en
Feedback
መስቆ ቫይን

መስቆ ቫይን

Open in Telegram
690
Subscribers
No data24 hours
-27 days
+130 days
Posts Archive
photo content

photo content

photo content
+2

photo content

photo content

#የመስቃን_ህዝብ_ሁሉ_ማወቅ_ያለበት_እውነታ #ሰሚ_ያጣ_ጩኸት_ሞትና_መፈናቀል #በምስራቅ_መስቃን_ህዝብ 👇👇👇👇👇👇👇👇 የማእከላዊ ኢ/ርእሰ መስተዳደር ክቡር አቶ እንዳሻው ጣሰው ሀገራችን ኢትዮጵያ ትልቅ አቅም ካላቸው መሪዎች ውስጥ እርሶ አንዱ ኖት ታዳ የምስራቅ መስቃን ህዝብ የንፁሀን ሞት ለምን ዝምታ ተመረጠ በንፁሀን ሞትስ ማነው ተጠቃሚው ሰሚ ያጣው ጩኸት መች የሆን ስሚ የሚያገኘው መስቃን ሲሞት ፅንፈኛ ማረቆ ሲሞት የቡሄር ስም እየተሰጠው በሟቾች ላይ ቀልድ መች ነው የሚያቆመው ክልሉ ስራ ከጀመረ ጀምሮ ቅድሚያ ለሰላም በሚል ዘርፈ ብዙ ስራ መከናወኑ ይትወቃል ለዚህም ማሳያ የመስቃንና የማረቆ የእርቅ ስነስራአት ነው ከዚህ እርቅ ስነ ስርአት ቡሀላ የተቀጠፉ ንፁን የሰው ፍጥረት አይደሉምን ለምንስ ዝምታ ተመረጠ ችግርስ ፈጣሪው አልታወቀም ነው ከእርቅ ቡሀሏ የተፈጠሩ ችግሮች በዝርዝር እንመልከት 1👉ዲዳ ላይ ስብሰባ ላይ የነበሩ የምስራቅ መስቃን ወረዳ አመራሮች ላይ በጠራራ ጸሀይ ሚሊሻ ገደሉ 2👉እዚያው ዲዳ ባልዋ መስቃን የሆነች ትልቅ እናት እስከነ ህጻን የልጅልጇ ጋር ተገደሉ በእድሜ ገፋ ያሉት ሽማግሌ ባላቸው የአካል ጉደተኛ አደረጉ 3👉ረመዳን ውስጥ ባቴ ፉጦ ወላጆቸውን ዘይረው ሲመለሱ የነበሩ አራት ሰዎች  ባጃጅ ላይ እንዳሉ በተተኮሰ ጥይት እድን ወንድ እንዲሁ አንድ ሴት እስከነ ሆድ ልጇ በመግደል አንዱን ያልጋ ቁራኛ አደረጉ 4እንዲሁ በረመዳን መግሪብ ሰላት ተሰግዶ ሁሉም እያፈጠረ ባለበት ሰአት አንድ ማረቆ ኢንሴኖ ፉጦ መውጫ ተገደለ ገዳይ ስራውን ከጨረሰ ቡሀሏ በጥቂት ደቂቃዎች ቡሀሏ በራሳቸው ፖትሮል ጩኸቴን ቀሙኝ ደባ ፈፀሙ 5ኦሮሚያ ድንበር ላይ መስማት የተሳናት እህታችን ተገደለች 6ከቅርብ ሳምታት በፊት  ከምሽቱ 1 ከሀያ አካባቢ ምሽትን ተገን በማድረግ ሶስት ሰዎች ተረሸኑ ሰኞ ማታ በቀን 25/10/16 በግድያ ወንጀል