en
Feedback
አጫጭር ግጥሞችና መጣጥፎች 📚

አጫጭር ግጥሞችና መጣጥፎች 📚

Open in Telegram

✔️📚ማንበብ ያሻግራል ❗️❗️❗️ በዚህ ቻናል እናንተን የሚመጥኑ የተለያዩ ግጥሞችን ፣ አጫጭር ና መሳጭ ታሪኮችን ታገኛላችሁ። እናንብብ ፤ በማንበባችን እናተርፋለን እንጂ ፤ ከቶ አንከስርም። @snetsehuf

Show more
546
Subscribers
+324 hours
+127 days
+5230 days
Posts Archive
ጥበበኛዋ ትል አንዲት ትል ከአንድ ራጅም ዛፍ ስር ሆና ወደ ላይ ስትመለከት ዛፉ በማፍራት ላይ ያለውን ፍሬዎች በመመልከቷ ከፍሬው ለመመገብ ወደ ዛፉ ላይ የመውጣትን ጉዞ ጀመረች፡፡ በእሷ ፍጥነት (ዝግመት) ዛፉን ወጥታ ያሰበችበት ለመድረስ ረዘም ያለ ጊዜ እንደሚፈጅ ከተሞክሮ ብታውቀውም በጣም የምትወደውን ዜማ እያንጎራጎረችና ወደላይ በወጣች ቁጥር በበለጠ ሁኔታ እየታያት የመጣውን የአካባቢ ገጽታ እያየች በደስታ ዳገቱን ተያያዘችው፡፡ ብዙም ሳትርቅ ከዛፉ ላይ ወደታች የምትወርድ አንዲት ምንነቷ በውል ያልታወቀ እንስሳ ቆም ብላ፣ “ወደየት ነው እንደዚህ በደስታ እየተፍለቀለቅሽ የምትሄጂው አለቻት”፡፡ ትል፣ “ዛፉ ጫፍ ላይ ያለውን ፍሬ ልበላ” አለች፡፡ እንስሳዋም፣ “በቅድሚያ እኔ ከዚያ ነው የመጣሁት፣ ፍሬዎቹ ገና አልበሰሉምና አትልፊ፡፡ ሲቀጥል ደግሞ አጉል ደስተኛነትና አዎንታዊነት አያጥቃሽ ጉዞው ቀላል እንዳይመስልሽ፣ ስለዚህ ብትመለሺ ይሻልሻል” አለቻት፡፡ ትሏም፣ ቆም ብላ እዚያ ለመድረስ የሚፈጅባትን ጊዜ ካሰላች በኋላ፣ “ችግር የለውም፣ እዚያ እስከምደርስ ድረስ ፍሬዎቹ ይበስላሉ” በማለት ጉዞዋን ቀጠለች፡፡ ያሰብከው ከፍታ ለመድረስና የለፋህበትን ፍሬ ለማግኘት . . . 1. ዓላማህን ከጊዜ አጣጥመህ እቅድ አውጣ ከሁሉ በፊት ለመድረስ የምትፈልግበትን የዓላማ ከፍታ ወስን፡፡ ከዚያም፣ እዚያ ዓላማህ ጋር ለመድረስ የሚፈጅብህን የጊዜ ሁኔታ አስላና ሁለ-ገብ እቅድ አውጣ፡፡ ሁለ-ገብ እቅድ ማለት፣ እንደ አንተ ሁኔታ ገንዘብን፣ ትምህርትን፣ እድሜን . . . ያካተተ ሊሆን ይችላል፡፡   2. የሰዎችን ሃሳብ ማመዛዘን ሁል ጊዜ ከፍ ያለ እቅድ ስታወጣና መንቀሳቀስ ስትጀምር ተቃራኒውን የሚነግሩህ ሰዎች እንደሚያጋጥሙህ አትርሳ፡፡ አንዳንዶች ለአንተ አስበው በቅንነት፣ ሌሎቹ ደግሞ በአንተ ላይ አስበው በምቀኝነት፡፡ በጭፍንነት ከሰማሃቸው ውጤቱ ው ስለሆነ ሁለቱንም ቢሆን በጥንቃቄ ማስተናገድ አስፈላጊ ነው፡፡ 3. በጉዞው መደሰት ወደ ዓላማህ በአንተ አቅምና ፍጥነት ስትጓዝ ፍጻሜው ላይ የመድረስን ደስታ እስከምታገኝ አትደበር፡፡ የጉዞ ደስታ የሚባልም ነገር እንዳለ አስብ፡፡ የመድረስ ደስታ ዓላማህ ላይ እስከምትደርስ ድረስ ያስጠብቅሃል፡፡ የጉዞው ደስታ ደግሞ አሁኑኑ በመደሰት ለጉዞው ጉልበትን ይሰጥሃል፡፡ በማንኛውም ጉዞህ ውስጥ “የምታዜመውን ዜማ” ፈልግ፣ የምትስቅበትን ምክንያት ፍጠር፣ ዙሪያህን እየቃኘህ ተደሰት፡፡ ጉዞው የፍጻሜውን ያህል አስፈላጊ ነውና፡፡ ያሰብከው ደረጃ መድረስህና ፍሬህን መብላትህ አይቀርምና፣ በፍጹም እንዳትቆም!!! @snetsehuf

✉️✉️✉️ በሰፈሩት ቁና መሰፈር ✉️✉️✉️ አንድ ቅቤ አምራች ገበሬና ዳቦ አምራች ነጋዴ እንደ አጋጣሚ ድግስ ላይ ተገናኝተው ያወራሉ፡፡ በጨዋታቸው በጣም ስለተግባቡ ከዚህ በኋላ አጋጣሚ ፈጥረው ለመገናኘት ይስማማሉ፡፡ ነጋዴው ጠዋት ጠዋት 300 ግራም ዳቦ ሲልክለት ገበሬው ደግሞ ማታ ማታ 300 ግራም ቅቤ ሊልክለት ተስማሙ፡፡ በዚህ መልኩ ብዙ ጊዜ ከቆዩ በኋላ ነጋዴ የቅቤ መጠን እየቀነሰ መሄዱን አየ፡፡ በመጨረሻም ሚዛን ላይ ሲያስቀምጠው 150 ግራም ሆኖ አገኘው፡፡ በዚህም በጣም አዘነ፤ ተበሳጨም፡፡ ገበሬውንም አስጠራው፡፡ ሌሎች ሰዎች እንዲያዳምጡት አድርጎ ‹ከተስማማነው ውጭ የቅቤውን መጠን ለምን ቀነስከው?› ሲል ጠየቀው፡፡ ገበሬውም ‹እኔ ፈጽሞ አልቀነስኩትም› ሲል በአግራሞት መለሰ፡፡ ነጋዴውም ቅቤውን በሚዛን ለክቶ አሳየው፡፡ 150 ግራም ነው፡፡ ገበሬውም አዘነ፡፡ ‹እኔ ቤት ውስጥ የ300 ግራም መለኪያ የለኝም፡፡ አንተ ጠዋት ዳቦውን ስትልክልኝ በእጅ ሚዛኑ አንደኛው ሰሐን ላይ አደርገዋለሁ፤ ከዚያም ቅቤውን በሌላኛው ሚዛን አስቀምጠዋለሁ፡፡ ልክ ከዳቦው ጋር እኩል ሲመዝኑ በዕቃ አዘጋጅቼ እልክልሃለሁ› አለው፡፡ ወዲያውም ጠዋት የላከለትን ዳቦ አውጥቶ ሚዛኑ ላይ አስቀመጠው፡፡ ዳቦው 150 ግራም ነበር የሚመዝነው፡፡ ነጋዴው አፈረ፡፡ ‹የምታገኘው ለሌላው ባደረግከው ልክ ነው፡፡ 150 ሰጥተህ 300 ልታገኝ አትችልም፤ እባብ ሰጥተህ ርግብ፣ ድንጋይ ሰጥተህ ዳቦ፣ እሬት ሰጥተህ ማር ልታገኝ አትችልም፤ አንተ ብቻ ብልጥ ልትሆን አትችልም፤ ሻማውን አጥፍተህ ብርሃን ልታገኝ አትችልም፤ ሌላው ገድለህ አንተ በሰላም ልትኖር አትችልም› አለው ገበሬው፡፡ ረምሃይም ኢትዮጵያዊ ቀለም  ፤  የሐበሻ ጦማር ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት! @snetsehuf

