Don't get caught by a cheater! Telemetrio finds and tags such channels 👉 If you want to see the tag, subscribe 👈
ከፍልስፍናው ጎራ <<❓>>
<<ደስታን ምን እንደሚያካትት መፈለግህን ከቀጠልክ ፈጽሞ ደስተኛ አትሆንም..! የሕይወትን ትርጉም እየፈለግህ ከሆነ ፈጽሞ ሕይወትህን አትኖርም..! >> አልበርት ካሙ ለማስታወቂያ ሥራ➝ @Naolviva
Show more📈 Analytical overview of Telegram channel ከፍልስፍናው ጎራ <<❓>>
Channel ከፍልስፍናው ጎራ (@phylosophy_gora) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 35 833 subscribers, ranking 9 114 in the Erotic category and 979 in the Ethiopia region.
📊 Audience metrics and dynamics
Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 35 833 subscribers.
According to the latest data from 07 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -572 over the last 30 days and by -8 over the last 24 hours, overall reach remains high.
- Verification status: Not verified
- Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 2.07%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 0.55% reactions from the total number of subscribers.
- Post reach: On average, each post receives 741 views. Within the first day, a publication typically gains 198 views.
- Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 24.
📝 Description and content policy
The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“<<ደስታን ምን እንደሚያካትት መፈለግህን ከቀጠልክ ፈጽሞ ደስተኛ አትሆንም..! የሕይወትን ትርጉም እየፈለግህ ከሆነ ፈጽሞ ሕይወትህን አትኖርም..! >>
አልበርት ካሙ
ለማስታወቂያ ሥራ➝ @Naolviva”
Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 08 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Erotic category.
...."ማንኛዉም ጠንካራ ሰው የጥንካሬዉ ምንጭ ያለፈበት የመከራ መንገድ ነው። ድሎት ዱለት እንጂ ጉልበት እና ጽናትን አያጠግብም። መከራ የጠንካራ ሰው አሻራ ነው። ክርስቶስን ማንም ሰው የሚያስታዉሰዉ በመስቀሉ እንጂ አሳ አበርክቶ በመቆለሉ አይደለም። ከታምራቱ ይልቅ ስቅላቱ አይረሴ አድርጎታል።
በምድር ላይ ጥልቅ ሃሳብ ይዘው እንደበጋ መብረቅ ምድርን ያናወጡ ፈላስፋወችማ ከክርስቶስ በፊት ስንት አዝማን ቀድመው ነበሩ። እነሶቅራጥስ እነቡድሃ... ሰዉን ሰዉ የሚአደርገው ቁመናው ሳይሆን ፈተናው ነው።"
ተልሚድ ይስማዕከ ወርቁ
