en
Feedback
አጫጭር ግጥሞችና መጣጥፎች 📚

አጫጭር ግጥሞችና መጣጥፎች 📚

Open in Telegram

✔️📚ማንበብ ያሻግራል ❗️❗️❗️ በዚህ ቻናል እናንተን የሚመጥኑ የተለያዩ ግጥሞችን ፣ አጫጭር ና መሳጭ ታሪኮችን ታገኛላችሁ። እናንብብ ፤ በማንበባችን እናተርፋለን እንጂ ፤ ከቶ አንከስርም። @snetsehuf

Show more
546
Subscribers
+324 hours
+127 days
+5230 days
Posts Archive
ክርስቶስ ወ ገብረክርስቶስ (በቴዎድሮስ ካሣሁን) እዩት ይሔን ጠቢብ ሸራው እስኪደማ፡ በቀይ እየወጋ በደም እየሣለው፡ እንጨት አመሳቅሎ፡ ዳግም ክርስቶስን ጨርቁ ላይ ሰቀለው፡፡ ቀራንዮ ሆነ የወጠረው ሸራ፡ ጎለጎታ ሆነ የወጠረው ሸራ፡ አሁን እስኪመስል ስቃዩ እያስፈራ፡፡ ደም ከደም አረገው አበዛበት ጣር ብሩሹን አሹሎት እንደ ጎኑ ጦር፡፡ እየወጋ ሣለው፡ በጣም ጨከነበት፡ ገብረክርስቶስም ክርስቶስ ላይ ከፋ፡ የቆዳው ዓይነቱ በደም ተከልሎ ዘሩ እስከሚጠፋ እየወጋ ሣለው፡ እየሣለ ወጋው፡ ዘሩ እስከማይለይ መልኩ ዝም ብሎ ደሙ እስከሚናገር፡ የትም ያለ ፍቅር እንዳይኖረው አገር፡ እንዳንለው ፈረንጅ እንዳንለው ጥቁር፡ እንዳንለው ቀይ፡ በመስቀል ላይ ሞቶ ያየውን ስቃይ በቆዳ በቀለም እንዳናሳንሰው በደሙ ተሰቅሎ ሰው ያዳነውን ሰው፡፡ ከቀናት ባንዱ ዕለት፡ ሰዎች ሲሟገቱ በቀለሙ ጉዳይ፡ ሲከራከሩበት በተመፃዳቂ የምሑር አንደበት፡ ባንዱ አፍ ሲጠቁር፡ ባንዱ አፍ ሲነጣ፡ መታገስ አቃተው ሠዓሊው ተቆጣ! ሥሜቱ ገንፍሎ በብሩሽ ጫፍ ወጣ፡፡ ሐሣቡን የሚገልፅ ቀለም እስከሚያጣ፡ ሸራ ላይ ሰቀለው እንጨት አመሳቅሎ፡ አልወጣልህ አለው ፍቅርን ሥሎ ሥሎ፡፡ ሥሎ---ሥሎ----ሥሎ፡ ፍቅርን ሥሎ ሥሎ፡ በሣለው እየወጋ፡ በደማው እየቀባ፡ 'ክርስቶስ ደሙ እንጂ ዘሩ አልተሰቀለም እንጨቱ ላይ ያለው ዕውነት ይሔ አይደለም፡፡' እያለ እስኪናገር የሥዕሉ አንደበት ገብረክርስቶስም ለክርስቶስ 'ሚሆን ቀለም እስኪያልቅበት፡ በነጩ ሸራ ላይ እስካሁን የሚወርድ ደም አፈሰሰበት፡፡ ቀለም፡ ቀይ ቀለም የደም ቀለም፡ የጥላ ቀለም የሁሉም ነው'ንጂ የማንም አይደለም፡ ፍቅር ዘር አይደለም፡፡ ለሠዓሊና ገጣሚ ገ/ክርስቶስ ደስታ የተፃፈ 👌👌👌 @snetsehuf

በቲክቶክ የተለያዩ መጻሕፍትን የሚተነትን አጫጭር ዳሰሳ ጀምረናል ። follow us on tiktok tiktok.com/@fikrel7

በቲክቶክ የተለያዩ መጻሕፍትን የሚተነትን አጫጭር ዳሰሳ ጀምረናል ። follow us on tiktok tiktok.com/@fikrel7