#እግረ_መንገድ ከተሰኘው የጋሽ ስብሀት መጽሐፍ የተቆነጠረች ንባብ... ፧ <<…ልጅ ሆኜ ነብሴን እጅግ ደስ የሚላት ጢቢ፣ ጢቢ ስጫወት ነበር። ጎረምሳ ሆኜ ነብሴን እጅግ ደስ የሚላት ሴት ልጅን ሳቅፍ ነበር። ዛሬ አርጅቼ ነብሴን እጅግ ደስ የሚላት ልጄ ስትስቅ ሳይ ነው። አሁን እነዚህን ሶስት እኔዎች ሳስተያያቸው አንድ ሰው ናቸው? እርግጠኛ መሆን ያስችላል። እኔ ሽማግሌውስ አንድም፣ አራትም ብሆን ይኸው እዚህ አለሁ። ያ እኔ የምለው ልጅና ያ እኔ የምለው ጎረምሳ ግን የት ሄዱ? የኔ ትውስታ ውስጥ ከልጅየውም ከጎረምሳውም ከብዙ በጥቂቱ እንደ ፊልም ተቀርፆ ይገኛል እንጂ እነሱ ግን የሉም። እኮ እንዴት እኔ ውስጥ ተቀርፀው ሊገኙ ቻሉ? ያን ጊዜ ልጅየው ሆነ ጎረምሳው ሲኖሩ እኔ እዚያ አልነበርኩም'ኮ። ገና አልመጣሁም ነበራ። ያን ጊዜ ያልነበርኩ ሰውዬ ትውስታ ውስጥ አሁን የሌሉ ያን ጊዜ የነበሩ ሰዎች ተቀርጸው ይገኛሉ። ይሄ እንዴት ሊሆን ቻለ? የጊዜና የትውስታ ምስጢራዊ ምትሀት ነው። ለመሆኑ ጊዘና ትውስታ ምንና ምን ናቸው?...>> ፧ ምንጭ ፦ እግረ-መንገድ...ገጽ 206-207 ስብሃት ገብረ እግዚአብሄር ጋሽ ስብሃት እቺን መጠይቃዊ ሃሳብ ያሰፈራት ከጆ እና ሀሪ "አራቱ እኔዎች" ፍልስፍና ተነስቶ ነበር...እኛም በጋሽ ስብሀት ሀሳብ ውስጥ እራሳችንን ልንመለከትበት እንችላለን...እሄንን ስናነብ ያለንበትን የዕድሜ ደረጃ እና ያ ካለፈ በኋላ የሚኖረን ስሜት...አሁን በአፍላነታችን የምንመለከትበት አይንና በዕሜው በሰል ስንል የሚኖረን ትርጓሜ ልዩነት እንደሚኖረው የሚካድ አይደለም... እግረ-መንገድ የሀሳብ እና የፍልስፍና ባህር ነው...እስካሁን ያልሰጠማችሁ ስመጡበት ለማለት እወዳለሁ...! መልካም ንባብ

#አስተማሪ የፍቅር ታሪክ💝 🚶‍♀አንድ ሴት መንገድ ላይ እየሄደች አንድ ልጅ ከኋላዋ ሲሮጥ ሰምታ ዞር አለች "ባንቺ ውስጥ ሴትነት ውበት አለ ወደድኩሽም" አላት 💔    😁ፈገግ ብላ "ከኔ በላይ ቆንጆ እና በሴትነቷም ከኔ የተሻለች ጓደኛዬ ከኋላክ አለች " ስትለው ዞሮ ፈለገ ግን ምንም ሴት አላየም" የታለች?" አላት እሷም #ፈገግ ብላ"ወደኸኝ ቢሆን ኖሮ ሌላ ባልፈለክ ነበር " ብላ መንገዷን ቀጠለች።       👌በአንድ ምክንያት የሚወድህ ሰው በሌላ ምክንያት ይለይሀል ለምን እንደሚወድህ የማያውቀው ግን ሁሌም ቢሆን ይወድሀል💔💓..... @snetsehuf

💎💎አልወለድም❗️ 💎💎 «እሺ ፡ መሬት ፡ አለሽ? » «የለምኝም» «ቤት እለሽ ?» «የለኝም ።» «ትምህርት እለሽ ?» «የለኝም ።» «ታዲያ ፡ ምን ፡ አለሽ ?» «ምንም ፡ የለኝ ።» «ታዲያ፡ድህነት፣ በሽታንና ድንቁርናን ልታወርሺኝ ፡ ነው ፡ ተወለድ የምትይኝ?» «ዕድልህን ፡ እንዴት ፡ ታውቀዋለሁ ፡ ልጄ?» አለች ፡ በትካዜ።» . . . .🧧'እውነት በሌለበት አለም ለመኖር አልወለድም'' * * *** እኔ👉ብዙ ሰው ይህንን ማድረግ ብችል የሚል ይመስለኛል! አልወለድም በሎ ማመፅ ቢችል! ነገር ግን የህይወት ኡደት ከእናትህ ሆድ ገፍቶ ያወጣሃል! ከዛስ ነው ጥያቄው? ከዛማ እናትህን የጠየቅካትን ነገሮች ሁሉ ራስህ ህይወት ላይ ደምረህ ልጅህ ያለአመፅ በደስታ ይወለዳል ወይ ለእናትህ የነገርካት ፍራቻ እውን ይሆንና ልጅህ አልወለድም ብሎ እየየ ይላል! እናማ አንዴ ተወልደሃልና ያለህ አማራጭ የሚገጥሙህን ነገሮች በሙሉ መጋፈጥና መታገል ብቻ ነው!! 🟦አቤ ጉበኛ አልወለድም መፅሐፍ 🟦 Share @snetsehuf

ፍቅር ያሸንፋል ባለጸጋ ብትሆን ሁሉም የተረፈው ባለ ስልጣን ብትሆን ሀገር ያከበረው ጉልበተኛ ብትሆን አለም ያደነቀው አንድ ነገር አለ ገፍተህ እማጥለው እወቀው ልንገርህ እሱ አይሸነፍም ዝቅ ያለ ሲያነሳ ከፍ ያለ ይጥላል ፍቅር አሸናፊ ሁሉን ድል ይነሳል https://t.me/snetsehuf

➧ የሚያነብ ሰው በሁለት ዘመን ይኖራል ።አንድም የራሱን ዘመን ሁለትም ያለፈውን ዘመን አንብቦ የሚፅፍ ግን በሦስት ዘመን ይኖራል ከላይ የተጠቀሱትን ሁለቱን ዘመናትንና የወደፊቱን ዘመን ይኖራል !!! ◦ ዶ/ር አለማየሁ ዋሴ https://t.me/snetsehuf

