en
Feedback
አጫጭር ግጥሞችና መጣጥፎች 📚

አጫጭር ግጥሞችና መጣጥፎች 📚

Open in Telegram

✔️📚ማንበብ ያሻግራል ❗️❗️❗️ በዚህ ቻናል እናንተን የሚመጥኑ የተለያዩ ግጥሞችን ፣ አጫጭር ና መሳጭ ታሪኮችን ታገኛላችሁ። እናንብብ ፤ በማንበባችን እናተርፋለን እንጂ ፤ ከቶ አንከስርም። @snetsehuf

Show more
546
Subscribers
+324 hours
+127 days
+5230 days
Posts Archive
ምድረበዳ ሌሊት (በእውቀቱ ስዩም) ስንት ዘመን ሆነ? ጥላሁን ገሰሰ “በምሽት ጨረቃ” ብሎ ከዘፈነ? አንዳንዴ ሳስበው፥ በጥላሁን ዘመን፥ ልክ እንደ አባት እቅፍ፥ ሌሊቱ ሲታመን ባውሬ በቀማኛ በሮንድ ፥በዘበኛ ላፍታ ሳይሸበር ፍቅር በፈቃዱ፥ ውጭ አዳሪ ነበር:: ዘመን ተቀይሮ ፥ እንኳን በሌት፥ በቀን ፍርሀት ሲሰፈን ማነው ዛሬ ደፍሮ “ በምሽት ጨረቃ?” ብሎ የሚዘፍን? ያስፈራል መንገዱ ያስፈራል፥ አጸዱ ያስፈራል አልፎሂያጅ ያስፈራል ጎረቤት የሁሉም ሰው መርህ-በጊዜ ወደ ቤት! ወትሮ እያባረረው፥ እየገፈተረው ሀቁና ፈጠራው፥ ባንድ ላይ አድሞ ወደ ቤቱ ገባ፥ ሰው ከጀንበር ቀድሞ ደጁ ተቆለፈ በሰአት እላፊ የታጠረ ትውልድ የሌሊቱን ውበት፤ ሳይቀምሰው አለፈ:: በሰዎች ልብ ውስጥ፤ ዜማ መቀስቀሷ ባፍለኞች ልብ ውስጥ፥ ፍቅር መጸነሷ እያፍለቀለቃት እስክታስለቅቃት ከቦታዋ ደርሳ፥ የማለዳ ጀንበር ጨረቃ ሰማይ ላይ ትንሰራፋ ነበር:: ዛሬ ሰው ቸግሯት ብቸኝነት ገርፏት መሪር እያነባች ዘግይታ፥ ብቅ ብላ፥ ያለጊዜ ገባች:: @snetsehuf

በመንገዳችን ላይ (በእውቀቱ ስዩም) በዚያ ሰሞን፥ በቦሌ መድሀኒያለም ጀርባ የተሰመረችውን ጎዳና ይዤ በእግሬ እወዘወዛለሁ፤ ብዙ ሳልርቅ፥ የእግረኞች መንገድ ላይ ሶስት የጎዳና አዳሪዎች ጎንለጎን ተደርድረው በጀርባቸው ተንዘራግተው እንቅልፍ ወስዷቸው ተመለከትኩ፤ አንድ በእድሜና በአካል የሚልቅ ብጢያቸው አጠገባቸው ቁጭ ብሏል፤ ሌላ አንድ ጎረምሳ ከ “ጽጌ” ሽሮ አቅጣጫ አንድ ፌስታል ሙሉ ፍርፋሪ ይዞ ደረሰ፤ ቁጢጥ ብሎ የፌስታሉን አፍ ለመክፈት ሲቃጣ ጠና ያለው ልጅ ወደ ተኙት ብላቴኖች በአገጩ እየጠቆመ እንዲህ ሲል አዘዘው፤ “ መጀመርያ እነሱን ቀስቅሳቸው !“ ደነቀኝ! ለምን ደነቀኝ? ሞልቶ ተርፎት ከማካፈል መድፋት የሚመርጥ ብዙ ሰው ያለበት አለም ውስጥ ነው እምንኖረው፤ ብዙዎቻችን በዚህ ጎረምሳ ቦታ ብንሆን ምንድነው የምናረገው? ነቅተው ሳይሻሙን እንበላ እንደምንል እገምታለሁ፤ ያንዳንድን ሰው ቸርነት እጦት እና ድሀነት አያከስመውም፤ በኔ ግምት ጠና ያለው ጎዳና አዳሪ ያንን ያደረገው ለታይታ አይደለም፤ የቲክቶክ ካሜራ እንዳላነጣጠረበት ያውቃል፤ ከተኙት ልጆች ደቃቃነት አንጻር ወጠምሻ እሚባል አይነት ነው፤ እና ብቻውን ቢበላ ፥ ቀጭም ሆነ ተቆጭ ያለበት አይመስልም፤ እንደመታደል ሆኖ፥ በመናመን ላይ ያለው የሰው ልጅ ህሊና እዚህ ልጅ ላይ ጨርሶ አልጠፋም፤ እንዲህ አይነቱ ትእይንት በሰው ልጅ ተስፋ እንዳትቆርጪ ያደርግሻል:: በአለማችን ሩህሩህ ሰዎች ብርቅ ናቸው፤ ርህራሄም ደረጃ አለው፤ ብዙ ሰው ፥ ለራሱ እና ለቤተሰቦቹ ብቻ ይራራል፤ ያንዳንዱ ሰው ደግነት ደግሞ ለጎረቤቱ ለወዳጆቹ ለዘመዶቹ ብቻ ተወስኖ ይቀራል ፤ ከሁሉ የላቀ መንፈስ ያላቸው ጥቂት ሰዎች ፥ ለሰው ዝርያ ብቻ ሳይሆን ለአራዊት አዋፋት ለነፍሳት ሳይቀር ቸርነታቸውን ያሳያሉ:: ሰዎች ሆድ የሚባል ጉድ የተገጠመልን ፍጡሮቸ ነን፤ ቢቸግረን ዶሮ ፥ በግ ፍየል በሬ አርደን እንበላለን፤ ግን ሳይቸግረን በእብሪት ወይም በግዴለሽነት ተነሳስተን የምናደርገው ጭካኔስ ምን ይባላል? ባለፈው እዚህ አክሱም ሆቴል ፊትለፊት ባለው መንገድ ላይ አንዱ አህያ እየነዳ ይሄዳል፤ አህያዋ በፍጥነት ትራመዳለች፤ ነጂው ግን በጎማ ዱላ እያከታተለ ይወግራታል፤ ለግማበት ነው እንዳልል በምትችለው አቅም እየተጣደፈች ነው፥ ሰውየው ከጭካኔ የተሻለ መዝናኛ ያለው አይመስልም፤ ወይም ደሀነቱ የፈጠረበትን ብስጭት እሚወጣው አገልጋዩን በመደብደብ ይሆናል፤ እስቲ ወደ ባለቤት አልባ ውሾች ተመልከቱ! አንድ አይኑ ያልጠፋ፥ ወይም እግሩ ያልተቀለጠመ ውሻ ማግኘት ይከብዳል! ከሩቅ ምስራቃውያን የመነጨ አንድ ፍልስፍና ሀሳብ እንዲህ ይላል፤ እኛ ሰዎች በዚህ አለም መኖር የምንፈልገውን ያህል አራዊት አእዋፍ እና ነፍሳት መኖር ይፈልጋሉ፤ ስለዚህ ሌሎች ፍጡራን ያንተ ብጤ ናቸው፥ ባንተ ልክ ተንከባከባቸው! ጋዜጠኛ ገነት አየለ ሸጋ አድርጋ፥ የተረጎመችውን የሚካኤል ዳባዲ ማስታወሻ ሳነብ ያገኘሁት አንድ ውብ አንቀጽ የድብርት መዳኒት ነው፤ ላጋራውና ልሰናበት፤ ደአባዲ የተባለ የፈረንሳይ አሳሽ የዛሬ ሁለት መቶ አመት ገደማ ጎጃም ሳርምድር ውስጥ አደን ለማደን ይሰማራል፤ ድንገት በለስ ቀንቶት አንድ አጋዘን ያይና አነጣጥሮ ሊኩስበት ሲዘጋጅ፥ በከፊል የተራቆተ ሰውየ ብቅ ይልና ተኩሱን ያደናቅፍበታል ፤ሰውየው በዳባዲ አጃቢዎች ተይዞ ሲመጣ በበረሀ የሚኖር ባህታዊ መሆኑ ይገለጣል፤ ባህታዊው አደኑን በማደናቀፉ ይቅርታ ከጠየቀ በሁዋላ እንዲህ አለ፤ “ይህ አጋዘን የከፋው(የተከፋ) እንስሳ ነው፤ በአቅራቢያ እያገሱ ያሉት ብዙ አንበሶች በጣም ያስጨንቁት ነበረ፤ ለኔ እንደ ባለንጀራየ ነው፤ አንዳንዴ በበረሀ አቁዋርጨ ስጓዝ ቀኑን ሙሉ እየተከተለኝ አብሮኝ ይሄዳል፤ አሁን በኔ ምክንያት ህይወቱ ድኖ ከሆነ ደስ ይለኛል “ @snetsehuf

