en
Feedback
ቦሌ ቡልቡላ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን (BBFGBC) No.1

ቦሌ ቡልቡላ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን (BBFGBC) No.1

Open in Telegram

Messages , sunday program and church announcement

Show more
452
Subscribers
+224 hours
+147 days
+4430 days
Attracting Subscribers
September '24
September '24
+44
in 0 channels
August '24
+48
in 0 channels
Get PRO
July '24
+47
in 0 channels
Get PRO
June '24
+45
in 0 channels
Get PRO
May '24
+28
in 0 channels
Get PRO
April '24
+13
in 0 channels
Get PRO
March '24
+37
in 0 channels
Get PRO
February '24
+45
in 0 channels
Get PRO
January '24
+70
in 0 channels
Get PRO
December '23
+227
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
25 September+1
24 September0
23 September0
22 September0
21 September+1
20 September0
19 September+1
18 September+3
17 September+3
16 September+4
15 September+2
14 September+1
13 September0
12 September+6
11 September+2
10 September+3
09 September+1
08 September+2
07 September+1
06 September+3
05 September+4
04 September+2
03 September+2
02 September+1
01 September+1
Channel Posts
የተወደዳችሁ ወገኖች ሠላም ለእናንተ ይሁን ።ዛሬ 24/11/2016 የምንችል ሁላችንም እህት ሶስና ቤት ለማጽናናት ከ11:00 ጀምሮ እንገናኛለን ።

2
Sent from Viber https://www.viber.com/invite/598065135206f1222155186fffb33bffabf48d21ec65c0d15d40bc4322b332f5
Sent from Viber https://www.viber.com/invite/598065135206f1222155186fffb33bffabf48d21ec65c0d15d40bc4322b332f5
344
3
የተወደዳችሁ ወገኖች ሠላም ለእናንተ ይሁን።የቤተክርስቲያናችን ሽማግሌ የነበረው ወንድም መካሻ የእህታችን ሶስና ባለቤት ወደሚወደው ጌታ ሄዷል።የቀብር ሥነሥርዓቱ በዮሴፍ ነገ ቅዳሜ በ 20/2016 ዓም ይፈጸማል።ሁላችንም በመገኘት ከዛሬ ጀምሮ ቤተሰቡን እንድታጽናኑ ይሁን።ጌታ ይባርካችሁ
621
4
መዝሙር 89 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁸ አቤቱ የሠራዊት አምላክ፥ እንደ አንተ ያለ ማን ነው? አቤቱ፥ አንተ ብርቱ ነህ፥ እውነትህም ይከብብሃል። ⁹ የባሕርን ኃይል አንተ ትገዛለህ፥ የሞገዱንም መናወጥ አንተ ዝም ታሰኘዋለህ። ¹⁰ አንተ ረዓብን እንደ ተገደለ አዋረድኸው፥ በኃይልህም ክንድ ጠላቶችህን በተንሃቸው። ¹¹ ሰማያት የአንተ ናቸው፥ ምድርም የአንተ ናት፤ ዓለምንና ሞላውም አንተ መሠረትህ።
520
5
No text...