ክስ ተይዞ በመስቃን ወረዳ ፖሊስ ጣቢያ በአደራ እንዲቆይ ተደርጎ የነበረው አማን ሜጤቦ በቀን13/10/16 ተለቀቀ እንዴት ተለቀቀ የሚለው ጥያቄ ከዞን አቃቢ አቶ ፋሲካ ስርሞሎና ሀብታሙ ዞን ፀጥታ ሀላፊዎች መጠየቅ እንፈልጋለን በዚህ ወንጀለኛ አማካኝነት አንዲት እናት ከ12ክፈል ተማሪ ልጇ በግፍ ተገደሉ በቀን26/10/16 ልጃቸውን በግፍ ያጡት  ትልቅ አባት ከነ ቤተሰቦቻቸው የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ ተካሄደባቸው እኔ መናገር የምፈልገው ይህ ሁለ እልቂት የኑፁሀን ሞት ሰሚ አነበረውም የህግ ያለህ ሲል ደሙ ፈሶ ሲቀር  አንድም እርምጃ አላየነም ለምን መስቃን ስለሆኑ ወይስ የሰው ፈጥረት አይደሉም ይህ የምለው ያለ ምክኛት አይደለም አንድ የማረቆ ወጣት መገደሉ ሲሰማ ከዞን ፀጥታ እስከ ክልል ተቀሳቀሰ የምስራቅ መስቃንና የኢኒሴኖ ፀጥታ ሀላፊዎች ልጥያቄ ትፈለጋላቹ በሚል ሆሳና ተወስደው ታሰሩ እኛ እያልን ያለነው አይታሰር ለምን እያልን አይደለም ወንጀለኛ ይታሰር ንፁሀን ይፈታ ነገር ግን የአንዱ ደም ውሀ ተደርጎ የሚታይበት ነገር ይቁም ገዳዮች ገለው  መቀመጫቸው አውሮፖ ያደረጉ በደም ነጋዴ ሚዲያዎች ላይ ሀሰት መረጃዎችን እያስተላለፉ የህዝብን ሰላም እየነሱ የመኖር መብቱን እየነፈጉት ነው አሁንም አሰምርበታለው መስቃኑ ሲሞት ፅፈኛ ማረቆ ሲሞት የብሄር ስም እየሰጡ የማእከላዊ ክልል በቅርቡ  እስር ቤት አስገብቶቸው የነበሩ እንደነ ሀቢብ ከድርና መለሰ አብራሀም አክትቪስቶችን ጨምሮ በኩሽ ነገድ ትስስር በመፍጠር  ወንጀል እንዲስፋፋና ንፁሀን እንዲሞቱ እየተደረገ ነው መለሰ አብራሀም ከእስር ቡሀላም ክልሉን የማመፅ ስራው ቀጥሉዋል ይህ ተግባር ክልል ፌድራል  ስልጣን ላይ ያሉ ዘረኝነት የተጠናወታቸው የደም ነጋዴ አመራሮች አሉበት ለሰላም ፍትህ ለሰላም ተዘረጉ እጆች አይቆረጡ ሞት ይብቃ መታወቅ ያለበት ሆን ተብሎ የኛን  ቀጠና ማለትም ምስራቅ መስቃን ለማመስ ታስቦ እንጂ  ለሞቱት ማረቆና የሌሎች ብሔር ተወላጆች ታስቦ አይደለም።   የነዚህ አጥፊዎች አላማ  ለወገን እዝነት ሳይሆን ሞታቸውን ለፖለቲካ ቁማር ነው ለመጠቀም ታሳቢ የተደረ መሆኑን ታውቆ ህግ ይከበርልን አሁን ፍትህ