ጥያቄዎቹ ቀጠሉ፡፡ ‹‹ዶሮ ተመግባችሁ የምታውቁ ከሆነ ስለ ጣዕሙ ግለጡ›› ይላል፡፡ የዶሮ አርቢዋ ልጅ ወደእናቱ ተጠጋናነገራት፡፡‹‹ወይጣጣ፤ እኔኮ አንተን የላክሁህ እንድትማር እንጂ እንድትራቀቅ አይደለም፡፡ አሁን ይሄ ልጅን ማጓጓትና ማሳቀቅ ትምህርት ይባላል፡፡ ለመሆኑ ራሳቸው መምህራኑስ የዶሮ መግዣ ዐቅም አላቸው? እኔኮ ስንት እንደምሸጠው ዐውቃለሁ፡፡ በሁለት መቶ ብር ለሦስት ወር የሚበቃ ሽሮ መግዛት ስችል የአንድ ቀን ዶሮ በልቼ የት ልደርስ ነው? በል ልጄ ‹ዶሮ ትሸጣለች እንጂ አትበላም በላቸው፡፡›› አለችው፡፡ ወዲያው ልጁ ቀበል አደረገና ‹‹እንዴ እማዬ መምህራችንኮ ዶሮ ይበላል ብሎናል›› አላት፡፡ ‹‹እኛ ዶሮ አንበላም፡፡ ፈረስ የሚበሉ አሉ፡፡ እኛ ግን አንበላም፡፡ እንትኖች ውሻይበላሉ ሲባልእሰማለሁ፡፡ እኛ ግን አንበላም፡፡ አይጥ የሚበሉ አሉ፤ ዝንጀሮ የሚበሉ አሉ፤ዕባብም የሚበሉ አሉ፡፡ ታድያ እኛ እነዚህን እንበላል?›› አለችና ጠየቀችው፡፤ የጠራችው ዝርዝር እያቅለሸለው ‹‹ኧረ አንበላም›› አላት፡፡ ‹‹አየህ ልክ እንደዚሁ ነው፡፡ ዶሮም የሚበሉ ይኖራሉ፡፡ እኛ ግን አንበላም›› አለችው፡፡ ‹‹ለምንድን ነው ግን እኛ ውሻ፣ አይጥ፣ ዝንጀሮ ያልበላነው?›› ‹‹ሃይማኖታችን አይፈቅድማ›› ‹‹ዶሮስ የማንበላው?›› ‹‹እንደዚያው ነው ልጄ›› ‹‹ታድያ እነ አካሉኮ ይበላሉ›› ‹‹አየህ የሀብታሞችና የድኾች ሃይማኖት እዚህ ሀገር ይለያያል፡፡ ሀብታሞች መብልንእኛ ደግሞጦምን እናበዛለን፡፡ እነርሱ በደም ብዛት እኛ በደምማነስ እንታመማለን፣እነርሱ በስኳር ብዛት እኛ በስኳር እጥረት እንቸገራለን፣ እነርሱን ውፍረት እኛን ክሳትያስቸግረናል፡፡ የነርሱ ልጆች አልበላም ብለው የኛ ልጆች እንብላ ብለው ይገረፋሉ፡፡ እነርሱገብርኤልን እኛ ሚካኤልን እንዘክራለን፡፡ በዚህ ምክንያት ሃይማኖታችን ተለያይቷል፡፡›› @snetsehuf