ልዠ ሆይ (በእውቀቱ ስዩም) ትናንት በቀበና ወንዝ ዳር ስራመድ አንድ ከየካ ተራራ ላይ አቅጣጫ የመጡ ጠቢብ አዛውንት አስቆሙኝ ፤ እና የሚከተለውን ለቀቁብኝ፤ “ ልዠ ሆይ! መስከረም ማለት ተፈጥሮ ከጸጋዎቹዋ ሁሉ የክት የክቱን መርጣ የምታቀርብበት ወር ነው፤ ላይንህ አሪፍ ህብረቀለም፤ ላፍንጫህ መልካም መአዛ፥ ለጆሮህ ቆንጆ ጣእመ ዜማ መርኣ ትለግስሀለች! በዚህች አለም ውስጥ ለጥቂት ጊዜም ቢሆን እንድትኖር ስለተፈቀደልህ የምታመሰግንበት ወር መስከረም ነው! ማንነው የማመሰግነው አትበል ? አላህን፥ እግዜርን፥ ዋቃዮን፥ እመቤት ተፈጥሮን ፥ እናትህን ፥ ቆሌህን ፥ ሊሆን ይችላል፤ እንደ መሬት ታጋሽ ፥ እንደ ገበሬ ውለታ አስታዋሽ ሁን! ገበሬ ወረተኛ አይደለም” አትኩራ ገብስ ጎመን ባወጣው ነፍስ ይላል” ገብስ ስለደረሰለት የጎመንን ውለታ አያጣጥልም፤ መስከረም የፈንጠዝያ ወር ነው፤ ሰርተህ ባይሞላልህ ተበድረህ ፥ ተመጽውተህ ያቅምህን ያክል ደግስ ፤ የቻልከውን ያህል አካፍል ! ብላ አብላ! ህዝብ ለህዝብ ሳይሆን ብርጭቆን ከብርጭቆን ማጋጨት ተማር! መጠነኛ ስካር በራስህ ላይ አፋፍም! መስከረም ፤ የሚለው ቃል ስ "መስከርያ" ከሚለው ቃል እንደመነጨ ከቶ አትዘንጋ! ፍቅረኛህን ወይም እማወራህን አውዳመቱን አስተካከህ የከበረ ስጦታ ስጣት! ቤት ባትገዛላት ቤት የሚመታ ግጥም ጻፍላት ! በስስት ሳማት! በልዩ ፈሊጥ እቀፋት ፤ ከምኝታ ፈሊጦች ውስጥ” የእንግላል “ የተባለው ፈሊጥ ለአዘቦት ቀን ብቻ የሚያገለግል መሆኑን አትርሳ ፤ በአውዳመት እና ለክብረበአለት ቀናት ግን ፥ እንደ “ ወስፌ ጥምዝ” “ ምሳር ባንገቴ “ “አሞራ ገፍገፍ ፥ ጫንቃ ሰበር” አይነት ፐዚኖችን መጠቀም ተፈቅዷል፤ ይህንን ሁሌም በልቦናህ መዝገብ አስቀምጠው! ምርጥ የምትለውን ስጥ፤ ኮሚክ ከሆንክ ከባለጌ ወንበራችን ላይ ገፍትሮ የሚጥለንን ቀልድ ልቀቅብን! ዘፋኝ ከሆንክ ወፍ ብቻ ሳይሆን ኮከብ እሚያረግፍ ዘፈን ልቀቅብን ! የቲክቶ ተሳዳቢ ከሆንክ የቸኩ የተሰለቹ ስድቦችን ትተህ ሌላ አምጣ፤ ለምሳሌ፥ ሰገጤ፥ እከካም! ቆማጣ፥ ግማታም፥ ከብት ወዘተረፈ አይነት ስድቦች ከበቂ በላይ ጥቅም ላይ ውለዋል፤ ባዲሱ አመት ብትደግማቸው ስሜት አይሰጡም ! ስድብ ሲደጋገም ቁልምጫ ይመስላል፤ ባዲሱ አመት አባቶቻችን ሲጠቀሙባቸው የነበሩትን አንጋፋ ስድቦችን አድሰህ ተጠቀምባቸው ! ለምሳሌ፥ “ደንደሳም፥” ቅንዳሻም” “ “ ስብድብድ ፥” ዞፍ” እና “ ኩስለመናም “ የመሳሰሉ አጥንት ሰባሪ ስድቦች ከፈለግህ በተመጣጠነ ዋጋ ከኔ መውሰድ ትችላለህ! በተቻለህ መጠን በጎ አድርግ ፤ ተፈለጥ! አልፎ አልፎም አውቀህ ተበለጥ! ያም ሆኖ፥ የሙሉ ጊዜ ጣድቅ ለመሆን አትጋጋጥ! ተሳሳት፤ ያነተ መሳሳት ለፕሮፌሽናል መካሪዎች ፥ ኑዛዜ ተቀባዮች፥ ንስሀ ሰጪዎች፥ ተቺዎች፤ ከሳሾች፥ አሜተኞች ስራ እንደሚፈጥርላቸው አትርሳ!

👉‹‹ጀርል ምንድነው?›› ‹‹አንቺ ጀርል› የሚለውን ቃል ስታነቢ ‹ገርል› ብለሽ ነው፡፡ የተማርሽው ሴንት ሜሪ ነዋ፤ እኔ ‹ፍሬ ለብዙሃን ስለሆነ የተማርኩት ሳነብ ጀርል እያልኩኝ ነው፡፡ ቲቸር በለጠ ‹ገርል› የሚለውን የእንግሊዝኛ ሆሄያት ጥቁ ሰሌዳው ላይ ፅፈው በዘንጋቸው እየጠቆሙ ‹ጀርል! ጀርል!› እያሉ በተደጋጋሚ ያስጠኑናል፡፡ እኛም በልጅ አንደበት ድግግሞሹን እንላለን፡፡ ይሄኔ የትምህርት ቤታችን ዳይሬክተር ወደ ክፍላችን ዘው ብለው ይገቡና፣ ‹እንዴ በለጠ ጥቁር ሰሌዳው ላይ የፃፍከው ገርል› ነው የሚለው ለምን ‹ጀርል› እያልክ ታስጠናቸዋለህ?› ይሏቸዋል፡፡ ቲቸርም በ65 ብር ደሞዝ ገርል እያልከ እንዳስተምር ትፈልጋላችሁ እንዴ?›› 👉 ደራሲ.... ዘነበ ወላ 👉 መልህቅ... ገፅ....257 @snetsehuf