630
6
🔈#የኢትዮጵያ_ቃለ_ሕይወት_ቤተክርስቲያን በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን የኩሪፍቱ ማዕከል ይዞታ ላይ በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት እየተወሰደ ነው ያለችው ሕገወጥ እርምጃ እንዲ+1
🔈#የኢትዮጵያ_ቃለ_ሕይወት_ቤተክርስቲያን በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን የኩሪፍቱ ማዕከል ይዞታ ላይ በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት እየተወሰደ ነው ያለችው ሕገወጥ እርምጃ እንዲቆም የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ጥሪ አቅርባለች። ቤተክርስቲያኗ በዛሬው ዕለት ስለጉዳዩ ሰፋ ያለ ዝርዝር መግለጫ ልካልናለች። ከመግለጫው መካከል ፦ " በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ እየተካሄደ ያለው ሕገወጥ አካሄድ፣ የፍርድ ቤትን ውሳኔን እና ከጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ ጉዳዩን ለማጣራት የመጣ ቡድን ግኝቱን ይዞ ሄዶ የበላይ ውሳኔ ባልተሠጠበት ሁኔታ የኮርደር ልማትን ሰበብ በማድረግ ከቤተ ክርስቲያን ይዞታ ላይ #መሬት_በጉልበት_ቀምቶ ለሁለት ግለሠቦች ለመሥጠት የሚደረገው ሥራ በወንጌላውያን አምነት ተከታዮች ላይ የተቃጣ የተቀነባበረ የግለሰቦችን ፍላጎት ለማሟላት ቤተ ከርስቲያናችን ላይ በተደጋጋሚ እየተሰነዘረ ያለ ጥቃት ነው። ይህ መላው የወንጌል አማኞችን የሚመለከት ኢ-ሕገመንግሥታዊ አካሄድ ስለሆነ፣ ጉዳዩን ለመንግሥትና ለፍትህ አካላት ማቅረባችን ይቀጥላል። ጉዳዩ የሚመለከታቸው የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ከፍተኛ አመራሮች እና የፌዴራል መንግስት አካላት ይህ ጉዳይ ጥቂት ግለሠቦችን ጠቅሞ ሚሊየኖችን የሚያስከፋ ሕገ ወጥ ድርጊት በመሆኑ አንድታስቆሙልን እና አስቸኳይ ምላሸ እንድትሰጡን በታላቅ አክብሮት እንጠይቃለን። በቤተ ክርስቲያናችን ላይ እየደረሰባት ያለውን ሕገ ወጥ እርምጃ አጥብቀን የምንቃወምና የምናወግዝ መሆኑን እንገልጻለን። መላው የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን እና የወንጌል አማኙ ማሕበረሰብ በአጠቃላይ ይህንን ህገመንግስታዊ መብታችንን የሚጋፋ ተግባር እስኪቆም ድረስ በያለንበት በጸሎት እንድንተጋ፣ በተለያየ መንገድ ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ ድምጻችንን እንድናሰማ፣ ጉዳዩ በዚህ የማይገታ ከሆነ ከወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጋር በመምከር ሌሎች ሊወሰዱ የሚገባቸውን እርምጃዎች እናሳውቃለን። " (ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል) @tikvahethiopia
293
7
መዝሙር 97 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁸ እግዚአብሔር ሆይ፤ ስለ ፍርድህ፣ ጽዮን ሰምታ ደስ አላት፤ የይሁዳም ሴት ልጆች ሐሤት አደረጉ። ⁹ እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ በምድር ሁሉ ላይ ልዑል ነህና፤ ከአማልክትም ሁሉ በላይ እጅግ ከፍ ያልህ ነህ። ¹⁰ እግዚአብሔርን የምትወዱ ክፋትን ጥሉ፤ እርሱ የታማኞቹን ነፍስ ይጠብቃልና፤ ከዐመፀኞችም እጅ ይታደጋቸዋል። ¹¹ ብርሃን ለጻድቃን፣ ሐሤትም ልባቸው ለቀና ወጣ። ¹² እናንተ ጻድቃን በእግዚአብሔር ደስ ይበላችሁ፤ ቅዱስ ስሙንም አመስግኑ።
