1 531
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ለደመራ በዓል ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን ይፋ ሆኑ‼️
በነገው ዕለት በመስቀል አደባባይ በሚከበረው የደመራ በዓል ምክንያት ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ ይፋ አድርጓል፡፡
በዚሁ መሠረት ነገ ከረፋዱ 5:00 ጀምሮ እስከ በዓሉ ፍፃሜ ድረስ፡-
➡️ከኡራዐል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኡራኤል አደባባይ ላይ
➡️ከቦሌ አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ
➡️ከመስቀል ፍላወር ወደ ኦሎምፒያ የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ ላይ
➡️ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ አጠገብ እንዲሁም ለቀላል ተሽከርካሪ ጥላሁን አደባባይ (አራተኛ ክፍለ ጦር ላይ)
➡️ከለገሀር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ለገሀር መብራት ላይ
➡️ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድዮም ለሚጓዙ ቴሌ ማቋረጫ
➡️ከራስ ሆቴል ወደ ስታድየም ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ራስ ሆቴል ላይ
➡️ከሃራምቤ መብራት ወይም ከአምባሳደር ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ሃራምቤ መብራት ላይ
➡️ከብሔራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ብሔራዊ ቤተ መንግስት አጠገብ
➡️ከዛንቺስ ሼል ወደ ባምቢስ የሚወስደው መንገድ ከዛንቺስ ሼል አጠገብ እንዲሁም
➡️ከጁፒተር ሆቴል ወደ ECA የሚወሰደው መንገድ ባምቢስ ሳልኮት ህንፃ አጠገብ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ፡፡
አሽከርካሪዎች ይህን ተገንዝበው አማራጭ መንገዶችን በመጠቀምና የትራፊክ ፖሊስ አባላት በሚያሳዩአቸው መንገድ በመጓዝ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪውን አቅርቧል።
@Adisnews
ፈተናውን 98.6 በመቶ ተማሪዎች አልፈዋል‼️
በትግራይ የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች 98.6 ከመቶ ወደ ቀጣዩ ክፍል ማለፋቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታውቋል።
ኮሮና ተከትሎ በትግራይ በተካሄደው ጦርነት ተቋርጦ የነበረው የመማርና የማስተማር ሂደት ከሚያዝያ 2015 ዓ.ም ጀምሮ በተሰጠው የማጠናከሪያ ትምህርት በመውሰድ የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና የተፈተኑ ተማሪዎች ውጤታቸዉ ይፋ ሆኗል።
በትግራይ ትምህርት ቢሮ የትምህርት ጥራትና ምዘና ኤጀንሲ ዳይሬክተር ዳይሬክቶሬት አቶ ክንፈ ፍስሃ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ከተፈታኞቹ 98.6 በመቶ ወደ ቀጣይ ክፍል ተሸጋገረዋል።
የነበረውን ክፍተት ለሞምላት የተሰጠው የማጠናከሪያ ትምህርት በቂ ባለመሆኑ በ2016 ዓ.ም ለ9ኛ ክፍል ተማሪዎች በሚሰጠው ትምህርት ፤ ሁሉም መምህራንና የሚመለከታቸው አካላት ልዩ ትኩረት በመስጠት ተማሪዎቹ ለማብቃት ጥረት ማድረግ አለባቸው ብለዋል ዳይሬክተሩ።