ዶሮና የሁለት ልጆች ፈተና በዳንኤል ክብረት ሁለት ተማሪዎች አንድ የቤት ሥራ ተሰጣቸው፡፡ የቤት ሥራው የተማሪዎችን ችሎታ ለመፈተን በከተማ ደረጃ የተዘጋጀ የዕውቀት መለኪያ ፈተና ነበር፡፡ ይህ ፈተና በሁለትትምህርት ቤቶች ለሚማሩ ተማሪዎች ተሰጥቷቸው ነበር፡፡ አንደኛው ተማሪ አባቱ የናጠጡ ነጋዴ ሲሆኑ እናቱም አሜሪካ ተወልደው አድገውበአንድ የውጭ ድርጅት ለመሥራትወደ ኢትዮጵያ የገቡ ናቸው፡፡ እርሱምየሚማረው ‹‹አበባየቀጠፈና አማርኛ የተናገረ ይቀጣል›› የሚል ማስታወቂያ በተለጠፈበት አንድ የግል ትምህርት ቤት ነው፡፡ሁለተኛው ተማሪ አባቱ የቀን ሥራ በመሥራት የሚተዳደሩ እናቱም ዶሮ የሚያረቡ ናቸው፡፡ ልጁም የሚማረው ከተቋቋመ ከሦስት ዓመቱ ጀምሮ መስኮቱ ተዘግቶ በማያውቅ አንድ የመንግሥት ትምህርት ቤት ውስጥ ነው፡፡ የቤት ሥራው እንዲህ ይላል ‹‹ዶሮን በተመለከተ የሚከተሉትን ጥያቄዎች እናንተ ከምታውቁትና ከወላጆቻችሁ ጠይቃችሁ መልሱ›› ሁለቱም ተማሪዎች ወደቤታቸው ከገቡ በኋላ የቤት ሥራውን መሥራት ጀመሩ፡፡ የነጋዴውልጅ ‹‹ዶሮ›› የሚለውነገር ግልጽ አልሆነለትምና እናቱ ከሥራ ስትገባ ጠብቆ ጠየቃት፡፡ ‹‹ዶሮ፣ ምን መሰለህ፣ ኦ ማይ ጋድ፣ ቺክን ማለት ነው›› አለችው፡፡ልጁም ፈገግ አለና ‹‹ኦኬ፤ ታደያ ለምን ቺክን አላሉትም›› አለና ጠየቃት፡፡ ‹‹ቺክንእዚህሀገርውድ ስለሆነብዙ ሰው ቺክን አይበላም፡፡ ለዚያ ነው ዶሮ ያሉት›› ስትል አስረዳችው፡፡ የመጀመርያው ጥያቄ እንዲህ ይላል ‹‹አንዳንድ እንስሳት አካላቸው በፀጉር የተሸፈነ ነው፤ ሌሎቹምበላባ ይሸፈናል፡፡ የዶሮ አካልበምንየተሸፈነ ነው?››የዶሮ አርቢዋ ልጅ ከት ብሎበመሳቅ በጥያቄው ተገረመና ‹‹ ዶሮ በላባ የተሸፈነች ናት›› ሲል መልሱን ጻፈ፡፡ የነጋዴው ልጅ ደግሞ ‹‹ዶሮ በሁለት ነገር ትሸፈናለች፡፡ ከላይ በላስቲክ የምትሸፈንሲሆን ከሥር ደግሞ በነጭ ካርቶን ትሸፈናለች›› ሲል ሱፐር ማርኬቱን እያስታወሰ መልሱን በኩራት ጻፈው፡፡ ከዚያም ሁለቱም በየቤታቸው ሆነው ወደ ሁለተኛውጥያቄ ተዘዋወሩ፡፡‹‹ዶሮ የሚገኘው ከየት ነው?›› ይላልጥያቄው፡፡ የዶሮ አርቢዋልጅፈጠንብሎ ‹‹ዶሮየሚገኘው ከዕንቁላል ተፈልፍሎ ነው›› ሲል በደብተሩ ላይአሠፈረ፡፡ የነጋዴውም ልጅ ሳቅ አለና ‹‹ዶሮ የሚገኘው ከኒውዮርክ ሱፐር ማርኬት፣ ከፍሎሪዳ ሱፐር ማርኬት፣ከሆላንድ ሱፐር ማርኬት፣ከኤክስ ዋይ ሱፐር ማርኬት ፍሪጅ ውስጥ ነው›› ሲል በኩራት መልሱን ጻፈ፡፡ ጥያቄው እንደ ቀጠለ ነው፡፡ ‹‹ውሻ ሲጮኽ ‹ዋው፣ ዋው› ይላል፡፡ ላም ‹እምቧ› ብላ ትጮኻለች፤ ጅብ ‹አውውውው› ብሎ ይጮኻል፡፡ ለመሆኑ ዶሮ ሲጮኽ ምን ይላል?›› የነጋዴው ልጅ አንገቱን ነቀነቀና ‹‹ዶሮ ድምጽ የላትም፤ ኢት ኢዝ ኦልሬዲ ዴድ››ሲል ሞላ፡፡የዶሮ አርቢዋም ልጅ ‹‹ዶሮ ሲጮኽ ኩኩሉ ይላል›› ብሎ ጻፈ፡፡ ‹‹በባህላችን ዶሮ አሥራ ሁለት ብልቶች አሏት ይባላል፡፡ ከወላጆቻችሁ ጠይቃችሁ ስማቸውን ዘርዝሯቸው፡፡›› ይላል ቀጣዩ ጥያቄ፡፡ የዶሮ አርቢዋ ልጅ ወደእናቱ ጠጋብሎጠየቃት፡፡ ‹‹አይየኔ ልጅ ዶሮኮ ድሮነበር እንጂ ዛሬ ከአሥራ ሁለት የሚበልጥ ብልትሊኖራትይችላል፡፡ በአሁኑጊዜ ምንያልጨመረ ነገር አለ፡፡ ወይም ደግሞ እንደ ድኻ ኑሮ ቀንሳ ከሆነም ቁጥሩ ቀንሶ ሊሆን ይችላል፡፡ ማን አይቷት ብለህነው፡፡ እኔእንደተሸፈነች ነው የምሸጣት፡፡ ዛሬ ዛሬኮ ዶሮ የሚሸጥ፣ ዶሮ የሚያይናዶሮ የሚበላ ተለያይተዋል፡፡ ዶሮ የሚሸጥ ዶሮ ያረባል እንጂ አይበላም፡፡ ቢበዛ ዕንቁላሏ ይበቃዋል፡፡ ዶሮ የሚያይ ደግሞ ገበያ ሲወጣ ዶሮ ከማየት ውጭ ዶሮም ዕንቁላልም በልቶ አያውቅም፡፡ ዶሮ የሚበላ ግን ዶሮ ከየት እንደምትመጣ ባያውቅም ዶሮ ይበላል፡፡ እኛ ዶሮዋ ተሸፍና ስለምንሸጣት ብልቷንረስተነዋል፡፡እነርሱደግሞስለብልቷ ስለማይጨነቁ አያውቁትም፡፡ አሁን ይህንን ጥያቄ ብለው የሰጧችሁ እንድትጓጉ ካልሆነ በቀር ምን ይጠቅማችኋል? በል ሂድና እመይቴ የዝናሽን ጠይቃቸው፡፡ እርሳቸው የደጃች ዘመዱ ወጥ ቤት ነበሩ፡፡ ልጁ ወደ እመይቴ የዝናሽ ዘንድ ሄደ፡፡ ‹‹አዬ ልጄ አሁንማ ረስቼ፡፡ ዶሮ በሁለት መቶ ብር እየተሸጠ ማን ብልት ያስታውሳል ብለህ ነው፡፡ አታጓጓኝ እባክህ፡፡ እኔኮ ዶሮ ሲያምረኝ ድሮ የበላሁትን እያስታወስኩ ነው የምጽናናው፡፡ ‹ድኻ በሕልሙ ቅቤባይጠጣ› ሲባል አልሰማህም፡፡ በልእስኪ ጣፍ ትዝ ካለኝ፡፡ አጭሬ ሁለት፣ መላላጫ ሁለት፣ ፈረሰኛ አንድ፣ መቋደሻ አንድ፣ ክንፍ ሁለት፣ እግር ሁለት፣ አቃፊ አንድ፣ ጉሮሮ አንድ፣ አሥራ ሁለት አልሆነም፡፡ወደፊትኮ የዶሮ ቅርጫ ካልተጀመረ ዶሮ እንዳማረንመቅረቱ ነው፡፡ ዱሮማ የዶሮ ዳቦም እንሠራ ነበር፡፡ ወዳጄ ዛሬ እንኳን ዶሮ ያለበት ዳቦ ባዶውም ዳቦ አልተገኘ› አሉና ሸኙት፡፡ የነጋዴው ልጅ ሁለት ነገር አልገባውም ‹‹ብልት›› ምንድን ነው?አለ ለራሱ፡፡ አሥራ ሁለት ብልት የሚባል ነገር ሰምቶ አያውቅም፡፡ ወደ እናቱ ሄደና‹‹ማማ የቺክንአሥራ ሁለት ብልት ምንድን ነው?›› አለና ጠየቃት፡፡ ‹‹አይዶኖ፡፡ እስኪጉግል ላድርግ›› ብላ ወደ ኮምፒውተሯ ሄደች፡፡ ‹‹ቆይ ብልት በእንግሊዝኛ ምንድን ነው? ሌት ሚ ሰይ ፓርትስ›› ‹‹ትዌልቭ ፓርትስ ኦፍ ቺክን›› ብላ ጉግል ላይ ጻፈችና ሰርች አደረገችው፡፡ ‹‹እንደዚህ የሚባል ነገር የለም››አላት ጉግል፡፡ ‹‹የሌለ ነገር ነው እንዴ የሚሰጧችሁ፡፡ ትዌልቭ ፓርት የሚባል የዶሮ ነገር የለም›› ትንሽ አሰበችና ‹‹እስኪ ቆይ ዲክሽነሪ ሪፈር ላድርግ›› ብላ ወደ ሳሎን ሄደች፤ አንድ የአማርኛ እንግሊዝኛ መዝገበ ቃላትም አወጣች፡፡ ‹‹ቆይ ‹በ›ከማን ቀጥሎ ነው፡፡››ከ‹ሀ› ጀምራ ወደ ‹በ› ለመድረስ አልቻለችም፡፡ ‹‹ሚኪ‹በ› ከማን አጠገብ ነው ያለው?›› ብላ ልጇን ጠየቀችው፡፡ ‹‹ከ‹ቡ› ጎን›› አለና መለሰላት፡፡ ከመጀመርያው ገጽ ጀምራ እያገላበጠችበመዝገበ ቃላቱ ላይ መፈለግ ጀመረች፡፡ ‹‹አማርኛ መሻሻል አለበት፡፡ ከ‹ኤ› ቀጥሎ ‹ቢ› እንዲመጣ ማድረግ አለባቸው፡፡›› ብላ አማረረች፡፡ ከዚያም በስንት ፍለጋ እንደምንም ብላ ‹ብ›ን አገኘችው፡፡ ‹‹ብልት›› ለሚለው ቃል መጀመርያ የተሰጠውን ትርጉም አየችና፡፡ ‹‹ማነው ግን ይህን ሆም ወርክ የሰጣችሁ›› አለችው ልጇን፡፡ ‹‹ሆም ሩም ቲቸር ነው›› ‹‹ባለጌ ነው፡፡ ብልትየሚል ቃል አሁን ለልጅ ይሰጣል፡፡ በቃዶሮ እንኳን አሥራ ሁለት አንድም ብልት የላትም ብለህ ጻፍለት›› አለችው ተናድዳ፡፡ ልጁም እንደ እናቱ ተገርሞ ወደ ቀጣዩ ጥያቄ አመራ፡፡ ‹‹የዶሮን ልዩ ልዩ ጥቅሞች ግለጡ›› ይላል፡፡ የዶሮ አርቢዋ ልጅ እናቱን ጠየቃትና እንዲህ መለሰችለት ‹‹ዶሮ ለሦስት ነገር ትጠቅማለች፡፡ አንደኛ ጠዋት ጠዋት ለመቀስቀስይጠቅማል፡፡ ሁለተኛ ተሽጦ ገንዘብይገኝበታል፡፡ ሦስተኛ ደግሞ ዕንቁላል ያስገኛል፡፡›› ልጁም ጻፈ፡፡ የነጋዴውም ልጅእንዲህ ሲል መልሱን ሰጠ‹‹ዶሮ ለወጥ፣ ለአሮስቶ፣ ለግሪል፣ ከሩዝ ጋር ለመብላት፣ ለሰላጣ ትጠቅማለች፡፡ አንዳንድ ሬስቶራንት ደግሞ እግሯን ለብቻ፣ ክንፏን ለብቻ ግሪል አድርገው ይሸጧታል፡፡ ዕንቁላሏ ደግሞ ለሳንዱች፣ ለዕንቁላል ፍርፍር፣ ለጥብስ፣ ለፓን ኬክ ይጠቅማል››

