cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Natinael Mekonnen

ይህ ቻናል ቴሌግራሜ hacked በተደረገበት ሳት ለግዝያዊነት የከፈትኩት ቻናል ነው ለችግር ጊዜ ይጠቅማል ተቀላቀሉ በቀጥታ መረጃዎችን ለመስጠት ከፈለጉ @NatnaelMekonnen7 በማለት መረጃዎችን ይላኩልን Facebook.com/natnaelmekonnen.et Instagram.com/natnaelmekonnen21 Telegram https://t.me/NatinaelMekonnen21

Show more
Advertising posts
7 891
Subscribers
+424 hours
+17 days
+2030 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ዩቲዩበሮቹ በቁጥጥር ስር ዋሉ...🇪🇹👌 ለማህበረሰቡ ወግና ባህል ፍፁም ተቃራኒ የሆነ ሐሰተኛ እና አፀያፊ የፈጠራ ታሪክ እያሰራጩ ህዝብን የሚያደናግሩ ዩቲዩበሮችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡ ሃሰተኛ መረጃ እና ከማህበረሰቡ መልካም ባህልና ወግ የተቃረኑ አፀያፊ የፈጠራ ታሪኮችን በማህበራዊ ሚዲያ እያሰራጩ በህዝብ ላይ ውዥንብር እና መደናገርን የሚፈጥሩ ግለሰቦች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል፡፡ ማህበራዊ ሚዲያን ለበጎ አላማ ከመጠቀም ይልቅ ገንዘብ ለማግኘት ሲሉ ብቻ ከእውነት የራቁ መሰረተ ቢስ የፈጠራ አፀያፊ ወሬዎችን እየፈበረኩ በማሰራጨት የህዝብን ደህንነት ስጋት ላይ የሚጥሉ ዩቲዩበሮችን በቁጥጥር ስር ማዋል መጀመሩን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡ በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 አማረ እና ቤተሰቦቹ በተባለ ህንፃ ላይ ቢሮ ተከራይተው የተለያዩ የዩቲዩብ ገፆችን በመክፈት የማህበረሰቡን ሥነ ልቦና የሚጎዱ የፈጠራ ታሪክ በማሰራጨት የተጠረጠሩ ስድስት ግለሰቦች በህዝብ ጥቆማ እና ፖሊስ ባደረገው ክትትል ተይዘው በየካ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ምርመራ እየተጣራ ይገኛል፡፡ በቁጥጥር ስር ከዋሉት መካከል መቅደስ መብራት መኮንን የተባለችው ግለሰብ ሮሄ፣ ልዩነት፣ ጣዕም፣ አዲስ አለም፣ ዘይቤ፣ ህይወት፣ እይታ፣ እና ዩኒት ህይወት የተባሉ የዩቲዩብ ገፆችን በመክፈት በስራ አስኪያጅነት ስትመራ የነበረች ናት ተብሏል፡፡ ብሩክ ወርቅነህ ጌታሰው የተባለ ግለሰብ ደግሞ ገፆቹን በምክትል ስራ አስኪያጅነት እና በአስተባባሪነት ሲመራ የነበረ ሲሆን ናትናኤል አበራ በቀለ፣ እየሩሳሌም አስማረ ምህረት እና ምህረት ያሲን ቲጋ የተባሉት ግለሰቦች ደግሞ በፕሮግራም አቅራቢነት እንዲሁም ናትናኤል ዮሃንስ አሸነፍ በካሜራ ባለሙያነት ሲሰሩ የነበሩ መሆናቸው ተገልጿል፡፡
Show all...
👍 5 2
„በኢትዮጵያ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለማስቀረት እንደ ሰጎን አንገትን በአሸዋ ስውጥ መደበቅ ሳይሆን፤ የችግሩን መንስኤ መጋፈጥና በሰከነ መንገድ መፍታት ይገባል“ አረጋዊ በርሔ (ዶ/ር) በታሪካዊው ራስ መኮንን አዳራሽ በተካሄደው 4ኛው ልዩ ሴሚናር ላይ ከተናገሩት የተወሰደ፡፡
Show all...