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
ቻናላችንን ሼር በማድረግ ይተባበሩን..!😊🔊▫️▪️▫️ ሰባተኛ ፎቅ
ሰውየው ሰባተኛ ፎቅ በረንዳ ላይ ሆኖ ንፋስ ይቀበላል። አካባቢውን እየቃኘ እያለ አንድ ሰው
ምድር ላይ ሆኖ እጁን ሲያውለበልብለት ይመለከታል።
በድምፅ መደማመጥ ስላልቻሉ ምድር ያለው ሰውዬ ሰባተኛ ፎቅ ላይ ያለውን ሰውዬ በምልክት 'ና' ይለዋል።
ሰባተኛ ፎቅ ላይ የነበረው ሰውዬ ስለሰውዬው ማንነትና ስለፈለገው ነገር እያሰበ ከፎቁ ይወርዳል። የምድሩ ሰውዬ ጋር እንደደረሰም: ፎቅ ላይ የነበረው: "አቤት ወንድሜ ምን ፈልገህ ነው?" ምድር ላይ ያለው: ፊቱን አሳዛኝ ካደረገ በኋላ "ይቅርታ ጌታዬ አለፋሁዎት አይደል? ለማኝ ነኝ። እስኪ ስለ እግዚአብሔር ብለው ያለዎትን ይመፅውቱኝ" ሲለው ሰውየው ከሰባት ፎቅ ድረስ በቁም ነገር ወርዶ በሰማው ነገር እጅግ ስለተበሳጨ
ለማኙን ካልገደልኩ ብሎ አስቸገረ።
ትርምሱ በአገላጋዮች ከረገበ በኋላ ለማኙ ላይ እየዛተ ወደነበረበት ፎቅ ይመለሳል።
እየተመለሰ እያለ ግን ለማኙ የምሩን ተቸግሮስ ቢሆን እያለ እያሰበ ነበር።
መጀመሪያ የነበረበት ሰባተኛ ፎቅ ላይ ደርሶ ወደታች ሲመለከት ለማኙ አሁንም አንጋጦ
ሲመለከተው ያያል።
ተስፋ ቆርጦ በረጅሙ ከተነፈሰ በኋላ ያፏጭና ለማኙን ይጠራዋል።
ለማኙ በደስታ እየተፍነከነከና የሰውዬውን ልብ ያራራለትን አምላክ እያመሰገነ ሰባተኛ ፎቅ ከወጣ በኋላ:
ምድር የነበረው : እየተቅለሰለሰ "አቤት የኔ ጌታ?" ቢለው
ፎቅ ላይ ያለው (ተለማኝ): "እግዚአብሔር ይስጥልኝ!!!"
🗞🗞🗞🗞
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
ቻናላችንን ሼር በማድረግ ይተባበሩን...😊"ራስህን በትክክል የምትወድ ከሆነ ሌላን የምትጎዳ አይነት ሰው አትሆንም "
/ ጉተማ ቡድሀ / ሰውን ለምን እንደሚጎዱ በሚጠየቁበት ሰአት #ሥለምወደው የሚል ምላሽ የሚሰጡ ሰዎች ስህተተኛ ብቻ ሳይሆን ሀሰተኛም ናቸው ። ሰውን ለመጉዳት የምንነሳው ስለምንወደው ሳይሆን የወደድነውን የራሳችን ብቻ ለማድረግ የሚገፋን ራስወዳድነት ሥለሚጫወትብን ነው።
፧
የወደድከው ነገር ሁሉ ያንተ ካልሆነ አጥፋው የሚል ስሜት ውስጥህ ካለ...ስሜትህ ውሸት ነበር ማለት ነው። ፍሬ ከናፍር እወደዋለሁ ያልከው ነገር ያንተነቱን እንጂ እሱነቱን አልወደድከውም ማለት ነው...። አንድን ነገር ስትወደው ተፈጥሮውን አድንቅለት...ነፃ አድርገው በቃ! ያንተ መሆን ያለመሆንን ምርጫ ለሱ ብቻ ተውለት...አንተ የመኖር መብት እንዳለህ ሁሉ የምትወደው ነገርም የመኖር መብት አለው...አንተ የመምረጥ መብት እንዳለህ ሁሉ የወደድከውም የመምረጥ መብት አለው...እዚህ መሀል ማስገደድ ካለ መውደድ የለም...!!
፧
የራስህን አስተሳሰብ ስርአት ባላስያዝክበት ሁኔታ ሌላ ላይ ጣትህን ለመጠቆም እንደማትበቃው ሁሉ ራስህን መውደድህን በትክክል ባላረጋገጥክበት ሁኔታም ሌላን ልትወድ አትችልም ። የፍቅርን ትርጉም የማያውቅ እና ራሱን አፍቅሮ የማያቅ ሰው...ሥላፈቀርኳት የሌላ ሆና ማየት ሥለማልሻ አጠፋኋት ሲል ባደባባይ ይዋሻል...ራስህን አትዋሽ...!!
በትክክል ራሱን የሚወድ ሌላን የሚጎዳ ስብዕና የለውም...!!
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
ቻናላችንን ሼር በማድረግ ይተባበሩን..!😊- አንተ ሰው ከየት መጣህ?
- ከግብጥ
- ምን ይዘህ?