አራንባ እና.......... 1.ዶሮን ሲያታልሏት ባነነችባቸው 2.አባይ ማደሪያ የለው አሁን ሊገደብ ነው 3.የትም ፍጪው ግን ወፍጮ ቤት ይሁን 4.ጅብ ከሄደ ሁለት ሰአት ሆነው 5.ስራ ያጣ መነኩሴ ማስታቂያ ያነባል 6.ሆድ ለባሰው ቡሌ አጉርሰው 7.የቆጡን አወርድ ብላ ብብቷ ታየ 8.ጆሮ ለራሱ ይሰማል 9.የነቶሎ ቶሎ ቤት ከኛ ቤት ጎን ነው 10.አባይን ያለየ ሄዶ ማየት ይችላል 11.ሌባ ላመሉ ሰው ኪስ ውስጥ ይገባል 12.ስራ ያጣ መነኩሴ ማስታወቂያ ያነባል 13..የጨነቀው ኤድናሞል ይገባል 14.በእጅ ያለ ወርቅ ብዙ ብር ይሸጣል 15.የቸኮለ በአውሮፕላን መሄድ መብቱ ነው

ሴትዮዋ፡በእንግሊዘኛ የሚቀበጣጥር ልጅ አላቸው፡፡ በልባቸው፡ ልጃቸው እንግሊዘኛ ቅልጥፍ አድርጎ እንደሚናገር ገምተዋል፡፡ አንድ ቀን በግ ሊሸጡ ከልጃቸው ጋር ገቢያ ይወጣሉ፡፡ባጋጣሚ ፈረንጅ ይመጣና ዋጋ ይጠይቃቸዋል፡፡ <<በል ልጄ፡ ትምህርት ለዚህ ጊዜ ነውና በደንብ ተከራከርና በጌን ሽጥለት>>ይሉታል፡፡ፈረንጁ ዋጋ ይጠይቃል፡፡ How much is it? it..this...are hunderd only...birr ልጅ እንደምንም መለሰ፡፡ What do you mean?Does it deserve? ፈረንጅ ኮስተር ብሎ ጠየቀ፡፡ ልጁ ግራ ገባው፡፡<<ፈረንጅ፡ ከገዜሽን ገዜሽን፡፡ ካልገዜሽን ኖ ክርክሬሽን መሄዴሽን!>>አለ ይባላል፡፡ @snetsehuf

ውድ የዚህ ቻናል አባላት አንኳን ከዘመነ ማርቆስ ወደ ዘመነ ሉቃስ በሰላምና በጤና አሸጋገራችሁ ። አዲሱ ዓመት 2015 የሰላም ፣ የጤና ፣የፍቅር ፣የስኬት ይሁንላችሁ ። መልካም በዓል ፤ መልካም አዲስ ዓመት።

ቅምሻ አንቶኒዮ ቡርጋስ ገና በ40አመቱ በጭንቅላት ካንሰር ምከንያት በህይወት የሚቆየው ለአንድ አመት ብቻ እንደሆነ ዶክተሮች ይነገሩታል። በጊዜው በጣም ያዝናል፣ ይሁን እንጂ ሚስቴ ከሞትኩ በኋላ እንዳትቸገር በማለት በቀረችኝ ጊዜ ስራ መስራት አለብኝ ለሚስቴ ጥሪት ማስቀመጥ አለብኝ ብሎ ወሰነ። አንቶኒዮ ባርጋሰ ኘሮፌሽናል ደራሲ አልነበረም ነገር ግን በዉስጡ የተዳፈነ የመፃፍ ችሎታ እንደነበረዉ ያዉቅ ነበርና ወረቀቱን ከመፃፍያ ማሽኑ ጋር አወዳጅቶ መፃፍ ጀመረ። በሚገርም ሁኔታ በቀረችዉ 1 አመት ውስጥ 5 መፅሀፎችን አሰናድቶ ጨረሰ ይህም ታዋቂዉ ደራሲ 'Em foster' በህይወቱ ሙሉ ከፃፈዉ በላይ እሱ በአንድ አመት ዉስጥ የፃፈዉ ይበልጥ ነበር። እንዲሁም 'J.D.stelenger' የተባለዉ ደራሲ በህይወት ዘመኑ ከፃፈዉ መፅሐፍ በላይ በእጥፍ ፃፈ። በካንሰር ለመሞት 1 አመት ቀረህ የተባለው አንቶኒዮ ከህመሙ ሙሉ በሙሉ አገገመ፣ በውስጡ የነበረው ካንሰርም ጠፋ። በኖረበት እረጅም እድሜ 70 መፅሃፍቶችን ለአንባቢያን አበረከተ። በተለይ 'clock work orange' በሚል ያሳተመዉ መፅሐፍ ታላቅ እዉቅናን ያስገኘለት ስራው ነበር። አንቶኒዮ ቡርጋስ ለመሞት 1 አመት ነዉ ያለህ ባይባልና ሚስቱ እንዳትቸገር ንብረት አስቀምጬ ልሙት በሚል ሀሳብ ባይነሳ፣ ይህን ያህል ቁጥር ያለው መፅሐፍ ባልፃፈ ነበር። ይህ ታሪክ ለአብዛኞቻችን አስተማሪ ይመስለኛል። በውስጣችን አዳፈንነው ያስቀመጥነው ተሰጥኦ እንዳለን አምናለሁ። ይህን ተሰጥኦ ከውስጣችን ጎትቶ የሚያወጣልን ውጫዊ አካል አንጠብቅ። የተሰጠን ቀን ዛሬ ነውና ለማናውቀው ነገ ቀጠሮ አንስጥ። ስለ ነገ ማንም አያውቅም የተሰጠን ዛሬ እንደሆነ አውቀን የተዳፈነውን ችሎታችንን አውጥተን ለሌሎች የብርሃን ችቦን እንለኩስ እላለሁ። @snetsehuf