photo content

"ሰላም ለሁሉም ፤ ሁሉም ለሰላም" በሚል መሪ ቃል ሰኔ 30/2016 ዓ/ም በቡታጅራ ከተማ የሩጫ ውድድር ይካሄዳል ሰኔ 26/2016 ዓ.ም (ቡታጅራ ) በሰላም ግንባታና አብሮነት ላይ ያተኮረ የሩጫ ው
"ሰላም ለሁሉም ፤ ሁሉም ለሰላም" በሚል መሪ ቃል ሰኔ 30/2016 ዓ/ም በቡታጅራ ከተማ የሩጫ ውድድር ይካሄዳል     ሰኔ 26/2016 ዓ.ም (ቡታጅራ ) በሰላም ግንባታና አብሮነት ላይ ያተኮረ የሩጫ ውድድር  በሰላም ሚኒስተር አማካኝነት በሀገር አቀፍ ደረጃ የተዘጋጀ ሲሆን ሰኔ 30/2016 ክልል አቀፍ የሩጫ ውድድር በዘቢዳር ፈርጧ በውቢት ቡታጅራ ከተማ ላይ እንደሚካሄድ የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ነጋሽ መሐመድ ገልፀዋል። የሩጫ ውድድሩ አስመልክቶ የምስራቅ ጉራጌ ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ እንዲሁም የዞኑ ወጣቶችና ስፖርት መምሪያው በጋራ በመሆን መግለጫ አውጥተዋል። የሩጫ ውድድሩ 6 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን ከ15ሺ በላይ የሚሆኑ ከተለያዩ ማኅበራዊ መሰረቶች የተውጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚሳተፉበት መሆኑንም ገልፀዋል። በምስራቅ ጉራጌ ዞን በቡታጅራ ከተማ የሚካሄደው ይህ የሩጫ ውድድር የህዝቦችን የአብሮነትና የአንድነትን እንዲሁም የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ ነው ተብሏል። የሩጫጠውድድሩ በ2ቱም ፆታዎች የሚሳተፉበት ሲሆን ከ1ኛ እስከ 3ኛ ለሚወጡ አትሌቶች ሽልማት እንደተዘጋጅ ተገልጿል። በውድድሩ ከፌደራል ከክልል ትላልቅ እንግዶች እና አትሌቶች የሚሳተፉበት ሲሆን የቡታጅራ ከተማና  ከመላው የዞኑ ማህበረሰብ እንዲሳተፍም ጥሪ ተደርጓል። በከተማዋ የሚደረገው ይህ ታላቅ የሩጫ ውድድር በሰላምና በስኬት እንዲጠናቀቅ የቡታጅራ ከተማ ፖሊስና የፀጥታው መዋቅር እንዲሁም የሰላም አምባሳደር የሆነው ወከተማው ወጣቶችና የህብረተሰብ ክፍሎችና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅትና በትኩረት እንደሚሰራም ተገልጿል።

