አጫጭር ግጥሞችና መጣጥፎች 📚
Open in Telegram
✔️📚ማንበብ ያሻግራል ❗️❗️❗️ በዚህ ቻናል እናንተን የሚመጥኑ የተለያዩ ግጥሞችን ፣ አጫጭር ና መሳጭ ታሪኮችን ታገኛላችሁ። እናንብብ ፤ በማንበባችን እናተርፋለን እንጂ ፤ ከቶ አንከስርም። @snetsehuf
Show more546
Subscribers
+324 hours
+127 days
+5230 days
Posts Archive
አስጨርሱኝ
(በእውቀቱ ስዩም)
አብቹ ወደ ስልጣን በመጣ ሰሞን ለቀቅ ያረግሁትን ሙገሳ ብጤ፥ ከማህደሬ ፈልፍላችሁ በማውጣት “ ሙድ “ ለመያዝ የምትሞክሩ ሰዎች፥ ዲያብሎስ በብርድ ቀን፥ ቆለጣችሁን በጋመ ወረንጦ ይያዝላችሁ ከማለት ውጭ ክፉ አይወጣኝም!
በጊዜው ከነበረው የማሽቃበጥ ፏፏቴ አንጻር ሲታይኮ የኔ ግሳጼ ነው ማለት ይቻላል: በጊዜው ማሽቃበጡን ከፊት ሆነው ሲመሩት ከነበሩት አርቲስቶች አንዱ በቅርቡ “ ይሄ ስሙን ልጠራው የማልፈልገው ሰውየ” ሲል ሰማሁት፤ ለሽንገላ የፈጠነ ለርግማንም የሚቀድመው የለም፤ እኛ ግን ዛሬም በሚሆነው አዝነን፥ ሂስ ስናቀርብ “ ክቡር ጠቅላይ ምኒስትር “ የሚል ማእረጋቸውን አንነሳቸውም ::
ብቻ የሆነውን ሁሉ ሳስበው የልጅነቴን አንድ ገጠመኝ ያስታውሰኛል :: በብላቴናነት ዘመኔ ፥ የሰፈራችን ኗሪዎች ፥ የገና በአል መዋጮ ሰብስበው ፥ ፍሪዳ ጥለው ይቀራመታሉ፤ የተረፈው ተደግሶ ከተበላ ከተጠጣ በሁዋላ፥ ታዳሚዎች ስእለት ማቅረብ ይጀምራሉ::
መጀመርያ የበውቄ አባት ጋሽ ስዩም ተነሱ: :
“በሚቀጥለው አመት ቢያደርሰን ቢያደርሳችሁ ከፍሪዳው በፊት እምንቃመሳት አንድ ጠቦት ፍየል አስገባለሁ”
እልልልል!
ጨብጨብ
ቀጥለው የመዋእለ ህጻናት መምህርት ወይዘሮ እታገኝ ተነሱና “በሚቀጥለው አመት ቢያደርሰን ቢያደርሳችሁ፥ አንድ ጥዋ የስጋ ማባያ ድቁስ አቀርባለሁ”
አነስ ያለ ፥ የተድበሰበሰ ጭብጨባ ተሰማ::
በማስከተል፥ የሰፈሩ ጋሪ ነጂ ጋሽ በላይ ብድግ አለና ለሁለት ደቂቃ ሳይናገር ዝም ብሎ ተገተረ፤ ከዝያ ከእንቅልፉ እንደመባነን አለና” በሚቀጥለው አመት ቢያደርሰን ቢያደርሳችሁ …ደስ ይለኛል “ አለና ተቀመጠ::
እድምተኛው አጉረመረመ::
መጨረሻ ወይዘሮ ማሚት ተነሱ፤ ሻሻቸውን ነጠላቸውን አስተካከሉ፤ ጠላ የረጠበውን ያፋቸውን ጠርዝ ጠራረጉ ፤
“ በሚቀጥለው አመት ፤ ቢያደርሰን ቢያደርሳችሁ፥ አንድ ጋን ጠጅ ...”
እድርተኛው አላስጨረሳቸውም ፤ እስከ ሰላሌ የሚሰማ ጭብጨባ ወረደ! ደን ጠባቂው አቶ ቢረሳውማ ነሽጦት ብድግ አለና ፥ ከ”ነጻ ርምጃ ወዲህ “ ተተኩሶ የማያውቀውን አብራራው ጠመንጃውን ወደ ሰማይ ደግኖ ሁለት ጥይት ለቀቀ! በጭብጨባው እና በተኩሱ መሀል ወይዘሮ ማሚት “ አስጨርሱኛ ! “ ሲሉ እሰማለሁ::
ጭብጨባው በረድ ሲል ፥ የባሩዱ መአዛ ገልል ሲል ፥ ማሚት እንዲህ አሉ፤
“ በሚቀጥለው አመት ቢያደርሰን ቢያደርሳችሁ አንድ ጋን ጠጅ የሚያስንቅ ፤ ማንቆርቆርያ ሙሉ ጠላ አቀርባለሁ”: :
✔️📚ማንበብ ያሻግራል ❗️❗️❗️
netsehuf
እንቶ_ፈንቶ
፡
፡
፡
««በጭራሽ አትምጪ በፍፁም አልመጣም፣
የፍቅርን ፅዋ ዳግም እንደገና ባብሮነት አንጠጣም።
ተቀብሯል ነገርሽ ተቀብሯል ነገሬ፣
በይ ትፊኝ አንቅረሽ ተፋውሽ አንቅሬ።»»
፡
፡
የሚል ግጥም ልፅፍ ብዕሬን ስመዘው፣
እጅ ለካ አይፅፍም ልብ እስካላዘዘው።
፡
፡
ቢፅፍም ቢጭርም በንዴት ተገፍቶ፣
ሀረጉ አርቲ ቡርቲ ስንኙ እንቶ ፈንቶ።
#ሄኖክ_ብርሃኑ
ድንቅ_እናት
ባለቤቷ ከሞተ በኋላ ልብሱን ቁም ሳጥን ውስጥ አንጠልጥላው በየጊዜው ገንዘብ ታስቀምጥበታለች ። ልጆቿ ለተለያየ ጉዳይ ወጪ ሲጠይቋት ሂዱ ቁም ሳጥን ውስጥ
ከአባታችሁ ደረት ኪስ ውሰዱ ትላቸዋለች "
እነሱም የሚያስፈልጋቸውን ብቻ ቆጥረው ከአባታቸው ኪስ ይወስዳሉ ከዕለታት አንድ ቀን ልጆቹ እናታቸውን ለምን እንደዚህ እንደምታረግ ሲጠይቋት የአባታችሁ ሩህሩህነትና ለጋስነት እንድታውቁትና አባታችሁ እዛም ሆኖ ለእናንተ እንደሚጨነቅ እንድታውቁ (አባት የሞተበት ) ነን ብላችሁም እንዳታስቡ ለማስታወስ ነው!::
#አስተዋይ_እናት_ትምህርት_ቤት_ናት_የምንለው_ለዚህ_ነው!::
@snetsehuf
ዕድሌ ነው...
