ማር ይስሐቅ
" መንፈስ ግን በግልጥ.....አንዳንዶች የሚያስቱ መናፍስትንና በውሸተኞች ግብዝነት የተሰጠውን የአጋንንትን ትምህርት እያደመጡ ሃይማኖትን ይክዳሉ ይላል'' 1ኛ ጢሞ 4÷1 ስለዚህ እንንቃ!!!
Show more2 670
Subscribers
No data24 hours
-67 days
-2230 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
እውነት አሁን ደብረሊባኖስ ገዳም ሊፈታ ነው /ችግር ላይ ነው/ ቢባል ማን ያምናል? ያ ሊጥ ተቦክቶ ተቦክቶ በስንት በርሜል የማይከደንበት፣ ያ ዳቤ ሲጋገር ርጥብ ወይራ እንደጧፍ የሚነድበት፣ ስንት ሺህ መናንያንን፣ ሊቃውንትን፣ ደቀመዛሙርትን ድርጎ ሰጥቶ የሚያኖር ግብር ቤት ወና ሆነ ቢባል ማን ያምናል?
ያ በመጻሕፍት ትርጓሜ፣ በዜማው፣ በቅኔው… ዛሬ ድረስ እንደ እሸት የተፈለፈሉ፣ እንደ እንጨት የተመለመሉ ቀን ከሌት ለስብሐተ እግዚአብሔር የማይደክሙ ሊቃውንት፣ መምህራን የሚያፈራ ገዳም ተቸገረ ቢባል ማን ያምናል?
በአካባቢው አይደለም ከአካባቢው በርቀት ላሉት ገዳማት እና አድባራት አገልጋይ መድቦ የሚያስገለግል የተክልዬ ገዳም ተፈተነ ቢባል ማን ያምናል?
ያ ለሀገር የሚተርፉ፣ በፋሺስት ዘመን በዱር በገደል የወደቁ ስንት ኢትዮጵያውያንን ያፈራ ገዳም ተፈተነ ቢባል ማን እውነት ነው ይላል?
ግን ተፈተነ። የማያልፍ ቀን የለም ግን ለሚያልፍ ቀን ተቸገረ። ችግሩም ብሶ ብሶ ይኸው እዚህ ደረሰ። እናም ካለንበት ሆነን ጥቂት ጥቂት ብንዘረጋ በረከትን እናፍሳለን።
--
የባንክ አካውንት
ደብረ ሊባኖስ የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም
CBE 1000280193667
D/L/AUNE T/HAYMANOT ANDNET GEDAM