እኔና አንቺኮ እናሳዝናለን ! መዋደድ ታድለን.. መፋቀር ታድለን... መች አንድ ላይ አለን ? እኔና እንቺኮ እናሳዝናለን ! ፍቅርን ያህል ትንፋሽ ሲገፋኝ ሲገፋሽ ጨዋታውን ትረካውን ላንችልበት የዚህን ዓለም ሰው አንደበት እንዲያው ዝም ተባብለን አለን፡፡ እኔና አንቺኮ እናሳዝናለን ! የነበረነው... ያነበርነው ነገን ብለነው የፈሪ ቆዳችንን ፈተግነው ፥ እስካይቀረን ፍርፋሪ እስክናልቅ እስክንጠፈጠፍ የልጅነታችን አበባ ፥ በየፍራሹ ሲቀጠፍ መች ልብ አልነውና ? ለእናት ለአባታችን ፥ ያልታዘዘን ጉልበት እንደጨረስነው ተሳስመንበት። መች ልብ አልነውና ? የአፍ ቃላት ጨረሰን ፥ ተቃቅፈን ተኝተን ነገ ለሚወዱን ፥ 'አቤት' ማለት እስኪያቅተን። መች ልብ አልነውና? ከቀትር ፥ እንደሚያቃጥል ከረሀብ ፥ ከፍቶ እንዲጥል ናፍቆትን መች አወቅን ? ናፍቆት ስንት ይፈጃል ? ያረጃል ? ፥ ወይስ ያስረጃል ? ይገላል ? ፥ ወይስ ያስገልላል ? ናፍቆት ምን ያህላል ? መንበረሥላሴን ? ፥ ወይንስ ሥላሴን ? ነገረሕይወትን ? ፥ ወይስ የሰው ሞትን ? የቀጣፊን ምላስ ? ፥ ወይስ የሳራን ዳስ ? የጋሽ ጥላሁንን ፥ የረዘመ ትንፋሽ ማንን ነው ሚያክለው? በናፍቆት የከፋኝ ፥ በናፍቆት የከፋሽ እኔና አንቺ እኮ እናሳዝናለን ! መነፋፈቅ መርገም... ክብራችን መለገም... የት ያደርስን እንደሁ ፥ ባናውቀውም እንጃ ሰው ከራስ ሲጣላ ፥ የት ይኬዳል ምልጃ ? እንጃ! እንጃ... የመናፈቅ መቅሰፍት ፥ አልፎ ላያልፍልን ያልቅብን ይመስል ፥ ገላ ተካፈልን ሰቀልነው... ገረፍነው... ገደልነው... ቀበርነው... የኔና አንቺ ፍቅር ፥ እሁድ ለሊት የለው መቃብር አይከፍትም ኮፈኑን አይቀድም የኔና አንቺ ፍቅር ፥ ትንቢትን አይወድም ለወሬ ለዓለም ፥ አልተረፈምና ነገርና ስሙ አረገ አይባል ፥ መላዕክት አልሰሙ፡፡ የት ገባ ይባላል ? ቀረ በነበረ በነበረ ቀረ እንደተነፋፈቅን... እንደተጠባበቅን በሌላ ሰው ናፍቆት ፥ እንደተቃጠረ በሰነፍ ኮረዳ ፥ እንደተበጠረ የትም ተበተነ ፥ የትም ቦታ ቀረ የኔና አንቺ ፍቅር መቃጠል እጣው ነው ፥ በፍም የታጠረ፡፡ መናፈቅ መፈለግ ፥ ስንት ህመም ያድላል ? ከስንቱ ያውላል ? በስንቱ ያስማል ? በስንቱ ያስምላል ? ተጠባብቀን ያለቀን መዓት ቢፍለቀለቅ እኔና አንቺ ላንላቀቅ። በቀረን ፥ እንደሐውልት ደርቀን እስከጌታ ፥ ፍርድ ቀን ስንቱን አወጣሁኝ ? ፥ ስንቱን አወረድኩኝ ? ስንቱን ቀባጠርኩኝ ? ናፈቀሽኝ ስንት ሆንኩኝ ? ቀጥረሽኝ በቆሞኩኝ፡፡ ሰበብ በሆንሽልኝ ቀጥራው ቀረች ብሎ ፥ ሰው በኔ እስኪያማሽ መቃብር መግባቴን ፥ አግብተሽ በሰማሽ፡፡ መናፈቅ እንደልጅ ፥ እያንቀለቀለኝ እንደሽማግሌ ፥ በቀኔ ገደለኝ እንደጠዋት ፀሀይ ፥ አሰኘኝ ልሞቅሽ እንደአድባር ስለት ፥ ስለቴ ባረግሽ እንደእናት ምርቃት ፥ ባልኩሽ አሜን አሜን አቤት ስል በኖርኩኝ ፥ ሆነሽ ቅፅል ስሜን፡፡ ናፈቀሽኝ... ናፈቀሽኝ... እኔና እንቺኮ እናሳዝናለን ! እየተዋደደድን... እየተፋቀረን... መች አንድ ላይ አለን ? እኔና እንቺኮ እናሳዝናለን ! ​​ ┈┈┈┈•◦●◉❖◉●••┈┈ ┈ ✍🏽© ኤልያስ ሽታኹን ╰══•••┈ ┈ ┈•◦●◉❖◉●••┈┈ ┈ @snetsehuf

ወጣቱና ሥነጽሑፍ (ሲሳይ ንጉሱ) 📗📒📕 ወጣትነት ውበት ነው፤ ወጣትነት ፍቅር ነው፤ ወጣትነት ኃይል ነው ። ትኩስ ጉልበት፣ ንቁ አዕምሮና ፈጣን እንቅስቃሴ ያለው፣ የደሙ መቀትና የጡንቻው ንዝረት በገፅታው ላይ የሚነበበው፣ አፍላ ስሜት የሚፈታተነው፣ ለወደደው ነገር ሕይወቱን የሚሰጥ፣ በጠላው ነገር ሕይወቱን የሚያጣ ከሚዛናዊነት ይልቅ በስሜታዊነት የሚጠቃ...ልበ ሙሉነት በደሙ ውስጥ የሚዘዋወር...ውጫዊውን ዓለም ሳያመዛዝን ወይንም ደንታ ሳይኖረው ውስጣዊ ስሜቱን ተከትሎ የሚሮጥና ለእሱነቱ ብቻ የሚታዘዝ...አብዛኛውን ጊዜ ወደፊቱ የሚሮጥ ...የፊት የፊቱን የሚያይ...ወደኋላ ዞሮ መመልከት የሚጨንቀው፣ ባለበት ረግጦ መታየት የሚያስጠላው፣ ገደልም ይሁን ሜዳ ወደፊት መገስገሱ ብቻ የሚያስደስተው...አዲስ ነገር በማለም አዲስ ነገር በማየትና ለአዲስ ነገር በመነሳት በየደቂቃው የደሙ ንዝረት የሚጨምረው...ለማጎብደድ ወገቡ፣ ለመንበርከክ ጉልበቱ፣ ለማጎንበስም አንገቱ የማይፈቅድለት...ቀጥታውን ቀጥ ያለ ግትር (...ሙሉ ፍቅር ሰጥቶ ሙሉ ፍቅር መቀበል የሚችል...ስሜቱን የማይሸራርፍ፣ ልቡን የማይከፋፍል፣ አዕምሮውን የማያስመነታ ቀጥታ) ይህንን ነው ወጣት የምለው ። 📋📋📋 ወጣት አበባ ነው ። ውሃ ሲጠጣ ሲኮተኮት፣ እንክብካቤ ሲያገኝ ያብባል፤ ድርቅ ሲመታው፣ ሐሩር ሲያጠቃው፣ አስተዋሽ ሲያጣና ተመልካች ሲያጣ ቶሎ የረግፋል ። 🗒🗒🗒 ሥነጽሑፍ ውበት ነው፤ ሥነጽሑፍ ፍቅር ነው፤ ሥነጽሑፍ ኃይል ነው ። ውበት ወጣትና ሽማግሌውን ሳይለይ ሁሉንም ያማልላል፤ ፍቅሩ ያነሆልላል፤ ኃይል ያጠናክራል ። የተዋጣለት ድንቅ ሥነጽሑፍ ሁልጊዜም አዲስ፣ ሁልጊዜም ትኩስ፣ ሁል ግዜም ጣፋጭ ነው ። ጊዜ አይሽረውም፣ ጊዜ አያበላሸውም፣ ጊዜ አይለውጠውም ። የሼክስፒርን ሥነጽሑፍ ሥራዎች ከ500 ዓመታት በኋላ መድረክ ላይ ስናያቸው እንደ አዲስ ስራ ለአዲስ ስሜት እንዋጣለን ። የሀዲስ አለማየሁ ፍቅር እስከ መቃብር ዛሬ ከዓመታት በኋላ እንደገና ሲነበብ አዲስ መንፈስ ጭሮ አዲስ ደስታን ይሰጣል እንጂ አይሰለችም ። ውበቱ አይረግፍም፤ ፍቅሩ አይነጥፍም፤ ኃይሉ አይበርድም ። ይህንን ጊዜ አይሽሬነት ለመጎናጸፍ ሥነጽሑፍ ከባለቤቱ የሚጠይቀው መስዋዕትነት አለ ። ታማኝነትን ይጠይቃል፤ ትዕግስትን ይጠይቃል፤ ችሎታን ይጠይቃል፤ ቆራጥነትን ይጠይቃል ከምንም በላይ ተሰጥዖን ይጠይቃል ። 📜📜📜 በቅጡ ካልተያዘ ደግሞ የሥነጽሑፍ ፍቅር አደገኛ ነው ። አንዳንዴ ያጃጅላል፤ አንዳንዴም ያሳብዳል ። ከወጣትነት እስከ እርጅና ሙሉ ሕይወታቸውን ለሥነጽሑፍ ሰጥተው ሙሉ ምላሽ ያገኙ በጣም ጥቂት ዕድለኞች ናቸው ። ብዙዎቹ ተገቢውን ምላሽ ሳያገኙ መስዋዕት እየሆኑ ነው ያለፉት ። 📜📜📜 ሥነጽሑፍ ጥንታዊ ዘመን አስተሳሰብ ባህልና አጠቃላይ ሕይወት ምን እንደሚመስል የሚያሳየን የኋላ መስተዋት የአሁኑ ማንነታችንን የምናይበት የጊዜ መስተዋት...የወደፊት ህልማችንን አሻግረን የምናይበት የትንቢት መነጽር ነው ። 📜📜📜 ወጣትነትና ሥነጽሑፍ ሁለቱም ውበት፣ ፍቅርና ኃይል ናችው ። ሁለቱም ትኩሳት ናቸው ። ሁለቱም የሚነዝር ደም ናቸው ። ሁለቱም የሚንቦገቦጉ እሳቶች ናቸው ። ይፈላለጋሉ ። ይሳሳባሉ ። የመፈላለጋቸውንና የመመሳሰላቸውን ያህል የተጣሉና የተራራቁ እንደሆነ ደግሞ ሆድና ጀርባ ሆነው ይቀራሉ ። ይህ እንዳይሆን ጉዳዩ ትኩረትን ይጠይቃል ። ....... (( ምንጭ "ደቦ" ከሚለው በስልሳ ነባርና አዳዲስ ጸሐፍት ተጽፎ በቅርቡ ለህትመት ከበቃው መጽሐፍ ከገጽ 178-180 የተቀነጨበ ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ያንብቡት ። )) @snetsehuf