በተያያዘ በክልሉ ትምህርት ቢሮና የፌደራል መንግስት ቅንጅት ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ መሆኑንና አገር አቀፍ ፈተና ከመስከረም 29 እስከ ጥቅምት 2/2016 ዓ.ም እንደሚወስዱ ከትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
@Adisnews
@Adisnews
የድህረ ምረቃ ተፈታኞች የምዝገባ ጊዜ ተራዝሟል‼️
የድህረ ምረቃ ተፈታኞች አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ባዘጋጀው የGAT መመዝገቢያ ፖርታል https://portal.aau.edu.et ላይ ምዝገባ የሚያደርጉበት ጊዜ ተራዝሟል።
ትምህርት ሚኒስቴር ዛሬ ለሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በላከው መልዕክት በGAT ፖርታሉ ላይ የተፈታኞች ምዝገባ የሚከናወነው ከመስከረም 21 እስከ 25/2016 ዓ.ም ድረስ በበይነ-መረብ መሆኑ ተገልጿል።
የመግቢያ ፈተና መስከረም 28 እና 29/2016 ዓ.ም በሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በበይነ-መረብ ይሰጣል።
@Adisnews
@Adisnews
አቶ እንዳሻው ጣሰው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሆነው ተሾሙ‼️
አቶ እንዳሻው ዛሬ በቀጠለው ጉባኤ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሆነው መሾማቸው ተገልጿል።
ከዚህ ቀደም የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር እንዲሁም በሌሎች ከፍተኛ የስራ ኃላፊነት ቦታዎች ላይ ተመድበው ሰርተዋል።
@Adisnews
በሱዳን ውጊያ ኢትዮጵያውያን መሞታቸው ተገለጸ‼️
በሱዳን የኢትዮጵያ ኤምባሲ በውጊያው ኮሞቱ መካከል ኢትዮጵያዊን እንደሚገኙበት መረጃዎች እየደረሱኝ ነው ብሏል። በሱዳን ጦርና ፈጥኖ ደራሽ መካከል በተፈጠረው ውጊያ ከ200 በላይ ሰዎች መሞተቸው ተነግሯል።
በሱዳን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ፤ በሱዳን እየተካሄደ ባለው ውጊያ በርካታ ሲቪሎች ለጉዳት መዳረጋቸውና ህይወትም እየተቀጠፈ መሆኑን ገልጿል።
ከእነዚህ መካከል ኢትዮጵያውያን እንደሚገኙበት መረጃዎች እንደደረሱት አመልክቷል።
ኤምባሲው ምን ያህል ኢትዮጵያውያን እንደሞቱ እና እንደተጎዱ በዝርዝር አልገለፀም።
ነገር ግን በኢትዮጵያውያን ሞት እና ጉዳት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እደተሰማው እና ለሟች ቤተሰቦች እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው መፅናናትን ተመኝቷል።
" ይህን አስቸጋሪ ጊዜ ለማለፍ ኢትዮጵያዊን የተቻላቸውን ሁሉ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ በድጋሜ እናሳስባለን " ብሏል።
@Adisnews
የጀማ ድልድይ ባልታወቀ ምክንያት መደርመሱ ተሰማ‼️
በሰሜን ሸዋ ዞን እንሳሮ ወረዳ እንሳሮ እና መራሐቤቴን የሚያገናኘው አገር አቋራጭ የጀማ ድልድይ በቀን 27/7/2015 ዓ.ም ሁለት ሲኖ ትራክ ተከታትለው ሲሆዱ አንዱ ሲኖ ትራክ የውሃ መያዣ ቦቴ የጫነ ሲሆን አደኛ በዶውን ሲጓዝ ባልታወቀ ምክንያት ድልድዩ ሊደረመስ ችሏል።
ከአዲስ አበባ - ሙከጡሪ አለም ከተማ - ደጎሎ መስመር ከሙከጡሪ 72.3 ኪ.ሜ. እርቀት ላይ የሚገኘው የጀማ ወንዝ ድልድይ ከተወሰነላቸው የክብደት መጠን በላይ በጫኑ ከባድ ተሽከርካሪዎች ሳቢያ ጉዳት ደርሶበታል ሲል የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር አስታዉቋል።