😍ይስጥሽ😍 (በዕውቀቱ ስዩም) እቴ… ይስጥሽ ከቁመቴ ከላዬ ቀንሶ ያስረዝምሽ አንቺን እኔን አሳንሶ ከሰጎን እረዝመሽ ስትቆሚ ከጎኔ ቁመቴን መጽውቼሽ ጫጩት ላክል እኔ፤ ይስጥሽ ከጸጉሬ ከአናቴ ላይ ዘግኖ ይገጠብ ራሴ ያንቺ ተጎንጉኖ አወይ ጸጉሯ ብለው ኮረዶች ሲያወሩ ድጥ ራስ ነህ ብሎ ይዝለፈኝ ሰፈሩ፤ እቴ… ይስጥሽ ከወዜ ላይ ጨልፎ ከፊቴ ይቅዳልሽ ከደሜ ጠልቆ ከጅማቴ ከአይን ያውጣሽ እያለ ሲመርቅ አድናቂ እስቲ እግዜር ይማርህ ይበለኝ ጠያቂ። እቴ… እጄን ብትፈልጊ እግሬን ብትፈልጊ አንገቴን ደረቴን ተሰጥኦ ሀሳቤን ያደምቀኛል ብለሽ ያሰብሺውን ሁላ እግዜር ከኔ ወስዶ ከሰጠሽ በኋላ ያስቀርልኝ አይኔን አንቺን ማየት ብቻ ያኖረኛል እኔን @snetsehuf

​​❍●●◦እኔ ወድሻለሁ◦●●❍ እኔ ወድሻለሁ፤ ታስሮ እንደመፈታት እንደጣኦስ ውበት፤ እንደ ዝሆን ብርታት ዳዊትን ከጎልያድ ፤ደርቦ እንደመምታት እኔ ወድሻለሁ፤ ጦም ውሎ እንደመጉረስ ወልዶ እንደመታረስ ቶምቦላ እንደመድረስ ካላሙዲን ንብረት፤ ግማሽ እንደመውረስ እኔ ወድሻለሁ፤ እንደ መቅደስ እጣን እንዳፍለኛ ስልጣን እኔ ያንች ቡዳ፤ ያንች ልዝብ ሰይጣን።. ✰ገጣሚ ፦በእውቀቱ ስዩም @snetsehuf

✔️📚ማንበብ ያሻግራል ❗️❗️❗️ በዚህ ቻናል እናንተን የሚመጥኑ የተለያዩ ግጥሞችን ፣ አጫጭር ና መሳጭ ታሪኮችን ታገኛላችሁ። እናንብብ ፤ በማንበባችን እናተርፋለን እንጂ ፤ ከቶ አንከስርም። @snetsehuf

የሳይኮሎጂ ፕሮፌሰሩ ወደ ክፍል ገብቶ የእለቱን ወሳኝ ትምርት ለመጀመር ወደ ቦርድ እንደዞረ ፉጨት ሰማ። ወደ ተማሪዎቹ ዞሮ ማን እንዳፏጨ ጠየቀቃቸው ፣ሁሉም ዝም አሉ። ፕሮፊሰሩ ተረጋግቶ ፣እስክሪቢቶውን ወደ ኪሱ እየከተተ ፣የዛሬው ሌክቸር እዚ ላይ ያበቃል፣ፈገግ ብሎ ነገር ግን መጀመሪያ አንድ ታሪክ እነግራችዋለው አላቸው።ሁሉም በጉጉት መጠበቅ ጀመረ " ትላንት ቤቴ እንቅልፍ ስላስቸገረኝ ፣ዝም ብዬ ተነስቼ ነዳጅ ልሞላም በዛውም ልናፈስ ለዛሬም ጊዜ ለመቆጠብ ከመሽ ወጣሁ ,ነዳጅ ከሞላሁ በኋላ ከትራፌክ ነጻ የሆነው መንገድ ላይ እየተንሸራሸርኩ ከሆነ ፖርቲ ነገር የወጣች የምትመል ቆንጂዬ ወጣት አየሁ። መኪናዬን አዙሬ እርዳታ እንደምትፈልግ ጠየኳት "ታክሲ እንዳጣች እና ቤቷ እንዳደርሳት ነገረችኝ" ጋቢና ገባች....ማውራት ጀመርን....ውበት ብቻ ሳይሆን ባወራነው ርእስ ሁሉ በጣም ስማርት ጭንቅላት እንዳላት ከምታወራው መገመት ቻልኩ። ቤቷ እንደደረስን ፣በጣም ጥሩ ሰው እንደሆንኩ ነገረችኝ፣እኔም ጥሩ አስተሳሰብ እንዳላት ነግሬአት እንደወደድኳት ነገርኳት፣ዩኒቨርስቲ ፕሮፌሰር እንደሆንኩ አውርተን ፣ስልክ ተለዋወጥን። አንድ ነገር ላስቸግርህ ስትለኝ ፣ምንም ችግር የለውም አልኳት ።"ወንድሜ አንተ የምታስተምርበት ዩኒቨርስቲ ተማሪ ነው፣በኛ ግንኙነት እንዳይጎዳ ቃል ግባልኝ" አለችኝ ....ችግር የለም ብዬ ስሙን ጠየኳት።አንድ መለያ ባህሪ አለው በሱ ታውቀዋለህ፣ፉጨት ማፏጨት ያዘወትራል። አለችኝ ከዛ ሁሉም ተማሪ ወደ አፏጨው ልጅ ዞሮ ማየት ጀመረ ፕሮፌሰሩ "የሳይኮሎጂ PHD ዬን አልገዛውትም፣ሰርቼ ነው ያገኘውት ና ውጣ " @snetsehuf