584
8
መለያየት ለክርስቶስ? ሰዎች፣ በመካከላቸው ክርክርና አለመስማማት ሊኖር ሲፈቅዱ፣ በመጀምሪያውኑ፣ ለምን እንደተገናኙ ማሰብ አለባቸው፡፡ ክርክርና አለመስማማት እየተደጋገመ ሲመጣ፣ አንድ የማይቀር አደጋ ይመጣል፣ መለያየት፡፡ ክርክር በብዙ ቦታ ሲከሰት እናያለን፡፡ በቤተሰብ መካከል፣ በስራ ቦታ፣ በማህበረሰብ መካከል፣ በቤተክርሲትያንም ጭምር፡፡ እግዚአብሔር በሕዝቡ መካከል እንዲኖር የሚፈልገው ነገር አንድነት ሆኖ ሳለ፣ ክርክርና መለያየት ተንሳራፍቶ ስናይ ይገርመናል፡፡ ለዚህ ነበር፣ ሐዋርያው ጳውሎሰ ከእግዚአብሄር የተቀበለውን መልዕክት እንዲህ በማለት የሚጽፈው፡፡ “ነገር ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ሁላችሁ አንድ ንግግር እንድትናገሩ በአንድ ልብና በአንድ አሳብም የተባበራችሁ እንድትሆኑ እንጂ መለያየት በመካከላችሁ እንዳይሆን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እለምናችኋለሁ። ወንድሞቼ ሆይ፥ በመካከላችሁ ክርክር እንዳለ ስለ እናንተ የቀሎዔ ቤተ ሰዎች አስታውቀውኛልና። ይህንም እላለሁ። እያንዳንዳችሁ። እኔ የጳውሎስ ነኝ፥ እኔስ የአጵሎስ ነኝ፥ እኔ ግን የኬፋ ነኝ፥ እኔስ የክርስቶስ ነኝ ትላላችሁ። ክርስቶስ ተከፍሎአልን? ጳውሎስስ ስለ እናንተ ተሰቀለን? ወይስ በጳውሎስ ስም ተጠመቃችሁን” 1ቆሮ. 1፡10᎐13 በጣም የሚገርም ነው፡፡ የእግዚአብሔር ሕዝብ የሰዎችን ስም ጠርተው ‘እኔ የዚያ ሰው ቡደን ነኝ፣’ ‘እኔ ደግሞ የእከሌ ቡድን ነኝ፣’ ብለው ክርስቶስን እንኳ የራሳቸው ቡድን አባል ለማድረግ ጥረት ያደርጉ ነበር፡፡ እስቲ ትንሽ ቆም ብለን እናስብ፡፡ የክርስቶስ ስቃይ እኛ አንድ እንድንሆን ሆኖ ሳለ፣ የእርሱ ስቃይ ምን ያህል የኛስ ስቃይ ሆኖ ይሆን? በጣም የሚገርም ነገር አነበብኩ፡፡ ዛሬ በዓለማችን 45 ሺህ ቤተእምነቶች አሉ፡፡ የክርስቲያን ቤተ እምነቶች፡፡ ይህን ማመን ትችላላችሁ? ከጥቂቶቹ በስተቀር እምብዛም ልዩነት የላቸውም፡፡ ይህ ብቻ አይደለም፣ በአንድ ቤተ እምነት፣ በአንደ አጥቢያ ቤተክርስቲያን ውስጥ ሆነው ሰዎች በቡድን ሲዘነጣጠሉ ማየት፣ አንደኛው፣ ሌላኛውን ‘አይንህ ላፈር’ ሲለው፣ ማየት የማይገርመን ነገር ሆኖአል፡፡ እንዳውም መለያየት ልክ እንደ የጽድቅ ስራ የተቆጠረበት፣ ሰዎች የራሳችውን ሀሳብ ብቻ ካልሆነ በስተቀር ሌላውን ላለመስማት ጆሮአቸውን የደፈኑበት ዘመን ነው፡፡ በጣም የሚያስገረመው ደግሞ፣ ጠልቶ ሲያበቃ፣ ተሳድቦ ሲያበቃ፣ በመራራነት ተሞልቶ ሲያበቃ፣ ‘ለእግዚአብሔር ቀንቼ ነው’፣ መባሉ ነው፡፡ የሰማይ አምላክ እግዚአብሄሔር ማስተዋል ይስጠን፡፡ ክርስቶስ ያንዳችንም ቡድን አባል አይደለም፣ ክርስቶስ የሁሉም ነው፡፡ ስለዚህ ወንድሞቼና እህቶቼ፣ መለያየትን እንድትተዉ፣ ክርክርን እንድታቆሙ በክርስቶስ ፍቅር እለምናችኋለሁ፡፡ በእውነት የክርስቶስ ከሆናችሁ፣ የተለያየ ቡድን ልትሆኑ አትችሉም፡፡ ይልቁን፣ የክርስቶስ መሆናችሁ የሚታወቀው ለክርቶስ አሳብ አንድ ልብና አንድ መንፈስ ካላችሁ ብቻ ነው፡፡ ጠንክር ቲኒ ሰኔ 24/2016 ዓ.ም.