በሆሮ ጉድሩ ወለጋ ዞን በሀሞሮ ወረዳ ላይ ለበርካታ ዓመታት የህዝብን ሰላም ሲያውኩ የነበሩ የሽኔ አባላት ለምዕራብ ዕዝ ክፍለጦር እጅ መስጠታቸው ተገለፀ። በጃን ኢፓ ሲመራ የነበረውና ሰላሳ አምስት የሰው ሀይል ያለው ቡድን ሙሉ ለሙሉ ከሰላሳ አራት የነፍስ ወከፍ መሳሪያ ጋር እራሱ አመራሩን ጃን ኢፓን ጨምሮ በቀጠናው ለሚገኘው መከላከያ ሰራዊት እጅ ሠጥተዋል። የክፍለጦሩ ምክትል አዛዥ ሻለቃ ወልዳይ አስፋው በአካባቢው ለብዙ ዓመታት ከህዝቡ ጋርና ከሽብር ቡድኑ ጋር ባደረግነው ውይይት ከጦርነት ይልቅ ሰላምን አማራጭ አድርገው በፈቃደኝነት ከፍተኛ አመራሩን ጃል ኢፓን ጨምሮ ሰላሳ አምስት ታጣቂዎች ከነ ሙሉ ትጥቃቸው እጅ እንዲሠጡ አድርገናል ብለዋል። በጦርነት የሚገኝ ትርፍ የለም ያሉት ሻለቃ ወልዳይ አስፋው ቀጣይም በድርድርና በሰላማዊ ውይይት የሚያምኑትን ታጣቂዎች እየመከርን ወደ ሰላም እንዲመጡ የማድረግ ስራዎችን ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር በመሆን አጠናክረን እንቀጥልበታለን ብለዋል። የሀሞሮ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ቀጤሳ ሽፈራው መከላከያ ሰራዊቱ በየጊዜው በሽብር ቡድኑ ላይ በሚወስደው እርምጃ ከፍተኛ ድል እያስመዘገበ መሆኑን ተናግረው ዛሬም አብዛኛው የሽብር ቡድኑ የሰላምን አማራጭ እንዲጠቀም ያደረገው ሠራዊቱ በመሆኑ ትልቅ ክብር ይገበዋል ሲሉ ተናግረዋል። የሽብር ቡድኑ ከፍተኛ አመራር ጃን ኢፖ አሁን እያደረግን ባለው የትግል አቅጣጫ ለኦሮሞ ህዝብም ሆነ ለኢትዮጵያ የማይጠቅምና እርስ በእርስ ደም የሚያፋስስ በመሆኑ የእስካሁኑ ይበቃል በማለትና በተሰጠን የሰላም አማራጭ መጠቀምን በመምረጥ በእኔ የሚመራውን ሙሉ ቡድን ይዤ ለመከላከያ ሰራዊቱ እጅ ሰጥቻለው ሲል አስረድቷል።
Show all...
👍 2
የቱሪዝም ሚንስትር አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ ለህዝብ ተወካዮች ምክርቤት የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረቡት የ9ወራት አፈፃፀም ሪፓርት ላይ ያነሷቸው ነጥቦች •የቱሪዝም መረጃ አያያዝን ለማዘመን የሚያስችል tourism satellite account(TSA) ስርአትን ወደ ስራ ለማስገባት ዝግጅት እየተደረገ ነው:: •የኮንሶ አለም አቀፍ ቅርስን ጨምሮ የ8 ቅርሶች ጥገና ስራ እየተከናወነ ነው:: •ኢትዮጵያ በዩኔስኮ የጌዲኦ መልካምድር እና የባሌ ተራሮችን በሚዳሰስ ቅርስነት በሀረሪ ክልል የሚከበረውን ሸዋል ኢድ ደግሞ በማይዳሰስ ወካይ ቅርስነት ከ 40 አመት በህላ ለመጀመሪያ ጊዜ በአንድ አመት ውስጥ ብቻ ሶስት ቅርሶቿን ማስመዝገብ የቻለችበት አመት መሆኑን:: •የሚንስቴር መስሪያ ቤቱን የስራ አካባቢ ምቹ በማድረግ እና የሰው ሀብት ልማት ላይ ውጤታማ ስራዎች ተከናውነዋል:: •የድሬ ሼክ ሁሴን መካነ ቅርስ ዙሪያ የሚስተዋሉ መሰረታዊ የቱሪስት አገልግሎቶች ጉድለቶችን ለመሙላት ፕሮጀክት ተቀርፆ ለትግበራ ዝግጁ ተደርጓል። •በነጭ ሳር ብሄራዊ ፓርክ የኬብል ካር እና ቱሪስት አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ፕሮጀክት ጥናት፣ የዲዛይን ስራ ማጠናቀቅ ተችላል፡፡ •የጂማ አባጂፋር ቤተመንግስት እድሳት ተጠናቆ በሚቀጥለው አመት መጀመሪያ ለአገልግሎት