🔆🌼መልካም አዲስ ዓመት🌼🔆            አዲስዓመት      መልካምአዲስዓመት   መልካም        አዲስዓመት መልካም           አዲስዓመት መልካም             አዲስዓመት መልካም             አዲስዓመት                         አዲስዓመት                        አዲስዓመት                      አዲስዓመት                    አዲስዓመት                  አዲስዓመት             አዲስዓመት         አዲስዓመት       አዲስዓመት አዲስዓመት አዲስዓመት                አዲስዓመት አዲስዓመትአዲስዓመትአዲስዓመት አዲስዓመትአዲስዓመትአዲስዓመት              አዲስዓመት         መልካምአዲስዓመት መልካምአዲስዓመትአዲስዓመት አዲስዓመት              አዲስዓመት አዲስዓመት              አዲስዓመት አዲስዓመት              አዲስዓመት አዲስዓመት              አዲስዓመት አዲስዓመት              አዲስዓመት አዲስዓመት              አዲስዓመት አዲስዓመት              አዲስዓመት አዲስዓመት              አዲስዓመት አዲስዓመት              አዲስዓመት መልካም አዲስዓመትአዲስዓመት     መልካምአዲስዓመትስዓመት           መልካምአዲስዓመት                  አዲስዓመት                   ዓመት             አዲስዓመት መልካምአዲስዓመት             አዲስዓመት             አዲስዓመት             አዲስዓመት             አዲስዓመት             አዲስዓመት             አዲስዓመት             አዲስዓመት             አዲስዓመት             አዲስዓመት             አዲስዓመት             አዲስዓመት አዲስዓመትመልካምአዲስዓመት አዲስዓመትመልካምአዲስዓመት አዲስዓመትመልካምአዲስዓመት              አዲስዓመት         መልካምአዲስዓመት መልካምአዲስዓመትአዲስዓመት አዲስዓመት              አዲስዓመት አዲስዓመት              አዲስዓመት አዲስዓመት              አዲስዓመት አዲስዓመት አዲስዓመትመልካምአዓመት መልካምአዲስዓመትአዲትዓመት አዲስዓመት              አዲስዓመት አዲስዓመት              አዲስዓመት አዲስዓመት              አዲስዓመት አዲስዓመት              አዲስዓመት አዲስዓመት              አዲስዓመት መልካም አዲስዓመትአዲስዓመት     መልካምአዲስዓመትስዓመት           መልካምአዲስዓመት                  አዲስዓመት                                                             🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆🔆 🔆🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🔆 🔆🌼🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🌼🔆 🔆🌼🔸🕊🌻🌻🌻🌻🌻🕊🔸🌼🔆 🔆🌼🔸🌻🌻 መልካም 🌻🌻️🔸🌼🔆 🔆🌼🔸🌻🌻  አዲስ    🌻🌻🔸🌼🔆 🔆🌼🔸🌻🌻  ዓመት    🌻🌻️🔸🌼🔆 🔆🌼🔸🌻️🌹⁣🌾🌻💐🌹🌻🔸🌼🔆 🔆🌼🔸🕊🌻🌻🌻🌻🌻️🕊🔸🌼🔆 🔆🌼🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🌼🔆 🔆🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 @snetsehuf

Happy New Year መልካም አዲስ ዓመት 🕊🌻🌻🌻🌻🌻🕊 🌻🌻 መልካም 🌻🌻️ 🌻🌻 አዲስ 🌻🌻 🌻🌻 ዓመት 🌻🌻️ 🌻️🌹⁣🌾🌻💐🌷🌻 🕊🌻🌻🌻🌻🌻️🕊
Happy New Year መልካም አዲስ ዓመት 🕊🌻🌻🌻🌻🌻🕊 🌻🌻 መልካም 🌻🌻️ 🌻🌻 አዲስ 🌻🌻 🌻🌻 ዓመት 🌻🌻️ 🌻️🌹⁣🌾🌻💐🌷🌻 🕊🌻🌻🌻🌻🌻️🕊