318
9
"➨ ንዴትህን ተቆጣጠር ! ለሰው ልጆች ከባዱ ነገር ንዴትን መቆጣጠር ነው ፤ ምክንያቱም በዚህ ወቅት አዕምሮ ከቁጥጥር ውጪ ይሆናል ፤ ምላስህን መቆጣጠር ያቅትሃል ፤ በንዴት ሰዓት ከአፍህ የሚወጣው ቃል ሰውን ሊሰብር እንዲሁም አደገኛ ቃላቶች ናቸው ፤ እንዲሁም ቶሎ የምትናደድ ከሆነ ድክመትህን ለሰዎች ታሳያለህ ፤ ድክመት ከታየ አንድ ሰው አንተን በቀላሉ ማጥቃት ይችላል ። ስለዚህ አዕምሮህን መረጋጋት አስተምረው ፤ እና ንዴትህን ለመቆጣጠር ሞክር ፤ ይህን ማድረግ የምትችል ከሆነ ትልቁን ፈተና ተወጥተሃል ማለት ነው። ➨ አስተውል ፦ ራስህን ከስሜትህ አስበልጠህን መቆጣጠር ከቻልክ አደገኛው ሰው አንተ ነህ ።"
659
10
"➨ የተለያዩ ሰዎች በህይወትህ ውስጥ ሊሄዱ እና ሊመጡ ይችላሉ ፤ እነዚህ ሰዎች በህይወት ውስጥ የተለያዩ ትምህርቶችን ይሰጡሃል ። ◉ ጥሩ ሰዎች ደስታን ያስተምሩሃል ◉ መጥፎ ሰዎች ጥንቃቄን ያስተምሩሃል ➨ ስለዚህ በህይወትህ ውስጥ የሚመጡ ሰዎችን እንደ አመጣጡ ማስተናገድ አለብህ ። ➨ አስተውል ፦ ሰዎች ከመፅሀፍ እና ከትምህር ቤት የበለጠ ስለህይወት ያስተምሩሃል ፤ ስለዚህ እንዳመጣጡ አስተናግደው።"
529
11
ሠላም የተወደዳችሁ ወገኖች የጌታ ጸጋና ሠላም ይብዛላችሁ ።የቤተ ክርስቲያናችን አባሎች እና ሥራተኞች የወ/ም ባይሳ ፣ተስፋዬ እና አብዲሳ አባታቸው አርፈው ቀብረው ስለመጡ በመድረስ ወይም የማትችሉ ስልክ በመደወል እንድታጽናኗቸው ይሁን ።ተባረኩ
541
12
የዛሬው እንግዳ መልዕክቱ የቆሙበትን ቃል፦ ዘፍጥረት 18:1-10 አብረሐም እግዚአብሔር አምላክ የሚወድለት አንድ  ከሌላው ሰው ለየት ነገር ነበረው። እንግዳ  መቀበል።  አብረሐም እርሱን ለመጠየቅ በቀጥታ  የመጡትን  ይቅርና በበራፉ የሚያልፈውን መንገደኛ ሁላ ለምኖ እየተቀበለ ያሳርፋቸው ነበር።ነብስም አይቀርለት ነበር ሲያስተናግዳቸው። ልበንፁሖች  እግዚአብሔርን ያዩታል አይደል የሚል ቃሉ? ማቲዎስ 5:8:: ይሕንን ቅንነቱን እያየ እግዚአብሔር በዚሁ ቅንነቱ በኩል ወደ አብረሐም እንግዳ መስሎ መጣ። አብረሐም መጀመርያ ያው የተለመደው አይነት እንግዳ መስሎት እንደሚከተለው ተቀበለው፦ $$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$ 1: በቀትርም ጊዜ እርሱ በድንኳኑ ደጃፍ ተቀምጦ ሳለ እግዚአብሔር በመምሬ የአድባር ዛፍ ተገለጠለት። 2: ዓይኑንም አነሣና እነሆ፥ ሦስት ሰዎች በፊቱ ቆመው አየ፤ ባያቸውም ጊዜ ሊቀበላቸው ከድንኳኑ ደጃፍ ተነሥቶ ሮጠ፥ ወደ ምድርም ሰገደ፥ 3: እንዲህም አለ፦ “አቤቱ፥ በፊትህስ ሞገስ አግኝቼ እንደ ሆነ ባሪያህን አትለፈኝ ብዬ እለምናለሁ፤ 4: ጥቂት ውኃ ይምጣላችሁ፥ እግራችሁን ታጠቡ፥ ከዚህችም ዛፍ በታች ዕረፉ፤ 5: ቍራሽ እንጀራም ላምጣላችሁ፥ ልባችሁንም ደግፋ ከዚያም በኋላ ትሄዳላችሁ፤ ስለዚህ ወደ ባሪያችሁ መጥታችኋልና።” እነርሱም፦ “እንዳልህ አድርግ፡” አሉት። 6: አብርሃምም ወደ ድንኳን ወደ ሣራ ዘንድ ፈጥኖ ገባና፦ “ሦስት መስፈሪያ የተሰለቀ ዱቄት ፈጥነሽ አዘጋጂ፥ ለውሺውም፥ እንጎቻም አድርጊ፡” አላት። 7: አብርሃምም ወደ ላሞቹ ሮጠ፥ እጅግ የሰባም ታናሽ ጥጃ ያዘና ለብላቴናው ሰጠው፥ ያዘጋጅም ዘንድ ተቻኰለ። 8: እርጎና ወተትም ያዘጋጀውንም ጥጃ አመጣ፥ በፊታቸውም አቀረበው፤ እርሱም ከዛፉ በታች በፊታቸው ቆሞ ነበር፥ እነርሱም8 በሉ።                                 ዘፍጥረት 18:1-8 $$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$ የዛሬው እንግዳ በዚሕ መልኩ በክብር በቸርነት ከተስተናገደ በኋላ   እንደሌሎቹ እንግዶች "'መጥተን አንጣቹ !' "የዓለሜ የሲሳይ ቤት ይሁን!" ብሎ መርቆ የሚሄድ አልነበረም፡፡ የዛሬው እንግዳ ግን ለየት ያለ ነው።ስለበላው ስለጠጣው ስለ አደረ አመስግኖ ብቻ  የሚወጣ አሌነበረም። የቤትን ዋና ችግር ነቅሎ ጉድለትን አሟልቶ የሚሄድ ነበር። በመሆኑም የዛሬው እንግዳ ከበላ በጠጣ ከረካ በኋላ  አብረሐምን  እንዲሕ ሲል ጠየቀው ፦ $$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$ እነርሱም፦ “ሚስትህ ሣራ ወዴት ናት?” አሉት። እርሱም፦ “በድንኳኑ ውስጥ ናት፡” አላቸው።9 እርሱም፦ “የዛሬ ዓመት እንደ ዛሬው ጊዜ ወደ አንተ በእውነት እመለሳለሁ፤ ሚስትህ ሣራም ልጅን ታገኛለች፡” አለ። ሣራም በድንኳን ደጃፍ በስተ ኋላው ሳለች ይህንን ሰማች።10                     ዘፍጥረት 18:9-10 $$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$ ሐሌሉያ !!! የዛሬው እንግዳ ለየት ያለ ነው። በልቶ ጠጥቶ መርቆ የሚወጣ ብቻ አይደለም።የዘመናት ጥያቄን የሚመልስ ነው። ሞተ አለቀለት ተብሎ የተቀበረ  የተደመደመን   የተረሳን ነገር ወዴት አለ እርሱ ብሎ ጠይቆ  ቃል አውጥቶ ሕያው የሚያደር ግ ነው። ልክ የአላዛርን ሬሳ ጌታ ኢየሱስ እንዲሕ ሲል እንደጠየቀ ማለት ነው፦ “ወዴት አኖራችሁት?” አለም። እነርሱም፦ “ጌታ ሆይ፥ መጥተህ እይ፡” አሉት።                                   ዮሐንስ ወንጌል 5:34 ክብር ለሁሉን ቻዩ ለአይሳነው ይሁን !!! ላጠቃለው፦ ወንድምዬ እሕትዬ ፦ ምን ይሆን የአንተ ሳራ?! ምን ይሆን የአንቺ ሳራ?!  ከዚሕ በፊት ቃል የወጣበት። ነገር ግን ጊዜው ከመቆየቱ የተነሳ የሞተ ያለቀለት የመሠላችሁ እና ተስፋ የቆረጣችሁበት ነገር ምን ይሆን? ሁሉን ቻይ የሆነው አይሳነው  እግዚአብሔር ወዴት ነው? ብሎ  እየጠየቃችሁ ነው። አይሞትም  ቃል ወጣ። ሕያው ይሆናል ያፈራል ። ሕዝብ ይሆናል። ክብር ለእግዚአብሔር ይሆን !!! አልሞትም ነገሬ ! አይሞትም አምላኬ የሠጠኝ ራዕይ አይሞትም አይሞትም አይሞትም !!! ቃል ወጣ ሕዝብ ሆነ !!! ሐሌሉያያያያያያያያ ! ከእኔ ከአንተ ከአንቺ  የሚጠበቅ ነገር አለ።  