የብስራት ዜና ለከተማችን ነዋሪዎች! የቡታጅራ ከተማ ማዘጋጃ ቤት 2.82 ኪሎ ሜትር አስፋልት ለማስገንባት ከኢትዮጲያ ኮንስትራክሽን ስራዎች የውል ስምምነት አከናወነ። ሰኔ 19/2016 ቡታጅራ ከተማ አስተዳደሩ በ3ተኛው ምዕራፍ ትልቅ ድልድይን ጨምሮ የ2.82 ኪሎ ሜትር ሁለት መንገዶችን አስፋልት ለማስገንባት 340 ሚሊየን ብር ውል ገብቷል። በቡታጅራ ከተማ በጉጉት ሲጠበው የነበረው በምዕራፍ 3 አስፋልት ለማስገንባት የተያዙት 2 መንገዶችን ለማስጀመር በዛሬው ዕለት ተፈርሟል። ከቴሌ እስከ መስቃን ወረዳ ፖሊስ ጣቢያ ፊት ለፊት ድረስ 0.42 ኪሎ ሜትር እና ከፈትኸል መስጂድ በነፃ ሰፈር አድርጎ ዝዋይ መንገድ ድረስ 2.40 ኪሎ ሜቶር አጠቃላይ 2.82 ኪሎ ሜትር ለማስገንባት ማዘጋጃ ቤቱ ከኢኮስኮ አዲስ አበባ በሚገኘው ዋናው ቢሮ ተፈራርሟል። የስምምነት ፈርማቸውን ያኖሩት በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስኪያጅ የሆኑት ኢ/ር ዮናስ አያሌው የስምምነት ፊርማቸውን ሲያኖሩ እንደተናገሩት፤ ቡታጅራ ከተማ በሁለት ምዕራፎች በድምሩ 8.79 ኪ.ሜ የውስጥ-ለውስጥ አስፋልት መንገዶች መገንባታቸውን አስታውሰዋል። ከተማዋ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገች በመምጣቷ ከተማ አስተዳደሩ በሶስተኛው ምዕራፍ ትልቅ ድልድይን ጨምሮ ሁለት መንገዶች በድምሩ 2.82 ኪሎ ሜትር በ 340 ሚሊዮን ብር በሚጠጋ ወጪ ለማስገንባት በዕቅድ ይዞ በመንቀሳቀስ ለዛሬ ፊርማ ማብቃቱ የሚያስመሰግነው ነው ብለዋል፤ በተጨማሪም የከተማው ህዝብ ተባባሪና ልማት ወዳድ መሆኑን በሁለቱ ምዕራፍ ግንባታዎች ያየን በመሆኑ ሦስተኛውንም ገንብቶ ለማጠናቀቅ የበኩላቸውን ይወጣሉ የሚል እምነት እንዳላቸው ገልፀዋል። በተለይም የወሰን ማስከበር ስራዎች ፈጥኖ ማጠናቀቅ ከተቻለ ፈጥነን ገንብተን ለአገልግሎት እናበቃለን ብለዋል። የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባና የኢንተርፕራይዞች ልማት ጽ/ቤት ኃላፊነት የሆኑት አቶ ደረጀ ራህመት በበኩላቸው ለመንገዱ መሰራት ከተማ አስተዳደሩ አስፈላጊው ድጋፍ እና ክትትል እንደሚያደርግ ገልፀዋል። ግንባታው በሚያልፍባቸው መንገዶች ያሉ ነዋሪዎች ግንባታው እንዲጀመር ተደጋጋሚ ጥያቄ ሲያቀርቡ እንደነበር እና ለልማቱ አስፈላጊውን ትብብር ለማድረግ ዝግጁነታቸውን ሲገልፁ እንደነበር አስታውሰው የወሰን ማስከበር ስራ በፍጥነት እንደሚጠናቀቅ አረጋግጠዋል። በመጨረሻም የውል ስምምነት ፊርማቸውን ያኖሩት የማዘጋጃ ቤቱ ሥራ አስኪያጅ አ/ር ተስፋዬ አህመድ ከኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን ጋር ያለን የስራ ግንኙነት በውጤት የታጀበ በመሆኑ ይህን የውል ስምምነት በመፈረማቸው ከፍተኛ ደስታ እንደተሰማቸው ገልፀዋል። ግንባታው በተያዘለት ጊዜ እንዲሁም በተቀመጠው የጥራት ደረጃ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊው ክትትል እንደሚደረግም አመላክተዋል።