❝ ሁሉም ነገር ለበጎ ነዉ ❞ "አንድ ንጉስ ከአጃቢው ጋር በመሆን ለአደን ይወጣል። ለአደን ሲወጡ ንጉሱ ወጥመድ እያጠመደ እያለ ወጥመዱ አምልጦት እጁን ቆረጠው። በዚህም አጃቢው በማዘን "አይዞህ ንጉስ ሆይ ሁሉ ነገር ለበጎ ነው!" ይለዋል። በዚህም ንጉሱ በንዴት እየጦፈ "የኔ እጅ መቆረጥ ነው ለበጎ?" ይለውና እስር ቤት አሳሰረው። ከብዙ ጊዜ በኋላ ንጉሱ ብቻውን ሀገሩን ሲዞር ሰው አርደው ለጣዖት መሰዋት የሚያደርጉ ጨካኝ ሰዎች ያዙትና አርደው መሰዋት ሊያደርጉት ሲሉ ቆራጣ እጁን አዩት። በእነሱ ህግ መሰዋት የሚያደርጉት ሰዉ ሙሉ ጤነኛ መሆን ስላለበት ለቀቁት። ንጉሱ አጃቢው 'ሁሉ ነገር ለበጎ ነው!' ያለው ትዝ አለውና እስር ቤት ሄዶ ስላሰርኩህ ይቅርታ አርግልኝ! ብሎ ታሪኩን አጫወተው። አጃቢውም "ማሰርህ ለበጎ ነበር! እኔም መታሰሬ ጠቅሞኛል።" አለው። ንጉሱ "እንዴት?" አለው አጃቢውም "ባልታሰር ኖሮ ከአንተ ጋር እሄድና አንተ ቆራጣ መሆንህን ሲያውቁ ይለቁህና አኔን ይገሉኝ ነበር" አለው። @snetsehuf

መስታወት ፊት ቆሜ እንዲህ እላለሁ (በእውቀቱ ስዩም) "በለስ ፍሬ ባትሰጥ" ፤ሎሚ መሽተት ቢሳናት ኤሊ ላባ ብትለብስ ፤ ወፌን ድንጋይ ቢጫናት ሰማይ እንዳለት ቢወቀር ጊዜ ደክሞት ቆሞ ቢቀር ጨረቃ አመድ ብትቅም ፀሀይ ጥርሷን ብትለቅም ስልጣኔን ነቀዝ በልቶት ፤ ኦና ቢሆን አገር ምድሩ ፒራሚዶች ባንድ ሌሊት፤ የኩበት ክምር ሆነው ቢያድሩ ተፈጥሮ ለህዝብ ቅነሳ ሰው በሰው ላይ ብታስነሳ አንዱ ካንዱ ቢታረረድ ጠፈር በከል ቢጋረድ ሙሴን ባህር ቢበላው፤ የኖህ መርከብ ቢሰጥም ህይወት ምስጢር ባትገልጥም የድል ድርሻየን ጥዋ፤ ጭላጭ ሳይቀር እስካጣጥም የምሻውን እስከማገኝ፤ ለመሸነፍ እጅ አልሰጥም እንኳን ተስፋ ፤ ጢም አልቆርጥም:: @snetsehuf

ዝግ ዓለም (በ.ሥ) ከትራሴ ግድም ፤በተደፋው ሰማይ ኮከብ እያበራ ፤በመከዳየ ላይ ምንም አላነበብኩ ፤ከህዋው ግድግዳ እውነትና ንጋት፤ እያደር እንግዳ፡፡ (ከስብስብ ግጥሞች) @snetsehuf

በእሾህ መንገድ መሀል (በእውቀቱ ስዩም) ያገሩ አየር ጠባይ፥ ቆላ ወይን -አደጋ ከላይ የሚያስፈራ፥ ከታች የሚያሰጋ ፥ አጉል ነው መንገዱ ቅጽሩም ሲገዝፍ ያድራል፥ በቁመት በወርዱ፥ እና ምን ይጠበስ? የማይቆም ጅረት ነኝ፥ የማይቀለበስ :: ቢገፏት ቢያዳፏት ከቅርንጫፏ ጋር የማትነጣጠል በወጀብ መሀከል፥ የምትደንስ ቅጠል፤ እንደዚህ ነኝ እኔ ምቾትስ ለምኔ ቀይ ምንጣፍ አያምረኝ ይመስገን ዘመኔ በእሾህ መንገድ መሀል፥ መጓዝ ላስተማረኝ :: @snetsehuf