ውድድር! "ከውሻ እና ከአቦሸማኔ የቱ ሊፈጥን ይችላል?" ተብሎ በዓለም ላይ ካሉ ፈጣን የውሻ ዝርያዎች ተመርጠው ከአንድ አቦሸማኔ ጋር የውድድር ፕሮግራም ይደረጋል። ውድድሩ ሲጀመር ውሾቹ ተፈትልከው ሲሮጡ አቦሸማኔው ስንዝር ያህል እንኳአ ለመሮጥ ፍላጎት አላሳየም። በዚህ የተገረሙት ታዳሚዎች የውድድሩን ሀላፊ "አቦሸማኔው ለምን ሊሮጥ አልሞከረም?" አሉት። አላፊውም "አንዳንዴ ምርጥነትህን የማይገባ (የማይመጥንህ) ቦታ ላይ ለማሳየት መሞከር የስድብ ያህል ነው" አላቸው። @snetsehuf

ሞት ማለት (ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም) ፨፨፨ ሞት ማለት ተንጋሎ መተኛት፤ አለመንቀሳቀስ ፍጹም የእንቅልፍ ዓለም፤ ፍጹም የሕይወት ቀውስ፤ አለመደሰት ነው፤ ተከፍቶ አለማልቀስ፤ የሬሣ እኩልነት፤ ርኩስ የለ ቅዱስ፤ በኅብረት መበስበስ፤ በየቀኑ መፍረስ ሞት አለመስማት፤ ነው ጆሮ ዳባ ልበስ፤ ክርስቶስ ሲሰቀል፤ ሲፈታ በርናባስ። ሞት ማለት ፦ አለመናገር ነው ጭው ያለ ዝምታ፤ የመቃብር ሰላም የሬሳ ጸጥታ፤ ደሀ በሰሌኑ ሳጥን ገብቶ ጌታ፤ የውሸት ልዩነት ተጋድሞ በተርታ፤ አይመሽ ወይ አይነጋ ጠዋት የለ ማታ ። ሐዘን የለ ለቅሶ፤ ደስታ፤ ፈገግታ፤ ዘፈኑና ለቅሶው የምስጥ ሹክሹክታ ። ሞት ማለት ፦ አይረገዝበት፤ አይወለድበት፤ የመቃብር ዓለም፤ ጭንጋፍ፤ የጭንጋፍ ቤት የሰው ልጅ አንደበት ትል የሚሆንበት፤ ክርክር የለበት፤ ውድድር የለበት፤ ውሸትና እውነት በማይበርድ ፍትወት የተሳሰሩበት የድብቅብቅ ዓለም ምስጢር የበዛበት፤ ሁሉም በየጉድጓዱ የተሸሸገበት ። ሞት ማለት ፦ አለመነቃነቅ፤ አለመነቃነቅ፤ እንደ ድንጋይ መድረቅ፤ ደርቆ መወላለቅ፤ ክብርና ውርደትን ለይቶ አለማወቅ አዘቅት ውስጥ ተኝቶ በክፋት መጥለቅለቅ፤ በተዋኅዶ መልክ ጠላትና ወዳጅ አብሮ ሲደባለቅ ድፍርሱ ከጠራው ባሕርዩ ሲደበቅ የሩቁ ሲጠጋ የቅርቡ ሲራራቅ ሞት አምሮት ሲጠፋ በልጦ ለመመረቅ ። ሞት ማለት ፦ ሞት አለመስጋት ነው የግዴለሽ ዓለም፤ ድንጋይ ተሸክሞ በውሀ ላይ መቆም፤ ጤንነት የለበት፤ አያጠቃው ሕመም፤ ትዝታ የለበት፤ አይታይበት ሕልም፤ ቡቃያው አያሽት፤ ፍሬው አይለመልም ። ዝናብ አይዘንብበት ድርቀት ነው ዘላለም ። ማንም አይጎዳ ማንም አይጠቀም ። ሞት ማለት ፦ የሞት ሞት ፦ አእምሮ ፈራርሶ ህሊና በስብሶ፤ ሰውነት ረክሶ፤ እንደግም፤ እንደጥንብ፤ የጭልፊቶች ምግብ፤ የሞት ሞት ይኽ ነው፤ ትንሳኤ የሌለው ። ፧ ምንጭ ፦ "ዛሬም እንጉርጉሮ" እንዲሁም "መክሸፍ እንደ ኢትዮጵያ ታሪክ" ከሚለው የፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም መጽሐፍት ላይ የተወሰደ 📖 እናንብብ ያነበብነውንም ለምንወደው ማካፈላችንን አንዘንጋ 📖 @snetsehuf