- ጭብጥ ጥጥ
- በምን አስረህ?
- በድጋይ ልጥ
- ይህስ ሰው ዋዘኛ ነው!
- ዋዘኛስ ክራር ነው
- ክራርስ ጥዝ ጥዝ ባይ ነው
- ጥዝ ጥዝ ባይስ ንብ ነው
- ንብስ ነዳፊ ነው
- ነዳፊስ ደጋን ነው
- ደጋንስ ጠማማ ነው
- ጠማማስ መንገድ ነው
- መንገድስ ወሳጅ ነው
- ወሳጅስ ውሃ ነው
- ውሃስ ብም ብም ባይ ነው
- ብም ብም ባይስ ጎሽ ነው
- ጎሽስ ዘላይ ነው
- ዘላይስ ፌቆ ናት
- ፌቆ ስትዘል አግኝቼ በልቼ መጣሁ
- ሰባች ጎፈየች?
- ሳትታረድ መጣሁ
- የሆነስ ሆነና ስምህ ማን ነው?
- ላገር አይመች
- ማን አወጣልህ?
- ጎረቤቶች
- የናትህ ስሟ ማን ነው?
- ሳልወለድ ሞተች
- የሆነስ ሆነና እግዚሀርን አይተኸዋል አላየኸውም?
- አዎን አይቸዋለሁ
- ቀይ ነው ጥቁር?
- ተከናንቦ ነበር
- ረጅም ነው አጭር?
- ቁጭ ብሎ ነበር
ስብሀት
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
ቻናላችንን ሼር በማድረግ ይተባበሩን...😊አስቄአቸው የማላውቅ እኔ ነኝ። ሲያወሩልኝ መስማት ብቻ። የሚወዱኝም በዚህ ነው። "እሱ ሰው ሲናገር ማቋረጥ አይወድም" እባልና። እኔ ግን ማውራት ስለሚደክመኝ ነው አፍ ፣ጥርስ፣ምላስ፣አገጭ፣ ጠቅላላ የፊት ጡንቻ፣ዐይኖች፣ግንባር፣እጅ ወዘተ....እነኝህን ሁሉ በአንድ ጊዜ አነቃንቄ ከእኔ ወደ ሌላ ሰው መረጃ ማስተላለፍ አድካሚ ነገር ይሆንብኛል። ያለማውራቴ ምክንያት ግን በተለያዩ ሰወች የተለያየ ትርጉም ይሰጠዋል:-
አክስቴ: "መልኬ በቃኝ ብሎ ነው"እያለች ታሽሟጥጠኛለች። የወጣልኝ አጎዶ።
አባባ: "ጨዋ ጨዋነት ነው" ይላሉ
ጋሸ: "ትዕቢት ፤ ትዕቢት ነው" ይላል
ጓደኛዬ: "መደበር ይወዳል ፣ ደባሪ ነው"ይላል
የጓደኛዬ ሴት ጓደኛ : ኩራት። ኩራት ነው። ሲበጣጠስ" ትላለች
የጋሸ ሚስት: ፍርሐት ፣ ፍርሐቱ ነው" ትላለች
ብቻ ሺህ ትርጉም ይሰጠዋል።
(ህማማትና በገና)
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
ቻናላችንን ሼር በማድረግ ይተባበሩን...😊"በድሮ ጊዜ ቀስት ሲሰራ ቂጡ ላይ ለሚዛን ላባ ይገባለታል፡፡ እና አንድ ጭልፊት ጎኑን በቀስት ተመቶ ከሰማይ ላይ እየወደቀ እያለ ዞር ብሎ የተወጋበትን ቀስት ሲያይ፤ የራሱን ዐይነት ላባ ተሰክቶበት አየ፡፡ ገባህ? በወገንህ እጅ እንደ መጥፋት ቀላልና ከባድ ነገር የለም ማለት ነው፡፡"
