en
Feedback
ቃሊቲ ቅ/ገብርኤል ወጣቶች ህብረት + መዝሙር ቻናል +

ቃሊቲ ቅ/ገብርኤል ወጣቶች ህብረት + መዝሙር ቻናል +

Open in Telegram
265
Subscribers
No data24 hours
+67 days
+4630 days
Posts Archive
ደስ ይበለን ዛሬ ደስ ይበለን  በጣም የመከራው ሌሊት ፈተናው ቢከብድም ይኸው ለዚ በቃን ይክበር መድሐኒአለም አዝ ደስ ይበለን    እንዳያልፉት የለም               ያም ዘመን ታለፈ እግዚአብሔር  ልጆቹን ደረሶ እየደገፈ                 በቀንና ሌሊት                  አብሮን እየሰራ እንደ ፀሃይ ፀዳል ገፃችን አበራ አዝ ደስ ይበለን       ጥበበኛው ንጉስ                      ባለፀጋ ጌታ እንደ ባለማረግ አቆመን በተርታ           ያንሰዋል ምስጋና           ያንሰዋል ወዳሴ ያስተማረን አምላክ  የአብርሃሙ ሥላሴ አዝ ደስ ይበለን      በትንሽ ትልቁ እየሰገን ሳለ ሁሉም ነገር ሆነ እግዚአብሔር እንዳለ ቀሚስ አክሊላችን አምሮበታል ዛሬ ምድር ያስተጋባ ታላቁን ዝማሬ አዝ ደስ ይበለን   ማን እንደ እግዚአብሔር                    ማን እንደ አምላካችን በሀዘንም በደስታ ለኛ መፅናኛችን                  ክብር ላንተ ይሁን                  የደመቀ እልልታ ይንን ቀን ባርከህ ለሰጠኸን ጌታ

👇መልዕክት👇 እንኳን ለፆመ ፍልሰታ በሰላም አደረሳችሁ እንደተለመደው ከነሐሴ 1 (ረቡዕ) ጀምሮ ማታ ከ12:00 -1:00 የሚቆይ 16ቱን ቀናት የህብረት ፀሎት ስለተዘጋጀ ሁላችንም በፆሎቱ እንሳተፍ። የበረከት ፆም ያድርግልን

+2
✞ እንወድሻለን ኪዳነ ምህረት ✞ ለእግዚአብሔር ታቦቱ መቅደሱ ቀርበናል ባንቺ ወደ ንጉሱ የክብራችን ጌጥ ሽልማት እንወድሻለን ኪዳነምህት በጨለማው ላለ ብርሃንን አየ ለርስቱ ተካፋይ እንዲሆን ተለየ ወደ ቀድሞ ክብሩ ሊመለስ ዳግመኛ አንቺ ነበርሽ ተስፍው ለአዳም መዳኛ         አዝ= = = = = ያንን ሁሉ ዘመናት የፈሰሰው ደም አለምን ከእስራት ሊፈታ አልቻለም ወደ ሚሻል ኪዳን በደም ሊያሻግረን ደምሽን ተዋህዶ መዳኃኒ አለም ዋጀን         አዝ= = = = = አለን ብዙ ምክንያት አንቺን ምንወድበት ዓለም ያልተረዳው ያላወቀው እውነት ያወቀ የተረዳ የመዳኑን ሚስጢር አያፍርም ክብርሽን ቆሞ ለመናገር         አዝ= = = = = አውቃለሁ እግዚአብሔር የሰጠሽን ክብር ላመስግንሽ እኔም  ሳልቀንስ ሳልጨምር ሚባርክሽ ብሩክ ነውና እናቴ ኪዳነ ምህረት ንገሽ እመቤቴ                 መዝሙር         ዲያቆን አቤል መክብብ