ጎልፃን ፨፨፨ ጎልፃን የግሪክ ቃል አይደለም፣ ላቲንም አይደለም ። እንዲሁም የግዕዝ የት-መጣ ያለው ቃልም አይደለም ። "ጎልፃን" የፒያሣ ናዝራውያን(ጠቢባን) የፈጠሩት ሁለት የአማርኛ ውህድ ቃል ነው ። ጎልማሳ እና ህፃን...በጉልምስናው እንደ ህፃን የሚያስብ በዕድሜው መግፋት ቁጥርን እንጂ የህይወት ልምድን ማካበት ያልቻለ ሰው "ጎልፃን" ይባላል ። ለፒያሳ ናዝራውያን ባልተፃፈ መዝገበ ቃላታቸው ውስጥ ። ፧ ጎልፃኖች ሁሉን ነገር ፓለቲካ ማድረግ መለያቸው ነው ። እናንተ አንድ ልታደርጉት ስለምታስቡት መልካም ሃሳብ ስታወሯቸው እነሱ ሃሳባችሁ መሆን የማይችልበትን መቶ መንገዶች ይጠቁሟችኋል ። የህይወታቸው ፍልሥፍናም ከዚህ ተቃራኒ ልማዳቸው የተቀዳ ነው ። ነገር በመጥለፍ እና የሚሆነው እንዳይሆን በማሠብ ። ፧ ብቻቸውን ሃገር ወዳድ ናቸው ። ብቻቸውን ለሃገር አሳቢ ናቸው ። ሁሉም ነገር የመንግስት ሥህተት ነው ። የነሱ የመሆን ፍላጎት ፍላጎት ብቻ ሆኖ የቀረው የመንግስት ሥህተት ነው ። በመንግስት አቅጣጫ የሚገኙ ጎልፃኖች ከሆኑ ደግሞ በተቃራኒው ናቸው ። እነዚህ መንግስት ሲሉ እነዚህ ደግሞ ህዝብ ይላሉ ። በቀኝም ሆነ በግራ በኩል የተሰለፉ ጎልፃኖች አንድ የሚያደርጋቸው ነገር ቢኖር በግለሠብ አመለካከት የማያምኑ መሆናቸው ነው ። ሁሉም ማለት ይቻላል መናጆዎች ናቸው ። ከመንጋጋት በስተቀር ነጠል ብለው መቆም አይችሉም ። በአንድነት እንጂ አንድ በመሆን አያምኑም ። ፧ ጎልፃኖች በግለሰብ አመለካከት የማያምኑበት ትልቁ ምክንያት ብቻቸውን ሆነው ስለማያውቁ ነው ። ለብቻ ቆም ብሎ ማሰብ ለጎልፃኖች ሞት ነው ። ዕድሜያቸውን የሚገፉት በብቸኞች ሃሳብ ላይ በማሳደም ስለሆነ ። ለብቻቸው ሲሆኑ የሚፈጠውን እውነት መሸከም ስለማይችሉ ግርርር ማለት እንጂ ነጠል ብሎ መገኘት እርማቸው ነው ።.... ፧ ጎልፃኖች የዘር ሃረጋቸው የሚመዘዘው ከተረት እና ከጭፍን ስሜተኝነት ነው ። ናዝራውያን ዘወትር የሚያነሱት ምክንያተኝነት በጎልፃኖች ዘንድ የሚታየው እንደ አባታቸው ገዳይ ነው ። ሁሉን እሺ ባይ ያልሆነ ሰው ከእነሱ ጋር መኖር አይችልም ። እነሱም ሁሉን ከሚጠይቅ ሰው ጋር ሰላምታ የላቸውም ። ጎልፃኖች ሰውን ጠልፈው የሚጥሉበት አንድ መፈክር አላቸው ። " ከእኛ ጋር ያልሆነ ከማንም አይሆንም " ከራሱም ጭምር እንደማለት ነው እንግዲህ ። ፧ "እንደኔ ካላሠብክ......ሃሳብህን ትተህ እኛን ምሰል..."ከሚል የጅምላ አስተሳሰብ ናዝራውያኑ የተለዩ ስለሆኑ ሁለት በደም የሚፈላለጉ ጎልፃኖች በአንድ ናዝራዊ ፊት "ከየት የመጣ ፍቅር ነው?" እስኪባሉ ድረስ ወዳጃሞች ይሆናሉ ። " የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው " እንዲል የጎልፃኖች የተረት አባት... ፨፨፨ ምንጭ ፦ "የአዋጁ ግዜ ምልክት ፍለጋ እና ሌሎችም ሃሳቦች" ከሚለው የደራሲ ኤፍሬም ስዩም መጽሐፍ የተቀነጨበ ስንት ጎልፃኖች በየግዜው ያጋጥሙን ይሆን ግን...? ፧ ፍርዱን ለአንባብያን... ያነበቡትን ለወዳጅዎ ያጋሩ ለመቀላቀል ደግሞ 👇👇👇 @snetsehuf

#እግረ_መንገድ ከተሰኘው የጋሽ ስብሀት መጽሐፍ የተቆነጠረች ንባብ... ፧ <<…ልጅ ሆኜ ነብሴን እጅግ ደስ የሚላት ጢቢ፣ ጢቢ ስጫወት ነበር። ጎረምሳ ሆኜ ነብሴን እጅግ ደስ የሚላት ሴት ልጅን ሳቅፍ ነበር። ዛሬ አርጅቼ ነብሴን እጅግ ደስ የሚላት ልጄ ስትስቅ ሳይ ነው። አሁን እነዚህን ሶስት እኔዎች ሳስተያያቸው አንድ ሰው ናቸው? እርግጠኛ መሆን ያስችላል። እኔ ሽማግሌውስ አንድም፣ አራትም ብሆን ይኸው እዚህ አለሁ። ያ እኔ የምለው ልጅና ያ እኔ የምለው ጎረምሳ ግን የት ሄዱ? የኔ ትውስታ ውስጥ ከልጅየውም ከጎረምሳውም ከብዙ በጥቂቱ እንደ ፊልም ተቀርፆ ይገኛል እንጂ እነሱ ግን የሉም። እኮ እንዴት እኔ ውስጥ ተቀርፀው ሊገኙ ቻሉ? ያን ጊዜ ልጅየው ሆነ ጎረምሳው ሲኖሩ እኔ እዚያ አልነበርኩም'ኮ። ገና አልመጣሁም ነበራ። ያን ጊዜ ያልነበርኩ ሰውዬ ትውስታ ውስጥ አሁን የሌሉ ያን ጊዜ የነበሩ ሰዎች ተቀርጸው ይገኛሉ። ይሄ እንዴት ሊሆን ቻለ? የጊዜና የትውስታ ምስጢራዊ ምትሀት ነው። ለመሆኑ ጊዘና ትውስታ ምንና ምን ናቸው?...>> ፧ ምንጭ ፦ እግረ-መንገድ...ገጽ 206-207 ስብሃት ገብረ እግዚአብሄር ጋሽ ስብሃት እቺን መጠይቃዊ ሃሳብ ያሰፈራት ከጆ እና ሀሪ "አራቱ እኔዎች" ፍልስፍና ተነስቶ ነበር...እኛም በጋሽ ስብሀት ሀሳብ ውስጥ እራሳችንን ልንመለከትበት እንችላለን...እሄንን ስናነብ ያለንበትን የዕድሜ ደረጃ እና ያ ካለፈ በኋላ የሚኖረን ስሜት...አሁን በአፍላነታችን የምንመለከትበት አይንና በዕሜው በሰል ስንል የሚኖረን ትርጓሜ ልዩነት እንደሚኖረው የሚካድ አይደለም... እግረ-መንገድ የሀሳብ እና የፍልስፍና ባህር ነው...እስካሁን ያልሰጠማችሁ ስመጡበት ለማለት እወዳለሁ...! መልካም ንባብ ✔️📚ማንበብ ያሻግራል ❗️❗️❗️ በዚህ ቻናል እናንተን የሚመጥኑ የተለያዩ ግጥሞችን ፣ አጫጭር ና መሳጭ ታሪኮችን ታገኛላችሁ። እናንብብ ፤ በማንበባችን እናተርፋለን እንጂ ፤ ከቶ አንከስርም። @snetsehuf