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
ቻናላችንን ሼር በማድረግ ይተባበሩን...😊ተስፋ
ተስፋ የመኖር ምክንያት ነው።ሰውን እንዲኖር የሚያደርገው ወይም የሚገፋው መለወጥ አለመለወጡ ሳይሆን የመለወጥ ተስፋው ነው።ቢሆንም ግን ህይወት ተከታታይ መሆኗን መገንዘብ ይጠቅማል።ዛሬ የምኖረው በትናንት ምክንያት ነው።
📓አለመኖር
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
ቻናላችንን ሼር በማድረግ ይተባበሩን..!😊ጦርነት እየተካሄደ የሚያርስ ገበሬ "ለማን ነዉ?" ሲሉት "አላህ ለሰጠዉ ይሰጣል እኔ ከደረስኩበት እበላለሁ ካልሆነ ደሞ የሚመጡት ይበሉታል" አለ አርሶ ባዶ መሬት ከመተዉ ከዚህ በላይ ምን አሪፍ ሰዉ አለ
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
ቻናላችንን ሼር በማድረግ ይተባበሩን...😊ሦስቱ ሴቶች የዘላለም መቆያቸው ሲኦል ይሁን መንግስተ ሰማይ ለማወቅ የተረኛ መላዕኩን ምዘና እየጠበቁ ነው።
የመጀመሪያዋ እንስት ቀረበች። በምድር ህይወቷ መነኩሲት ነበረች።
ተረኛው መላዕክ " በምድር ሳለሽ ምን ያህል ግዜ ዘሙተሻል ?" ይላታል።
"አንዲትም ግዜ አልዘሞትኩም። ገዳም የገባሁትም እንዲሁ እንደተፈጠርኩ አንዳች ነገር ሳላጎድል ነው። እዛም የሚፈታተነኝ ቢበዛም ግን ተወጥቼዋለሁ።"
መላዕኩም " ማነህ የ መንግስተ ሰማያትን ቁልፍ ስጣት።" በማለት ትዕዛዝ አስተላለፈ።
ሁለተኛዋ ቀረበች
"በምድር ህይወትሽ ምን ያህል ግዜ ዘሙተሻል?"
"አንዳችም አልዘሞትኩም። ለአቅመ ሄዋን ስደርስም በወግ ማዕረግ ተዳርኩ። ከባሌ ጋር አራት ልጆች ወልደናል። ከአራት ግዜ ውጪ ከባሌም ከማንም ተነካክቼ አላውቅም።"
" የመንግስተ ሰማያትን ቁልፍ ስጣት" አለ መላዕኩም
ሦስተኛዋ ቀረበች ። እጅግ የሚያምር አቋምና መልክ አላት። ንቃትና በራስ መተማመኗም የላቀ ነው። ጡቷን በከፊል የሚያሳይ የሙት ልብስና የዳሌዋንም አስደንጋጭ ውበት የሚያጎላ ፒንክ ታይት ለብሳ ነበር።
ተመሳሳይ ጥያቄ አቀረበላት
"በጣም በልጅነቴ ስለጀመርኩ ልከኛ ቁጥራቸውን በግልፅ አላውቀውም። ግን በምድር ህይወቴ ሳለው የወሲብ ቪዲዮ እሰራ ስለነበር ቢያንስ በሁለት ቀን አንዴ የግድ እዘሙታለሁ።"
መላዕኩ እያያት ምራቁን ሲውጥ የምራቁ ጉምጉምታ ሰማየ ሰማያት ተሰማ።
ከምራቁ እየታገለም እንዲህ አለ።
"ማነህ የክፍሌን ቁልፍ ስጣት!!"