ምሕረቱ እና ቸርነቱ እንደተጠበቀ ሆኖ እግዚአብሔርን ወደ እኔ ወደ አንተ ወደ አንቺ   የሚያስገባ ምን ቅንነት አለን? አብረሐም እንግዳ ተቀባይ እንደ ነበረ እግዚአብሔር ለአንተ ለአንቺ የሰጠሕ ፀጋ በለው መክሊት ምንድነው? ምን እያረክበት ነው? ከረሳሐው አስታውስ። አንሳው !!! እግዚአብሔር እንዲሕ ስላደረኩኝ እንዲሕ ያደርግልኛል ሳትል በተሰጠኽ ጸጋ ዋጋ እየከፈልክም ቢሆን አገልግል ጥቀም። ከዳንክ በኋላ በምድር ላይ የምትቆይበት መሠረታዊ ዓላማ  ጋር የተያያዘ በመሆኑ ቸል አትበለው። ያው የቤትሕን  ጥያቄም ለመመለስ  እግዚአብሔር ወደ አንተ መምጫ መንገዱ ከምሕረቱ እና ቸርነቱ ቀጥሎ ቅንነትሕ መሆኑን አትርሳ። ቅኖች እግዚአብሔርን ያዩታልና። ክብር ለቃሉ ባለቤት ለመንፈስ ቅዱስ ይሁን !!! አወቀ ገብሬ 0911175603 gebreaweke2010@gmail.com
582
13
No text...
500
14
ልጆች ከማይደርሱበት ስፍራ ይቀመጥ ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። አንዳንድ መድሀኒት የያዙ ብልቃጦች ወይንም መሸፈኛዎች ላይ እንዲህ የሚል ማስጠንቀቂያ ነገር ተጽፎበት ይታያል፦ ልጆች ከማይደርሱበት ቦታ ላይ አስቀምጡት፡፡ በፈረንጆቹ አፍ እንዲህ ነው መሰለኝ  የሚለው፦  Keep out reach of Children.  ያው ዝቅ ካለ ስፍራ ከተቀመጠ  ልጆች መድሀኒቱን አላግባብ  ወስደውት በመጀመርያ ልጆቹ ቀጥሎ መድሀኒት የታዘዘለትን ሰው ስለሚጎዳ ማለት ነው፡፡ በጌታ ያገኘነው  ማንነት  ከ…ፍ  ! ራ….ቅ !   አድርገን  ካላስቀመጥነው  ማንም እየነካ ሊያጣጥልብን ይችላል፡፡ በጌታ ያገኘነው የልጅነት ስልጣን በዚህ ምድር ኑሮ መሳካት እና አለመሳካትም ጋር መገናኘት የለበትም፡፡   ከድህነታችንም  ሆነ   ከባለጸግነታችን፣ ከችግራችንም ሆነ ከተድላችን  ርቆ መቀመጥ አለበት፡፡ የአስተዋዮችን ምክር መስማት ያለብን ቢሆንም  በሰው ሙገሳ የሚወጠር በሰው ትችትም የሚኮሰምን ማንነት ሊኖረን አይገባም፡፡  የተነሳሁበት መሰረተ ሀሳብ ሰፊ ቢሆንም በሰፊ ሀሳብ ውስጥ ጭብጡን በአጭሩ ለማካፈል እሞክራለሁኝ ፡፡ ዳዊት ጎልያድን ሊገጥም በተነሳ ጊዜ ንጉስ ሳኦል እና ታላቅ ወንድሙ ዳዊትን የተናገሩትን ልብ ይሏል፡፡ ታላቅ ወንድሙ ፦ "የልብህን ክፋት አውቃለሁ እነዚያን ጥቂት በጎች ትተህ…"እያለ ቁጣውን አወረደበት (1ኛ ሳሙ.17፡28) ያዉ ለኤሊያብ ዳዊት ዝም ብሎ ጥቂት በጎች የሚጠብቅ ተራ  እረኛ ነበር ፡፡ ሳኦል ደግሞ " አንተ ገና  ብላቴና ነህ  …. እርሱ  …." (1ኛ ሣሙኤል 17፡33) እያለ የእርሱን(የዳዊትን )ትንሽነት እና የጎልያድን ትልቅነት ለዳዊት ይነግረው ጀመር  ፡፡ እንዴ !  