(መላኩ አላምረው )
.
ዕድሌነው...
በሚስትልወሰን፣ እኔ ትዳር ሲያምረኝ፤
ሳታገባ 'ምትቆይ፣ አንድም ሴት አትገኝ
.
ዕድሌነው...
እኔዲግሪ ስይዝ፣ ዲግሪ ዋጋ ያጣል፤
ገንዘብ ያለው ሁሉ፣ ዶክትሬት ያመጣል
.
ዕድሌነው...
እኔመድረክ ስይዝ፣ ይፈታል ጉባኤ፤
እኔ መጾም ሲያምረኝ፣ ይሆናል ትንሣኤ።
.
ዕድሌነው...
በቁርባንለመኖር፣ ንሰሐ ስገባ፤
አቁራቢው ፖትልኮ፣ ቤተመንግሥት ገባ።
.
ዕድሌነው...
እኔኳስ ስገዛ፣ ሜዳው ይታረሳል፤
እኔ ቤት ሲኖረኝ፣ ሰፈሬ ይፈርሳል።
.
ዕድሌነው...
ለተሾመሁሉ፣ እንዳልኖርሁ ስለፋ፤
እኔ አለቃ ስሆን፣ የሚታዘዝ ጠፋ።
.
ዕድሌነውና...
ከዕለታትአንድ ቀን፣ መንገሤ ባይቀርም፤
እኔ ንጉሥ ስሆን፣ ሀገሪቱ አትኖርም።
ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት!
@snetsehuf
በሴቶች ቀን የምትታወሰው የኔ ጀግና!!
‹‹ወደቀጭንዋ አርሶአደር እናት ስመለስ፤ ማለዳ ተነስታ ያ ልጅዋም ሳይለያት እንዲሁ ጎንበስ ቀና እንዳለች ይረፋፍዳል፡፡ ውሃ ካለበት በዛ መከረኛ ቢጫ ጄሪካን ቀድታ ባንድ እጅዋ እሱን በሌላኛው እጅዋ ልጅዋን ከጎንዋ ይዛ ትመለሳለች፡፡ ጤዛ ሳይረግፍ አረም ማልደው ለሄዱት ቤተሰቦችዋ ከመስክ የሚጠበቅ በግ፣ ፍየልና ከብት ካለ እረኝነት ለሄዱትም ሆነ፣ የሚጠበቅ ምንም ነገር ከሌላት ደግሞ ከቤት ሆነው አይን አይንዋን የተራቡ አይኖቻቸውን እያንከራተቱ ለሚጠብቁዋት ልጆችዋ ምሳ ለማዘጋጀት ደፋ ቀና ማለትን ትያያዘዋለች፡፡
‹‹ እኩልቀን ላይ ከቤት ላሉም ሆነ ወይም በእረኝነት ለዋሉት ልጆችዋ ምሳ ሰጥታ ስታበቃ እያረሙ ላሉት ቤተሰቦቸዋ ምሳ ባገልግል ወይም በሌማት አድርጋ፣ ያንን ልጅዋን ወይ ከጀርባዋ አሊያም ከጎንዋ ይዛ ወደማሳ ትሄዳለች፡፡ ምሳውን ከሰጠች በሁዋላ ቁጭ አትልም፣ ወይም አብራ አትበላም፡፡ የሁሉም ግምት እቤት ሳለች በልታ ነው የመጣችው የሚል ነው፡፡ እስካሁን እህል ባፍዋ ይዙር አይዙር እስዋና አንድ እግዚአብሔር ብቻ ናቸው የሚያውቁት፡፡ አለመብላትዋን በሆነ አጋጣሚ ያወቀ ሌላ ሰው ቢኖር እንኩዋን…እህሉ በጅዋ…ማን አትብዪ አላት? የሚልን አኞ አኞ ያለ፣ ካስፓልት የደደረ፣ ከጎማ የገነተረ አስተያያየት አይሉት ጥያቄን ማትረፍ ብቻ ነው ትርፏ፡፡
‹‹ አረም የዋሉት ቤተሰቦችዋ ምሳቸውን ሲበሉም ሆነ በልተው ካበቁ በሁዋላ እስዋ ቁጢጥ ብላ ታርማለች፡፡ አረም ሲታረም ዝርፍጥ ተብሎ ተቀምጦ አይደለም፡፡አንድም በሁለት እግር ቆሞና ከወገብ አጎንብሶ፣ አንድም ቁጢጥ ተብሎ ነው አረም የሚታረመው፡፡ አለበለዚያ በውልድ ወይም በአንጉዋ ደረጃ ያለው ቡቃያ ድምጥማጡ ይጠፋል፡፡ ስለዚህ ነው እግር የሚያርፍበት ክፍት ቦታ በጥንቃቄ እየተፈለገ በቁጢጥታ ወይም ወገብን አጉብጦ የሚታረመው፡፡ ያቺ ቀጭን እናት ልጅዋ ጡት እያለ በየመሃሉ ሲያስቸግራት ለሱ ጡትዋን በምታጎርስበት ጊዜ ከምትኖራት ፋታ በተቀር ለተጨማሪ ሁለትና ሶስት ሰአት ቁጢጥ ብላ ወይም አጎንብሳ ታርማለች፡፡
‹‹ያቺ ጠልጣላ አርሶአደር እናት ግን ሊያውም ችግርዋን ሊረዳላት በማይችልበት እድሜ ላይ ያለ ልጅዋ የማያቁዋርጥ ጥያቄና መነጫነጭ ሳትበሳጭ ለሰአታት ምናልባትም በባዶ አፍዋ ቁጢጥ ብላ ታርማለች፡፡ እንዲህ አይነቱን አካላዊ ተግዳሮት ተጫዋቾቻን መቋቋም ቢችሉ ያለጥርጥር የአለምን ዋንጫ እናነሳለን፡፡
እንቁርቁሪት፡- የስናዳር ስንክሳር በምንዳርየለው ዘውዴ
@snetsehuf share እያደረጋችሁ
"ለስህተትህ ፣ለውድቀትህ ፣ለድክመትህ ፣ ለጥፋትህ ሌሎችን ምክንያት አታድርግ፡፡ ላንተ
ማጣት ሌሎችን ተጠያቂ አታድርግ፡፡ በወደክ ቁጥር ጣትህን በሌሎች ላይ ከቀሰርክ
ወድቀህ ትቀራለህ፡፡ለምታደርገው ነገር በሙሉ ራስህን ጠይቅ፡፡ለምትራመደው እርምጃ ራስህ ሀላፊነት ውሰድ!!!