አላፊ ወግ (በእውቀቱ ስዩም) ትናንት ለምኡዝ ደወልኩለትና “ ለ” እናቶች ቀን “ ምን ለማድረግ አቅደሀል?” አልኩት:: “የሶስት ልጆች እናት የሆነች ደርባባ ሴትዮ በመጀንጀን ለማሳለፍ አስቢያለሁ፤ ለጅንጀናው ማስኬጂያ ደግሞ ከ” እናት ባንክ” የተወሰነ ብር ማውጣት ይኖርብኛል” “አሰለፈች ፥ ባር” ገብተን እኔ የተልባ ጭማቂ እየጠጣሁ እሱ “ዘገሊላ” የተሰኘ ወይን እየጠጣ ስለ ሂሩት በቀለ ተነሳ:: ከዚያ እንዲህ አለ፤ “ ሂሩት በአለማዊ ህይወት ነበረችበት ጊዜ ውብ፥ ጆሮ- ገብ የፍቅር ዘፈኖች ዘፍናለች፤ ሞቷን ተከትሎ በየሚድያው እየተደጋገመ ያዛገን ዘፈን ግን “ ሕይወት እንደሸክላ" የተባለው ድብርት እሚለቅ ዘፈን ነው፤ ግጥሙ ምን ነበር የሚለው? እ! አዎ...እ... ..እድሜ መገስገሱን ከንቱ ሰው ዘንግቶት ነገ አልፎልኝ ይላል ፤ ማለፉን ረስቶት አይቀር መንፈራገጥ፥ ያው ሆድ እስኪሞላ. ወድቆ እስከሚሰበር ፥ ሕይወት እንደ ሸክላ.. ! ህም ! “ አለና በማሽሟጠጥ አይነት ከንፈሩን ጠመዘዘ:: “ ምንድነው ችግሩ? “ አልኩት:: ችግሩማ፥ ሰው በዚህ ምድር ላይ ለጥቂት ዘመን መኖሩ ሕይወቱን “ ከንቱ “ አያደርገውም፤ በጥቂት ዘመኑ ለራሱና ለወገኑ ብዙ ስራ ሊሰራ ይችላል፤ ተደስቶ ያስደስታል፤ አገር ያቀናል፤ ያፈቅራል፤ ይመራመራል፤ ይፈጥራል፤ ችግሩ እንዲያልፍለት ተስፋ ማድረጉና ለማሳለፍ መፍጨርጨሩ ሰው አይበገሬ እንጂ ምስኪን ፍጡር እንዳልሆነ የሚያሳይ ነው፤ የኢትዮጵያ ባለቅኔ የተረገመ ስለሆነ የኑሮ ውብ ገጽታ አይከስትለትም! ህይወትን በመቀደስ ፈንታ እንደ ጉድፍ ያራክሳታል፤ ህይወት አላፊ ነው ፤ ውበት እረጋፊ ነው እያሉ ይነዘንዙናል፤ ውበት መርገፉ አደለም ጉዳዩ፤ ከመገርገፉ በፊት የታደሉ ሰዎች የደስታ ምንጭ ሆኗል! ያገሬ ከያኒ ችስታ ስለሆነ ሀብትን ይራገማል፤ ሀብት በጥረት እና ባግባቡ ካገኘኸው በጎ ነው! በነገራችን ላይ በጥረት የተገኘ ገንዘብ ጥሪት ይባላል! ያንተንም ሆነ የወገንህን አላስፈላጊ ስቃይ ይቀንሳል! “ ‘ ተከትሎ አይሄደም ሀብት የስጋ ዘመድ “ ይባልልኛል ደግሞ! who cares! ሲጀመር ፥ ሀብት የሚፈጠረው ህይወትን ለማገልገል ነው፤ ግን እውነት ለመናገር ሀብት ሞትንም መሻገር ይችላል! በልምላሜ ያሸበረቁ ውብ የመቃብር አጸዶችን መገንባት የሚቻለው በሀብት አይደለም ወይ? ያማረ የመቃብር ቦታ ደግሞ የተከበረ ሕይወት አንድ ቅጥያ ሆኖ ሊታይ ይችላል፤ ባጭሩ፤ ለኔ ህይወትን እንደ ሸክላ የሚቆጥሩ ሰዎች የህይወትን ጣእም እና ዋጋ አያውቁም!” “ አንተ በሂሩት በቀለ ቦታ ብትሆን ኖሮ ምን ብለህ ነበር የምትዘፍነው”? ብየ ጠየቅሁት:: “ ሕይወት እንደ ሸክላ ጥብስ! “ @snetsehuf

ያልተነገሩ የሀዲስ ዓለማየሁ ታሪኮች በእሱባለው አማረ ___ ሀዲስ ዓለማየሁ ዘመናዊ ትምህርት የመማር ፍላጎት አልነበራቸውም፡፡ ከብዙ ማባበልና ልመና በኋላ ስዊዲን ሚስዮን ትምህርት ቤት ገቡ፡፡ የአስኳላ ትምህርት ላለመማር ያቀረቡት ምክንያት፤ ‘የፈረንጅ ትምህርት ሃይማኖት ያስለውጣል’ የሚል ነበር፡፡ * ሀዲስ ዓለማየሁ “እንኳን ቀምሰነው ሥሙን እንኳን ሰምተነው የማናውቀው ነገር” ሲሉ የገለፁትን ሻይ ለመጀመሪያ ጊዜ የቀመሱት የ16 ዓመት ታዳጊ ሳሉ ነበር፡፡ * ሀዲስ የሲዊድን ሚሲዮን ትምህርት ቤት ተማሪ በነበሩበት ጊዜ፣ በጥቂት የእንግሊዝኛ ቴአትሮች ላይ ተዋናይ በመሆን ሠርተዋል፡፡ * ደብረማርቆስ በአስተማሪነት ተቀጥረው በሚሠሩበት ወቅት ጣሊያን ኢትዮጵያን ወረረች፡፡ ጠመኔያቸው ጥለው ጠበንጃ አነሱ፡፡ የዘመቻ ጠበንጃ ከመንግሥት አልተቀበሉም፡፡ ራሳቸው ጠበንጃ ገዝተው ዘመቱ እንጂ! በራሳቸው አንደበት፤ “ጎጃም የመንግሥት ትምህርት ቤት አስተምሬያለሁ፡፡ መጀመሪያ ዳንግላ ከዚያ ደብረ ማርቆስ፡፡ ደብረ ማርቆስ አስተማሪ ሳለሁ ጣሊያን ኢትዮጵያን ወረረች፡፡ እኔም ማስተማሬን ትቼ፣ ጠበንጃ ገዝቼ ዘመትኩ፡፡” * ‹‹ፍቅር እስከ መቃብር›› ሃያ ዓመታት የፈጀ መጻሕፍ ነው፡፡ መጀመሪያ በእንግሊዝኛ ነበር የተጻፈው፡፡ እንግሊዝ ሀገር ለሚገኝ ማተሚያ ቤት ሰጥተውትም ነበር፡፡ ሕትመቱ ሲዘገይባቸው በአማርኛ ጽፈው አሳተሙት፡፡ * ሀዲስ ዓለማየሁ ከሚያደንቋቸውና ከሚወዷቸው መጻሕፍት መካከል የከበደ ሚካኤል ‹‹ከይቅርታ በላይ›› የተሰኘው የትርጉም መጻሕፍ የመጀመሪያው ነበር፡፡ * ሀዲስ ለመጀመሪያ ጊዜ በሥራ ምክንያት ከኢትዮጵያ ውጭ የኖሩት ኢየሩሳሌም ነበር፡፡ በኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ቆንስል ሆነው ለሁለት ዓመታት አገልግለዋል፡፡ ከባለቤታቸው ወይዘሮ ክበበፀሐይ በላይ ጋር ተዋውቀው ለጋብቻ የበቁት በዚህ ወቅት ነበር፡፡ በጊዜው ወይዘሮ ክበበፀሐይ ከአያታቸው ጋር ኢየሩሳሌም ይኖሩ ነበር፡፡ ከ15 ዓመት የትዳር ሕይወት በኋላ አሜሪካ፣ ኒውዮርክ በህክምና ላይ እንዳሉ አረፉ፡፡ ሀዲስ ዓለማየሁ ከዚህ በኋላ እስከ ሕይወት ፍጻሜያቸው ድረስ ሌላ ሚስት አላገቡም፡፡ ከባለቤታቸው ሞት በኋላ ሌላ ሚስት ለምን እንዳላገቡ በአንድ ወቅት ተጠይቀው ነበር፡፡ የሰጡት መልስ፡- “ይሄንን ንስሀ አባት ስትሆን ጠይቀኝ” የሚል ነበር፡፡ * ከባለቤታቸው ሞት በኋላ መኖሪያ ቤታቸውን የሕጻናት ማሰደጊያ እንዲሆን አድርገዋል፡፡ ቀጨኔ መድኃኔዓለም አካባቢ “ክበበፀሐይ የሕጻናት ማሳደጊያ” በሚል መጠሪያ ተሠይሞ፣ አያሌ ወላጆቻቸውን በሞት የተነጠቁ ሕጻናት አድገውበታል፡፡ * ሀዲስ ዓለማየሁ ከቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ጋር ሁለት ጊዜ ተጋጭተዋል፡፡ የትምህርት ሚኒስቴር በነበሩበት ጊዜ የአፍሪካ የትምህርት ሚኒስቴሮች ስብሰባ ይደረጋል፡፡ ጉባኤው መሃይምነትን በሃያ ዓመት ውስጥ ከአፍሪካ ምድር ለማስወጣት ያቅዳል፡፡ ሀዲስ በጉባኤው ዕቅድ ተስማሙ፡፡ በትምህርት ሚኒስቴር የነበረው ባጀት እጅግ አነስተኛ ስለነበር፣ የተጨማሪ ባጀት ጥያቄ አቀረቡ፡፡ የተሰጣቸው መልስ አስገራሚ ነበር፤ “የገንዘብ እጥረት በመኖሩ ከትምህርት ሚኒስተር ባጀት እሩቡ ይቆረጥ፡፡” ሀዲስ በተሰጣቸው ምላሽ ተቆጡ፡፡ ሥልጣናቸውን በገዛ ፈቃዳቸው ለቀቁ፡፡ የእነ መንግሥቱ ንዋይ የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ በተደረገበት ወቅት፣ የሀዲስ ዓለማየሁ ጓደኞች ያለጥፋታቸው በሙከራው ተጠርጥረው ታሰሩ፡፡ ሀዲስ ስለ ጉዳዩ 13 ገፅ ልዩ ማስታወሻ ጽፈው ለጃንሆይ ሰጧቸው፡፡ ጃንሆይ ልዩ ማስታወሻውን አነበቡት፡፡ ጃንሆይ የግስላን ያህል ተቆጡ! በልዩ ማስታወሻው የተካተተች ‹‹ከንቱ ውዳሴ›› የምትል ሀረግ ጃንሆይን ጭራ አስበቀለቻቸው! ሀዲስ ቤተ-መንግሥት ተጠሩ፡፡ ጃንሆይ በአንዲት ቃል ተቀበሏቸው፤ “ሰደብከን!”፡፡ ጽሑፉን አርመው እንዲያመጡ ጃንሆይ አዘዙ፡፡ ሀዲስ ይህንን ተናግረው ከቤተ-መንግሥቱ ወጡ፤ “ምንም የማርመው የለኝም”፡፡ * ሀዲስ ዓለማየሁ ጥቅምት 10 ቀን 1992 ዓ.ም እንዲህ ብለው ነበር፡- “ደርግ ሥልጣን ሲይዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ሁን ተባልኩ፡፡ ለውጥ ለውጥ ይባላል ለውጡ ምን ልታመጡ ነው? ስላቸው ዝርዝሩን በኋላ እናመጣለን አሉኝ፡፡ እኔ ላምጣና ቁጭ ብለን እንስማማበት ስላቸው አይሆንም አሉ፡፡ እንግዲያውስ እኔም አይሆንም አልኩ፡፡” @snetsehuf