ሃቺኮ፡ የዓለማችን እጅግ ታማኙ ውሻ 100ኛ ዓመት ተዘከረ “ምንም ያክል ጊዜ ይፍጅ እጠብቅሃለሁ” ይህ አገላለጽ እውነተኛውን የሃቺኮ ታሪክ ያስታውሳል። ሃቺኮ ውሻ ነው። ለባለቤቱ እጅግ ታማኝ የነበረ ውሻ። ሃቺኮ አንድ ልማድ ነበረው። ባለቤቱን ባበሩር ጣቢያ ላይ ጠብቆ ከዛ ወደ ቤት አብሮ መሄድ። ባለቤቱ ድንገት ሕይወቱ አለፈ። ሃቺኮ ግን ሰውዬን ለዓመታት ባቡር ጣቢያ ጋር ቆሞ ጠብቆታል። ይህ ውሻ የተወለደው የዛሬ 100 ዓመት ነበር። የውሻው ታሪክ በፊልም እና መጽሐፍ ሚሊዮኖች ጋር ደርሷል። ቶኪዮ በሚገኘው ባቡር ጣቢያም ሃውልት ተቀርጾለት የበርካታ ጎብኚዎች ቀልብን እንደሳበ ነው። ጃፓናውያን ተማሪዎች በትምህር ቤቶች ውስጥ ታማኝነትን ከሃቺኮ ተማሩ ይባላሉ። የሃቺኮ ታሪክ አኪታ የተባለ የውሻ ዝርያ የሆነው ሃቺኮ የተወለደው በ1923 በጃፓኗ ከተማ ኦዳቴ ነበር። ዝርያቸው አኪታ የሆኑ ውሾች የተረጋጉ፣ ብልህ፣ ደፋር እና ለባለቤቶቻቸው ታማኝ የሆኑ ውሾች መሆናቸው ይገለጻል። ሂሴሳቡሮ ኡኤኖ የተባሉ አንድ የግብርና መምህር እና ውሻ አፍቃሪ ተማሪዎቻቸው የአኪታ ዝርያ የሆነ ቡችላ እንዲፈልጉላቸው ይጠይቃሉ። ሃቺኮን አገኙ። ከረዠም የባቡር ጉዞ በኋላ ሃቺኮ ከመምህሩ መኖሪያ ቤት ይደርሳል። ቡችላው ከመምህሩ ቤት ሲደርስ እጅግ ከመዳከሙ የተነሳ የሞተ መስሎ ነበር። መምህሩ እና ባለቤታቸው ሳይሰላቹ ለተከታታይ ስድስት ወራት ለቡችላው እንክብካቤ አድርገው የውሻው ጤና ተመለሰ። መምህሩ ኡኤኖ ለአዲሱ ቡችላቸው ሃቺ (በጃፓንኛ ስምንት ማለት ነው) የሚል ስም ሰጡት። ‘ኮ’ የምትለው ቅጥያ በመምህሩ ተማሪዎች የተሰጠች ነች። @BBC Amharic

ከበዓሉ ግርማ ስድስት ረዣዥም ልብወለዶች ውስጥ ዝነኛው ኦሮማይ ነው፡፡ ኦሮማይ፤ በ1975 ዓ.ም. በማንኩሳ አሳታሚ ለህትመት ብርሃን በቃ፡፡ ርዕሱ ‹‹አለቀ፣ አበቃ፣ ደቀቀ›› የሚል ፍቺ የሚሰጥ የትግርኛ ቃል ሲኖረው፤ መጽሐፉ የሚደመደምበት ቃልም ጭምር ነው፡፡ መጽሐፉ የደርግ መንግሥት ‹‹የኤርትራን ችግር›› ለመፍታት ባካሄደው የቀይ ኮከብ ዘመቻ ወቅት የጋዜጠኝነት ሙያ ግዳጁን ለመወጣት ዘመቻውን የተቀላቀለ ጋዜጠኛ ላይ ያተኩራል፡፡ በዓሉ ራሱ በመጽሐፉ እንደሚመሰክረው የጸጋዬ ኃይለ ማርያም ቁንጽል ታሪክ ነው፡፡ ታሪኩ ከመጀመርያ መደብ አንጻር በራሱ በጸጋዬ ሲተርክ፤ መኃል መኃል ላይ ደግሞ ‹ደራሲው› በሶስተኛ መደብ ጸጋዬ ማየት የማይችላቸውን እና መገኘት የማይችልባቸውን ቦታዎች ይተርካል፡፡ ይህም በአብዛኞቹ ደራሲዎች ያልተለመደ ከመሆኑም ሌላ የጸጋዬን አስተሳሰብ እና ስሜትን መረዳት ሳይጎድልብን ሌሎች ገጸ ባህርያትና ሁነቶች ጋር በደንብ እንድንተዋወቅ ይረዳናል፡፡ መቼቱን 1974 ዓ.