@snetsehuf ለወዳጅዎ ማጋራት አይዘንጉ
የእያደር ሀገር ህዝቦች
እያደር ይፋጃል፣የጉድ ሀገር ገንፎ
እያደር ውድ ነው፣የጉድ ሀገር ክትፎ
እያደር ይበላል፣የጉድ ሀገር ቴሌ
የጉድ ሀገር ተስፋ፣ይነጋል ነው ሁሌ
ጉድ አንድ ሰሞን ነው፣የጉድ ሀገር ተረት
ለአንዲት ቀን እንኳን፣ጉድ አልቻለም መቅረት
እያደር እንቧ ነው፣የጉድ ሀገር በረት
የጉድ ሀገር ወሬ፣እያደር ሰቀቀን
የጉድ ሀገር ንጋት፣እያደር አንድ ቀን
እያደር እያደር
አድሮ ቃሪያ መሆን፣ወይም ከርሞ ጥጃ
የጉድ ሀገር ምላሽ፣እያደር እኔንጃ
የጉድ ሀገር ፍርሀት፣እያደር ጠብመንጃ
@snetsehuf ሼር እያደረጋችሁ 🙏
✍️✍️በላይ በቀለ ወያ
መለያየት ማለት
እየው ትላንትና ከትላንትም በስቲያ
ያዩሽ ሰዎች ሁሉ ከእቅፌ ጉያ
ዛሬን ተራርቀን ብቻዬን ቢያዩኝ
ከድታዋለች ብለው ከንፈር መጠጡልኝ
እባክሽ የኔ ዓለም ፈጥነሽ ንገሪያቸው
ሴትን ማፍቀር እንጂ ማባበል አይችልም ብለሽ አስረጃቸው
ለእኔ እና ለአንቺ እኮ መለያየት ማለት
በሩቅ መፋቀር ነው ያለመተያየት
ያለመተያየት መፋቀርም ማለት
በምናልባት ተስፋ የምትቆም ሕይወት
ዘወትር ዘወትር ምናልባት
ምናልባት እያለች የምትኖር ሕይወት
በተስፋዋ መሀል ጥቂት ደስታ አላት
በተስፋችን መሀል መፋቀሩ ካለን
ናፍቆት አካል ገዝቶ እንተያያለን
ብለሽ ንገሪያቸው
ልቤና ልቡናው ተጣብቋል በያቸው
እንጂ በእኛ መሀል መለያየት ማለት
በሩቅ መፋቀር ነው ያለመተያየት
በሩቅ መሰማማት በድምፅ አልባ ቃላት
✍️✍️ ኤፍሬም ሥዩም
@snetsehuf ለወዳጅዎ ያጋሩ
አየር ላይ
(በእውቀቱ ስዩም )
በቀደም ለት፥ ከአሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ ባውሮፐላን መጣሁ ፤ እና በሎንቺና ልትመጣ ኑሯል? አለኝ አንዱ አሁን በውስጥ መስመር፥ እስቲ ትረካውን እስክጨርስ እንኳ ታገሱኝ!
ወደ አይሮፕላኑ ገብቼ ሻንጣ ለመስቀል ሳንጋጥጥ እግረመንገዴን ፈጣሪየን አመሰገንሁ:: “ ጌታየ ሆይ! ከሙስና ባስ የሰወርከኝ፥ ባውሮፕላን ያሳፈርከኝ እኔ ማነኝ? በግሬ ንቅቃት መሀል አንድ ቁና ቀይ አቧራ ተሸክሜ ከማንኩሳ የወጣሁ ልጅህ በደመና ላይ እንድረማመድ ስለፈቀድክልኝ አመሰግናለሁ “ አልሁና ጅንን ብየ ወንበሬ አመራሁ፤ አውሮፐላኑ ሲነሳ እንደ ጀማሪ ሹፌር እጄን ካውሮፐላኑ መስኮት አውጥቶ ማናፈስ አማረኝ::
ከጥቂት ጊዜ በሁዋላ ሽንት ቤት ጎራ ለማለት ስሞክር በስህተት የ” የቢዝነስ ክላስ” መንገደኞች ክፍል ውስጥ ራሴን አገኘሁት፤ እዚያ በተመለከትኩት ነገር እጀግ ከመደንገጤ የተነሳ ቆቡ ላይ ደርሶ የነበረው ሽንቴ ወደ ፊኛየ ተመለሰ! እንደኛው፥ የቢዝነስ ክላስ መንገደኛ አባቴ ድሮ እሚተኛበትን ሞዝቦልድ አልጋ በሚያክል ሶፋ ላይ ፈልሰስ ብሏል:: ከፊትለፊቱ ባለው ጠረጴዛ ላይ Diamond label ውስኪና ጣፋጭ የአማልክት ምግቦች ተደርድረውለታል፤ በቃ ምን ልበላችሁ ዙርያውን ፍሬሽ ኮርነርን አስመስለውለታል! የተቀመጠበት ሶፋ መደገፍያ ጀርባውን ማሳጅ ሲያደርገው የሚያወጣው ድምጽ እኔ ከሚስቴ ጋራ ግብረ- ፍስክ ስፈጽም ከማወጣው አንጸባራቂ ድምጽ ጋራ ይቀራረባል፤ ከፊትለፊቱ ያለው ቲቪ መለስተኛ ሲኒማ ያክላል፤ ጫማውን ሲያወልቅ የበረራ አስተናጋጇ ፈጠን ብላ መጥታ የእግር ውሀ እና ነጠላ ጫማ አቀረበችለት፤ ነጠላ ጫማው ሲራመድበት ፥ነጠላ ዜማ እንዳይለቅ ፥ ሳይለንሰር (ማፈኛ) ተገጥሞለታል፤