#የእምነት_አጥር አንድ ቀን አንድ ወጣት ወደ አንድ አገር ለመሄድ በጉዞላይ ሳለምሽት አሸነፈውና በጅብ ከመበላት ብሎ ከፊት ለፊቱ የምትታየው ትንሽ መንደር አመራ ከመንደሩ ደርሶ "የመሸብኝእንግዳ ነኝ አሳድሩኝ?" ሲል ይማፀናል ። የቤቱን ባለቤት ደግሰውና እንግዳ ተቀባይ ነበርና "ይግቡ" በማለት እንግዳውን ወደ ጠባብ እልፍኙ ይጋብዘዋል ። ወጣቱም ወደ ቤት ገብቶ ትንሽ እንዳረፈ ለእግሩ ውሀ ተሰጥቶት ከታጠበ ብኋላ እራት ይቀርብለትና ይበላል ። ; የቤቱ ጌታ ለወጣቱ ልጅ መኝታ ሲያስብ የመኝታ ቦታ ስለሌለ ትንሽ ጊዜ ያስብና አንድ ሀሳብ ይመጣለታል ። ይህም ሃሳብ ሌላ አማራጭ ስለሌለው ከልጃገረድ ልጁ ጋር እንዲተኛ ይወስናል ። "እንግዳው ልጄ እዚህ አልጋ ላይ ከልጄ ጋር ተኛ" ይለውና አልጋውን ሁለት ቦታ በትራስ ይከፋፍልና ያስተኛዋል ። እንግዳው ልጅም በተመደበለት ቦታ አንድ ጊዜ እንኳንሳይንቀሳቀስ ለሊቱ ነጋ ። ጠዋት ቁርስ በልቶ ከቤት ተሰናብቶ መንገዱን ሲቀጥል ማታ አብሯት የተኛችው ልጅ አበባ ስትኮተኩት በአጥር ያያታትና "እህት መሄዴ ስለሆነ በአጥር ዘልየ ልሰናበትሽ" ሲላት ትሰበራለህ ስትለው "ግድ የለሽም አልሰበርም" ይላታል ። ; ልጅቱም "እህ ማታ ትራስ መዝለል ያቃተህ አሁን እንዴት አጥርልዝለል ትላለህ ?" ትለዋለች • • አንዳንድ ሰዎች አለመቻልና መተውሲደባለቅባቸው አያለሁ ። መተው አለመቻል አይደለም ። ሰው የቻለውን ሁሉ አያደርግም ማድረግ ያለበትን ብቻ ነው ማድረግ ያለበት ። የሚችለው ነገር ቢሆን እንኳ ማድረግ ከሌለበት ይተወዋል ። ያቅተዋልሳይሆን ይተወዋል ብሎ ይመልስላታል ። ★ ምን ለማለት ፈልጌ ነው ያ እንግዳ አክባሪ ሰው ያሰመረው ትራስ የእምነት መስመር ነው ። የመታመን አጥር ነው ። አጥሩ ይርዘምም ይጠር ብቻ ታጥሯል ። ያንን አጥር ማክበር የእምነት ወሰንን አለማለፍ እንጂ አለመቻል አይደለም ። ☞☞ •ሰው መጮህ ስለቻለ ዝም ብሎ አይጮህም ፣ •ሰው መሳቅ ስለቻለ ያለ ምክንያት አይስቅም ፣ •ሰው መልበስ ስለቻለ ያገኜውን አይለብስም . . ለራሱ በተረዳውና ባመነበት መንገድ መስመር ያበጃል ። ካሰመረው መስመር ላለማለፍ የሚችለውንም ይተዋል ማድረግ ስላልቻለ አይደለም መስመር ማለፍ ስላልፈለገ ነው። @snetsehuf

ከታፈንኩ ኋላ ድፍን ሀገር ታሞ ፣ ሀኪም ሲቸግረው "መድሀኒቴ አንቺ ነሽ" ፥ ስል ማንጎራጉረው አንዴ ላስነጠሰሽ ይማርሽ እያልኩኝ ፣ ስጨነቅ የማድረው ሀገር እያነባ ስላንቺ ሳቅ ቅኔ ፣ የምደረድረው ለምን ይመስልሻል? ።።። ከታፈንኩ ኋላ... የማይ የምሰማው ፣ እየሰቀጠጠኝ ዛቻው እንደ በሶ ፣ እየበጠበጠኝ እንደ ባህር ሞገድ ፣ ፍርሀት እየናጠኝ ዝምታን መርጬ ፣ ጨለማ ሲውጠኝ "ጀግና " ያለኝ ሁላ "ፈሪ አረጉት" ብሎ ፣ ውብ ስሜን ሲያጎድፈው ጊዜ እንደ ምዕራብ ሀገሩን በሙሉ ፣ ፅልመት ሲያስታቅፈው "ዐይኖቿ እንደኮከብ ያበራሉ " የሚል ፣ ግጥም የምፅፈው ለምን ይመስልሻል? ።።። ከታፈንኩ ኋላ ሲቃና መከራ ደም እና ደንባራ መቼም የማይለቃት ፣ አንድ ሀገር መውደዴን የሚያውቁ በሙሉ ፣ ሳያውቁልኝ ጉዴን "ዝመት እንጂ" ሲሉኝ ፣ ከፍቶኝ ማኮርፈው ለምን ይመስልሻል ስጋዬና ነፍሴን ፣ መንፈሴን ሚቀፈው? . . . . ከአንቺ ርቄ ብዘምት እኔም ሀገሬም ነን ፣ የምንሸነፈው ።😉😂 ✍ Belay bekle weya

አንቺን እንዲሰጠኝ - ሆንኩኝ አምላክ ለማኝ፤ ጧፍ መባ ገዛሁ - ልሰጠው ከሰማኝ፡፡ አንቺዬ... ፀሎቴን ሳልጨርስ - ብትይ እመጣለሁ፤ እኔ እኮ ሞኝ ነኝ፣ ፈጣሪዬን ትቼ - እጠብቅሻለሁ፡፡ እጠብቅሻለሁ!!! በተገተርኩበት፤ እጠብቅሻለሁ፤ በተፈጠረኩበት፡፡ ጊዜ አይፈራረቅ - አይጮኹም አእዋፍ፤ አንቺን ስጠብቅሽ... ለኮስኩት ጨክኜ - ለስለት እንዲሆን የገዛሁት ጧፍ፡፡ ትመጫለሽ አይደል? (ኤልያስ ሽታሁን) @snetsehuf

