cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

The power of Holy Spirt

#ከእኔ የሰማችሁትን #አብ_የሰጠውን_የተስፋ_ቃል #ጠብቁ፤ ሐዋ 1:4 Follow us on Facebook "The power of Holy Spirt " በ ፌስቡክ ይከተሉ"The power of Holy Spirit ''

Show more
Advertising posts
246
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
+430 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ሙሴ አምላክ አልነበረም አሮንም ነብይ አልነበረም ብዙ ጊዜ የተለያዩ የእምነት ሰዎች በተለይም የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት የማይቀበሉ ሰዎች ኢየሱስ አምላክ ነው አምላክ ተብሎአል ስንላቸው እንዲህ ይሉናል፦ << አምላክ መባልማ ሙሴም አምላክ ተብሎአል >> ይሉናል የኔ መልስ አምላክ አልተባለም ነው ምክንያቱም አምላክ ለማለት የተባለ ስላልሆነ ጥቅሱን እንመልከት “እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ “ልብ በል፤ እኔ አንተን ለፈርዖን #እንደ አምላክ (ኤሎሂም) አድርጌሃለሁ፤ ወንድምህ አሮንም #ያንተ ነቢይ ይሆናል።” — ዘጸአት 7፥1 (አዲሱ መ.ት) ይሄን ጥቅስ ለመረዳት ከዚህ በፊት ያለውን ምዕራፍ ወይም ጥቅስ መመልከት ይኖርብናል። ለምን ሙሴ እንደ አምላክ ተባለ? ሙሴ በዘጸአት 4:10-16 እንዲሁም 6:10-12 ለይ ወደ ፈርኦን ስላክ ሙሴ መናገር አልችል እኔ ተነጋሪ አይደለውም ወይም አፈ ቱብ አይደለውም ብሎ ስከራከር እናያለን እግዚአብሔር እሰከሚቆጣበት ድረስ እናም እግዚአብሔር በኃላ የሙሴ ወንድም አሮን ጎበዝ ተናጋሪ ስለሆነ እግዚአብሔር ወንድምህ ስለ አንተ ወይም በአንተ ቦታ ይናገራል አለው አንተ ደግሞ በእግዚአብሔር ፈንታ ትሆናለታለህ ተባለ እንጂ ሙሴ አምላክ ነው ለማለት አይደለም። ሙሴ እንደ አምላክ የተባለበትም ምክንያት ሙሴ የተናገረውን አሮን ለፈርኦን ስለምናገር ሙሴ ለአሮን እንደ እግዚአብሔር ነው አሮን ደግሞ ከሙሴ ስለሚሰማ እንደ ነብይ ነው ። ይሄው ብቻ ነው ነገሩ ሙሴ አምላክ አልነበረም አሮንም ነብይ። ኢየሱስ ግን እንደ አብ እውነተኛ አምላክና የዘላለም ሕይወት ነው። 1ኛ ዮሐ 5:20 ወንድማችሁ ሙሉቀን
Show all...
ዘዳግም 8 (Deuteronomy) 3፤ ሰውም ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ነገር ሁሉ በሕይወት እንዲኖር እንጂ ሰው በእንጀራ ብቻ በሕይወት እንዳይኖር ያስታውቅህ ዘንድ አስጨነቀህ፥ አስራበህም፥ አንተም ያላወቅኸውን አባቶችህም ያላወቁትን መና አበላህ።
Show all...
“ሀብት ሲበዛ የሚበሉት ይበዛሉ፤ ሀብቱን በዓይኑ ብቻ ከማየት በቀር ለባለቤቱ ምን ይጠቅመዋል?” — መክብብ 5፥11
Show all...
በምዕራብ ዓለም መማሬ ሆነ መኖሬ፣ አንድ ትልቅ ነገር እንዳውቅ  ዕድል ሰጥቶኛል። ምዕራባውያን በነጻነት የመጠየቅ፣ጠንካራ ባህል አላቸው። የሰዎችን ንግግር እንዲያው በድፍን ቅል፣ ቅል ይሆናል በሚል አይተረጒሙም። የተባለውን ነገር ምን ማለት እንደሆነ ማብራሪያ ይጠይቃሉ። እኛ ኢትዮጵያውያን ግን በዚህ መጠን የመጠየቅ ባህሉ ያለን አይመስልም። እንደውም በአብዛኛው፣ለንግግሮቹ አሉታዊ ትርጓሜ በመስጠት ፣ ጉዳዩን በጥሬው (በራሳችን ግምት) የምንወስደው ይመስላል። አንድ ወዳጄ ይህ ችግር አትመረምርም፣ አትጠይቅ ከሚለው ጨቋኝ ባህላችን እንደሚነሣ ይናገራል። እንደውም አሁን የምናየው የአገሪቱ ዝርክርክ ፖለቲካ ከዚህ ፈላጭ ቆራጭ አኗኗር እንደሚመነጭ ያስረዳል።  ምዕራባውያኑ ግን ጥያቄንና ምርምርን የእውነት መንሸራሸሪያ ሠረግላ አድርገው ይጠቀሙበታል። ብንጠይቅ፣ ብንመራመር፣ ሰዎች ይቀየሙናል በሚል አምባጓሮ የሚነሣ፣ ጦር የሚሰብቅ፣ ፍልሚያ የሚገጥም ሰው ፈጽሞ አይገኝም። እኛ ግን ጥያቄ ያበዛብንን ሰው እንደ ጠረጠረን ምናልባትም ክብረ-ነክ በሆነ መንገድ እሥደ ሰደበን እናስባለን። ሥነ አመክንዮ  መጽሐፍ ከገጽ 40&41 ዶክተር ተስፋዬ ሮበሌ ✍️
Show all...
ሰለ እስልምና ምንነት የሚያውራ መጽሐፍ ነው 👇
Show all...
ዓለም ሁሉ የሆነው የተፈጠረው የገዛ ወገኖቹም ባልተቀበሉት በኢየሱስ አይደለምን ? ዮሐንስ 1 ¹⁰ በዓለም ነበረ፥ ዓለሙም በእርሱ ሆነ፥ ዓለሙም አላወቀውም። ¹¹ የእርሱ ወደ ሆነው መጣ፥ የገዛ ወገኖቹም አልተቀበሉትም።
Show all...
ሐዋ. ሥራ 26 (Acts) 17-18፤ የኃጢአትንም ስርየት በእኔም በማመን በተቀደሱት መካከል ርስትን ያገኙ ዘንድ፥ ከጨለማ ወደ ብርሃን ከሰይጣንም ሥልጣን ወደ እግዚአብሔር ዘወር እንዲሉ ዓይናቸውን ትከፍት ዘንድ፥ ከሕዝቡና ወደ እነርሱ ከምልክህ ከአሕዛብ አድንሃለሁ።
Show all...
“ስላደረግነው የጽድቅ ሥራ ሳይሆን፣ ከምሕረቱ የተነሣ አዳነን። ያዳነንም ዳግም ልደት በሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ መታደስ ነው፤”   — ቲቶ 3፥5 (አዲሱ መ.ት) እስቲ ልብ ብሎ ያነበበ ❓ @like #845e4ecb056bb5080
Show all...
“ስላደረግነው የጽድቅ ሥራ ሳይሆን፣ ከምሕረቱ የተነሣ አዳነን። ያዳነንም ዳግም ልደት በሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ መታደስ ነው፤” — ቲቶ 3፥5 (አዲሱ መ.ት)
Show all...