እኔም ይህን አይቼ፥ እንደ ድንክ ከዘራ አቀርቅሬ ወደ ወንበሬ መመለስ ጀመርኩ፤ ሰፊው ህዝብ ተገጥግጦ የተቀመጠበትን ኢኮኖሚ ክላስ አለፍሁ፤ ያውሮፐላኑ ጅራት ማብቂያ ላይ Under-developed economy class እሚባል አለ፤ እዚያ ውስጥ የኤሌክትሪክ መግደያ በሚመስል ወንበር ላይ ተጎልቼ እንደሚከተለው ማማረር ጀመርሁ” ጌታሆይ ! ከሰው የተለየ ምን በድየ ነው ክንፍ ያለው ሀይገር ባስ ውስጥ ያሳፈርከኝ? በውኑ በዚህ አለም ስኖር፥ “ለቢዝነስ ክላስ” እሚያበቃ ትሩፋት አልሰራሁምን? በውኑ ጌቶች በምባልበት እድሜየ “ ጌቶ” ውሰጥ ስማስን መገኘት ነበረብኝ ? እኔ ጀርባየን ማሳጅ የሚያደረግ ወንበር አልጠየቅሁህም! ግን ቢያንስ ጀርባ የሚያክ ወንበር አያምረኝም? ወይ ወረድ ወይ እኔ ልውጣና እንዋቀስ! “
የኢራንን ሰማይ ስናቋርጥ፥ በቀኝ በኩል ከጎኔ የተቀመጠው ህንዳዊ መንገደኛ እንደ ፍቅረኛ ትከሻየ ላይ ተኛ፤የሰውየው ራስ፥ ራስ ሆቴልን ያክላል፤ ይባስ ብሎ ግብዳ ጥምጥም ጨምሮበታል፤ ትከሻየን ሸክሽኮ ሆዴ ውስጥ ከመክተቱ በፊት ገፈተርኩት::
የበረራ አስተናጋጅዋ ስለ በረራ ድህንነት ገለጻ ስታደርግልን፥
“ አውሮፐላኑ ባህር ላይ ለማረፍ ቢገደድ ለቢዝነስ ክላስ መንገደኞች መንሳፈፍያ ከረጢት እና ሞተር ጅልባዎች አዝጋጅተናል፤ ለኢኮኖሚ ክላስ መንገደኞች ደግሞ “ ውሀ ዋና ያለ አስተማሪ “ የሚል መጽሀፍ እናድላለን ስትል ፤ በተራየ የህንዱ ትከሻ ላይ ዘንበል ብየ አለቀስኩ::
በግራየ በኩል ለተቀመጠው አበሻ ተሳፋሪ፥ ስለ ቢዝነስ ክላሱ ምቾት ነገርኩት::
“ ትርፍ ቦታ ካላቸው ይሰጡሀል፤ ሰለብሪቲ መሆንህን ብቻ መንገር ነው እሚጠበቅብህ “ አለኝ::
“ ሰመጥር መሆኔን እነሱ የት ያውቁልኛል ?”
“ አታስብ ! ከተጠየቅህ እኔ እመሰክርልሀለሁ”
ተነሳሁና ወደ ቢዝነስ ክላሱ ሄድኩ፤ እንደመታደል ሆኖ አንድ ስራ የፈታ ወንበር አየሁ::
ሳላቅማማ ተንሰራፋሁበት::
ካንድ ደቂቃ በላይ አላጣጣምኩትም::
“ የሰው ወንበር ለመንጠቅ እንዲህ ያለ ድፍረት ካለህ ለምን ኩዴታ አትሞክርም?” የሚል ድምጽ ሰማሁ::
ሰውየው ሸንቶ መመለሱ ነው፤ ራሴን ለማስተዋወቅ እንኳ ጊዜ አልሰጡኝም፤ የአውሮፕላኑ ደህንነት አስጠባቂ ተጠርቶ መጣ! ያድዋ ዋዜማ ስለነበር ትንሽ ልታገለው ሞከርኩ፤ እንደ ሰርቶ ማሳያ ካሮት አንጠልጥሎ ወስዶ ወንበሬ ላይ ጣለኝ፤ በመጨረሻ አጋዥ ፍለጋ ወደ አበሻው ተሳፋሪ ዞርሁ ::
አጅሬ በተቀመጠበት ወደ ደንብ አስከባሪው ቀና ብሎ እያየ እንዲህ አለው፥
Share eyaderegachihu @snetsehuf
በኋለኛው ዘመን ...
ስሙን ሊሸፍኑ ታሪኩን ሊከድኑ
ከብሔር በሽታ ፈጽመው ያልዳኑ
ንጉሱን በመተው በሎሌው አመኑ ።
ከአዕምሮ ቅኝ ግዛት ያልወጡት መኳንንት
ድግሱን ቢያደርጉም የንጉሱን ዘነጉት ።
በዚህን ጊዜ ...
ነፃነት የሰጠህ ምን ይበል ምን ይልክ
ከፋሽስት ሳላቶ ከባንዳ አንሰህ ሲያይክ
ጣይቱ ዕጣውን ከስንቅ ስትለይበት
ምን ይበል ምን ይልክ ሀገርህን ስትከዳት ።
አንተ ሰው ...
የጦርነቱን ውል ቋንቋውን ቀይረው
የአድዋን መነሻም ታሪኩን በርዘው ።
ከቶ ምን ያደርጋል የአማርኛም ቃሉ
ፊርማውን ያኖረው ምን ይልክ ነው አሉ ።
አንቀጽ ሶስት ዘጠኝ ሀገር እነፈየመራህ
አንቀጽ አስራ አስራ ሰባት ምን ሊፈይድልህ
ከአንቶኖሊ ሚሻል ሰዋዊነት ካጣህ
በል ፋቀው ሰርዘው በቀረችው ጊዜህ ።
ቀጣዩን አድዋም ሮም ሄደህ አክብረው
ስሙ ይቀየርልህ ዘግላዲያተር በለው ።
ድርሰትህን ከትብ ያለሐፍረትም ደስኩር
ምኒልክ ምን ይልክ ከአጠገብህ ቢኖር ።
ቅሉን ወዲያ ገፍተህ ማንጠልጠያ ይዘህ
ውሃ ልጠጣ አትበል መንግስት ሆይ እባክህ !