ክፍት ይደረጋል:: •ከፈረንሳይ መንግስት ጋር በመተባበር በላሊበላ ከተማ በዋናነት ቱሪስቶች በከተማዉና አካባቢዉ የሚገኙ ቅርሶችን ከመጎብኘት ባሻገር ያለዉን ዕምቅ የባህል ሀብት በአንድ ስፍራ መጎብኘት የሚችሉበት ደረጃዉን የጠበቀ የባህል/ቱሪዝም ማዕከል ግንባታ በመጠናቀቅ ላይ ነዉ፡፡ •በአፋር ክልል በኤርታኢሌ የእሳተ ጎመራ ድንቅ የተፈጥሮ ትዕይንት መመልከቻ ቦታ ላይ ለጎብኝዎች መወጣጫ የሚሆን ደረጃዎች ግንባታ ለማስጀመር የቅድመ ዝግጅት ስራዎች በመከናዎን ላይ ናቸዉ፡፡ •በተለያዩ የቱሪዝም ኢንቨስትመንት ዘርፎች 75 የሀገር ውስጥ እና 16 የውጭ ባለሃብቶች ሴክተሩን ተቀላቅለዋል፡፡ •ከዘርፉ በ9ወራት የሚገኘውን የውጪ ምንዛሪ ገቢ3.5 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቅዶ 3.2 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ማግኘት ተችሏል፡፡ •በዘርፉ ባለፉት 9ወራት 81,673 የስራ እድሎች ተፈጥረዋል፡፡ ከዚህ መካከል 30,968 ቋሚ የስራ እድሎች ሲሆኑ 50,705 ደግሞ ግዚያዊ ናቸው::
Show all...
👍 7
የሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የ2016 ዓ.ም አጠቃላይ ክልላዊ የፖሊስ አመራርና አባላት የፍትህ ማሻሻያ (ትራንስፎርሜሽን) ግምገማ ተካሄደ። በአጠቃላይ የግምገማው አፈፃፀም በተቀመጠለት የጊዜ ሰሌዳ የተከናወነ ሲሆን 12700 የሚሆን አመራር እና አባላት በግምገማው ሂደት አልፈዋል። በዚህም በግምገማው 291 የሚሆኑ አመራሮች በከባድ ማስጠንቀቂያ ያለፉ ሲሆን 41 አመራር እና አባላት ላይ በብልሹ አሰራር በተጨማሪም ህዝብን የሚያማርር ተግባር በመፈፀማቸው በህግ እንዲጠየቁ እና ከስራ በማገድ እርምጃ ተወስዶባቸዋል። የክልሉ ሰላምና  ፀጥታ ቢሮ ሀላፊ  አቶ አለማየሁ ጢሞቲዎስ  እንደገለፁት የፖሊስን ተቋም ለማዘመን በሚደረገው ርብርብ አባሉ በተሰማራበት የስራ ዘርፍ ቁርጠኛ ሆኖ ለማሳካት ርብርብ ሲያደርግ ጥቂት አመራርና አባላት እየተከናወነ ያለውን ስራ የሚያደናቅፉ የስነ-ምግባር ችግር የሚስተዋልባቸው  በመኖራቸው በየጊዜው በመከታተል  የእርምት እርምጃ በመውሰድ ማስተካከሉ ለተቋማዊ ለውጡ ወሳኝ ነው ብለዋል። ሀላፊው አክለውም ፖሊስ ውድ የሆነውን ህይወቱን ሳይሳሳ ለሀገርና ህዝብ የሚሰጥ ይህ ሀይል በጥቂት አባላትና አመራር የሙያ ስነ-ምግባር ችግር ሊወቀስ ስለማይገባ በየጊዜው አባላቱ ያለበትን ቁመና በመገምገምና በመከታተል የዘመነና ብቃት ያለው አባልን ለመፍጠር በትኩረት ይሰራል ብለዋል። የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሽመልስ ቶማስ በበኩላቸው የቱሪስት መስህብ የሆነው ክልሉ ላስመዘገበው አስተማማኝ ሰላም ህብረተሰቡና የፀጥታ ተቋሙ እያከናወነ ያለው ቅንጅታዊ ስራ ነው ያሉት ኮሚሽነሩ ይህንን አጠናክሮ ለማስቀጠል አመራርና አባላቱ የተሰጣቸውን ሀላፊነት በብቃት መወጣት ይኖርባቸዋል ብለዋል። ከምን ግዜውም በተሻለ ህብረተሰቡ ለፖሊስ አለኝታነቱን በተግባር እያሳየ ባለበት በዚህ ጊዜ አንዳንድ አመራርና አባላት ከሙያዊ ስነ-ምግባር ባፈነገጠ የተቋሙን ስም የሚያጠለሹ መኖራቸው በግምገማው የተለየ በመሆኑ እነዚህን አመራርና አባላት አስተማሪ እርምጃ በመውሰድ ለተቋማዊ  ስኬት ይሰራል ብለዋል።
Show all...