✞ የከበረ ስሙን የከበረ ስሙን እንድታስከብር ጠላት ዲያብሎስን እንድታሳፍር አንተን የመረጠ እግዚአብሔር ይክበር ገድልህን ልናገር ጊዮርጊስ አባቴ ፅናትህ አስቀናኝ ልቁም በሀይማኖቴ የሄድክበት መንገድ ቢሆንም ጠባብ ልቤን ማሳረፊያ ሆኖኛል መደብ       መንፈሳዊ ጀግና ጠላት ያልገታህ       ሰይጣንን ተዋጋ ጎልማሳው ስጋህ   አዝ_    በኃያሉ እግዚአብሔር ፀንቼ አምናለሁ ሁሉን ለፈጠረ አምላክ እሰግዳለሁ የስቃይ መሳሪያ አያስፈራራኝም እኔ ክርስቲያን ነኝ ወደኋላ አልልም አዝ_ በብረት ጫማ እግርህ ሲቸነከር ስርህ ተበጣጥሶ ጉልበትህ ሲሰበር አጎንብሰህ ስትሄድ መቆም አቅቶህ ወጣቱ ጊዮርጊስ ለፍቅር ብለህ መከራው ቢፀና ጊዮርጊስ ታግሶ ቀራንዮ ሄደ በልቡ ገስግሶ አዝ_ ህመሙ ርቆለት ታግሶ ቢታየው ደግሞ ሊያሰቃየው ዱዲያኖስ ጠራው በጋለ ብረት ድስት አምጥተው ቀቀሉት አንጎሉ እስኪፈርስ በመዶሻ መቱት ጊዮርጊስ ስቃይህን መናገር አቃተኝ ሰውነቴም ፈራ ልቤንም ጨነቀኝ ╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮   @Yemezmur_Gitimoche ╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯

🌹 “ማርያም ማርያም“ 🌹 ማርያም ማርያም ልበል እረፍቴሆይ በስምሽ ልጠለል የቃል እናት ያድናል ቃልሽ ታምር ይሰራል ስምሽ #አዝ__ ማር ልበል በምድር ያም ልበል በሰማይ የማይጠግቡት መና የማይጨርሱት ሲሳይ መንፈስ ቅዱስ ቃኝቶ ሰርቶ በሚስጥሩ አፌ ላይ ጣፈጠኝ ስምሽ አጠራሩ (2) #አዝ___ መዳኒት ታቅፈሽ  የአለሙን ጌታ ከቤተልሄም ደጅ እስከ ጎለጎታ የዓለሙን ህምም የዓለሙን በሽታ ታክሚው ነበረ ድንግል በዝምታ (2) #አዝ___ በምን እንመስልሽ የለሽም ምሳሌ አንጠግብም ብንጠራሽ ብንዘምርልሽ ሁሌ ምስክር አያሻም ያንቺ ልእልና የአለሙን ንጉሥ ወልደሺዋልና (2) #አዝ___ የወርቅ ማእጠንት እሳት የታቀፍሽ የአዲስ ኪዳን ኪሩብ ማርያም አንቺ ነሽ የአርያም እጣን ነሽ መአዛሽ ያማረ ዘላለም አይወድቅም አንቺን ያከበረ (2)

👇 መልዕክት👇 ሐሙስ ሐምሌ 11 ቀን ከ12:00 ጀምሮ ሁሉም የህብረቱ አባል በተገኘበት የፊታችን ሐምሌ 19 ለሚከበረው የቅዱስ ገብርኤል ክብረበዓል እንዴት ማገልገል እንዳለብን የአገልግሎት ገለፃ እና መመሪያ ይሰጣል ። ስለሆነም ሁላችንም ጥሪውን በማክበር እንገኝ !! ♦️ማሳሰቢያ♦️ ማንኛውም የህብረቱ አባል የሆነ ሁሉ መገኘት እንዳለበት በቅዱስ ገብርኤል ስም እናሳስባለን።

ሶበሰ ኪዳንኪ ምክንያተ ድኂን ኢሀሎ/2/ ፈለገ እሳት ወደይን እም አሰጠመ ኩሎ /3/

#አለማመኔን_እርዳው አለማመኔን እርዳው ጌታዬ/2/ አንተ ነህና መሸሸጊያዬ አለማመኔን እርዳው ጌታዬ ፍሬ ያላዘልኩኝ ብሆንም ጎስቋላ ነፍሴ አብራህ ትኑር በማደሪያህ ጥላ አታውጣኝ ከቤትህ ባጣም ቅድስና ይህቺን አመት ተወኝ ጉልበቴ እስኪጸና     አዝ===== ያልጸናው ሕይወቴ ቢያስቸግረኝ ላልቶ እስኪቆም ታገሰኝ ጉልበቴ በርትቶ እንደ ቃልህ ባልኖር ደስም ባላሰኝህ ዛሬም ከኔ ጋር ሁን በጸናው ኪዳንህ     አዝ===== ለምጼ እጅግ በዝቶ ከሰዎች ብገለል ልትዳስሰኝ ፍጠን ምሕረትን ልታደል ደባልቀኝ ከመንጋው ከበረታው ወገን አዘንብል ወደኔ በፍቅርህ ልሸፈን     አዝ===== መዓዛዬን ለውጥ ጠረኔን ቀይረው እንደ ናርዶስ ሽቶ የከበረ አድርገው ቅረበኝ በፍቅርህ በደሌን ትተኸው ሳበኝ በምሕረትህ ፊቴን ደስ አሰኘው