👐#አስተማሪ የፍቅር ታሪክ💝 🚶‍♀አንድ ሴት መንገድ ላይ እየሄደች አንድ ልጅ ከኋላዋ ሲሮጥ ሰምታ ዞር አለች "ባንቺ ውስጥ ሴትነት ውበት አለ ወደድኩሽም" አላት 💔    😁ፈገግ ብላ "ከኔ በላይ ቆንጆ እና በሴትነቷም ከኔ የተሻለች ጓደኛዬ ከኋላክ አለች " ስትለው ዞሮ ፈለገ ግን ምንም ሴት አላየም" የታለች?" አላት እሷም #ፈገግ ብላ"ወደኸኝ ቢሆን ኖሮ ሌላ ባልፈለክ ነበር " ብላ መንገዷን ቀጠለች።       👌በአንድ ምክንያት የሚወድህ ሰው በሌላ ምክንያት ይለይሀል ለምን እንደሚወድህ የማያውቀው ግን ሁሌም ቢሆን ይወድሀል💔💓..... መልካም ምሽት🙏

።እቴ። ይስጥሽ ከቁመቴ ከላዬ ቀንሶ ያስረዝምሽ አንቺን እኔን አሳንሶ ከሰጎን እረዝመሽ ስትቆሚ ከጎኔ ቁመቴን መጽውቼሽ ጫጩት ላክል እኔ፤ ይስጥሽ ከጸጉሮቼ ከአናቴ ላይ ዘግኖ ይገጠብ ራሴ ያንቺ ተጎንጉኖ አወይ ጸጉሯ ብለው ኮረዶች ሲያወሩ ድጥ ራስ ነህ ብሎ ይዝለፈኝ ሰፈሩ፤ ... እቴ ይስጥሽ ከወዜ ላይ ጨልፎ ከፊቴ ይቅዳልሽ ከደሜ ጠልቆ ከጅማቴ ከአይን ያውጣሽ እያለ ሲመርቅ አድናቂ እስቲ እግዜር ይማርህ ይበለኝ ጠያቂ። እቴ እጄን ብትፈልጊ እግሬን ብትፈልጊ አንገቴን ደረቴን ተሰጥኦ ሀሳቤን ያደምቀኛል ብለሽ ያሰብሺውን ሁላ እግዜር  ከኔ ወስዶ ከሰጠሽ በኋላ ያስቀርልኝ አይኔን ያስቀርልኝ አይኔን አንቺን ማየት ብቻ ያኖረኛል እኔን ©✍በእውቀቱ  ስዩም @snetsehuf

በላይ በቀለ ወያ) . . አንቺ ሚያስጨንቅሽ የአንዲት ቆንጅዬ አርቲስት ፣ የአለባበስ ፋሽን እኔን ሚያስጨንቀኝ እንዴት እንደማወልቅ ፣ በፆም ቀሚስሽን😂 ።።። አንቺን ሚያስገርምሽ ፣ ሴት ስትታይ እርቃን እኔን ሚያስገርመኝ ከየት እንደተገኘ ፣ ይሔ ሁሉ ፃድቃን😂 ።። አንቺን ሚያሳስብሽ የሰው አለባበስ ፣ የሰው አካሔዱ እኔ ሚያሳስበኝ ጤፍ በርበሬ ሽሮ ፣ ዘይት መወደዱ የሰው ልጅ እንደበግ ፣ ሰርክ መታረዱ። ።።። በምን እንግባባ ፣ ታዲያ እኔና አንቺ አንቺ ሚያስጨንቅሽ ፣ የሰው ትዳር ፍቺ እኔን ሚያስጨንቀኝ በየ መታጠፊያ ፣ ያለ ማጅራት መቺ ወሬያችን አንድነት ፣ ኑሯችን ለየቅል አንቺ ሚያምርሽ ልቤ ፣ እኔ ሚያምረኝ ቅቅል 😂(የድንች😂) የኔ ተስፋ አንድነት ፣ያንቺ ተስፋ አንድ ቀን ቋንቋ እንዴት ያግባባን ፣ ኑሮ እያራራቀን? ።።።። @snetsehuf

ስብሃት ገ/እግዚዓብሄር ሁሌ በተቻለኝ መጠን የምሰብካት ስብከት አለችኝ። የምሬን፤ በተቻለኝ መጠን። ጠዋት ስትነቃ ተመስገን በል ! በረከቶችህን ቁጠር።! ርዕሷ ነች ይህቺ ፡፡ ተመስገን በል ! ሞተህ ልታድር ትችል ነበራ ! ወይ ደግሞ ከዛ ከአልጋህ ወርደህ ስትቆም ተመስገን በል! በሆነ ምክኒያት የአልጋ ቁራኛ ሆነህ ልትቀር ትችል ነበር ፡፡ እ….ደግሞ ስትንጠራራ ደግሞ ደስ አይልም ? እ እ …ን.ዲ.ህ ስትል ደስስ አይልም ? መንጠራራትን የሰጠኸን እያልክ ተመስገን በል! እያልክ ደግሞ ከዛ በፊት ሽንትህ ወጥሮህ ስትሸና የጠጣኸው ውሃ ሸንት ሆኖ መውጣቱ ፤ይሄ የማናውቀው ተዓምር ውስጣችን መሰራቱ ፤ ተመስገን በል !። ከዛ ደግሞ ወጥተህ ስትሄድ መ..ን..ገ..ዱ. . ሁሉ ጤና ነው ፡፡ ታክሲው ፤ ሰዉ ፤ ምኑ ለማኙ መነኩሴው ፤ እሱን ስታይ ተመስገን በል ! ምክኒያቱስ ? ጄኔራል ፀጥ አርጋቸው የሚባሉ ጄኔራል ጨለማን ተገን አድርገው ፤ በታንክ ገብተው አገሩ ፀጥ ብሎ ቢቆይህስ? ምን ታደርግ ነበር |? ጠላት አለኝ ይሆን እንዴ ? ተመልሼ ልግባ ? ደግሞ ተመልሶ ገባ ይሉኛል ፤ ምናምን ትል ነበር። አገር ሰላም በመሆኑ ተመስገን በል ! እያልክ …. እያልክ ትሄዳለህ ፤ ቆማጣ ስታይ ውይ ረ…ስ..ቼ…ው መዓት ነው ፤ ሁልጊዜ ተመስገን በል፤ ተመስገን በል ! አሁንም ፡፡ ማዕደ ጥበብ @snetsehuf

ትግርኛ አትችልም "አባቴ ይሙት !" አለችኝ እየሳቀች። እውይ ጥርሶቿ ታይተው አይጠገቡም። የውበት አምላክ በጥንቃቄ የደረደራቸው የቀይ ባህር ዕንቁዎች ይመስላሉ። "ይህ ጉሮሮ የሚፍቅ ቋንቋ ! መጓጉጥ ነው። አልኳት "እንጥላችሁ ስላልተቆረጠ ይሆናል " "እሰኪ መቶ በይ " "ሞቶ " " እስኪ አንተ በይ " "አንቴ " " አንቺም አማርኛ አትችይም አባቴ ይሙት " አልኳትና መጠጧን ላመጣላት ሄድኩ። መጠጧን አመጣሁላትና " ሕራይ ትግርኛ ክትምህርኒ እሺ " ሺ እምበአር ? ጸጋዬ ኃይለማርያም እባላለሁ " አልኳትና መጠጧን ቀምሼ ሰጠኋት። እውነትም ጥሩ መጠጥ ነው። "በቲቪ አውቅሀለሁ አንተም አማርኛ ታስተምረኛለህ "አለች ፡ ጠጉሯን እየነሰነሰች ፈገግታዋ ይናፍቃል። " ማን ብዬ ልጥራሽ ሰሜናዊት ጽብቖቲ ?" ብዬ ስሟን ጠየኳት ሳቀችና "ፊያሜታ ጊላይ እባላለሁ " ብላ ስሟን ነገረቺኝ። ስሟ ደንቆኝ ቅንድቤን ከፍና ዝቅ ሳደርግ አይታኝ "ምነው አለች። " እንግዳ ስም ነው ...." "የጣሊያን ስም ነው ...." "ምን ማለት ነው ? " "ትንሽ ነባልባል ...." "እውነት አንቺን ከሩቅ መሸሽ ይሻላል "አልኳት " "ለምን አለችኝ " " ስምን መላክ ያወጣዋል ይባላል። እንደ ስምሽ ከሆንሽ አደገኛ ነው። በትንሽ ነበልባል ተቃጥሎ ማለቅ ደግ አይደለም። እንደ ስምሽ እንዳልሆንሽ ተስፋ አደርጋለሁ አልኳት። "ነኝ አባቴ ይሙት "አለች ስቃ" #ኦሮማይ #በዓሉ ግርማ @snetsehuf