Fekremichael Zeyede
#ኡቡንቱ!
አንድ የስነ-ሰብ (Anthropology) ተመራማሪ ወደ ደቡብ አፍሪካ ገጠራማ መንደር ለስራ ያቀናል። በቆይታውም ከህጻናት ጋር መግባባትን ይፈጥራል። እናም ሕጻናቱን ለማስደሰት አንድ ሽልማት ያለው ጨዋታ ያዘጋጃል።
ጨዋታውም፣ በማንጎ የተሞላ አንድ ቅርጫት ከዛፍ ስር ያስቀምጣል፣ ህጻናቱን ከዛፉ አንድ መቶ ሜትር እንዲርቁ አደረገ፣ ከዛም እንዲህ አላቸው:-
"እኔ ጀምሩ ስል ቀድሞ ቅርጫቱ ጋ የደረሰ የፈለገውንና የሚችለውን ያህል ማንጎ ይበላል:: "
ጨዋታው ተጀመረ።
ህጻናቱ ግን ከጨዋታው ህግ ውጪ ያልተጠበቀ ነገር አደረጉ።
ይህም ሁሉም እጅ ለእጅ ተያይዘው እኩል ወደ ቅርጫቱ ሮጡ። ከዚያም አንድ ላይ በቅርጫቱ ውስጥ ያለውን ማንጎ በአሸናፊነት መንፈስ ተካፍለው መብላት ጀመሩ::
የስነ-ሰብ ተመራማሪውም በመገረም "ለምን እንዲህ አደረጋቹ?"ሲል ጠየቃቸው።
ሁሉም በአንድነት "ኡቡንቱ! " በማለት መለሱለት።
በመቀጠል አንዱ ህፃን እንዲህ አለው:-
"እንዴት ሌሎች ጓደኞቻችን ተከፍተው አንድ ልጅ ብቻውን ይደሰታል? ይሄ ባህላችን አይደለም::"
"ኡቡንቱ" የቃሉ መሠረት የደቡብ አፍሪቃው የዙሉ ማሕበረሰብ ሲሆን፤ ትርጓሜውም:-
“ለመኖሬ ምክንያት አንተ ነህ፤ ላንተም መኖር እኔ!” የሚል ሰብዓዊነትን ያዘለ ፍልስፍና ነው።
ራሴን ወግቼ ላንቺ የምወግን
(በእውቀቱ ስዩም)
አይደለሁም ጀግና
ልቤን እና ክንዴን ፥እጠራጠራለሁ
ግን ተኩሼ ባልጥል፥ አነጣጥራለሁ
ቀማኛ ቢከብሽ፥ ፖሊስ እጠራለሁ::
ቅዱስ አይደለሁም፥
የጻድቃን ቤት ካለ፥ በውስጡ የለሁም::
መናኛው ራሴ፥ ቢበጠር፥ ቢላጭም
ለሳር ባርኔጣ እንጂ፥ ላክሊል አይታጭም::
ምንድን ሆኘ ነው ግን?
ራሴን ወግቼ ላንቺ የምወግን
ምኔን አሞኝ ነው ግን ?
እንችን የማሞግስ፥ ራሴን ወቅሼ
ሳቄን የማካፍል፤ ለብቻየ አልቅሼ፤
እንደ ጋሻ ጃግሬሽ ፤ ከሁዋላሽ ስባክን
ከፊትሽ ቀድሜ፥ እንቅፋት ሳመከን
አይተሽ እንዳላየ
ጀግኖች ምናረጉ
ሰማታት ምን ሰሩ፤ ከዚህ የተለየ፥
🇪🇹"ኢትዮጵያን ልዩ ሀገር የሚያደርጋት!"
🫧የአስራ ሶስት ወር ካላንደር ያላት አለም ከሚጠቀምበት የጎርጎሪያን ካላንደር በ8 አመት የዘገየ የቀን አቆጣጠር ያላት ሀገር.
🫧የተለየ የሰዓት መለኪያ አላት፣ ፀሐይ ስትወጣ አንድ ሰዓት፣ ጀምበር ስትጠልቅ አስራ ሁለት ሰዓት.....
🫧ከቅኝ አገዛዝ ጋር የተዋጉ እና ያሸነፉ ብቸኛዋ አፍሪካዊ ሀገር......
🫧የራስተፈሪያን ንቅናቄ መፍለቂያ.....
🫧የቡና መገኛ......
🫧የአለማችን አንጋፋ ህዝቦች መገኛ ናት፣ ሉሲ የተገኘችው በግምት 3.2 ሚሊዮን ዓመታት ነበር፤ የትውልድ ሀገር..