👍 3
የፌዴራል ቤቶች ኮፖሬሽን የጽዱ ኢትዮጵያን ንቅናቄን በመቀላቀል የ 5 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገ ኮርፖሬሽኑ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋ ለሆነው የ“ጽዱ ጎዳና - ኑሮ በጤና” ንቅናቄ የ5 ሚሊየን ብር የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል፡፡ የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ውብና ዘመናዊ ከተማ ለመፍጠር የሚደረገውን አገራዊ ጥረት የሚያግዙ በርካታ ሥራዎችን እያከናወነም ነው ፡፡ በሚገነባቸው ዘመናዊ ሕንጻዎችና የመኖሪያ መንደሮች ውበትን ፣ጥራትንና እና ዘመናዊነት ታሳቢ ያደረጉ ግንባታዎች እንዲሆኑ በማድረግ ላይ የሚገኝ ሲሆን በቀጣይ ለጽዱ ኢትዮጵያ ንቅንናቄ መሰል ድጋፎቹን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ኮርፖሬሽኑ አስታውቋል፡፡ የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በአምስት ዓመታት ውስጥ ብቻ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ታሳቢ በማድረግ ከግማሽ ቢሊየን ብር በላይ ድጋፍ አድጓል፡፡
Show all...
👍 5
ጠሚ አቢይ አህመድ ዛሬ ወለጋ ነቀምት ሲደርሱ የተደረገላቸው አቀባበል
Show all...
" ከቅርብ ጊዜ ወዲህ #ጅቦቹ ሰው መተናኮስ ፤ በቀን መታየትና #ሰብሰብ ብሎ መሄድ ጀምረዋል " - ነዋሪዎች " በኛ ቀበሌ ብቻ 3 ህጸናት በጅቦች ተበልተዋል። 2ቱ ሲሞቱ አንዷ ተርፋለች " - አቶ ማርቆስ ቡታ ከሰሞኑን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ውስጥ የተራቡ ጅቦች እያደረሱ ስላለው ጥቃት የሚመለከቱ መረጃዎችን ማጋራታችን ይታወሳል። በተለይ በስልጤ ዞን እና በሀላባ ዙሪያ በተፈጸሙ የጅብ ጥቃቶች ምክኒያት የሰው ህይወት መጥፋትና የአካል ጉዳት መድረሱን መግለጻችን አይዘነጋም። በወቅቱ " የጅብ መንጋ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ  ተከስቷል " የሚለውን ዜና የሰሙ የሲዳማ ክልል፣ የሀዋሳ ከተማ ዙሪያ ነዋሪዎች " ችግሩ እኛም ጋር አለ እንዲያዉም ከህጻናት ባለፈ አዋቂዎችንም አሳስቦናል " በማለት መልዕክቶቻቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አድረሰዋል። ጉዳዩን በተመለከተ የቲክቫህ ኢትዮጵያ የሀዋሳ አባል በሀዋሳ ዙሪያ ቡሽሎ ፣ ፊንጭ ውሀና ገመጦ... ወዘተ ቀበሌዎች ያሉ ማህበረሰቦችና የጸጥታ አካላትን አነጋግሯል። የአካባቢው ነዋሪዎች በጊዜ ወደ ቤታቸው መግባት መጀመራቸውን በመጥቀስ ህጻናት ልጆቸውም ፍርሀት እንዳደረባቸዉ ገልጸዋል። በተለያየ ጊዜ በ5 ሰዎች ላይ የጅብ ጥቃት ደርሶ እንደነበር እና 2 ህጻናት እንደሞቱ 1 ህጻን እንዲሁም 4 አዋቂዎች ደግሞ እንደተጎዱ አስረድተዋል። የሚመለከተው አካል አንዳች መፍትሄ እንዲሰጣቸውም ጠይቀዋል። በአካባቢው ለረዥም ጊዜያት ጅቦች እንደነበሩ የሚገልጹት ነዋሪዎቹ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ሰው መተናኮስ ፤ በቀን መታየትና #ሰብሰብ ብሎ መሄድ መጀመራቸው እንዳስገረማቸው ገልጸዋል። ጉዳዩን በተመለከተ ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡት የቡሽሎ ቀበሌ ሰላምና ጸጥታ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ማርቆስ ቡታ ፤ " በእኛ ቀበሌ ብቻ 3 ህጻናት በጅቦች ተበልተዋል " ሲሉ ተናግረዋል። 2ቱ መሞታቸውን ፤ አንዷ ህጻን በወቅቱ በተደረገ ርብርብ ተርፋ በተደረገላት ህክምና መዳኗን ገልጸዋል። በአጎራባች ቀበሌያት ውስጥ በ2 አዋቂ ሰዎች ላይ አሰቃቂ አደጋ ቢደርስም ለመትረፍ እንደቻሉ የጠቀሱት አቶ ማርቆስ ችግሩ አሳሳቢ በመሆን የጸጥታ አካላት እየተነጋገረበት ነው ብለዋል። ማህበረሰቡ በጊዜ በመግባት የሚሰጠዉን የጥንቃቄ መልእክት በአግባቡ እንዲተገብርም ጠይቀዋል።
Show all...
👍 5 2
በስልጤ ዞን ኬራቴ ከተማ ለመዋኘት ወደ ወንዝ የወረደች የ8 አመት ታዳጊ ሰጥማ ህይወቷ ማለፉ ተነገረ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስልጤ ዞን ሁልበረግ ወረዳ ለመዋኘት ወደ ወንዝ የወረደች የ8 ዓመት ታዳጊ በዉሃ ሰጥማ ህይወቷ ማለፉ የወረዳዉ ፖሊስ ገልጿል። የ8 ዓመቷ ታዳጊ ሚያዝያ 29 ቀን 2016 ዓ.ም 6:00 ሰዓት ግድም የሁልባረግ ወረዳ ዋና ከተማ ኬራቴን አቋርጦ በሚያልፈዉ የፉርፉሮ ወንዝ ላይ ለመዋኘት ከወረዱ ህፃናት መሀከል መስጠሟ ተነግሯል። ሟች ህፃን ከወላጅ እናቷ ጋር ሆና ከምትኖርበት ሀዋሳ ከተማ በእንግድነት ወደ ሁልባረግ የመጣች ሲሆን አስከሬኗ በተሽከርካሪ ተጭኖ ወደ ሀዋሳ ተመልሷል። እንዲህ አይነቱ አሳዛኝ አደጋ ዳግመኛ እንዳያጋጥም ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ለህፃናት ተገቢዉ ጥበቃና ጥንቃቄ እንዲያደርግ ፖሊስ መልእክት አስተላልፏል።
Show all...
👍 1
ዛሬ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ቁጥር ET154 ከሀዋሳ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ እያለ በአውሮፕላን ውስጥ ጭስ ታይቷል። ነገር ግን አውሮፕላኑ በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፍያ በተመደበለት የመንገደኞች ማስተናገጃ በር ያለ ምንም እክል መቆሙን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አሳውቋል። መንገዶኞቹም ከአውሮፕላን ላይ ደህንነታቸው እንደተጠበቀ መወርዳቸውን ገልጿል። " በአሁኑ ሰአት የክስተቱ መንስኤ በመጣራት ላይ ይገኛል " ያለው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለተፈጠረው ክስተት ደንበኞቹን ይቅርታ ይጠይቋል።
Show all...
👍 1