በመሆኑም ይህ ድልድይ በአሁኑ ወቅት ለተሽከርካሪዎች አገልግሎት መስጠት የማይችልበት ደረጃ ላይ መሆኑን ብስራት ከአስተዳድሩ ካገኘዉ መረጃ ተመልክቶታል።
ይህንን ድልድይ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለአገልግሎት ለማብቃት እንዲያስችል አስፈላጊውን የጥገና ሰራ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የሚከናወን መሆኑንም ገልጿል ። በመሆኑም የዚህ መስመር ተጠቃሚዎች ለድልድዩ አስፈላጊውን የጥገና ስራ ተከናውኖ ለአገልግሎት እስኪበቃ ድረስ ሌሎች አማራጮችን እንድትጠቀሙ አስተዳድሩ አሳስቧል።
@Adisnews
በዓለም የነዳጅ ዋጋ መጨመሩ ተሰማ‼️
ለዋጋ መጨመሩ ዋና መንስኤ የነዳጅ ላኪ አባል ሀገራት (ኦፔክ) ለዓለም ገበያ የሚያቀርቡትን የነዳጅ መጠን ለመቀነስ ውሳኔ ላይ መድረሳቸውን ተከትሎ መሆኑን አልጀዚራ ዘግቧል።
በስምነቱ መሰረትም አባል ሀገራቱ የእለታዊ የነዳጅ ምርታቸውን በ1 ነጥብ 16 ሚሊየን በርሜል ለመቀነስ መስማማታቸውን ተከትሎ እንደሆነ መረጃው ያሳያል።
ነዳጅ ላኪ አባል ሀገራቱ ከሚቀጥለው ግንቦት ወር ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚያደርጉ ጠቅሰው በዓለም የነዳጅ ገበያው መጠን በአንድ በመቶ ይቀንሳል ተብሏል፡፡
በዚህ ውሳኔ መሰረትም የዓለም ነዳጅ ዋጋ በመጭው ጊዜ በበርሜል የ10 ዶላር ጭማሪ እንደሚያሳይ ተመላክቷል፡፡
@Adisnews
በአዲስ አበባ የዓድዋ ድል በዓል ሲከበር ያልተገባ ተግባር በፈፀሙ የፖሊስ አባላት ላይ ህጋዊ እርምጃ ተወሰደ‼️
በአዲስ አበባ የዓድዋ ድል በዓል ሲከበር ያልተገባ ተግባር በፈፀሙ የፖሊስ አባላት ላይ ህጋዊ እርምጃ መወሰዱን የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ-ኃይል አስታወቀ።
በአዲስ አበባ የአድዋ ድል በዓል ሲከበር ያልተገባ ተግባር በፈፀሙ የፖሊስ አባላት ላይ ህጋዊ እርምጃ መወሰዱንና ሌሎች የምርምራ ስራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን ግብረ-ኃይሉ አስታውቋል።
ለአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እና የዓድዋ ድል በዓል አከባበር በሰላም መጠናቀቅ የመዲናዋ ነዋሪዎች ለነበራቸው ጉልህ ድርሻም የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ-ኃይሉ ምስጋና አቅርቧል።
የዓድዋ ድል በዓል በተከበረበት እለት የመዲናዋን ሰላም ለማናጋት ሁከትና ብጥብጥ ለመፍጠር አቅደው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 878 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን እና ከእነዚህ መካከልም 557ቱ ከሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች የመጡ መሆናቸው መረጋገጡም ተገልጿል።
@Adisnews
በየካቲት 5 ቀን 2015 ዓ.ም ለማድረግ የታቀደው ሀገር አቀፍ እና ዓለም አቀፍ ሰላማዊ ሰልፍ ያለማንም ከልካይነት እንደሚደረግ ቅዱስ ሲኖዶሱ አሳወቀ‼️