photo content
+1

photo content

ሰኔ 14/2016 ቡታጅራ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር በአገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረው የኮሪደር ልማት በከተማችንም ለማስቀጠል ውስጥ ለውስጥ ከተገነቡበት የአስፋልት መንገዶች ውስጥ ከሆሳዕና ሆቴል ጀርባ እስከ ትልቁ መስጂድ ድረስ የ1.1 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው የአስፋልት መንገድ ግራና ቀኙ የእግረኛ መንገድ ቴራዞ ለማንጠፍና አረንጓዴ ለማድረግ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ሲሰሩ ቆይቶ ከመንገዱ ወሰን ከማስከበር (Right-of-Way) ጋር በተያያዘ ከነዋሪዎች ጋር በ13/2016 ዓ/ም በሴራና ሁለገብ አዳራሽ ውይይት ተካሄዷል። በውይይቱም ከኮሪደር ልማቱ በተያያዘ ገለፃ ያደረጉት አቶ ተስፋዬ አህመድ የማዘጋጃ ቤቱ ስራ አስኪያጅ የኮሪደር ልማቱ ግራና ቀኝ ላለው ነዋሪ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው በማብራራት በዋቢነትም በከተማችን በሁለት ምዕራፎች ያስገነባናቸውን የአስፋልት መንገዶች ግራና ቀኝ ያሉ መኖሪያ አካባቢዎች እንዴት ለውጥ እንዳመጡ ማየት ብቻ በቂ ነው ብለዋል። በመቀጠልም የማዘጋጃ ቤቱ ምክትል ስራ አስኪያጅና የማስፈፀም ዘርፍ ኃላፊ አቶ ወልዩ ከበደ ህብረተሰቡ ያልተሳተፈበት ማንኛውም ልማት መልማት እንደማይችል ገልፀው ከዚህ ቀደም መንገዱ አስፋልት በሚሰራበት ወቅትም የወሰን ማስከበር ችግር ከህብረተሰቡ ጋር በመወያየት በአጭር ጊዜ ውስጥ ችግሮቹን በመፍታት መንገዱ በተያዘለት ጊዜ አልቆ ለአገልግሎት መብቃቱን አስታውሰዋል። አሁን በተጀመረው የኮሪደር ልማት ከወሰን ማስከበር ጋር ተያይዞ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ችግሮች ተነስተው ችግሮቹ እንዴት መፈታት እንዳለባቸው በዝርዝር በውይይቱ ላይ ተነስቶ በመጨረሻም ነዋሪው ልማቱ በቅድሚያ ወደ መንደራቸው መምጣቱ ደስተኛ መሆናቸውን የሚጠበቅባቸውን ሁሉ ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀው እንደሚጀመር ቃል በተገባው መሰረት ወሰን የማስከበር ስራው ዛሬ በ14/10/2016 ዓ/ም በይፋ ተጀምሯል። መረጃውን ያደረሰን ማዘጋጃ ቤቱ ነው