🫧በ1970ዎቹ ከአፄ ኃይለ ሥላሴ ጋር ያበቃው ረጅሙ ሥርወ መንግሥት ነበራት። ሥርወ መንግሥቱ ከሰለሞን ጊዜ ጀምሮ እስከ መጨረሻው አፄ ኃይለ ሥላሴ ድረስ ቆይቷ።
🫧የቃል ኪዳኑ ታቦት እንዳለ ይታመናል።
🫧ዳሎል በኢትዮጵያ ሞቃታማ ነው።
🫧አዲስ አበባ ዋና ከተማ
በአፍሪካ ከፍተኛ ቦታ የምትገኝ ዋና ከተማ ነች።
🫧በቀጥታ ጅቦችን እንደ የቱሪስት መስህብ የምትመግበው ብቸኛ ሀገር ናት።
🫧"የገሃነም መግቢያ በር" የተሰኘው ረጅሙ የውሃ ሐይቅ አላት።
🫧የኤርታ አሌ እሳተ ገሞራ በዓለም ላይ በጣም ንቁ ከሆኑ እሳተ ገሞራዎች አንዱ ነው።
✍️ ስሙ ከመቃብር በላይ የዋለለት ውሻ🐕
~~~~~~~
የማታውቁት ተዋወቁት ይህ ውሻ ስሙ ሀቺኮ ተብሎ የሚጠራ ሲሆን የፕሮፌሰር ኢዛብሮን (Hidesa buro ueno) ውሻ ነበር። ጃፖናውያን ይበልጥ ይወዱታል ፤ ይኮሩበታልም።
ፕሮፌሰር ኢዛቡሮን ወደስራ በሚሄዱበት በአንዷ ቀን አንድ ቡችላ አገኙ ወደቤታቸውም አመጡት ተንከባከቡት፤ በፍቅር አሳደጉት አቆላምጠውም ስሙን በፍቅር 'ሀቺ' ሀቺኮ አሉት።
ሁሌም ውሻውና(ሀቺኮ) ፕሮፌሰር ኢዛብሮን የለመዱት ነገር አለ ሁሌ ፕሮፌሰሩ ወደስራ ሲሄዱ ጠዋት አብሮ ባቡር ጣቢያ ድረስ ሄዶ ፕሮፌሰሩን ሸኝቶ ይመለሳል ማታ 11 ሰዓት ባቡር ጣቢያ ሄዶ ይቀበለውና ቤት ድረስ አብረው ይመጣሉ።
ይህ ሁሉ እያለ ታድያ ከእለታት በአንዱ ክፉ ቀን በግንቦት 21/1923ዓም ውሻው ፕሮፌሰሩን ሸኝቶ ማታ እንደልማዱ ሊቀበላቸው ባቡር ጣቢያ ቢጠብቃቸው ሰውየው ለካ በልብ ህመም(heart failure) ሞተው ኖሯል ሳይመጡ ቀሩ ውሻው ግን ይመጣሉ ብሎ ፕሮፌሰሩን ጠበቀ አንድ ቀን ብቻ አይደለም፤ ጥቂት ወራትም ብቻ አይደለም።
ድፍን አስር አመት እንጂ! ዘወትር እየተመላለሰ እሳቸውን ጥበቃ እዛችው ባቡር ጣቢያ ጋር አስር አመት ጠብቆ እሱም እዛው አሳዳጊውን ሲጠብቅበት ከነበረው አደባባይ ላይ/canccer & filaria infection/ ምክኒያት ህይወቱ አልፋለች።
ሀቺኮ ለጃፓናውያን ብሎም ለመላው አለም ስሙ ከመቃብር በላይ የዋለለት ታማኝ ውሻ ሆነ። ሀቺ ለሚልዮኖች ገደብ የሌለው ፍቅርና የታማኝነት ትርጉምን፤ በፍቅር መተማመንን ያስተማረ ውሻ ነበር።
በስሙም ብዙ ሆቴሎች፣ ካፌዎች፣ ጎዳናዎችና ሙዚየሞች ተሰይመውለታል፤ እግር ጥሏችሁ ወደቶኪዮ ብታቀኑ በዛው ባቡር ጣቢያው ላይ ይህ የምትመለከቱት ሀውልት ቆሞለት እስካሁን በቱሪስት መስህብነት ይጎበኛል።
ለዚህ ታማኝ እና አስደናቂ ውሻ በ2009 'Hachi: a dogs tale' የሚል ሪቻርድ ጌር የተወነበት ልብ አንጠልጣይ ድንቅ ፊልምም ድንቅ ፊልምም ተሰርቶለታል።
ምንጭ- ከመፅሃፍ ዓለም book shelf
ከወደዳችሁት ለወዳጅዎ ያጋሩ @snetsehuf
➤በቤርሙዳ ትሪያንግል አካባቢ ገብተው ከመሰወራቸው በፊት ፓይለቶች እና ካፒቴኖች የመጨረሻ ቃላቸውን በዝርዝር እንመልከት
➤አንዳንዶቹ የተናገሩት በጣም ሚያስደነግጥ ነው። በዛ ሰአት ምንድን ነው ያዩት ?
➤ታህሳስ 15 1945 ከጠፉት 19 አውሮፕላኖች ውስጥ አብራሪዎቹ ለመጨረሻ ጊዜ ቃላቶቻቸው የሚከተሉት ናቸው። እና እነዚ የመጨረሻ ቃላቶቻቸው record ተደርጎ ተቀምጧል።
➤የመጀመሪያው ጥሪ
"ሄሎ ይሄ አስቸኳይ ጥሪ ነው። መሬት አይታየንም , ከበረራ መስመራችን የወጣን ይመስለኛል።"
➤ሁለተኛው ጥሪ
"ያለንበት ቦታ የት እንደሆነ እርግጠኞች አይደለንም። መንገዱ የጠፋን ይመስላል።"
➤ሶስተኛው ጥሪ
" ምእራብ በየትኛው አቅጣጫ እንደሆነ አናውቅም። ሁሉም ነገር ትክክል አይደለም ይገርማል።" ብሎ ተቋርጧል ጥሪው
➤አራተኛው ጥሪ
"ውቅያኖሱ የተለመደ መልኩን አልያዘም።" ብሎ የዚኛውም ጥሪ ተቋርጧል።
➤አምስተኛው ጥሪ
"እኔን ተከትላቹ አትምጡ። ከሌላ አለም የመጡ ይመስላሉ። ብሎ የዚኛውም ጥሪ ተቋርጣል።
➤ ስድስተኛው ጥሪ
"ወደ ነጭ ውሀ እየገባን ነው , መንገድ ስተናል በጣም ሀይለኛ ንፋስ አለ።" ብሎ የዚም ተቋርጧል።
➤ሰባተኛው ጥሪ