ወድጄ ነው እንዴ እኔ የዚህን ጽሁፍ ርዕስ   ማንነታችሁን ልጆች ከማይደርሱበት ስፍራ አስቀምጡት ማለቴ?!   ታላቅ ወንድሙ ኤሊያብ እና  ንጉሱ ሳኦል ዳዊትን ሊያጣጥሉ ቢሞክሩም ዳዊት አስቀድሞ በእግዚአብሔር ላይ ያለውን ፅኑ እምነት   ልጆች ከማይደርሱበት ስፍራ ያስቀመጠ በመሆኑ  አልሰማቸውም። በመሆኑም ዳዊት ጎልያድን ገና እንዳየው -----የሕያውን አምላክ ጭፍሮች የሚገዳደር ይህ ያልተገረዘ ፍልስጥኤማዊ ማን ነው? ብሎ ተናገራቸው ፡፡ ዳዊት እግዚአብሔር አምላኩ እንደ ሆነ አብሮት እንዳለ  ጠንቅቆ የሚያውቅ በመሆኑ፦ ለጎልያድ ግዝፈት እና ፉከራ ፣  ለኤሊያብ ትችት እና ለሳኦል ተስፋ የሚያስቆርጥ ንግግር ቦታም  አልሰጠውም ነበር፡፡ እግዚአብሔር እንደሚዋጋለት  የተረዳው ዳዊት  በእግዚአብሔር ላይ ያለውን ጠንካራ እምነት ልጆች   እንዳይነኩበት  አስቀድሞ ራ…ቅ አርጎ ነበር  ያስቀመጠው።  የታመነበቱ እግዚአብሔርም  አላሳፈረውም። ጎልያድን አሳልፎ ሰጠው። ሲጠቃለል ፦ ራሳችንን  የእግዚአብሔር ቃል በሚገልፀን መልኩ እንገንዘብ። በሰው ትችት  ሊኮሰምን በሰው  ሙገሳም የሚወጠር ማንነት ሊኖረን አይገባም። እኛም ራሳችን ብንሆን በክርስቶስ ኢየሱስ አዳኝነት በማመን ከእግዚአብሔር የአገኘነውን የልጅነት ስልጣን ከዚሕች ዓለም ሞላ ጎደለ ጋር ሳናገናኘው ራ...ቅ! አርገን ልናስቀምጠው ይገባል እላለሁኝ። ምክንያቱም እኛ አገራችን በሰማይ የሆነ በዛም ርስት ያለን የእግዚአብሔር ልጆች ነን። ክብር ለመንፈስ ቅዱስ ይሁን ! ተባረኩ !!! አወቀ ገብሬ 0911175603 gebreaweke2010@gmsil.com
614
15
No text...
620
16
No text...
687
17
አሳዳጅ ወይንስ አሳርፍ? በመ ጽሀፍ ቅዱስ ውስጥም ሆነ ዛሬ በቤተክርስትያን ውስጥ ከጎናቸው ካለው  ወንድማቸው ጋር በተገናኘ መልኩ  ሁለት አይነት ሰዎችን እናያለን፡፡  አሳዳጅ ወይንም አሳርፍ ፡፡ አሳዳጆችን ተቀናቃኝም ብለን ልንወስዳቸው  እንችላለን ፡፡  የሚገርመው ደግሞ አሳዳጆች ተቅበዝባዥ አይነት ሲሆኑ ተሰዳጆች ደግሞ ለወንድማቸውም ሆነ ለሚያገለግሉት ሰው የሚያሳርፍ ማንነት አላቸው፡፡ ከልዩ ልዩ ችግር ነጻ የሚያወጣ መንፈስ አላቸው፡፡ የተወሰኑትን በአጭሩ እንመልከት ፡፡ ለዛሬ  ዮሴፍና ወንድሞቹን እንቃኝ፦ ዮሴፍ  እና ወንድሞቹ፦ ዬሴፍ ወንድሞች  ሊገድሉት አሰቡ(ዘፍጥረት 37፡18-20)፡፡ በአስተያየት ከጉድጓድ ውስጥ ተጣለ ቀጥሎ  ተሸጠ(ዘፍጥረት 37፥21-28)፡፡ ብዙ መከራ አየ፡፡ የእዚህ ሁሉ መከራ ምንጩ ከእግዚአብሔር ዘንድ  ያየው ሕልም ነበር ፡፡ ታድያ ወንድም ሕልሙ ይፈጸም ዘንድ ይታገዛል እንጂ ግድያ ይመከርበታል