አሊ ዩሱፍ ከኢጋድ ዋና ፀሃፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ጋር ተወ
የአፍሪካ ህብረትና ኢጋድ ለቀጣናው ዘላቂ ሰላም መረጋገጥ ትብብራቸውን ለማጠናከር ተስማሙ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሞሐመድ አሊ ዩሱፍ ከኢጋድ ዋና ፀሃፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም ሁለቱ ወገኖች የምስራቅ አፍሪካ ቀጣናን ሰላም እና ደህነት ማረጋገጥ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት ÷ በሱዳን ሰላም ለማስፈን ጥረት ከሚያደርገው የሱዳን የሰላም ተልዕኮ ጋር የነበራቸውን ቆይታ አስመልክተው ገለጻ አድርገዋል፡፡ በውይይቱ በሱዳን ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን በሚደረገው ጥረት ኢጋድ እና የአፍሪካ ህብረት ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ስምምነት ላይ መድረሳቸውን የህብረቱ መረጃ ያመላክታል፡፡ https://t.me/voa_amharic1 https://t.me/voa_amharic1

ኢዜማ በአዲስ አበባ ጉዳይ ላይ የተዋቀረውን ኮሚቴን ውድቅ ማድረጉን ዛሬ በሰጠው መግለጫ አስታወቀ። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) ዛሬ ረቡዕ በሰጠው መግለጫ፤ በአዲስ አበባ ጉዳይ
ኢዜማ በአዲስ አበባ ጉዳይ ላይ የተዋቀረውን ኮሚቴን ውድቅ ማድረጉን ዛሬ በሰጠው መግለጫ አስታወቀ። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) ዛሬ ረቡዕ በሰጠው መግለጫ፤ በአዲስ አበባ ጉዳይ ምክረ ሃሳብ እንዲያዘጋጅ የተሰየመው አስማሚ ኮሚቴ አሰራር የኮሚሽኑን ሕጋዊ ማዕቀፍ የጠበቀ አይደለም ብሏል። የፓርቲው መሪ አቶ እዮብ መስፍን እንደገለጹት፤ የኮሚቴው አወቃቀርና አካሄድ የኮሚሽኑን ሕግ ያልተከተለ በመሆኑ ፓርቲው አጠቃላይ ሂደቱን ውድቅ በማድረግ ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ቅሬታ አቅርቧል። ኢዜማአክሎም በአዲስ አበባ ጉዳይ ላይ ካለው ተቃውሞ በተጨማሪ፤ በምክክሩ ወቅት የቀረቡ 400 ያህል ምክረ ሃሳቦችና የውይይት ቃለ ጉባኤዎች ለሕዝብ ግልጽ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርቧል።" https://t.me/voa_amharic1 https://t.me/voa_amharic1

በደቡባዊ ሱዳን በጎሳዎች መካከል በተቀሰቀሰ ግጭት 27 ሰዎች ተገደሉ በደቡባዊ ሱዳን በጎሳዎች መካከል በተቀሰቀሰ ግጭት በትንሹ 27 ሰዎች ሲገደሉ ከነዚህ አራቱ ህፃናት መሆናቸውን የሀገር ውስጥ የህ
በደቡባዊ ሱዳን በጎሳዎች መካከል በተቀሰቀሰ ግጭት 27 ሰዎች ተገደሉ በደቡባዊ ሱዳን በጎሳዎች መካከል በተቀሰቀሰ ግጭት በትንሹ 27 ሰዎች ሲገደሉ ከነዚህ አራቱ ህፃናት መሆናቸውን የሀገር ውስጥ የህክምና ቡድን አስታውቋል። በሱዳን ሕዝቦች ነፃነት ንቅናቄ (SPLM-N) አማፂያን በደቡብ ኮርዶፋን የኦቶሮ ጐሳ አባላት በሚኖሩባቸው ቃርዱድ እና አቡ ሃማማ በተባሉ አካባቢዎች ባደረሷቸው ጥቃቶች ግድያው መፈጸሙን የጉዳተኞችን ቁጥር የሚከታተለው የሱዳን ሀኪሞች መረብ አስታውቋል። በዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይ በ SPLM-N እና በደቡብ ኮርዶፋን ኑባ ተራሮች ውስጥ አነስተኛ ቁጥር ባለው የኦቶሮ ጐሳ መካከል ብርቱ ውጊያ ተቀስቅሶ እንደነበር ዘገባው አመልክቷል። በመሬት ይገባኛል ሰበብ የተቀሰቀሰው አዲሱ የጎሳ ግጭት በሀገሪቱ በብሄራዊ ጦር ኃይሉ እና በፈጥኖ ደራሹ ኃይል መካከል እየተካሄደ ያለውን ጦርነት አወሳስቦታል ነው የተባለው። ጥቃቱን ተከትሎ በርካታ ሰዎች ቤት ንብረታቸውን ትተው ወደ አቅራቢያ መንደሮች እና ከተሞች መፈናቀላቸውን ሀኪሞቹ ገልጸዋል። የሱዳን ዶክተሮች መረብ በፌስቡክ ገጹ ባወጣው መግለጫ «በብሔር ማንነት ላይ ተመስርቶ ሕፃናትንና ሴቶችን ጨምሮ ያልታጠቁ ንጹሃን ዜጎችን ማጥቃት የዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ሕግን በግልጽ መጣስ ነው» ብሏል። https://t.me/voa_amharic1 https://t.me/voa_amharic1