"...መንግስት ከአጉል እልከኝነቱ ወጥቶ ከሕገ ወጦቹ ግለሰቦች ጋር በመተባበር በአደባባይ እየፈጸመ ያለውን የሕግ ጥሰት ዛሬን ጨምሮ በቀጣዮቹ ፪/ሁለት/ ቀናት ውስጥ እንዲያቆም እና ሕግ እና ሥርዓትን እንዲያስከብር፣ በኃይል የወረራቸውን መንበረ ጵጵስና እና አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ለቆ ለቤተክርስቲያኒቱ ሕጋዊ መዋቅር እንዲያስረክብ፣ ያለአግባብ ያሠራቸውን ካህናት እና ምእመናን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲለቅ፣ ቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ ለፈፀመው በደል በአደባባይ ይቅርታ እንዲጠይቅ፤ በካህናት እና ምእመናን ላይ ለደረሰው ሞት እና የአካል ጉዳት ተገቢውን ካሳ እንዲክስ እና የወደሙ ንብረቶቿን እንዲጠግን በጥብቅ እንጠይቃለን።
በየካቲት ፭ (5)ቀን ፳፻፲፭(2015) ዓ.ም ለማድረግ ያቀደችውንና ያሳወቀችውን ሀገር አቀፍ እና ዓለም አቀፍ ሰላማዊ ሰልፍ ያለማንም ከልካይነት በራሷ አደባባይ የምታከናውን መሆኑን እያሳወቅን መንግሥትም ድርሻው ሰልፉ ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ መንግሥታዊ ኃላፊነቱን በአግባቡ መወጣት ብቻ መሆኑን እያሳሰብን ዛሬም ቢሆን መንግሥት ቆም ብሎ በማሰብ ከእኛ ከአባቶች ጋር ሃይማኖታዊ፣ ቀኖናዊና መንፈሳዊ የአስተዳደር ሥርዓታችንን ባልጣሰ መልኩ ለመነጋገር እና ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ጥረት ካደረገ በውይይት ለመፍታት መንፈሳዊ በራችን ክፍት መሆኑንም እናሳውቃለን፡፡ ፡፡..."
ሙሉ መግለጫው ከላይ ካለው ፋይል ጋር ተያይዟል
@Adisnews
@Adisnews
ኢትዮ ቴሌኮም ግብርን በቴሌ ብር ለመክፈል የሚያስችል አሰራርን ይፋ አደረገ‼️
ኢትዮ ቴሌኮም ገንዘብን በቀላል ፣ፈጣን ፣ ምቹ እና አስተማማኝ በሆነ መልኩ ግብርን በቴሌ ብር ለመክፈል የሚያስችል ስምምነት ከኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ጋር በዛሬው እለት ተፈራርሟል ።ደንበኞች ግብርን መክፈል የሚችሉበት የተለያየ መተግበሪያዎች መኖራቸው ተጠቁሟል።
ከነዚህም ውስጥ የቴሌ ብር የደንበኛ መተግበሪያ፣ የደንበኞች መተግበሪያን፣ እንዲሁም *127# በመጠቀም የብሄራዊ ባንክ ህግን በማክበር ግብርን መክፈል እንደሚቻል ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል ።ግብር ከፋዮች ኢ ታክስ ሲስተምን መጠቀም የሚችሉበት አሰራር ሲሆን የአጋርነት ስምምነቱ ለገቢዎች ሚኒስቴር የገቢ ግብርን እና የግል ሰራተኞች የጡረታ መዋጮ ፣ የፌደራል ታክስ ክፍያዎችን በወቅቱ ለመሰብሰብ እና ለማሳለጥ ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተገልጿል ።
ቴሌ ብር አገልግሎት እስካሁን 28.2 ሚሊዮን ደንበኞችን ማፍራት የቻለ ሲሆን ፣112 ዋና ወኪሎች ፣ ከ98 ሺህ በላይ ወኪሎችን እና ከ25 ሺህ በላይ ነጋዴዎችን ማፍራት ችሏል።በቀጣይም ጊዜያት ኢትዮ ቴሌ ኮም ከሌሎች ተቋማት ጋር በመተባባር የክፍያ ስርዓትን በቴሌ ብር የሚተገብርበት አሰራር በማመቻቸት ደንበኞችን የዲጂታል ክፍያ ስርዓት ተጠቃሚ ለማድረግ እንደሚሰራም የኢትዮ ቴሌ ኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ወይዘሪት ፍሬህይወት ታምሩ ገልጸዋል ።
@Adisnews
ሼር ሼር በማድረግ ይተባበሩን
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን! ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ የጾምና የምሕላ አዋጅ አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ‼️
"የነነዌም ሰዎች እግዚአብሔርን አመኑ ለጾም አዋጅ ነገሩ!