አስገራሚ ታሪክ!!. ወጣቱ ልጅ የመጀመሪያ ደረጀ ት/ቤት አስተማሪውን በአንድ ቦታ ላይ ያየዋል። ሮጦ ሄዶ በትህትናና በአድናቆት ሰላም ካለው በኃላ አስተማሪውን "አስታወስከኝ ወይ?" አለው። አስተማሪውም ግራ በመጋባት ውስጥ ሆኖ፦ "ይቅርታ አላስታውስኩህም። እንዴት እንደተዋወቅን ልትነግረኝ ትችላለህ?" አለው። ወጣቱም ልጅ እንዲህ እያለ ተረከለት። "3ኛ ክፍል እያለን ያንተ ተማሪ ነበርኩ፤ታዲያ አንድ ቀን የክፍል ጓደኛዬን ቆንጆና ልዩ የሆነውን የእጅ ሰዓቱን ሰርቄበት ነበር። እሱም እያለቀሰ ሄዶ የእጅ ሰዓቱ እንደተሰረቀበት ላንተ ሄዶ ይናገራል፤አንተም መጥተህ፤ ልትፈትሸን፦ ሁላችንም ክፍል ውስጥ ያለን ልጆች አይናችንን ጨፍነን እጃችንን ከፍ አድርገን ፊታችንን ወዴ ግድግዳ ኣዙረን እንድንቆም አዘዝከን። በዛን ጊዜ እኔ የፍተሻውን ውጤት እያሰብኩ በጣም ተረበሽኩ፤የምገባበትን አጠሁ። አስበው ሰዓቱ በኔ ኪስ ውስጥ ተገኝቶ ሁሉም ተማሪ ሌባ እያለ ሲሰድበኝ፤ ግቢ ውስጥ መጠቋቆሚያ ስሆን፤ ከት/ቤት ተባርሬ ወላጅ አምጣ ስባልና ወላጆቼ ይሄን አሳፋሪ ድርግቴን ሲሰሙ። "በዚህ ጭንቅ ውስጥ እያለሁ የፍተሻው ተራ ደርሶ እጅህ ወደ ኪሴ ስገባና ሰዓቱን ቀስ አድርገህ ከኪሴ ስታወጣ ተሰመኝ፤ 'ሊናገር ነው፤ አለቀልኝ ብዬ' ስጠባበቅ አንተ ግን ምንም ሳትል የመጨረሻው ልጅ እስክትደርስ ፍተሻውን ቀጠልክ። ፍተሻውም ስያልቅ አይናችሁን ግለጡና ወደየቦታችሁ ተመለሱ አልከን። እኔ ግን መልሰህ ታስቆመኛለህ ብዬ መቀመጡን ፈራሁ።በጣም የሚገርመው አንተ ሰዓቱን አውጥተህ ለባለቤቱ መለስክለት፤ግን ከማን ኪስ ውስጥ እንዳገኘህና ማን እንደሰረቀበት ምንም አልተናገርክም ነበር። በት/ቤት ቆይታዬም ምን እንደተፈጠረ ማንም አላወቀብኝም ነበር፤አንተም ምንም ብለኸኝ አታውቅም።እኔ ግን ስሜንና ክብሬን እንዳደንክና ስብዕናዬ እንደጠበክልኝ ዛሬም ድረስ አስታውስሃለው።አንተም ይሄን ታሪክ ቶሎ ትረሳለህ ብዬ አልገምትም። አሁንስ አስታወስከኝ?" አለው። አስተማሪውም በመገረም ውስጥ ሆኖ "ትንሽ ትንሽ አስታውሳለሁ። በማን ኪስ ውስጥ እንዳገኛሁ ግን አላስታውስም፤ ምክንያቱም እኔም ስፈትሻችሁ የነበረው አይኔን ጨፍኜ ነበር!!"አለው። # NB በህይወታችን ለሚናከናውናቸው ነገሮች ሁሉ ጥበብ ያስፈልገናል።እንደ አስተማሪ እንደ ወላጅ እንደ መሪ...ወዘተ ለአንዳንድ ነገሮች አይናችንን መጨፈን አለብን ምክንያቱም ሁሉም ጥፋቶች በቅጣት ብቻ አይታረሙም!!!! ...... From Facebook @snetsehuf

ድሮ አስረኛ ክፍል ሳለን ነፍሰ ቀጭኑ የኬሚስትሪ መምህራችን እንዲህ ሲሉ ጠየቁን:- “ውሃ ከምን እና ከምን ንጥረ ነገሮች ነው የተፈጠረው?” ብዙ ተማሪዎች ይህችን ቀላል ጥያቄ ለመመለስ ተቅለበለብን። መምህሩ ግን ከሁሉም ተማሪ ይልቅ ትኩረታቸውን ቦጋለ ላይ አድርገው እንዲመልስ አስገደዱት። ቦጋለ ከእንቅልፉ የተነሳ ይመስል አይኑን አሻሽቶ ትንሽ ቆየና መምህሩ ጥያቄውን እንዲደግሙለት ጠየቃቸው። (በነገራችን ላይ የቦጋለ አባት ልጃቸው ትምህርት እንዳይገባው ተደግሞበታል ብለው ስለሚያስቡ፣ እሱን ይዘው ያልተንከራተቱበት ጸበል አልነበረም። ኋላ ላይ ቢታክታቸው ጊዜ እርግፍ አድርገው ተውት! እርሱም ትምህርት አይንህን ላፈር ብሎ ማንበብና ማጥናቱን እርግፍ አድርጎ ተወው) “እኛ የምንጠጣው ውሃ ከምንና ከምን ውህደት ተፈጠረ?” ብለው ጥያቄውን ደገሙለት። “ውሃ ልማት እና ቀበሌ ተዋህደው በገጠሙት የቧንቧ መስመር ነው የተፈጠረው!” ብሎ ሲመልስ ያልደነገጠ ተማሪ አልነበረም። ሁላችንም እያሾፈ ነው ብለን በትኩረት አየነው። እሱ እቴ! ልቡ ደጭ እንኳ አላለም! ሰው እንዴት ይህን የሚያክል ተራራ ስህተት ሰርቶ ትንሽ ሀፍረት እንኳ አይሸብበውም? “ስ! ውይ ይቅርታ” አለን መልሶ… በቃ ኦክስጂንና ሀይድሮጅን ታውሰውት ነው ማለት ነው ብለን ማስተካከያውን በጉጉት መጠባበቅ ያዝን! ቦጋለ እጅ አውጥቶ መልሶ፣ የተሳሳተውን አውቆ ትክለኛ መልስ ከመለሰ፣ ዘጠነኛው ሺህ አልፎ አስራ ዘጠነኛው ሺህ ገብቷል ማለት ነው በቃ! ቦጌ ጉጉታችን ላይ በረዶውን ሲከለብስ፤ “ቅድም ተሳስቼ ነው መምህር! እህ ህ-- ውሀ ልማት እና ሰሜን ሸዋ ዞን በመተባበር ነው” ብሎ እርፍ አለው። ነፍሰ ቀጭኑ መምህራችን በንዴት ተነፋፍተው ነብር አከሉ! አለ አይደል ቤት ውስጥ ድመት ስትቆጣ እንዴት ነው ኩፍ የምትለው? መምህራችን ኩፍ አሉ። በስመአብ! አስተማሪ ሲናደድ ለካ እንደዚህ ነው? ከአስተማሪም ሁሉ ደግሞ ኬሚስትሪ አስተማሪ ሲናደድ በጣም ያስፈራል። የሆነ ሰልፈሪክ አሲድ ከላብራቶሪ አንስተው ፊቱ ላይ የሚከለብሱበት ሁሉ መሰለን። የቦጋለና መምህራችን መጨረሻ የተዘጋው ዶሴ ሊሆን ነው ስንል ሰጋን! “ተነስ!” ቦጋለ ተነሳ። ደግሞ አነሳሱ እኮ እንደ ንጉስ ክቡር ዘበኛ ቀብረር ኮራ ብሎ ነው። ግዳይ የጣለ ጀግና የነብር ቆዳ ለብሶ ቢመጣ እንኳ መቼ ይሄን ያህል ይጀነናል? ጅ---ንን--ን--ን ቅብርርርርርርርር-- ከሴክሽን አንደኛ የሚወጣው ፍቅሩ የሚባለው ቸካይ ተማሪ እንኳ መምህር ሲያስነሳው አንገቱን ሰበር ያደርጋል እኮ! ቦጌማ ጭራሽ ተንጠራራ… ደረቱን ነፋ! “እነ ሚካኤል፣ እነ እዮብ፣ እነ አቤል-- ኢንጅነር ወይ ዶክተር ሲሆኑ ሻንጣ ተሸካሚያቸው እንደምትሆን አልጠራጠርም” ብለው ሞራሉ ላይ ቀዝቃዛ ውሃቸውን ከለበሱት። በቃ ቦጊሻ ሊተነፍስ ነው አልን! ደግሞ እኮ እንደፈራነው ከወራት በኋላ ማትሪክን ወደቀ። እኛ ፈተናውን በጥሰን አለፍን። እኛ አስራ ሁለተኛ ክፍል አልፈን ለዩኒቨርስቲ ስንዘጋጅ፣ ቦጋለ የሆነ ትምህርት እንደከረሜላ አሽጎ የሚሸጥ ኮሌጅ ዲፕሎማ መማር እንደጀመረ ሰማን። አውቶቡስ ተራ አለመሄዱም የመምህሩ ትንቢት እውን እንዳይሆን ስለሰጋ እንጂ የሱ መጨረሻ ከወያላነት ይዘላል ብሎ ማን ያስብ ነበር? ግን ሁለተኛ ዓመት ተማሪ ስንሆን ቦጋለ ቀበሌ ስራ አግኝቶ መግባቱ ተነገረን። ያኔ በሱ ሙድ ያልያዘ አልነበረም። እንደውም አንድ ቀን ፍቅሩ የሚባለው ቸካይ የነበረ ተማሪ ወደኔ ጠጋ ብሎ፤ “ቦጌ በዚህ ከመሬት አልሮ ማርስ የምትባል ፕላኔት ላይ እንኳ በማይገኝ ድድብናው ቀበሌ ስራ ማግኘቱም ተመስገን ነው” ብሎ ገለፈጠ። “ቦጋለ እኮ ቀን ስራ እንኳ ይበዛበታል። እንደ ህንዶች ሰባቴ ቢፈጠር ሰባት ጊዜም ትምህርት አይገባውም” አለን ቀጥሎ። ሁላችንም ጎበዝ ተብዬ ተማሪዎች ስንመረቅ ግን የነፍሰ ቀጭኑ ሰውዬ እርግማን ለቦጋለ ምርቃት ሆኖ እርፍ አለው። የከተማችን አስተዳደር ተመራቂ ተማሪዎች ተደራጅታችሁ ኮብልስቶን አንጥፉ ምናምን ብሎ በስብሰባ ሰበብ ሲጀነጅን፣ ቦጌ ተከብሮ የከተማችን ከንቲባ ሆኖ ነበር። ጭራሽ እዛ አመዳችን ቡን ባለ ተመራቂ ተማሪዎች ፊት ቀርቦ፣ ስለ ስራ ፈጠራ ሰፊ ማብራሪያ ሰጠን። አቤት የምስሉ ፍጥነት! አቤት የንግግሩ ስድርነት! መጥበሻ ሆኖ የተማሪውን ልብ አቀለጠው። ከኔ ጎን ተቀምጣ የነበረችው ጸሐይ የምትባል ጓኛችን፣ ዛሬውኑ ጀበና እና ስኒ ገዝቼ ስራ ካልጀመርኩ በሚል ሀሳብ ጦዛ ብንን ብላ ጠፋች። “ኢንጅነር ነን ዶክተር ነን ብላችሁ አትኮፈሱ፤ ጀበና ቡና ብታፈሉ ትችላላችሁ። ለምሳሌ ሚካኤል እዮብ አቤል በኢንጅነሪንግ እና ዶክትሬት ተመርቃችሁ ሰፈር ለሰፈር ከምታውደለድሉ---ጀበና ቡና ብታፈሉ ምን ችግር አለው? ብሎ በምሳሌነት ጠቀሰን። እኔ እንዳስተማረን ሳይሆን እንደ ሰደበን ቆጥሬው እሳት እንደነካው ላስቲክ ተኮራመትኩኝ። አቤል፣ እዮብ፣ ሚኪ ምንም ጎበዝ ተማሪ ሆናችሁ ስታስጨንቁን ብትኖሩም፣ አሁን ግን መጨረሻችሁ እጣን እያጫጫሱ፣ አላፊ አግዳሚውን መካደም ነው ማለቱም አይደለ? እዮቤ ጓደኛችን ፊቱ በርበሬ ሆኖ ቀላ! አይ መንግስት የስራህን ይስጥህ፤ አንድ የተከበርኩ ዶክተርን ለመንደር ስኩፒኒ አሳልፈህ ትሰጠኝ ብሎ ክፉኛ ቆዘመ! እኔም አነጋገሩ ትንሽ ሸንቆጥ ስላደረገኝ፣ ከስብሰባው በኋላ ቦጋለን ለማናገር ከተቀመጥኩበት ተነስቼ ተራመድኩኝ። ዛሬ ምንም ጉድ ይለይለታል! በዛ ቢባል ከንቲባውን ገላመጥክ ተብዬ ብታሰርም አይደል? የልጅነት ጓደኛዬ ስለሆነ ትንሽ ራሮት ተሰምቶት፣ ከሳምንት በኋላ ራሱም ሊያስፈታኝ ይችላል የሚል ድፍረት አደረብኝ። ጀርባውን ተከትዬ ተጠጋሁት። በሰዓቱ ከየት መጣ ያልተባለ ጠባቂው በመዳፉ ጨብጦ አሽቀነጠረኝ። የጠባቂው መዳፍ ጎትቶ እዛው የተመረቅሁበት ዩኒቨርስቲ ግቢ ሊዶለኝ ምን ቀረው? ቀና ብዬ አየሁት! “ምን አጠፋሁ አለቃ?” ፈርጣማው ጠባቂ በቁጣ ቱግ ብሎ እንዲህ አለኝ፡- “አንተ ምን አይነት ደፋር ነህ ባክህ? ክቡር ከንቲባችንን ለመቅረብ አይደለም ሻንጣቸውን ለመሸከም ብትመጣ እንኳ ማስፈቀድ ነበረብህ” ✍️ከሚካኤል አስጨናቂ “ሸግዬ ሸጊቱ” የወግ መድበል የተወሰደ @snetsehuf