ም. በተለያዩ የኤርትራ ከተሞች ይበልጡን ግን በአስመራ ያደረገው ኦሮማይ በመጀመርያዎቹ ጥቂት ገጾች ብቻ አዲስ አበባ ይነካል፡፡ በቀይ ኮከብ ዘመቻ ላይ የተሳተፉ ባለስልጣናትን፣ ወታደሮችን፣ ‹ገንጣይ አስገንጣይ› ተብለው የተፈረጁ ቡድኖችን እንዲሁም የህዝቡን ስነልቦና በጥልቀት የሚዳስስ ነው፡፡ የጦርነትን መራርነትም በሰፊው ያወሳል፡፡ ከፖለቲካዊ እና ታሪካዊ ጎኑ በተጨማሪ ዘመን ተሻጋሪ የሆነውን የጸጋዬ የፍቅር ታሪክ የተተረከበትም ነው፡፡ ጸጋዬ በአዲስ አበባዋ ሮማን እና በአስመራዋ ፊያሜታ መካከል የፍቅር አጣብቂኝ ውስጥ ገብቶ ሲሰቃይ ይታያል፡፡ አንዳንድ የስነ ጽሁፍ ባለሙያዎች ይህ አጣብቂኝ የማዕከላዊ መንግስት ከኤርትራ ጋር የነበረውን ቁርኝት እና እልህ ሁለቱንም ሊያሳጣው እንደሚችል የሚያሳይ ፈሊጥ ነው ይላሉ፡፡ ኦሮማይ በታተመ በጥቂት ጊዜ ውስጥ ባለስልጣናትን በማጋለጥ እና የአብዮቱን ስም በማጉደፍ በሚል ምክንያት ከህትመት ታገደ፡፡ በወቅቱ የማስታወቂያ ሚኒስቴር ሰራተኛ የነበረው በዓሉ ግርማም ከስራው ተሰናበተ፡፡ እነኚህ ሁሉ በሆኑ በጥቂት ጊዜያት ውስጥም በዓሉ ግርማ በወጣበት ቀረ፡፡ እስከዛሬም ምስጢሩ አልተፈታም፡፡ ኦሮማይ ግን ከስምንት የእግድ ዓመታት በኋላ በ1984 ዓ.ም. በድጋሚ ለህትመት በቃ፡፡ እስከዛሬም እየታተመ እና እየተነበበ ነው፡፡ በተነበበ ቁጥር አዲስ ነው፡፡ አንዳንዴ ስለፍቅር ሌላ ጊዜ ስለጦርነት ሌላ ጊዜ ስለሐገር ደግሞ ስለታማኝነት ደግሞ ስለመገፋት እና ሀዘን ብቻ ብዙ ብዙ ሐሳቦች ያነሳል ይጥላል፡፡ ከሐሳቦች በተጨማሪ የከተሞቹን ውበት እና የሰውን አኗኗር በሚገባ የሚያስረዳ መሆኑ በአእምሮ ምስል ከሳች ነው፡፡ በርካቶች የኤርትራን ምድር ባይረግጡ እንኳ ምስጋና ለኦሮማይ ይሁንና ስለ ኤርትራ ድባብ ሐሳብ አላቸው፡፡ የስነ ጽሁፍ ውበቱን ረጃጅም ውይይቶች እና ስብሰባዎች እንደሚያደበዝዙት አይካድም፡፡ በአንድ ልብወለድ ውስጥ መገኘቱን ማመን እስከሚያቅተን ድረስ የሚያሰላቹ ፕሮፓጋንዳዎች እና ንግግሮች አሉት፡፡ ደራሲው ወቅቱን በትክክል ለመግለጽ ያደረገው ጥረት ቢሆንም መጽሐፉን ጠየም እንዳደረገው ግን አሌ የማይባል ሐቅ ነው፡፡ ከሁሉ በላይ ኦሮማይን ኦሮማይ ያደረገው ግን እውነት ማከሉ ነው፡፡ ባንወደውም ልንቀበለው ባንፈልግም ገሀዱ ፍጥጥ ብሎ ይታያል፡፡ እውነት መሆኑም ጭምር ነው በዓሉ እንዲሰወር ያደረገው፡፡ ምናልባት አንባቢዎች ሐቁ ልቧን ስብር እንዳደረጋት እንደ ሮማን ወይም አንደ ጸጋዬ ነን፡፡ ኦሮማይ ሕይወትን ያክላታል:: ስለ ኦሮማይ እና በዓሉ ምን ትሉናላችሁ? ለደራሲው ያላችሁን ክብር በ ኮሜንት ግለጹልን from NeBeb Facebook page