ከታላቁም ጀምሮ እስከ ታናሹ ድረስ ማቅ ለበሱ።"
ትንቢተ ዮናስ ምዕራፍ 3 ቁጥር 5
ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በተከሰተው ሃይማኖታዊ፣ ቀኖናዊና አስተዳደራዊ መዋቅሮቿን በመጣስ መፈንቅለ ሲኖዶስ በማድረግ በሕገወጥ መንገድ ኤጲስ ቆጶስነት ሢመት በሰጡትና በተሾመ ግለሰቦች ላይ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ጥር 18 ቀን 2015ዓ.ም. ቃለ ውግዘት ማስተላለፉ ይታወቃል።
ይሁን እንጂ እነዚህ ሕገወጥ ቡድኖች ከድርጊታቸው ሊታቀቡ ካለመቻላቸውም በላይ በመንግሥት ኃይሎች በመታገዝ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የምታስተዳድራቸውን መንበረ ጵጵስናዎችንና ቢሮዎችን በኃይል በመውረርና በመስበር ከፍተኛ ጥፋት እያደረጉ ከመሆኑም በላይ የአህጉረ ስብከት ሥራ አስኪያጆችን ሠራተኞች ካህናትና ምእመናን በማሰርና በማንገላታት ላይ ይገኛል፡፡ መንግሥትም ሕግ ከማስከበር ይልቅ ለሕገ ወጥ ቡድኖች ድጋፍ በመስጠት የቤተ ክርስቲያኒቱን ሕግና መብት ሊያስከብር ስላልቻለ ሁሉን ማድረግ ወደሚቻለው አምላካችን በመማፀን ጸሎትና ምሕላ ማድረጉ አስፈላጊ መሆኑን ቅዱስ ሲኖዶስ ተረድቷል።
በመሆነም ጾመ ነነዌን ምክንያት በማድረግ በመላው ዓለም የሚገኙ ሕዝበ ክርስቲያን ጥቁር ልብስ ብቻ በመልበስ በጾምና በጸሎት ምሕላ በመያዝ በቤተ ክርስቲያን ዓውደ ምሕረት በመገኘት ወደ እግዚአብሔር ጾም፤ ጸሎትና ምሕላ እንድታቀርቡ ቅዱስ ሲኖዶስ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡
ጥቁር ልብስ የምንለብሰው በመከራ መጽናት ለመግለጽ ነው፡፡
እንደሚታወቀው ጥቁር የእውቀት ምልክት ነው ተማሪዎች አውቀናል ሲሉ ጥቁር ልብስ ይለብሳሉ፡፡ እኛ ከእውቀት በላይ የሆነውን አምላካችንን በመማፀን ከዚህም ማንም ሊያናውጽን እንደማይችል የምናረጋግጥበት፤ ጥቁር የእውነት ምልከት ነው ዳኞች እውነት እንፈርዳለን ሲሉ ጥቁር ልብስ ይለብሳሉ፡፡ እኛም መከራው የሚያሰቅቀን ሳይሆን ይበልጥ ልንጸናና ልንበረታ የሚገባ መሆኑን ለዓለም ሕዝብ የምናሳይበት በመሆኑ ከጥር 29 እስከ የካቲት 1 ቀን 2015 ዓ.ም ለሦስት ቀናት በጾምና በጸሎት በአንድ ልብ ሆነን ወደ ፈጣሪያችንን እንድንጮህ አደራ እንላለን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ጥር 26 ቀን 2015ዓ.ም. አዲስ አበባ
@Adisnews
@Adisnews
ዕድሜ በሚያጭበረብሩ አትሌቶች ላይ እርምጃ መውሰድ ተጀምሯል‼️
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዕድሜ በሚያጭበረብሩ አትሌቶች ላይ እርምጃ መውሰድ መጀመሩን አስታወቀ።
ከጥር 23-28 ቀን 2015 ዓ.ም በአሰላ አረንጓዴው ስታዲየም እየተካሄደ በሚገኘው ከ20 ዓመት በታች የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ ከዕድሜ ተገቢነት ጋር በተያያዘ ከዕድሜ በላይ ሆነው የተገኙ አትሌቶችን በሠነድ እና በአካላዊ ምርመራ ከውድድር ውጭ ማድረጉን ፌዴሬሽኑ ገልጿል።ፌዴሬሽኑ ቁጥራቸው ከ80 የሚልቁ አትሌቶችም ስማቸውን ይፋ አድርጓል።
ተግባሩን በፈፀሙ ቡድኖች አሰልጣኞች ላይም እርምጃ እንዲወሰድ ለየክልላቸው፣ ከተማ አስተዳደራቸው፣ ክለባቸውና ተቋሞቻቸው ፌዴሬሽኑ ማስጠንቀቂያ አዘል ደብዳቤ እንደሚልክ አሳውቋል።