አበቦች ሲፈኩ እንደሚደርቁ ያውቃሉ፣ ግን እደርቃለሁ ብለው ሳይፈኩ አይቀሩም፡፡ ሰውም ሟች ነው ግን ሟች ነኝ ብሎ መተው የለበትም፡፡ ሁሉም ሰው በየመስኩ ያብብ፡፡ ወዳጄ ይህቺ አለም ትልቅ ዳመራ ናት አንተ በዳመራው ስር ያለህ አንድ ችቦ ነህ አንተ ስትጠፋ የዳመራው ብርሀን ይቀንሳል፡፡ የቻልከውን ያህል ብራ አንተ ከነገሮች በላይ ነህ፡፡ በነገሮች አትረበሽ፡፡ አየህ አንፖል ተቃጠለ ተብሎ ቤት አይቀየርም፡፡ አንፖል ተቃጥሏል ብሎ ቤት የሚቀይር ሞኝ ነው፡፡ አንተም አንዱ የህይወቴ ጉዳይ አልተሳካም ብለህ ራስህን አታጥፋ፡፡ ይልቅስ አምፖልህን ቀይር ችግርህን ተጋፈጠው፡፡ ጭንቀትህን አስጨንቀው፡፡ "ካህሊል ጅብራል እንዲህ ይላል ህይወት ልክ እንደ ክራር ጨዋታ ነው፡፡ አጨዋወቱን ያወቀ ጥሩ ሙዚቃ ይሰማል ያላወቀ ደግሞ ዝብርቅርቅ ጩኸቷን ለመስማት ይገደዳል፡፡ " አሁንም እልሀለው ህይወት በደመነፍስ አትሄድም ስልቷን እወቀው፡፡ በህይወትህ ትላንት ያለፈውን መጥፎ ታሪክህን መቀየር ማስተካከል መሰረዝ አትችልም፡፡ የምትችለው አምኖ መቀበልና ለተሻለ ነገ መስራት ብቻ ነው፡፡ "መቀየር የማንችለውን ነገር መቀበል ማለት ተስፋ መቁረጥ ማለት ሳይሆን አቅማችንን የምንችለው ነገር ላይ ማዋል ማለት ነው::" በፍፁም ተስፋ አትቁረጥ ግን አቅምህን የምትችለው ነገር ላይ አውለው የምን ተስፋ መቁረጥ ✍ጋሽ ስብሀት ገ/እግዝያብሄር ውብና ደስ የሚል ቀን ይሁንልን🙏 @snetsehuf