ማስታወሻ: ለአሁናዊ የግል ህይወቱ ደህንነት ሲባል የመላዕኩ ስም አልተጠቀሰም።
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
ቻናላችንን ሼር በማድረግ ይተባበሩን...😊ሕይወት ዘላለማዊ ናት፣ አለመኖርን እንድንኖር ምርጫ እንኳን አልተሰጠንም አብዛኛው ሰው ሞት አለመኖር ይመስለዋል በተቃራኒው ግን ሞት ማለት መለየት ብቻ ነው ደግሞም ድልድይ ነው ወደ ትክክለኛ ሕይወት፤ሩሲያ ውስጥ የሚማር የሌላ ሃገር ዜጋ አንድ ተማሪ እንዲህ ይላል፦
"በሩሲያ ውስጥ ለአብዛኞቹ ፈተናዎች ከፍተኛው ውጤት 5 ነው ፡፡ አንድ ተማሪ ማንኛውንም ጥያቄ ካልመለሰ እና የፈተና ወረቀቱን ባዶውን ከመለሰ፣ ከ5 ውስጥ 2 ያገኛል። በሞስኮ ዩኒቨርስቲ የመጀመሪያ ቀናት ውስጥ ስለዚህ ስርዓት አላውቅም ነበርና በመገረም ዶ / ር ቴዎዶር ሜድራቭን ጠየቅኩ፦
“አንድ ተማሪ ማንኛውንም ጥያቄ ሳይመልስ እርስዎ ከ5 ውስጥ 2 ሲሰጡት ይህ ፍትሃዊ ነው? ለምን ዜሮ አይሰጡትም? ትክክለኛው መንገድ እንደዚያ አይደለምን?"
መምህሩ ሲመልሱ፦
"ለሰው ልጅ ዜሮን እንዴት መስጠት እንችላለን? ሁሉንም ትምህርቶች ለመከታተል ከጠዋቱ 1 ሰዓት ለሚነሳ ሰው ዜሮ እንዴት ልንሰጠው እንችላለን? በዚህ በቀዝቃዛ አየር ከእንቅልፉ ተነስቶ፣ የህዝብ ማመላለሻን ተጠቅሞ፣ ፈተናውን በወቅቱ ለማከናወን በመድረሱ እና ጥያቄዎቹን ለመፍታት ሞክሮ እንዴት ዜሮ እንስጠው? ብዕር፣ የማስታወሻ ደብተር፣ የጥናት ኮምፒተር ገዝቶ ለብዙ ሌሊቶች ላጠና ሰው እንዴት ዜሮ እንሰጠው ?? ሌሎች የሕይወት ዘይቤዎችን ሁሉ ትቶ ትምህርቱን ሲከታተል ለከረመ ተማሪ እንዴት ዜሮ ልንሰጠው እንችላለን? ልጄ! እዚህ አንድን ተማሪ መልሱን ባለማወቁ ብቻ ዜሮ አንሰጠውም፡፡ እኛ ቢያንስ ይህ ሰው ነው ፣ እናም አንጎል አለው የሚችለውን ሞክሯል የሚለውን እውነታ ለማክበር እንሞክራለን፡፡ ምክንያቱም እኛ የምንሰጠው ውጤት በፈተና ወረቀቱ ውስጥ ላሉት ጥያቄዎች ብቻ አይደለም ፣ ይህ የሰው ልጅ ስለሆነ እና ነጥብ ማግኘት ለሚገባው ተማሪ እውነታ አድናቆት እና አክብሮት ማሳየትም ጭምር ነው።"
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
ቻናላችንን ሼር በማድረግ ይተባበሩን...😊እግርህ ስር የሚያደናቅፍህ ድንጋይ ተቀምጦ ዓይንህን ከድንጋዩ ለማሸሽ ብትሞክር ራስህን ማታለልህ በቅፅበት ይገለጥልሀል። ድንጋዩ የሚመታው ዓይንህን ሳይሆን እግርህን ነዋ! ብዙዎች ራሳቸውን በማታለልና በመሸንገል መንገድ ሲሄዱ እውነት እያሰናከለች ስትጥላቸው የምንመለከተውም ለዚህ ነው!
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
@phylosophy_gora🇪🇹
ቻናላችንን ሼር በማድረግ ይተባበሩን...😊Content available for users 18+
By signing in to the service, you confirm that you are 18 years of age or older.