የዋጋ ግሽበት በሐምሌ ወር ወደ 15.3 በመቶ ከፍ ማለቱን የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት አስታወቀ! በ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ የዋጋ ግሽበት በሐምሌ ወር ብቻ ወደ 15.3 በመቶ ከፍ ማለቱን የኢ
የዋጋ ግሽበት በሐምሌ ወር ወደ 15.3 በመቶ ከፍ ማለቱን  የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት አስታወቀ! በ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ የዋጋ ግሽበት በሐምሌ ወር ብቻ ወደ 15.3 በመቶ ከፍ ማለቱን የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት አስታወቀ።አገልግሎቱ ባወጣው የወርሃዊ የዋጋ ንረት መረጃ፣ በሐምሌ ወር የተመዘገበው የዋጋ ግሽበት ከባለፈው አመት ጋር ከነበረው 13.7 በመቶ  ጋር ሲነጻጸር ጭማሪ አድርጓል።  ሰኔ ወር ላይ የነበረው 14.8 በመቶ ነበር። በዚህ ወር የምግብ ዋጋ ንረት 15.7 በመቶ ሲሆን፣ የምግብ ያልሆኑ ዕቃዎችና አገልግሎቶች የዋጋ ንረት ደግሞ 14.8 በመቶ ደርሷል ሲል አገልግሎቱ ገልጿል።የዋጋ ንረቱ በ2018 ዓ.ም. መጀመሪያ ወራት ላይ በመቀነስ ዝቅተኛ ደረጃ ላይ ከደረሰ በኋላ ከሚያዝያ ወር ጀምሮ ዳግም እየጨመረ የመጣ ሲሆን በመጋቢት ወር የነበረው የዋጋ ንረት ከወራት ዝቅተኛ ደረጃዎች አንዱ ሲሆን፣ በቀጣዮቹ ወራት ግን ጭማሪ ታይቷል። በተለይም የምግብ ዋጋ ጭማሪ ለአጠቃላይ የዋጋ ንረቱ መጨመር ዋነኛ አስተዋጽዖ ካደረጉ ምክንያቶች መካከል ሲሆን የምግብ ዋጋ ንረት 15.7 በመቶ መድረሱ የዋጋ ጭማሪው በቤተሰቦች የዕለት ተዕለት ወጪ ላይ ጫና መፍጠሩን ያሳያል። ባለፈው አመት ከነበረው የዋጋ ግሽበት ከ13.7 በመቶ ጀምሮ በዓመቱ መካከል እስከ 9 በመቶ አካባቢ ዝቅ ብሎ ነበር።ይሁን እንጂ ነገር ዳግም በመጨመር በሰኔ 14.8 በመቶ እና በሐምሌ 15.3 በመቶ ደርሷል። á‰ áˆ˜áˆ†áŠ‘áˆ የቅርብ ወራት የዋጋ ንረት አዝማሚያ በኢትዮጵያ የእቃና የአገልግሎት ዋጋ ጭማሪው እንደገና እየተፋጠነ መምጣቱን ያሳያል ሲል የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ገልጿል። https://t.me/voa_amharic1 https://t.me/voa_amharic1

በኢራን አዲስ የ200 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት ተገኘ በደቡባዊ የፋርስ (Fars) ግዛት ውስጥ ከ200 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ በላይ የሚገመተው አዲስ የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት መገኘቱን የ
+2
በኢራን አዲስ የ200 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት ተገኘ በደቡባዊ የፋርስ (Fars) ግዛት ውስጥ ከ200 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ በላይ የሚገመተው አዲስ የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት መገኘቱን የኢራን የፔትሮሊየም ሚኒስትር ሞህሴን ፓክኔጃድ ይፋ አደረጉ። ሚኒስትሩ እንደገለጹት፣ ከተገኘው አጠቃላይ ክምችት ውስጥ ከ160 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ በላይ የሚሆነው የተፈጥሮ ጋዝ በቀላሉ ወጥቶ ጥቅም ላይ ሊውል የሚችል ነው። አዲሱ የተፈጥሮ ጋዝ በጥራት ደረጃው «ጣፋጭ» (sweet gas) የሚባል ሲሆን፣ መርዛማ የሆነውን የሃይድሮጅን ሳልፋይድ (hydrogen sulphide) ጋዝ ይዘት አነስተኛ በመሆኑ ማውጣትና ማልማት የሚጠይቀውን ወጪ በእጅጉ ይቀንሰዋል። ብሉምበርግ (Bloomberg) የዘርፉን ባለሙያዎች ጠቅሶ እንደዘገበው፣ አዲሱ ክምችት ተለምቶ ሙሉ በሙሉ ወደ ምርት ለመግባት እና ለገበያ ለመቅረብ በርካታ ዓመታትን ሊወስድ ይችላል። ይህ አዲስ ጥራት ያለው የጋዝ ግኝት ይፋ የተደረገው፣ በቅርቡ ከተቀሰቀሰው የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በኋላ በአሜሪካ እና በእስራኤል በጋራ በተሰነዘሩ ጥቃቶች ምክንያት የኢራን የጋዝ ማውጫ ተቋማት፣ የነዳጅ ማከማቻዎች እና የትራንስፖርት መሠረተ-ልማቶች ከፍተኛ ውድመት በደረሰባቸው ወቅት ነው። https://t.me/voa_amharic1 https://t.me/voa_amharic1