ለግዜር የተፃፈ ደብዳቤ እንደምነህ እግዜር ሰማይ ቤት እንዴት ነው እመጣለሁ ብለህ ቆየህሳ ምነው? እኛማ..... ለእልፍ አእላፍ አለቃ… ማመልከቻ ፅፈን ለወፈ ሰማይ ህዝብ …መድረክ ላይ ለፍፈን ፀሎት ቤታችንን ….እኛው ላይ ቆልፈን የምድር አተካራ …..ህግጋቱን አልፈን ደብዳቤ ላክንልህ፤ አይንህን ካየነው ሁለት ሽ ዘመን እንደቀልድ አለፈ የመምጣትህ ተስፋ እየኮሰመነ መቅረትህ ገዘፈ እንደውም እንደውም... ‹‹በመጣለሁ ተስፋ ሁለት ሽ ዘመን ቀጥሮን ከጠፋ በቀጠሮው ሰአት መምጣት ከተሳነው ‹‹እግዜር አበሻ ነው›› እያሉ ያሙሃል!! እኔ ምን አውቃለሁ... አመስግነው ሲሉ እልልታ የማቀልጥ ቃሉን ስማ ሲሉኝ ...ሰባኪው እግር ስር በደስታ እምቀመጥ እግዚኦ በሉ ሲባል ...እንባየን የማፈስ ሃሌ ሉያ ሲሉኝ ...በሳቅ ልቤ እሚፈርስ ምናምኒት እውቀት ውስጤ ያልፀደቀ እንበረከክበት ጉልበቴ ያለቀ እኔ ምን አውቃለሁ... ግን አንተ ደህና ነህ? ከምር እንደሚያሙት ምፅአት ቀረ እንዴ ? የሰናፍጭ ቅንጣት ታክል ጥርጣሬ አትከፋም አንዳንዴ! ከሆነስ ሆነና ሰማይ ቤት እንዴት ነው? አብረሃም ሰላም ነው... እዛስ ቤት ገነባ ዛሬም በድንኳን ነው ? እኛማ ይሄውልህ... በቤት ኪራይ ችንካር እየተሰቀልን ‹‹ኤሎሄ›› እንላለን ጎጆ እንድጥልልን.... ወደላይ ገነባን ወደጎን አሰፋን ወደላይም ከላይ ወደጎንም ከጎን እ ን ደ ጉ ድ ተገፋን ቤት ለእንግዳ ማለት ጭራሹኑ ጠፋን !! አባታችን ሙሴ እነዴት ነው ለክብሩ ውቂያኖስ መክፈያው ደህናናት ብትሩ? እኛማ ይሄውልህ.... እንጀራ ፍለጋ ባህር ስናቋርጥ የተስፋዋን ምድር አሸዋ ሳንረግጥ የትም ውሃ በላን የትም አሳ ላሰን ን ገ ር ል ን ና ብትሩን ያውሰን ?! እናልህ እግዜር ሆይ.... ከተስፋዋ ምድር ወደሌላ ተስፋ አለን እየኳተን መሄጃው ሲገርመን መመለሻ መንገድ መቆሚያ ቦታ አጥተን...! ላባታችን ሙሴ እንደምትልልን... ‹‹የመሄድ ዘመን ነው ባህር የመሻገር ‹‹ዱላህን ላክልን›› ብሎሃል በልልኝ!! ሰማይ ቤት እንዴት ነው? ....ዳዊትስ ደህና ነው? ዛሬም ይዘምራል ...ዛሬም ይፎክራል ? ሰላም ነው ጠጠሩ .... ሰላም ናት ወንጭፉ? እዛስ አቅል ገዛ ጎሊያድ ተራራው ጎሊያድ ግዙፉ? እልፍ አላፍ ጎሊያድ ከቦን ሲደነፋ ወንጭፉን ጠቅልሎ ምነው ዳዊት ጠፋ ? ብሎሃል በልልኝ!! ለረከሰ ጠጠር ለሞላ ወርዋሪ ‹‹ወንጭፍህን ስጠው ለዚህ ታሪክ አውሪ›› ብለህ እዘዝልን!! እንዴት ነህ ጌታ ሆይ... ሰማይ ቤት እንዴት ነው? የሙሴ አልጋ ወራሽ እያሱ ሰላም ነው....? ያቆማትን ፀሃይ ግቢ ቢላት ምነው?! ያው እንደምታውቀው አስራ ሶስት ወራት ነው ፀሃይ የምንሞቀው... ኧረ ፀሃይ በዛ ኧረ ፀሃይ በዛ ኧረ ፀሃይ በዛ የመጣው ወር ሀሉ ፀሃይ እያዘለ የተሸመው ሁሉ ‹ፀሃይ ነኝ› እያለ ያስራ ሶስት ወር የግዜር ፀሃይ ያስራ ሶስት ወር የሰው ጀምበር ባቃጠላት ምድጃ አገር ምን ታምር ሊኖር ይችላል ፀሃይ ሁኖ እንደመፈጠር!! ኧረ እግዜር በናትህ.... ኧረ እግዜር በናትህ...በጭንቅ አማላጇ ባዘለህ ጀርባዋ ባቀፉህ እጆቿ ወይ ዝናብ ላክልን ወይ ዝናብ ሁነህ ና ሙቀት ገደለና!! እናልህ እግዜር ሆይ ማጣፊያው አጥሮናል ስም ያለው ሞኝ ነው ሁሉም ይጠራናል... ጳውሎስ ሲሉን ...አቤት ጴጥሮስ ሲሉን ...ወይየ ይሁዳ ሲሉንም አቤት እንላለን ስማችንን ሸጠን ...ሰላሳ ጭብጨባ እንቀበላለን! ስንቱ ባለካባ ክብርህ የተሰጠው ለሰላሳ ፍራንክ ለተራ ጭብጨባ አደራህን ሸጠው ! ተወው የኛን ነገር ...ሰማይ ቤት እንዴት ነው .... ሂዋንስ ደህና ናት? ያው የልጅ ልጆቿ በግሯ ተተክተው የፍሬው ሲገርምህ ግንዱንም አንክተው ለፍጥረተ አዳም ባይኑ ያገምጡታል ሰይጣንም ደህና ነውኑሮ ተስማምቶታል.... ሰውን ለማሳሳት ላይ ታች ማለት ትቷል ሳይጠራው የሚጎርፍ ህዝብ በዝቶለታል...! ኧረ እግዜር በናትህ በጭንቅ አማላጇ ባዘለህ ጀርባዋ ባቀፉህ እጆቿ ወይ ዝናብ ላክልን ወይ ዝናብ ሁነህ ና ሙቀት ገደለና!! ©✍አሌክስ አብርሃም

ጋዜጠኛና ጸሐፊ ተውኔት ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ ፍልስምና ፩ ፣ ፪ እና ፫ን ደምሮ ባወጣው መፅሐፉ ጋሽ ስብሃትን እየጠየቀው ነው። #ቴዎድሮስ :- እንደው ጋሽ ስብሃት በስጨት ብለህ "በዚህ ዓለም ባልተፈጠርኩ" ያልክበት ጊዜ ኖሮ ያውቃል? #ስብሃት :- የለም። በፍፁም ኖሮ አያውቅም። የመረረ ችግር ገጥሞኝም አያውቅም። እኔ ችግር የምለው በጣም ርቦህ የምትበላው ካጣህ ፣ በጣም በርዶህ የምትለብሰው ከሌለህ ነው። ይህ እኔን ገጥሞኝ አያውቅም። የገጠመኝ ከእናቴ ተለይቼ ወደ እዚህ ስመጣ ናፍቆት ነው። ምናልባት ለዓመት ያህል ማታ ማታ አለቅስ ነበር። ይህ ችግር ነው። #ቴዎድሮስ :- ደስተኛ ነህ? #ስብሃት :- በጣም! #ቴዎድሮስ :- ምንድንነው ደስታ ማለት? #ስብሃት :- እግዜር ካልበደለህ ወንድ ከሆንክ ሴት አቅፈህ ለብቻህ ስትሆን ነው - ደስታ። ከእሱ ቀጥሎ ርቦህ ስትበላ ነው - ደስታ። ከእሱ ቀጥሎ ሽንትህ ወጥሮህ ስትሸና ነው - ደስታ። ደስታ መዓት ነው መቁጠር ከፈለክ። ግን ለምን ትቆጥራለህ? ዝም ብለህ መኖር ነው። #ቴዎድሮስ :- ችግር ወደን የማንገባበት ት/ቤታችን ነው። ለመሆኑ ባንተ ሕይወት ውስጥ ትልቅ ትምህርት ሰጥቶህ ያለፈና እንደ ባለውለታዬ እቆጥረዋለሁ የምትለው የችግር ጊዜ ነበር? #ስብሃት :- አዎን። ሕይወቴን መለወጥ ሳይሆን ቀርፆታል የምለው የችግር ጊዜ ነበር። ልጅ ሆኜ እስከ አስር ዓመቴ (ከወላጆቼ ጋር ሆኜ) ማለት ነው እስኪተርፈን የምንበላው በዓመት ሶስትና አራት ጊዜ ይሆናል። ጠገብኩ እንላለን እንጂ አንጠግብም። ይርበናል። ከዚያ በኋላ አዲስአበባ መጥቼ ርቦኝ አያውቅም። ግን የራበውን ሰው ገና ሳየው መራቡን አውቃለሁ። የሚርባቸው ደግሞ ብዙ ጊዜ የማይናገሩ ናቸው። ይታየኛል። በቃ ኪሴ ገንዘብ ይኖራል አውጥቼ እሰጠዋለሁ። እሱም ደስ ይለዋል ፤ እኔም ደስ ይለኛል። ይህን ሁሉ ለማሰብ " እንኳንም እየራበኝ አደግሁ" እላለሁ። @snetsehuf share