የወንድ ዱላ የሴት መላ (በእውቀቱ ስዩም) ስለ ጠለፋ በተነሳ ቁጥር ብልጭ እምትልብኝ ታሪክ አለች፤ የባለቅኔ መንግስቱ ለማ አባት አለቃ ለማ ተርከዋታል፤ ጊዜው በዘመነ መሳፍንት ሳይሆን አይቀርም፤ ከመንግስት የታዘዘ ጦር ከበጌምድር ወደ የጁ እየተመመ ነው፤ ሰራዊቱ ዋድላ ላይ ሲደርስ የሰራዊቱ መሪ አይናቸው አንድ ነገር ላይ አረፈ : : አንዲት ትንሽ ልጅ ከጓደኞቿ ጋራ ከገበያ ትመለሳለች፤ የጦሩ መሪ ሲያይዋት አለቅጥ ጎመዡ፤ አሸከራቸውን “ ያዝና ጫንልኝ “ ብለው አዘዙት፤ አሸከርየው እየጋለበ ደረሰባትና ብድግ አድርጎ ፈረሱ ላይ አፈናጠጣት ፤ ጓደኞቿ አካባቢውን በጩኸታቸው አቀለጡት : : እድለቢሷ ብላቴና ከደብረታቦር በታች ወደ ሚገኝ አገር ተወሰደች፤ የበጌምድሩ መኮንን ልጆችን አስወለዳት፤ በጥንቱ ልማድ ተጠላፊዋ ሀይለኛ ዘመድ ካላት በጠላፊ ላይ ይዘምታል፤ በዚህ ምክንያት ድንብን ያለ ጦርነት ሊቀሰቀስ ይችላል ፤ የዚች ልጅ አባት ግን ለውጤ ሀይሉ የተባሉ አንድ የዋድላ ደብተራ ነበሩ፤ አቅማቸውን ገምተው ዝም ያሉ ይመስላል፤ ተጠላፊዋ ባለችበት ሆና አገርዋን ልጅነቱዋን እና ቤተሰቧን ስትናፍቅ ኖረች፤ አንዳንድ ጊዜ የሆነ የቆሎ ተማሪ ደጇ ላይ ቆሞ “ በእንተ ማርያም ‘ብሎ ሲለምን ትሰማለች፤ እንጀራ ይዛ ትወጣና፥ “ከየት አገር ነው የመጣህ?” “ ከመቄት" “ለውጤ ሀይሉ የሚባል ሰው ታውቃለህ?" “ እሳቸውን ማን እማያውቅ አለ! እንደ ወንድማችን ናቸው “ “አባቴ ነው፤ ስታገኘው መጥተህ አትወስደኝም ወይ በልልኝ ! “ አባትየው ግን ገስግሰው መጥተው አልወሰዷትም፤ ተራኪው ከላይ በራሴ አማርኛ ያቀረብሁትን ታሪክ ሲደመድሙ እንዲህ በሚል ልብ ሰባሪ ቃል ነው፤ “’ እንዲህ እንደ ለፈለፈች ሞተች” 2 ታሪካችን ባያሌው የጦርነት ነው ፤ በጦርነት ያሸነፈው የተሸናፊውን ንብረት እና ሚስት ይማርካል፤ ዳግማይ ቴዎድሮስ በሀያልነታቸው አነጋግ ላይ የሸዋን ግዛት በጦር አስገበሩ፤ ያጤ ምኒክን አባት የሸዋው ንጉስ ሀይለመለኮት የድል አድራጊውን ፊት ከማየታቸው በፊት ታመው አረፉ: : ቴዎድሮስ በተሸናፊው ቤት ሰተት ብለው ገቡ፤ ሀይለመለኮት ሁለት ሚስቶች ጥለው ሄደዋል ፤ የመጀመርያዋ የምኒልክ እናት ወይዘሮ እጅጋየሁ ሲሆኑ ሁለተኛይቱ ወይዘሮ ትደነቂያለሽ የተባሉት ወይዘሮ ናቸው ፤ ትደነቂያለሽ እጅግ ውብ ነበሩ ይባላል፤ ቴዎድሮስ ባልየውን ሊማርኩ መጥተው በሚስቲቱ ተማረኩ፤ ግን ፍቅር አለዝቧቸው፥ አሽከራቸውን “ ያዝና ጫናት “ ለማለት ሳይደፍሩ ቀሩ፤ “ እቴጌ! በጌምድር አብረን እንሂድ” ብለው ጋበዟቸው፤ ሴት ያልፈለገችውን ሀይለኛ ወንድ የምታመልጥበት መሳርያ አላት፤ ያ መሳርያ መላ ወይም በሾፐንሀወር አገላለጽ “ ማታለል “ሊሆን ይችላል፤ ወይዘሮ ትደነቂያለሽ የአሸናፊውን ንጉስ ልብ በሚያቀልጥ ፈገግታ የታጀበ መልስ ሰጡ፤“ደስ ይለኛል ፤ ግን ከዛ በፊት ኢየሩሳሌምን ተሳልሜ ለመመለስ አስቢያለሁ፤ ይፍቀዱልኝ “ ንጉሱ ስንቅ ሰጥተው፥ አጃቢ ጨምረው ወደ እየሩሳሌም ሸኗቸው፤ ውቢተን ሸኝተው ወደ ቤታቸው ሲመለሱ የሀይለመለኮት እናት ወይዘሮ በዛብሽ ፤ “ሸዋ እንዲገብር እርዳታ አድርጊያለሁና ሹመት ይስጡኝ “ ብለው ጠየቁ፤ በዚህ ጊዜ ነበር አሸናፊው ንጉስ ከወደ ኢየሩሳሌም መርዶ የሚያክል ዜና የመጣላቸው፤ "ወይዘሮ ትደነቂያለሽ “ከሀይለመለኮት ወድያ አለም አልሻም ብለው መንነዋል “ ይህንን ሲሰሙ ቴዎድሮስ ይቺን ግጥም ወደ ታሪክ ወረወሩ፤ “አወይ ጉድ ሚስቱ መናኝ እናቱ ሹመት ለማኝ “ ታሪክ መዝጋቢው ዘንግቶት ይሆናል እንጂ ግጥሙ “ እኔን ብሎ ሰው አማኝ “ ብሎ የሚደመደም ይመስለኛል : : @snetsehuf

ርዕስ የለውም " ኤልያስ ሽታሁን ⛴⛴⛴ #አታውቂም 〔 -ገፅ 110 〕 አታውቂም.... ከጠረንሽ ጋራ ፥ ሱባኤ እንደገባሁ፤ አታውቂም! “ወንድ አይደል እንዴ” እስኪሉኝ ድረስ፥ ቁጭ ብዬ እንዳነባሁ። አታውቂም! ባገኘሁት ዘፈን፥ ሆድ እንደሚብሰኝ፤ አታውቂም! ስለአንቺ ለማሰብ፥ ዘመን እንደሚያንሰኝ። አታውቂም! ከለበስሽው ጋራ፥ መቀመጥ ማምሸቴን፤ አታውቂም! እኩያ እስከማጣ፣ ብቻዬን መቅረቴን። አታውቂም!        ፧        ፧ አታውቂም!        ፧ ብታውቂም፥ አትመጪም፤ አትመጪም፥ አታውቂም፤ ምን ብዬ ልፀልይ፥ ከሕይወቴ ይዤ ቂም። @snetsehuf