"ነገሮች እየተቀያየሩ ነው አቅጣጫ ጠቋሚው ኮምፓስ በፍጥነት ይሽከረከራል። እንደዚ ሆኖ አይቼው አላቅም። ሞተሩም ፣ electric system ሁሉም ነገር ቀጥ ብሏል። ሰማዩና ውቅያንሱ የተላጠፉ ይመስላሉ። ሰማዩ እና ውቅያንሱ የት እንደሚጀምሩ እና እንደሚያቁ አይታወቅም። ውቅያንስም ሆነ ሰማይ የሌለ አይነት ነገር ሆኖ ነው ሚታየው። ወደ ታች ስመለከት ወተት የመሰለ ጭጋግ ነገር ነው ሚታየኝ። መርከቡ በሁለት አቅጣጫ ሲጎተት አይነት እየተሰማን ነው።
➤ከላይ የዘረዘርንላቹ የአውሮፕላን ፓይለቶች እና የመርከብ ካፒቴኖች የመጨረሻ ቃላቸው ነው። ከ Record ክፍል የተገኙ ናቸው። በዚ ቤርሙዳ አካባቢ ቁጥር ስፍር የሌላቸው መርከቦች እና ፓይለቶች ገብተው ተሰውረዋል። ሌላው ሳይቀር ተከስክሰው ነው ተብሎ እንኳን ቢታሰብ ስብርባሪያቸው እንኳን አይገኝም። ሳይንቲስቶች በዚህ አካባቢ ሚያልፉትን መርከቦች እና አውሮፕላኖች time traveler እያረጋቸው ነው ሚሰወሩት ይላሉ።
➤ነገሩን አስደንጋጭ ሚያደርገው ቤርሙዳ ትሪያንግል ገብተው ያመለጡ ሰዎች ምን እንዳጋጠማቸው እና ምን እንዳዩ ተጠይቀው ምንም አናውቅም ማለታቸው ነው። አንዳንድ ያመለጡት ሰዎች ግን አሁን ላይ ትንሽ እየተናገሩ ነው። አንድ አውሮፕላን አብራሪ ከቤርሙዳ ገብቶ የተረፈ ደሞ የተናገረው " ምንም ነገር አይታየኝም ነበር። እጅግ ከፍተኛ ሚንቦገቦግ ብርሀን ነበር። ሁሉም ነገር ነጭ ሆኖ ነበር ሚታየኝ, ሞተሩም ሁሉም ነገር ለአምስት ደቂቃ ቀጥ ብሎ ነበር። ከዛ በሗላ ግን ወደ ቀድሞ ተመለስኩ እና በፍጥነት ከዚህ አካባቢ እያበረርኩ ወጣው" ብሏል።
➤ሳይንቲስቶች እስካሁን የቤርሙዳ ሚስጥር ምን እንደሆነ ሊገባቸው አልቻለም። በተለይ ከላይ እንደፃፍነው አምስተኛው ጥሪ ላይ አንዱ ፓይለት እንዳለው "እኔን ተከትላቹ አትምጡ ከሌላ አለም የመጡ ይመስላሉ" ያለው, ሳይንቲስቶች እንደሚሉት ይሄ አብራሪ በዛ ሰአት በእርግጠኝነት Aliens ወይም ባእድ ፍጡራን እየተከተሉት እንደነበር እና አግተው ወስደውትም እንደሆነ ደምድመዋል። እና እኛ የሰው ልጆች ከእነዚህ ባእድ ፍጡራን በእጅጉ በ technology ወደ ሗላ የቀረን እንደሆንን ይናገራሉ። እና ሳይንቲስቶች እንደሚሉት እነዚ Aliens ከኛ ከሰው ልጆች በ technology በብዙ እጥፍ የተራቀቁ እንዳሉ። ➤
#እውነት እና #ውሸት
እውነት እና ውሸት አንድ ቀን ተገናኙ። እናም ውሸት እውነትን እንዲህ አለው "የዛሬው ቀን ግሩም ድንቅ ነው።" እውነትም ሽቅብ አንጋጦ ሰማዩን ተመለከተና "ኣህ" ብሎ ትንፋሽ ካስወጣ ቦሀላ "በርግጥም የሚያምር ቀን ነው" ሲል አደነቀ።
አብረው ጥሩ ጊዜ እያሳለፉ እየተዝናኑ ሲጓዙም ወደ አንድ የጉድጓድ ምንጭ ውሀ ዳርቻ ደረሱ። ውሸትም ለእውነት የውሀውን ጥሩነት ከነገረው ቦሀላ በጋራ እንዲተጣጠብ ጋበዘው እውነት ግን ጥርጣሬ ቢያድርበትም ገብቶ በመሞከር የውሀውን ጥሩነት ለማረጋገጥ ፈለገ።
እናም እውነት እና ውሸት ልብሳቸውን አወላልቀው ከውሀ ውስጥ ገብተው እየተጣጠብ እያለ ድንገት ውሸት ከውሀው በመውጣት የእውነትን ልብስ ለብሶ ከአካባቢው በጣም ራቀ።በሁኔታው የተናደደው እውነት ከውሀው በመውጣት ውሸትን ፍለጎ ልብሱን ለማስመለስ ባገኘው አቅጣጫ መሮጥ ጀመረ። አለም የተራቆተውን እውነት በንቀት እና በተቆጣ መንፈስ ያፈጥበት ጀመረ።
ምስኪኑም እውነትም በፍርሀት ወደ ጉድጓድ ተመልሶ እራሱን በመደበቅ ተሰወረ። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ውሸት የእውነት የቀናና ያማረ አለባበስ ተላብሳ የማህበረሰብ ፍላጎትና መውደድ ልታሟላ በአለም ዳርቻ ትመላለሳለች።
ምክንያቱም በማናቸውም ሁናቴና ምክንያት አለም እራቆቱን የተጋለጠውን እውነት ማየትም ሆነ ማግኘትን አይፈልግምሃዋርድ ጋርደነር የተባለ የሥነ-አእምሮ ሊቅና ፈላስፋ «መጥፎ ሰው ጥሩ ባለሙያ ሊሆን አይችልም፤ መጥፎ ባለሙያም ጥሩ ሰው ሊሆን አይችልም።» በማለት እንደጻፈ አንብቤያለሁ።
እውነት ነው። የተዋጣለት ባለሙያነትን የሚሸከመው የተስተካከለ ሰብዕና ይፈልጋል። ሰይፍና ሰገባ፣ ጎራዴና አፎት፣ ዳዊትና ማኅደር፣ ፅላትና ታቦት፣ ነፍስና ሥጋ ናቸው። ሙያና ተግባር የሌለው ጥሩ የሚባል ሰው "ጅል" እንጂ ሌላ ሊሆን አይችልም።