#Frog_Experiment ______ ውሃ በተሞላ ድስት አንዲት እንቁራሪት ብንጨምር እና ከዛም ውሃውን ማፍላት ብንጀምር ፤ ውሃው እየፈላ በሄደ ቁጥር እንቁራሪቷም የሰውነት ሙቀቷን ማስተካከል ትጀምራለች። የውሃው ሙቀት ከፍተኛ እየሆነ ሲሄድ እሷም የሰውነቷን ሙቀት በዛው ልክ ማስተካከሉን ትቀጥላለች። የውሃው ሙቀት ጨምሮ የመፍላት ደረጃ (boiling point) ላይ ሲደርስ ግን ማስተካከል ማትችልበት ደረጃ ስለሚደርስ እራሷን ለማዳን ከድስቱ ዘላ ለመውጣት ትፈልጋለች ፤ ትሞክራለችም ፤ ግን ዘላ መውጣት አቅም አይኖራትም አትችልም። ምክንያቱም ያላትን አቅም ሁሉ ሙቀቷን በማስተካከል የውሃውን ቃጠሎ ለመከላከልና ለመላመድ ባደረገችው ተጋድሎ ጨርሳዋለችና ወድያው ትሞታለች፡፡ እንቁራሪቷን ምን ገደላት ??? አብዛኞቻቸችን የፈላ ውሃ እንል ይሆናል ፤ እውነታው ግን ይህ አይደለም። እንቁራሪቷን የገደላት የፈላው ውሃ ሳይሆን መች መዝለል እንዳለባት የመወሰን እቅም ማጣቷ ነው። አብዛኞቻችን ከሰዎችም ይሁን ከነገሮች ጋር ያለንን ነገር ለማስተካከልና ለመላመድ እንሞክር ይሆናል፤ ግን እስከ መች ማስተካከል እንዳለብንና መች መወሰን እንዳለብን ማውቅ ይሳነናል። አንዳንዴ ነገሮችን እንለምዳቸውና ለኛ የማይጎዱ መስለው ይታዩናል፤ በመጨረሻው ቅፅበት ግን እንዳለመድናቸው ቢገባንም ማመልጥና መውጣት የማይቻለን ሰአት ይሆናል። በጥፋት/ወንጀል መንገድ ውሰጥም ስንሆን እንዲሁ ነው፤ ትንሹን ወንጀል እንለምደዋለን የሚጎዳን አይመስለንም፤ ደስታ ውስጥ ያለን ይመስለናል፤ ደስታው ሙቀት ይፈጥርልናል፡፡ ሙቀቱ ወደ እሳት የተቀየረ ጊዜ ግን ፍፃሜው ግልፅ ነው፡፡ ከሙቀቱ መውጣት ካልቻልን ከእሳት እንደማንወጣ ግልፅ ነው። እናም ለውሳኔ አንዘግይ !!! Share @snetsehuf

ቴዎድሮስ፦ በተማርከው ትምህርት ለምን ደስተኛ አልሆንክም? ምን አጣህበት? ቡርሐን፦ ምንም አገላገኘሁበትም፡፡ ከጠቀመኝ ያጣሁት ይበልጣል፡፡ የመመላለሴን እና የመጨናነቄን ያህል ምን አወኩ? በራሴም ሆነ በሐገር ላይ ምን ለውጥ አመጣሁ? ምንም፡፡ በተግባር ምን ሆነ? ስትል ዘመናዊ ትምህርቱን አከሸፉት፡፡ በጣም ጐበዝ የሆነ ተማሪ ተመርቆ ሲወጣ በስራ ላይ በምንድነው የሚለካው? ሰዓት አክብሮ በመግባቱና በመውጣቱ ነው፡፡ ጉብዝናህ አዲስ ነገር በመፍጠርህ ሳይሆን ሰንጠረዥ በሞላኸው ልክ ነው የሚለካው፡፡ ሌሊቱን ምርጥ የተባለ ሥራ ስትሠራ አድረህ ጠዋት አርፍደህ ቢሮ ብትገባ ቅጣት ይጠብቅሀል፡፡ ምክንያቱም የሥራህ መለኪያ ውጤትህ ሳይሆን ሰዓትህ ስለሆነ፡፡ ሲሲተሙ ሥራ አምላክህ እንዲሆን ተደርጐ ነው የተቀየሰው፡፡ መኖር የምትችለው ስለ ሠራህ ሳይሆን በሥራ ገበታ ላይ ስለተገኘህ ነው፡፡ በእስልምና እና በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት የሚሰጡ የአብነት ት/ቤቶች ልብ ብለህ ካየሀቸው አርባውም ተማሪዎች ይጮሀሉ። ስትሰማው ሊረብሽህ ይችላል። ግን አርባውም አንድ አይነት ሐሳብ አይደለም የሚያነበንቡት፡፡ እንደየ አቅማቸው የደረሱበት የደረሱበትን ነው የሚያነበንቡት። ጐበዙ የራሱን ሲጨርስ ሰነፉን ቆሞ አይጠብቀውም። የመምህሩ ድርሻ ሁሉንም መቆጣጠርና ሳያጠና ተደብቆ የሚቀመጥ እንዳይኖር ማድረግ ነው፡፡አንተ ጐበዝ ከሆንክ ለመምህሩ አሳውቀህ ተከታዩን ምዕራፍ ትቀጥላለህ። አርባውም እንደየ እውቀት ደረጃቸው የተለያየ ትምህርት ተምረው ይወጣሉ። ይህ ለሺህ ዓመታት የተሰጠ የእኛ ባህላዊ የትምህርት ስርዓት ነው፡፡ ይህ የትምህርት ክፍል በጣም ትልልቅ አሳቢዎችን አፍርቷል፡፡በፍጥነትህ መጠን ነው የምትሔደው፡፡ ቴዎድሮስ፦ ዘመናዊው ትምህርትስ ከዚህ አንፃር ጉድለቱ ምንድነው? ቡርሐን፦ ጉደለቱማ ግልፅ ነው፡፡ መምህሩ መጥቶ የሚናገረውን አርባውም ተማሪ እኩል ይሰማል፡፡ “እሱ ገብቶኛል” ብትልም ካልገባው ጋር ትቀመጣለህ ወይም መምህሩን ተዳፈርክ ተብለህ “F” ታገኛለህ፡፡ ታችኛው ክፍል ከሆንክ ደግሞ ትገረፋለህ፡፡ ገባህም አልገባህም የግድ ጊዜውን መጠበቅ አለብህ፡፡ ውሻ እንደምታሰለጥነው ሰልጥኖ ይወጣና ጐበዙ ተማሪም ታዛዥ ይሆናል፡፡ ሰላምታ አሰጣጡን ሳይቀር ይሰለጥናል፡፡ የምሁር ገፅታ እንዲላበስ ይሰለጥናል፡፡ በጥልቀት ማሰብና አዲስ ሐሳብ ማመንጨት ሳይሆን በተቀደደለት ቦይ የሚፈስ ወራጅ ውሃ ሆኖ ይቀራል፡፡ አረማመዱ፣ አቀማመጡ፣ አነጋገሩ ሳይቀር ተቀርፆ የተሰጠውን ይሆናል፡፡ የታዘዝከውን ሆነህ መገኘት አለብህ፡፡ አዲስ ነገር ለመፍጠር አይደለም የምታስብው፡፡ “ሰው ምን ይለኛል?”፣ “አለቃዬ ምን ይለኛል?”፣ “የመ/ቤቱን ህግ አክብሬያለሁ?” ነው የምትለው፡፡ ይህን ህግ አለማክበርህ እንጂ አንድም ጊዜ አዲስ ሐሳብ አለማፍለቅህ አስጠይቅህ አያውቅም፡፡ ኢንጂነሩን “ቤት ሥራ” ስትለው ሃያ ሰላሳ ዓመት ስለሚጥለው እቁብ እንጂ ጭንቅላቱ ሐሳብ ፈጥሮ ገንዘብ እንደሚያመነጭ አይደለም የሚያስበው፡፡ በተማርን ቁጥር ከተግባሩ እየራቅን ነው የምንሔደው፡፡ አርባ ሃምሳ ዩኒቨርስቲ እያለህ፣ ሰቃይ የኢንጂነሪንግ ተማሪዎች እያሉህ ለእንቦጭ አረም መፍትሔ ማበጀት ሳትችል ስትቀር ክሽፈት ከዚህ በላይ ምን አለ? ሃላፊነት የማይሰማው ምሁር የሚፈጠረው የትምህርትን ፋይዳ ካለመገንዘብ ነው፡፡ “ቀን አምላክ ሰውን እንዳልፈጠረ እያስተማረ ማታ ቤተክርስቲያን ሄዶ ‘አምላኬ ሆይ!’ እያለ ይፀልያል” ያለከው እኮ ነው፡፡ የሚታይ ጨለማ እኮ ነው የከበበን፡፡ እኛ ሐገር ትምህርት ለውጥ የፈጠረበት ሰው ቢኖር ኖሮ ነጮቹ ትልቅ ቀውስ እየፈጠሩብን እንደሆነ ተረድቶ ያስረዳን ነበር።

ከእለታት ሶስት ቀን ከ "ተ"እስከ "ፐ" ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ወድቄም አልቀረሁ ቀና ብየ አየሁ እርሷን ስመለከት መጥታለች ከፊቴ አይኗንም ስቃኘው አንብታለች ስንቴ አካሌን ስዳብስ በደም ተጨማልቋል መላ ሰውነቴ ምን ነካህ?አለችኝ አይኗን ጣል አድርጋ በመላ አካላቴ እኔም ምንም አልሆንኩ ብየ ትቻት ሄድኩኝ ቤቴ እቤቴ ገብቼ ተኛሁኝ ከአልጋየ ደሜ እየፈሰሰ አየሁት ዝም ብየ ምክንያቱን ባላቅም ይወርዳል እንባየ ሳገኛት ጨነቀኝ የማወራት አጣሁ ሳጣት ናፈቀችኝ አቀርቅሬ አነባሁ እርሷ ማናት ብየ ልረሳትም ሞከርሁ አልሆነም አልሆነም ምን ላድርግ በማለት ውስጤ እንደጨነቀኝ "በላይ"የሚለው ድምፅ ከህልሜ አባነነኝ ይህን ሁሉ መንገድ አይኔ የፈለገ እግሬ የዳከረ ለካ .... በእውን አለም ሳይሆን በህልሜ ነበረ ተፈፀመ!!!!!