photo content
+3

photo content
+3

photo content
+2

ኢድ ሙባረክ አቤም 1445 ዓመተ ሂጅራ የሙላ የአረፋ አመትባል አሰላናሁ መስቃን ወረዳ ባህል ቱሪዝም ጽ/ቤት ከነ 8/10/2016 እስልምና የትሄተለ እንም አኋም አቤም አሰላናሁ ። በእስልምና ዒማን ውስጥ ወደል አመትባል ነኖ !! በእስልምና ዒማን ውስጥ ያኖ እንም በጉጉት ይቅሮዮ ኖ!! ኽኖም 1/ኢድ አል አደሀ 2/ኢድ አልፈጥር 3/ መውሊድ በመስቃን ወረዳ ደግሞ በነን በጠቀስክኖም ሌላ የሶመን ፊቸ በድባድንቅ ሀለት ያከብር። አኋ ተከዋዪ አመትባል ትንዠበር አረፋ ይቡሪ ወደሊ አመትባል እረኽብነ ። አረፋ ብዠጌ የሀጅ ሴራ ተወሰክት ጌ የጥባበጠው ። በዚ ! አመትባል በእስልምና ውስጥ ወደል መደር ያነን የአረፋ ኒሻው! ። በመካ ውስጥ ቢትረከቦ ኒሻ አቲ ቲይኸን አባ አደም ዋ ዳኮና ሀዋ የትራከቦቧው። አባና አደም አትብራ የቧሪ ቅጠል በናም በጅነት አባና አደም ዋ ሀዋ ሰጀጂዮም ተዱኒያ አርዱላ አወሪጂዮም በዠጌ ቲሸሸዎ ነበሮም በአረፋ ኒሻ ተራከቦም አሺ ሟንሽ??? ባረም አባና አደም የሀዋ ቲሰላ ዠበረችም አሀሽ ሟንከ ትትብር ተሳለቹ?? በሂ ባቄውታን ኌትመህኖ ተሄሄሮም የትራከቦቧ መደር አኳም ስን አረፋ ኒሻ ቲዪቡሪ መደሪ ይጠሬ ። በአረፋ ወቅት ቢሸኩቺ የእስላማዊ ሴራ ውስጥ ቢቤድር ነዚ ይሸኩችዮ!! 1/ የሀጅ ሴራ ይሸኪቺ (ካዐባ ወዘይር ወበሩ) 2/ ሰላቲ ሰጕጅም በፏጂ አንቄ የኡድህያ ሴራ( እርድ ወሰክት) ያስናጅቧ !! ኡድሁያ ወበር ያስናጅቧ ምክናያተው አላህ(ሱ.ዐ) የነብዩ ኢብራሂም(ዐ.ሰ) የርጀህኖ እስማኤል(ዐ.ሰ) ያርዶ ኸማት ኤዘዘኖም ያርዶዬ ፊዳ ያቀርቦዬ ቲይኸን ጔታ ኤዘዘንም ጅብርል ቸኘም (ዐ.ሰ) በጤ ሸገረኖ ። የኢብራሂም(ዐ.ሰ) እርጅ እስማኤል ባለወታረደው ዋ የብዠ ዘበን ስን አደም(ዐ.ሰ) ተሀዋጌ ቴትራከብ ኤከሰም ባቄ በአረፋ ኒሻ ተራከቦም በነበረ አንቄ አላህ(ሱ.ዐ) እንጌ ተኬበረም ይወል ኸማት ኤዘዘ ተ! ሀቸውት ቀረሰም በእስልምና ዒማን ውስጥ በአመት በአመት በጉጉት ይቁሬ አመትባል ኸነም በሰ አመተው ቅየም ያከብር። ሙዕሚንሚ የብልቃቲ ከነ ብልቃት በብልቃት በወኽን ከነዪ ያቼልፉ። የአረፋ የዚ! ቅጫን በዝነጒሁ ያሰላ ተሂ ! ሀቸውት በመስቃን አበሮስ ምን ይመስር ይቡሪ ቃር አዥነ!!! አረፋ በመስቃ አብሮስ ምን ይመስር ይቡር ቃር ደሞ ንዥነ!!! አረፋ በምን ሀለት ያከቡሪ? ?? ያንን ጥቅምሽ በጀማ ውስጥ ምንቅጫኑ??? በመስቃ ወረዳ የእስልምና ኢማን የትሄተለ አረፋ ቲቸኝ በወደል ነሲብ ትኩረት አቢም ቢደንቅ ሀለት ያከቡሪ። አረፋ ተወስላውት በደረም ያነዪ ይሸኩቺ ቃር በመሬቲ ወስጥ ይፏጂ ። በዚ! መሰረት ዳኮ ያመትባሊ ይኸን ቃር ታስናጅ ወልተት ትሸክት!! 1/ የእርድ ይኸን ቦራ 2/ ውሳ/ ውሳ ያዝጓጂ በፋቒ አቄ ስድስት መሬት ስን በጎጀ ያወኔም የአመትባሊ ከነ ቲቸኝ ለየት አቧንም ያዝጓጂ። 