በሌላ በኩል ብዙ የሚያውቅ፣ ብዙ የተማረ፣ በሙያው የተካነ ቢመስልም ክፉ ሰው ከሆነ ሙያውን አንድም ለግል ጥቅም ማካበቻ፣ ለርካሽ ተወዳጅነት ማፍሪያ፣ አለዚያም ለሰው ልጅ መጥፊያ አውሎት መጨረሻ ክፋቱ ሲገለጥ ሙያውን ያረክሰው እንደሆን እንጂ አያኮራውም። የመርዝ ጋዝ የተሠራው ክፉ ሰብዕና ባላቸው "ጥሩ" ባለሙያዎች ነበር።
ክፉ ሰው መልካም ተግባር ሊወጣው አይችልም። መልካም ተግባር የሚመነጨው ከበጎ ሕሊናና ከንፁሕ ልብ ብቻ ነው። እርግጥ በጎ ሐሳብ ያመነጨ ሁሉ ወደ ተግባር ላይቀየር ይችላል። ነገር ግን የበጎ ተግባር ምንጩ በጎ ሐሳብና ቅን ልብ ናት። ከኩርንችት በለስ፣ ከበለስም ኩርንችት አይለቀምምና።
«የሀገራችን የትምህርት ሥርዓት ትልቁ ድክመቱ መልካም ሰብዕና ሳይቀርፅ ጥሩ ባለሙያ ለማፍራት ማሰቡ ነው። እናም ብዙ ባለዲግሪዎች፣ ብዙ ባለ ሰርተፍኬቶች ብናፈራም በተግባር ከማይምነት አልወጣንም።
ሰይፉን እንጂ ሰገባውን፣ ጎራዴውን እንጂ አፎቱን አላዘጋጀንም። ያለአፎት የተሳለው ጎራዴ ያገኘውን ሁሉ ሸረካከተና ብዙ ሳይቆይ ዶለዶመ። ዳግም እንዳይሞረድም ደንደስ አውጥቶ ቁጭ አለ። ነፍስ ሠርተን ሥጋ አልነበረውምና ተንሳፎ መሬት ሣይነካ ሰው ሳይሆን መንፈስ ሆኖ ቀረ።» ይለኝ ነበር ዶ/ር ክብረ በዓል።
━━━
📖 117 - 118
⛴⛴⛴
@snetsehuf
📍ብርሃን ከፀሐይ ተነስቶ ማርስ ከደረሰ በኃላ አንፀባርቆ ወደ ምድር ይመጣና አይናችን ውስጥ ይገባል።
📍አይናችን ወደ አይምሮ ይልከዋላ ይሄንን ብርሃን አይምሯችን ደግሞ ወደ ምስል ይቀይረዋል ከዛም አየን እንላለን። የሰው ልጆች ሆነ አብዛኛዎቹ እንስሳት ማየት የሚችሉት ብርሃን ሲኖር ብቻ ነው።
#ሁሉም በአይናችን የሚታዩ ነገሮች በሙሉ ከፀሐይ የመጣው ብርሃን እነሱ ላይ አርፎባቸው ወይም አንፀባርቆ ወደ አይናችን ሲሄድ ብቻ ነው ወይም ሰው ሰራሽ ብርሃን #ለምሳሌ ባትሪ መብራት ወዘተ እቃዎች ላይ አንፀባርቆ ወደ አይናችን ሲገባ ብቻ ነው።
📍በዚህ የተነሳ የሰው ልጆች እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ብላክ ኦልን (#Black hole) ማየት አልቻሉም ነበር። ይሄም የሆነው ብላክ ኦል ብርሃንን አንፀባርቆ እንዲሄድ ከማድረገ ይልቅ ውጦ ማስቀረቱ ነው። 🫧የሰው ልጅ የብላክ ኦል መአከላዊ ቦታ (#Center area) ማየት ያልቻለው ለምን ይሆን? 🤔 #ምክንያት...?! ሀሳቡን ከወደዱት ሼር ይደረግ!!
#3 ፓውሎ ኩዌሎ
ክዌሎ … አሁን እድሜው 30ዎቹን ተሻግሯል፡፡ የተጫነው ፍርሃት ተገፍፎ የድሮ እሱነቱ ቢመለስም ግን፣ አሁንም ውስጥ ውስጡን የሚበላው … ያ የወጣትነት ደራሲ የመሆን ህልሙ … የተዳፈነ መሻቱ እረፍት አልሰጥህ አለው …!! አዎን … የክዌሎ የምንጊዜም ሕልሙ ደራሲ መሆን ነው፡፡ምንም እንኳ በዘፈን ግጥም ፀሐፊነቱ ዝናን ቢያገኝም፣ በቂ ገንዘብ ባያጣም፣ ይህ ለታዋቂ ብራዚላውያን ድምጻዊያን የሚፅፈው የዘፈን ግጥም ግን ፈፅሞ የደራሲነት ጥሙን አያረካም! ለክዌሎ የዘፈን ግጥም መፃፉ ደራሲነት ካለመሆኑም በላይ እንዲያውም ሙሉ ለሙሉ ወደ ድርሰቱ ዓለም እንዳልገባ እንቅፋት የሆነኝ እሱነው ብሎ ደምድሟል፡፡እና ከዚህ አጣብቂኝ የመውጫው መንገድ ምን ይሆን ?ክዌሎ ይሄን ወቅት አስታውሶ ሲናገር፣ “በቂ ገንዘብ ነበረኝ፡፡ የምወዳት ሴት ከጎኔ አለች፡፡ ደስተኛ ነኝ፡፡ ቢሆንም ግን አንድ የጎደለኝ ነገር እንዳለ ይሰማኛል፡፡ ደራሲ መሆን እፈልጋለሁ፡፡ በዚህ አቅጣጫ ግን አንዲትም መስመር ፅፌ አላውቅም፡፡ 38 ዓመቴ ነው፡፡ ከዚህ በኋላ ሕልሜን መከተል ምን ዋጋ አለው ? እያልኩ እብሰለሰል ነበር” ይላል፡፡እንዲህ በሀሳብ በሚናጥበት ወቅት በአንድ የአምስተርዳም ካፌ ውስጥ ያገኘው አንድ ሚስጥራዊ ሰው ግን የክዌሎን ሕይወት ሙሉ ለሙሉ ቀየረው፡፡ ክዌሎ መምህሬ እና አቅጣጫ ጠቋሚዬ ነው የሚለው ይህ እንግዳ ሰው ክዌሎን ከፈረንሳይ ተነስቶ ስፔን የሚዘልቀውንና 700 ኪሎሜትሮች የሚረዝመውን ሳንቲያጎ ዲ ኮምፖስቴላ የተባለውን መንፈሳዊ ጉዞ እንዲያደርግ ነገረው፡፡ ክዌሎ በዚህ መንፈሳዊ ጉዞ ወቅት አንዳች ነገር ተገለጠልኝ ይላል፡፡ ከጉዞው በኋላ ክዌሎ ጥሩ ገቢ የሚያገኝበትን በሙዚቃ ኢንደስትሪው ውስጥ ያለውን ሥራውን ርግፍ አድርጎ ትቶ ሙሉ ጊዜውን በድርሰት ሥራው ላይ ለማዋል ወሰነ፡፡እናም ሥራውን ለቅቆ ወጣ፡፡
@snetsehuf
