𝗔𝗽𝗼𝘀𝘁𝗼𝗹𝗶𝗰 𝗦𝗼𝗻𝗴𝘀 ℠
Open in Telegram
💠“እኔም በበገና ስለ እውነትህ አመሰግንሃለሁ፤ የእስራኤል ቅዱስ አምላክ ሆይ፥ በመሰንቆ እዘምርልሃለሁ።” መዝሙር 71፥22 for any comment 👉 @ApoSonBot 💥YouTube https://www.youtube.com/c/ApostolicSongs 💥Facebook https://www.fb.com/ApoSongs 💥Instagram https://www.instagram.com/apostolic_songs
Show more2 953
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
2 953
እንኳን ለ33ኛው ዓመት የዋራ ቤቴል አለም አቀፍ ጉባኤ በሰላም አደረሳችሁ!
በኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን የዲጂታል ሚዲያ አገልግሎት መቋቋሙ ይታወሳል። የሚዲያ አገልግሎት ክፍሉ ስራውን በይፋ የጀመረ ሲሆን፣ ቤተክርስቲያንን በሚመጥን ደረጃ ዝግጅቱን ለማቅረብ እንቅስቃሴ መጀመሩን ሲያበስር በታላቅ ደስታ ነው።
አገልግሎቱም እንደ መነሻ “አሜን-የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን መልቲ ሚዲያ አገልግሎት” የተሰኘ የቴሌግራም ቻናል የከፈተ ሲሆን በቅርቡ ለታሰቡት የማህበራዊና ዲጂታል ሚዲያ አማራጮች እንደ መደላድል የምንጠቀምበት አማራጭ ይሆናል። ከዚህም በተጨማሪ ከክፍሉ የሚተላለፉ የጅማሬ ማስታወቂያዎችና ዝግጅቶች ወደ ቅዱሳን የሚደርሱበት መንገድ ይሆናል።
Link: https://t.me/AmenApostolicMedia
የዲጂታል ሚዲያ አገልግሎት ክፍል
2 953
የአባታችን የአምላካችንና የጌታችን ብሩካን ሁሉ ሰላም ለእናንተ ይሁን!
የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ኦዲዮቪዥዋልና ስነ-ጽሑፍ ክፍል በይዲድያ መዘምራን ህብረት በኦሮምኛ ቋንቋ የተዘጋጀውን 2ኛ የዝማሬ ሰንዱቅ (Album) ለመታነጽና ለበረከት እንዲሆንላችሁ ወደ እናንተ በዚህ እሁድ ያቀርባል።
ሐዋርያው ጳውሎስ በ2ኛ ቆሮንቶስ 9፥12 “ደግሞ በብዙ ምስጋና ለእግዚአብሔር ይበዛል፤” እንዳለ የዝማሬ ጸጋ ከላይ በተቀበሉ ወንድሞችና እህቶች የሚዘጋጁትን መዝሙሮች በትክክለኛው መንገድ በማግኘት ምስጋናችን ለእግዚአብሔር እንዲበዛ ምክንያት እንደሚሆኑልን እምነታችን ብሎም ጸሎታችን ነው።
በኢትዮጵያ ያላችሁ ተጠቃሚዎቻችን ዝማሬዎቹን ለማውረድ የምትጠቀሙበትን ኮድ በቴሌግራም ቦት @ApostolicPayBot ላይ ማግኘት የምትችሉ ሲሆን ከኢትዮጵያ ውጪ ያላችሁ ደግሞ ክሬዲት ካርድ በመጠቀም አልበሙን ማግኘት እንደምትችሉ እንገልፃለን።
የኦዲዮ ቪዥዋልና ስነ-ጽሑፍ ክፍል
ህዳር 2016 ዓ.ም
Source: @ApostolicSongsApp
2 953
የኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን ኦዲዮቪዥዋልና ስነ-ጽሑፍ ክፍል አዲስ የዝማሬ ሰንዱቅ (Album) ውስጥ ወደ ጆሮአችሁ ሊያደርስ ጥቂት ቀናቶች ቀርተዋል። ክብር ለኢየሱስ ይሁን!
በዚህ አልበም ውስጥ በተለያየ ጊዜ ከእግዚአብሔር በተቀበሉት መዝሙር የታነጻችሁና አምላካችንን ለማመስገን ምክንያት የሆኗችሁ አራት ዘማሪያን አሁንም ለቅዱሳን መታነጽና ለእግዚአብሔር ክብር የሚሆኑ ዝማሬዎች ይዘው መጥተዋል! እንደምትባረኩበት ጥርጥር የለንም!
ከሶሎ ዝማሬዎች በተጨማሪ ቀደም ባሉት አመታት የእግዚአብሔር ህዝብ ሲጽናናባቸው ከነበሩ መዝሙሮች ጥቂቶቹን በህብረ ዝማሬ መልክ ተዘጋጅተው ተካተዋል።
በዚህ የዝማሬ አልበም በተለያየ መንገድ የተሳተፉትን ሁሉ እግዚአብሔር በርከት ብሎ በሚጠራው ነገር ሁሉ እንዲባርካቸው ምኞታችንም ጸሎታችንም ነው!
ሚክሲንግና ማስተሪንግ
አሰግድ ፍቅሩ
ቅንብርና ሚክሲንግ
ኢያሱ ጸጋው ፣ ናትናኤል ጸሐይ፣ ዮናታን ሳሙኤል፣ አብርሃም ታደሰ፣ አቤንኤዘር አስራት
አጃቢዎች
ወይንሸት አለሙ፣ ሙሴ ሲሳይ፣ ኤክሶደስ ጌታሁን፣ በረከት አለምዘውድ፣ ኢቮን መሀመድ፣ ቤቴል አዳነ፣ እያኤል አሰፋ፣ አቤንኤዘር ደሳለኝ፣ ኢዮስያስ ደስታ፣ ዳዊት ንጋቱ
የኦዲዮ ቪዥዋልና ስነ-ጽሑፍ ክፍል
መስከረም 2015 ዓ.ም
2 953
አቤት እጅህ አገኘችኝ ምህረትህ
ነፍሴን ባረካት ከመልካምነትህ
እኔም ቤት ምስጋና አለ ምስክርነት
ቆሜ በአደባባይ የማወራለት
ነቅንቆ መዘነልኝ
አትረፍርፎ ሰፈረልኝ
እንደቼርነቱ መጠን ባረከኝ
እየጨመረ /2* ደግሞ የሚበዛ ሰላም ሰጠኝ
@ApoSon
2 953
ጦሩ የጦር ወሬው የምጥ ጣር ነው መጀመርያ
እርሃብ ቸነፈሩ ማሳያ ነው ማስጠንቀቅያ
አምልጥ ግባና ወደ መርከቡ
እያለ ጊዜ እያለ እድሉ
ባለማስተዋል ባለመንቃት
በጥፋት ውኃ እንዳትወሰድ
👉 https://youtu.be/mWgVZW2s4OA