3/ ቅብ ያነጥሪ 3/ ብሻ አሶ ያዝጓጂ 4/ አምብር ያቀርቢ 5/ ነቀባ ተዚ ነን የነሳኽኖ እንም በወቅተሁ በእንሽታ አመትባል ወቅት ወትረኸብ ነነወ። የግሬድ ደሞ ይነብሮቧ ወገ በዋድምቅ ፤ ወፈንቸ በወጥርግ፤ ልባስ ወጥብ ዋ የቧረቧ ግብር የዋስናጅ ሜና ይሸክቶ። ልክ የግሬዲ ኸማት ዴንጋም ይቂየቦ ቃር እንም ይሸክቶ ። የእርድ ይኸን ቦራ ፤ የሳት ይኸን ኸጨ ፤ ጎሎዶ ዋስናጅ ፤ እሰት በጓራ ዋስናጅ የዳኮ የአመትባል ይኸን ወጪ ዋብ ይብሪ ቃር እንም ይሸክት ሁቱቱ!!!። የአረፋ አመትባል ያነን የጀማ ጥቅመውታ!!! በአርበትሚ ቂልባ አመትባል የዋክበር ተጨኘወ ገኝ የቸኚ ሙዕሚን የአበሮሲ ጨኘት በጀማ ወባጀ በወበር ችግር ኸነም የታዠኖ ቃር እንም ችግሪ ይፏቸቧ ወቅቱ። የቤተሰበውታ ፤ የሞጣዬ ኑሮ ይሸሸል ኸማት ወባጀ ቧርም ሞጣዪ በምንከም ናለቅነ ባሮም ወባጀ (ምክክር) ልማት የዋንዝራባ በቁኒነት ምን ንሰክትነ ባሮም ወባጀ ይቡሪ ። የግሬድ አረፋ የግሬድ የአረፋ አመትባል ታፍቲ አመትባል በደረሙ ይቀረስ ። መካ ተከፈተም ይብርቧ ወቅቱ!! በዚ ከነ ግሬ የአመትባል ያዝጋደማይ ቃር እንም ወፍጀኽኖ ያርጋግጦቧ ከነው። የግሬድ አረፋ ከነ ግሬድ የአምብር ወላዳ፤ ድማሞሻት(የጎመን ቅልቅል)፤ ፍንታፍንቶ(ግማሽ አይብ ግማሽ ጎመን)፤ በቁና ቁና ጣባት በዋውና በቅብ ይሼሺም ተነቀባ ጌ በግብት ግብት ያስናጂ ። ስናጀ ቃዋ በቅብ ፤ በቅዋ በብጭወ አፏለም ቤተ -አበሮስ ተስበሰበም፤ ኦላ ጠሬም ብልቃት በብልቃት ይኽንቧ ወቅቱ።። አዳብና አረፋዋ መስቀል ቲቸኝ አዳብና ኤገፉሪ!! አዳብና ወበር (ባህል ) ገና አረፋዋ መስቀል ይገባዬ አስር ከነ ቲቐይን ደርስ ይቐርሽቧ ወቅቱ ።ከነዪ በሜና ይወልም ምሸቲ የደርስ ያሪ!! በአዳብናዪ ውስጥ የትዳር የሸውያ ገረድ ይሜጥርቧ ፤ ተዛም ነን የሸውያ ገረድ ባነቺ በጅራፍ ያቄታን ይጠቡሺያ ኽትም በሸች ፈገግ በወበር የህን ወበሬታን ታቴዥን በሂ ባሊቅ ይለኇም የባዬታዋ የዳዬታ ይሰልዮ የህን በባሮ ቀጠፍ ያጉጅናም ሸቤ ይሸኩች። አዳብናዪ ግን አረፋም ኸነ መስቀል በወጣ ከነ ቀረሰም አስር ከነ ዬክስ።።። አኋም በድጋሚ እንኳን የአረፋ አመትባል አሰላናሁ ። መስቃን ወረዳ ባህል ቱሪዝም ጽ/ቤት። የመስቃን ወረዳ ባህል ቱሪዝም ጽ/ቤት የተሌግራም ቻናል https://t.me/mesqantour https://t.me/+RdumCSV1g0g3NTM0 የመስቃን ወረዳ ባህል ቱሪዝም ጽ/ቤት የፌስቢክ ፔጅ https://www.facebook.com/profile.php?id=100088531813054