@Adisnews
@Adisnews
ቶሎ ቶሎ እንዲደርሶ ለእኛም ብርታት እንዲዎን ሼር ያደርጉ እናመሰግናለን።
አዲስ ነገር
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ አማካሪ ቡድናቸውን አነጋገሩ‼️
በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነውን የጠቅላይ ሚኒስትር አማካሪ ቡድን በዛሬው ዕለት ሰብስበው ማነጋገራቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ አስታወቁ።
የአማካሪ ቡድኑ አባላት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ጠንከር ያሉ ግብአቶችን የማምጣት እና ለትግበራ ሊሆኑ የሚችሉ ሐሳቦችን የማመንጨት ሥራ እንዲሠሩ አቅጣጫ ማስቀመጣቸውንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባጋሩት ፅሁፍ ገልፀዋል።
@Adisnews
@Adisnews
@Adisnews
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ለከፍተኛ የመንግስት ሃላፊነት ቦታዎች ሹመቶች ሠጡ‼️
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 74(2) መሰረት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፤ የሚከተሉትን ሹመቶች እንዲያጸድቅ ጠይቀዋል፦
1. ዶ/ር አለሙ ስሜ - የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር
2. ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኝ - የማዕድን ሚኒስትር
3. ዶ/ር ግርማ አመንቴ - የግብርና ሚኒስትር
በተጨማሪም ከጥር 10፣ 2015 ጀምሮ የሚከተሉትን ሹመቶች ሰተዋል፦
1. አቶ ማሞ ምሕረቱ - የብሔራዊ ባንክ ገዢ
2. ወ/ሮ አለምፀሐይ ጳውሎስ - የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ኃላፊና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር
3. ዲያቆን ዳንኤል ክብረት - የማኅበራዊ ዘርፍ አማካሪ ሚኒስትር
4. አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ - የውጭ ፖሊሲ አማካሪ ሚኒስትር
5. አቶ መለሰ አለሙ - በሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ የዘርፍ አስተባባሪ
@Adisnews
ሰበር ዜና‼️
ሕወሃት በአፍሪካ ህብረት መሪነት የሚደረግ ድርድርን እንደሚቀበልና በአቸኳይ ጦርነት ቆሞ ወደ ድርድር ለመግባት መዘጋጀቱን አስታወቀ።
ሕወሃት ቀደም ሲል የአፍሪቃ ሕብረትን አደራዳሪነት ገለልተኛ ስላልሆነ አልቀበልም ማለቱ ይታወሳል። ሕወሃት ማምሻውን ባወጣው መግለጫ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ግጭት ቆሞ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ዘላቂ ተኩስ አቁም እንዲደረግ ለመደራደር መዘጋጀቱንና ለዚህም ፃድቃን ገብረተንሳይና ጌታቸው ረዳን ተደራዳሪ አድርጎ መሰየሙን አስታውቋል።
በድርድሩ አለማቀፉ ማኅበረሰብ በታዛቢነትና ድጋፍ በማድረግ እንዲሳተፍ እንደሚፈልግም ሕወሃት አስታውቋል። የኢትዮጵያ መንግስት በጉዳዩ ላይ እስካሁን ምላሽ አልሰጠም።
@Adisnews