ይሸጣል? ወንድማችንን ገድለን ደሙን ብንሸሽግ  ጥቅማችን ምንድር ነው? አለ ይሁዳ (ዘፍጥረት 37፡26) ፡፡ ግን በአውነት ሰው ተገድሎ ጥቅም ይገኛል? ያውም በቅናት  ፡፡ ከወንድሞቹ በተቃራኒ ዮሴፍ ጋ ያለው መንፈስ ደግሞ የሚያሳርፍ ነው፡፡ዮሴፍ የመፍትሄ ሰው ነው፡፡  ዮሴፍ ባለበት ቦታ አትጨነቀም፡፡  በረከትን  የሚስብ ማንነት አለው፡፡ ሲጀመር ጲጢፋራን አሳረፈ፡፡  ዮሴፍ ቤቱ በነበረ ጊዜ ከሚበላው እንጀራ በስተቀር ጲጢፋራ ስለቤቱ የሚያውቀው ነገር አልነበረም(ዘፍጥረት 39፡1-6) ፡፡ ዮሴፍ እስር ቤትም ገብቶ የእስርቤቱን አለቃ ኣሰረፈው፡፡ ከእርሱ ቀጥሎ ሾመው የእስርቤት አለቃ አረገው( ዘፍጥረት 39፡ 20-23) ፡፡ ዮሴፍ ከእስርቤት ሲወጣ ደግሞ ቀጥሎ  ፈርኦንን አሳረፈው ዙፋኔጋ  ብቻ  አትጠጋ እንጂ ግብጽ እንደ ሆነ  ይቿትልህ ብሎ አስረከበው(ዘፍጥረት 41፡ 39-44)፡፡ ዮሴፍ በመጨረሻም ወንድሞቹን የግብጽ ሕዝብንም ሆነ የቀረውን የዓለም ሕብረተሰብ ከረሀብ  አሳረፈ፡፡ ከዚህ ከላይ አጠር አርጌ ካስቀመጥኩት ቃል ውስጥ ሁለት  መሰረታዊ ነጥቦችን  እንማራለን፡፡ አንደኛው የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበትን ሰው  የሚገባውን ስፍራ መስጠት ወይም በሚገባው ልክ መቀበል ከሰውዬው ባልተናነሰ መልኩ  ተቀባዩን  ሰው ይጠቅመዋል፡፡  አንተ ወንድምህን ስታሳርፍ  ስትቀበል  አንተም በእርሱ ውስጥ ባለው ጸጋ ታርፋለህ፡፡ ወንድምህን የምታሳድድ የምትገድል ከሆነ አሳደህ ገድለህ ለማግኘት ያሰብከውን ክብር  ጥቅም አታገኘውም፡፡ በእጅህ ቢገባ እንኳን አያሳርፍምህ፡፡ ተቅበዝባዥ ነው የምትሆነው፡፡ ሁለተኛው ወንድምሕን ልትቀበለው በሚገባ ልክ ስትቀበለው በእርሱ ውስጥ ባለው ፀጋ አንተም ታርፋለሕ። እስቲ ዮሴፍ  በውስጡ ያለውን ጸጋ  ተመልክተው የሚገባውን ስፍራ የሰጡት ሰዎች  ምን ተጎዱ? ጲጢፋራን የእስርቤት አለቃውን እና ፈርኦንን በሕሊናችሁ  ቃኟቸው፡፡ ዮሴፍ ውስጥ ባለው ጸጋ ተጠቀሙ እንጂ ምን ተጎዱ?  አሳዳጆቹ የዮሴፍ ወንድሞች ተጨንቀው ሳለ በመጨረሻም በአሳደዱት ወንድማቸው አረፉ፡፡ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበትን ሰው ማሳደድ ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ ያመዝናል፡፡ ሁላችን በክርስቶስ ባለጸጎች ነን፡፡ ባለን ጸጋ አንዳችን ለአንዳችን  እረፍት እንሁን፡፡ ወንድማችንን እንደግፈው እንምከረው እናቅናው  እንጂ  አናሳደው፡፡ በአለው ጸጋ በቅንነት እንጠቀም፡፡ ክብር ለመንፈስ ቅዱስ ይሁን ! ተባረኩ ! አወቀ ገብሬ 0911175603 gebreaweke2010@gmail.com
768
18
No text...
810
19
No text...
766
20
No text...
740