ሼር በማድረግ ይተባበሩን
ህወሓት የቅድመ ግጭት ጩኸቱን እያሰማ ነው ሲል የመከላከያ ሚኒስቴር ገለፀ‼️
ህወሓቶች "የሰላም ድርድሩ ቴክኒካል ፈርሷል፣ መከላከያ ኃይሉን እያስጠጋ ነው፣ መከላከያ በከባድ መሳሪያ እየደበደበን ነው፣ ከላይ እስከታች የዕዝ ሰንሰለቱን ጠብቆ እየተፈፀመ ያለ ጥቃት ነው" ወዘተ በማለት የቅድመ ግጭት ጩኸታቸውን በስሙልኝ ፕሮፖጋንዳቸው እያስተጋቡ ይገኛሉ ሲል መከላከያ ሚኒስቴር ገልጿል።
ሚኒስቴሩ ዛሬ ባወጣው መግለጫ የሠራዊቱን ወቅታዊ ሁኔታ ባልተረጋገጡ፣ ባልተገቡ መረጃዎችና አሉባልታዎች የመዘገብ ወይም የማራገብ አሉታዊ ሙከራዎችም በአስቸኳይ እንዲቆሙ ሲል በጥብቅ አሳስቧል።
@Adisnews
@Adisnews
"የ2014 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከመስከረም 30 /2015 ዓ/ም ጀምሮ በ2 ዙር እንዲሰጥ ታቅዷል"‼️
🗣ትምህርት ሚኒስቴር
የ2ዐ14 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት መልቀቂያ ፈተና በዩኒቨርስቲዎች እንዲሰጥ መወሰኑ ይታወቃል፡፡
ፈተናው ከመስከረም 30 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ #በሁለት_ዙር እንዲሰጥ መታቀዱን በትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ተፈርሞ ለ42 ዩኒቨርሲቲዎች በተላከውን እና ቲክቫህ ኢትዮጵያ ትክክለኛነቱን ባረጋገጠው ደብዳቤ መመልከት ችለናል።
በዚሁ መሠረት ከመስከረም 28 እስከ ጥቅምት 17 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ዩኒቨርስቲዎች ፦
1. ምንም አይነት የመደበኛ ተማሪ በግቢ እንዳይኖር እንዲያደርጉ፤
2. በቀጣይ በሚገለጸው ተማሪ ቁጥር ልክ ምግብ እንዲቀርብ ዝግጅት እንዲያደርጉ፤
3. ለፈተናዎች ማቆያ ቦታ እንዲዘጋጅ እና
4. የፈተናውን አሰጣጥና ደህንነት የሚቆጣጠር በፕሬዚዳንት የሚመራ ዋና ግብረ-ኃይልና በየካምፓሶቹ በዲን /ካምፓስ ኃላፊ የሚመራ ንዑስ ግብረ-ኃይል እንዲያደራጁ መልዕክት ተላልፎላቸዋል።
ዩኒቨርሲቲዎች የ2ዐ15 የአካዳሚክ ካላንደር የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት መልቀቂያ ፈተና ወቅት (ከመስከረም 28 - ጥቅምት 17) ታሳቢ በማድረግ እንዲያዘጋጁ የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ አሳስበዋል።
@Adisnews
@Adisnews
የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና ማስፈፀሚያ መመሪያ ፀደቀ‼️
የከፍተኛ ትምህርትን አገራዊ ቅድመ ምረቃ የመውጫ ፈተናን በአግባቡ ለመምራትና ለማስተዳደር የተዘጋጀው የከፍተኛ ትምህርት መውጫ ፈተና ማስፈፀሚያ መመሪያ ፀድቋል። መመሪያው በፍትህ ሚኒስቴር ተመዝግቦ እና ፀድቆ ለትግበራም ይፉ ሆኗል።
መመሪያው በመውጫ ፈተና ዝግጅት ሊካተቱ ስለሚገባቸው ሃገራዊ ዝቅተኛ የትምህርት ብቃት መመዘኛዎችን ፣ የሙያ ሥነምግባር ደምቦችን እና ተቋማት ሊከተሏቸው የሚገቡ የአሠራር ስነ- ስርዓቶችን አካቷል። ከሚቀጥለው የትምህርት ዘመን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲሆን ለሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መላኩ ተገልጿል፡፡
@Adisnews
@Adisnews
Repost from ሰብለ ሱዙኪ መኪና አስመጭ እና ላኪ
✨✨#እኛም_አሐዱ_ብለናል✨✨
የመኖሪያ ቤት ሽልማት ለባለ እድለኞች ከአሀዱ ባንክ፡፡
ሰላም ፍቅር ጤና እንዲሆንላቹ እየተመኘን የባንኩ ቦርድ ሊቀመንበር #አቶ_መላኩ_ፋንታ ሀገራዊ ለዉጡን ተከትሎ ሀገራዊ ኢኮኖሚዉን ለማሳደግ የተከፈተ ባንኩ ሲሆን በሀገሪቱ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ላይ አስተዋጽዎ ለማድረግ የተጀመረ #ባንክ ነዉ ብለዋል። በዚህም ባንካችን ስራ በመጀመሩ ምክንያት ለመላው ኢትዮጵያውያን መልካም ስጦታ ይዘን ቀርበናል እናም እድለኛ ለሆኑ 3 የአዲስ አበባ ወይም ከአዲስ አበባ ውጪ ለሚኖሩ ነዋሪዎች የመኖርያ ቤት አፓርታማ ልንሸልምዎ ዝግጅታችንን ጨርሰናል፡፡
#1ኛ_እጣ ባለ 3 መኝታ ከነሙሉ እቃው፡፡
#2ኛ_እጣ ባለ 2 መኝታ ከነሙሉ እቃው፡፡
#3ኛ_እጣ ባለ 1 መኝታ ከነሙሉ እቃው፡፡
ቀጥሎ ላሉ 100 እድለኞች የ6000 ብር ሽልማት ይኖረዋል፡፡ ይህ እጣ የሚቆየው እስከ ንሀሴ 30 ሲሆን በኮምፒዩተር እጣ አወጣጥ ዘዴ በመታገዝ እድለኞችን ንሀሴ 30 በዚ ቻናል ላይ ይፋ የምናደርግ ይሆናል፡፡
ከእናንተ ሚጠበቀው ቻናላችንን እና ቦታችንን መቀላቀል እንዲሁም ደግሞ ለዘመድ አዝማድዎ ለወዳጅቾ #በቦቱን እድላቸውን እንዲሞክሩ ቢያንስ ለ40 ሰዎች ሼር በማረግ እንዲቀላቀሉ መጋበዝ ብቻ ነው፡፡ #ከ_40_ሰው በላይ መጋበዝ እድልዎን ያሰፋል፡፡
#ቦቱ 👉@Ahadu_bank_bot
መልካም እድል ከ አሀዱ ባንክ፡፡
https://t.me/bank_ahadu
https://t.me/bank_ahadu
የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብር ኃይል ለአትሌቲክስ ቡድናችን አቀባበል ህብረተሰቡ የተለመደውን ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ አቀረበ‼️
በ18ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ደማቅ ውጤት ላስመዘገበው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ የልዑካን ቡድን አባላት አቀባበል ሲባል ለተሸከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብር ኃይል ይፋ አድርጓል፡፡
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድን ዛሬ ምሽት አዲስ አበባ የሚገባ ሲሆን÷ ለቡድኑ ደማቅ አቀባበል እንደሚደረግ የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታውቋል፡፡
በአቀባበሉ ወቅት የትራፊክ መጨናነቅ እንዳያጋጥም የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ስለሚደረጉ ህብረተሰቡ የተለመደውን ትብብር እንዲያደርግ ግብረ ኃይሉ ጥሪ አቅርቧል፡፡
ለአትሌቲክስ ቡድኑ አባላት ሐምሌ 21 ቀን 2014 ዓ.ም በአዲስ አበባ ደማቅ አቀባበል የሚደረግ ሲሆን የአትሌቲክስ ቡድኑ ካረፈበት ስካይላይት ሆቴል ከጠዋቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ በአጀብ በአዲስ አበባ ከተማ ዋና ዋና ጎዳናዎች ስለሚጓዝ የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ ግብረ ኃይሉ ማስታወቁን የአዲስ አበባ ፖሊ ኮሚሽን መረጃ ያመላክታል፡፡
@Adisnews