#ሰላሜ_በአንተ_ነው    ሰላሜ ባንተ ነው የኔ ጌታ እረፍቴ ባንተ ነው የኔ ጌታ አልከለከል ምስጋና አልከለከል ውዳሴ ለአንተ ውለታ ጨለማዬ በአንተ በራልኝ ከሰው ትከሻ ወረድኩኝ የምመራበት ዱላዬ በአንተ ተጥሏል ጌታዬ    አሁን በግላጭ አያለሁ    ሙሉ ሰው ባንተ ሆኛለሁ አዝ= = = = = የመውገሪያው ድንጋይ ቀረልኝ ጠላቴ በፊቴ አፈረልኝ በፊትህ አቆምከኝ በጸጋ ገዝተኸኛልና በዋጋ     ለውለታህማ ምን እላለሁ     ተመስገን ብዬ አልፈዋለሁ አዝ= = = = = ሰላላውን እጄን አቅንተሃል ሽባነቴንም ተርትረሃል ደካማነቴ ተወገደ ያክፉ መንፈስ ተሰደደ    ታውጆልኛል ነፃነቴ    አመልክሃለሁ በሕይወቴ አዝ = = = = = የአይኔ ላይ ቅርፊት ወለቀ ሸክሜ ከላዬ ወደቀ በደማሰቆ ብርሃን መራኸኝ የራስህ ምርጥ ዕቃ አረግከኝ    ያከንቱ ድካሜ አለፈ    ልቤ ለፍቅርህ ተሸነፈ    ሁላችንም በሥላሴ ስልጣን አምነን በአንድነት እንዘምር እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን    መዝ 150:6  

አምነንህ ተነስተናል ስምህን ይዘን ፍቅርህን ማዳንህን ተስፋ እያደረግን አብረኸን ስትወጣ እናሸንፈለን ቀኝህ ስትረዳን ምድርን እንወርሳለን አብርሃም አመነ ፀደቀች ህይወቱ ቃለህን ሰምቶ ወጣ ከዘመድ ከሀብቱ ጌትነትን አምኖ ታዞ ስለኖረ በነፍስም በስጋ መንገዱ ሰመረ ማለፍ እንችላለን የእሳቱን ቅጥር ያመነው ታማኝ ነው የማያሳፍር ከዮርዲያኖስ ማዶ ተረስተን አንቀርም ቃል የገባልንን ሳንወርሰው አንሞትም ነገስታት ድል ነሱ ከሰይፍ አመለጡ የአንበሳን አፍ ዘጉ ከእሳት ውስጥ ወጡ ሁሉን ነገር ትተው በስምህ መነኑ ከበሩተሾሙ አንተን ስላመኑ ጀልባችንን ቀዝፈን ከመሃል ደርሰናል መረባችንን በቀኝህ ጥለናል ከንቱ ሆኖ እንዳይቀር ልፋት ድካማችን ፍፃሜው እንዲያምር እርዳን አምላካችን

ዝቅ ብዬ ላመስግነው ጉልበቴ ነው ላወድሰው የፍቅሩ እሳት ልቤን ነክቷል የድል ዜማ ባፌ ሞልቷል ምን አገኘህ ሰው ይለኛል ላያኖረኝ ይጨነቃል መኖርያዬ በሰማይ አባት አለኝ ኤልሻዳይ አባትና ንጉስ ጌታ ቅዱስ በነብስ ህይወቴ ነው ክርስቶስ ተራመድኩኝ በጉልበቴ ስላቆመኝ ደጉ አባቴ እሩቅ አይደል ቅርቤ ላለው ምስጋናዬ ለርሱ ይድረሰው አባትና ንጉስ፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፧፦፦፦፦፦፧፧ የከበረ የተፈራ ምህረት ያለው የሚራራ ያገኘኝን አይቻለው ሞት አያየኝ ፊቱ እያለው አባትና ንጉስ ፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦ ርህራሄው ስላኖረኝ ከሰው ድንኳን በክንፍ አለኝ የኔስ ጌታ ያስደንቃል በልቤ ላይ ቤቱን ሰርቷል አባትና ንጉስ፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦ ╭══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|: ══╮ ✥ @yaredaweyan25_6 ✥ ✥ @yaredaweyan25_6 ✥ ╰══•|❀:✧๑✞✞๑✧❀|:══╯ ✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥

ሚካኤል ስዩም (2)ሊቀ መላእክት መዝገበ ርራሄ(3)ወየዋህ አዝ....... የደሀ አደጉን ልጅ ስለተቀበልከኝ በአውደ ምህረትህ በፍቅር አሳደከኝ ከመቅደስ ተክለህ መገብከኝ ህይወት አዘጋጅተኸኛል ለሰማይ መንግስትህ አዝ....... በከንቱ እንዳልደክም ነብሴ እንዳትዝል ትመግበኝ ነበር የህወትን ቃል ወጣሁኝ ከአለም ተሰሎንቄን ረሣሁ መጠማቴ ቀረ የህይወት ውሀ ጠጣሁ አዝ....... መዳንን እንድወርስ ሞትን እንዳላይ ትረዳኝ ነበረ ከኔ ሣትለይ በመንገዴ ሁሉ ከፊቴ ቀደምክ አማኑኤል ብዬ ጌታን እንዳመልክ አዝ...... ምልጃህን ታምኜ ስኖር በመቅደስህ ታሻግረኝ ነበር እጆቼን ይዘህ በጎልማሣ ነቴ ነህና ከጎኔ ጉልበቴም አንተው ነህ በእርጅና ዘመኔ          https://t.me/zemariwochu3 ✍🏽 @DA121922 For any comment

🌹 #ማሪኝ_እና_ልሂድ 🙏 🌿🌿🌿🌿🌿 ማሪኝ እና ልሂድ ወደ ቤቴ ልግባ ይበቃሃል በይኝ የማነባው እንባ ደጅሽ ላይ ከወደኩ አለፉ ዘመናት ፈውስን ተጠምቼ #አቃተኝ_መጽናናት(፪)        ✝️ አዝ ✝️ ቆዩ ከተዘጉ የቤቴ መቃኖች እጅግ ራቁብኝ የመዳኔ ቀኖች ዛሬስ ይበቃኛ ልነሳ ካልጋዬ በምልጃ ፀሎትሽ *በሽታዬን ጥዬ/2/ አይነቀል እግሬ ዘላለም ከደጅሽ ተመላለስ ብሎ ካልዳሰሰኝ ልጅሽ        ✝️ አዝ ✝️ ወገን ዘመድ የለኝ የሚረዳኝ ቀርቦ ልቤ ተሰበረ በሃዘን ተከቦ እንኳን የሚደግፍ ሚሰማኝም ጠፋ አሳይኝ በአይኔ* ይህቺም ቀን አልፋ/2/ ያሰብኩት እስኪሆን አይኔ አያንቀላፋ ምህረት ከሞላበት ከደጅሽ አልጠፋ        ✝️ አዝ ✝️ የሚያድንህ የለም እያሉኝ ብዙዎች ገብተው ቆጠሩብኝ የሞቴን ቀናቶች ባሃዘን አጎንብሼ እንባዬን እረጫለሁ ድንግል ካልዳሰስሽኝ* መቼ ቀና እላለሁ/2/ እኖራለሁ በተስፋ አንቺን ተጠግቼ አልቀርም ዘላለም የተገፋሁ ሆኜ        ✝️ አዝ ✝️ የእግሮቼን ሰንሰለት ላውልቅ ተፈውሼ አዲሱን ሰውነት በምልጃሽ ለብሼ አትድንም ባሉኝ ፊት ልቁም በምስጋና ህመሜን መሸፈን *ይቻልሻል እና/2/ ማቃሰቴ ቆሞ ልሞላ ዝማሬ ድንግል በጸሎትሽ ታጥሮልኝ ድንበሬ ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈      https://t.me/Mezmur20      ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈

𓆩 ያዳነኝን አውቀዋለው 𓆪
ያዳነኝን አውቀዋለው የሞተልኝ ኢየሱስ ነው ስለሌለኝ የምከፍለው ስጦታዬ ምስጋና ነው ጨለማዬን አስወግዶ ያበራልኝን አውቃለሁ ሙሉ ሰው ነኝ ከንግዲህስ ስከተለው እኖራለሁ የብርሃኔን ልዩ ውበት ፊት ለፊቴ ቆሞ አየሁት ፍቅሩ ማርኮኝ በመቅደሱ ሰገድኩለት አመለኩት
ላመስግነው ላመስግነው ላመስግነው ፍቅሩ ማያልቅ ነው(2)
አሳደረኝ በእቅፉ መጠውለጌን አለምልሞ በመስቀል ላይ ተሰቀለ ዳንኩኝ እኔ እርሱ ታሞ በማይዝለው ክንዶቹ ላይ እኔን በክብር እያኖረ እንዲመቸኝ ዝቅ ብሎ በበረት ውስጥ እርሱ አደረ
ላመስግነው ላመስግነው ላመስግነው ፍቅሩ ማያልቅ ነው(2)
ቅኔ ባፈስ ምን ይደንቃል ደሙን በመስቀል አፍስሶ ስለ ልጁ መዳን ብሎ ነፍሱን ሳይቀር ለኔ ክሶ ፍቅር ይዞት ከጸባኦት በትትና ወቶ ወርዶ ተቀደስኩኝ በነጩ በግ ቀራንዮ ጌታ ታርዶ
ላመስግነው ላመስግነው ላመስግነው ፍቅሩ ማያልቅ ነው(2)
አክሊል ሶክ አጠለቀ ግርማ ክብሩን ሁሉ ትቶ አሻገረኝ ወደ ክብሬ በቅዱስ ደም እኔን ዋጅቶ አጎንብሶ ቀና አረገኝ ፊቴን በጽድቅ እያበረ እኖራለሁ ለዘለአለም ካከበረኝ ጌታ ጋራ
ላመስግነው ላመስግነው ላመስግነው ፍቅሩ ማያልቅ ነው(2)
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈      https://t.me/Mezmur20      ┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈

.               ☑️ ደረሰ ደረሰ ደረሰ  ☑️ በጉጉት የምንጠብቀው አመታዊው የቅዱስ ገብርኤል ክብረበዓል (ሐምሌ ቅዱስ ገብርኤል) ጥቂት ቀናት ብቻ ቀርተውታል ። ስለዚህ እራሳችንን ለአገልግሎት እናዘጋጅ። በህብረቱ የሚከናወኑ የአገልግሎቶት አይነቶች         ✔ማስተባበር        ✔ ስነ-ስርዓት ማስከበር        ✔ ማስዋብ          ✔ ዝክር        ✔ መለከትና ነጋሪት         በተጨማሪ በቅርብም በሩቅም ያላችሁ በእያንዳንዱ አገልግሎት ላይ ሀሳብ አስተያየታችሁን ቢጨመር የምትሉትን ሀሳብ ካላ በፅሁፍ ወይም በድምፅ ሀሳባችሁን አስቀምጡ ! 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://t.me/+S7_mTM1ZbuL9t_KE “ለሰው ሳይሆን ለጌታ እንደምታደርጉ፥ የምታደርጉትን ሁሉ በትጋት አድርጉት፥” |ቆላስይስ 3፥23|

አክሊሌ ነሽ ማርያም ሞገሴ ነሽ አክሊሌ ነሽ (2)ማርያም ሞገሴ ነሽ ዮሴፍም ይናገር በስደት ተጽናንቷል ያዕቆብም በሕልሙ መሰላሉን አይቷል የበገናው ሚስጢር ምን እንደነበረ ጽዮን ሆይ እያለ ዳዊት መሰከረ አዝ፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠ ትውልድ እንዲጠቀም ስምሽን አንስቶ እነኋት ብሎናል ጌታ ተሰውቶ የፍቅር ስጦታ የድሆች እናት የክብር አክሊል ናት ዘውድ ሽልማት አዝ፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠ ሙሴ በበረሃ ምን ተገለጠልህ ሐመልማል በእሳት ሳይቃጠል አይተህ ነቢያት ተነሱ ትንቢት ተፈጽሟል ቃል ከሰማይ ወርዶ ሥጋን ተዋህዷል አዝ፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠ ለዓለም ሞኝነት ነው በስምሽ ማመኑ ታምርሽን መስማቱ ውዳሴን መድገሙ እኔስ ምስክር ነኝ ዛሬም ለዘለዓለም ማርያም ሳይጠሩ ከቶ መጽደቅ የለም

ምስጋና አምልኮት ስግደት ምስጋና አምልኮት ስግደት ውዳሴ ይገባል በሉ ሰዎች ለቅድስተ ስላሴ 4× ዘላለም አለም ቅዱስ ነህ አምሳያም ወገን የለለህ መተማመኛ ሆነኸኛል ስላሴ ባንተ ደስ ይለኛል አዝ................... ዘመናት በጁ በመዳፉ ሁሌም የርሱ ነው ሁሉ ሰልፉ የሳት መድረኮች ያሉት ጌታ የማያልፍ ነው ማይረታ አዝ.................... አብርሃም አምኖ ተሰደደ በእርጅናው ወራት ልጅ ወለደ የተስፋውን ቃል ፈጸመለት ስላሴ በሉ በቀን በሌሊት አዝ.................. የታመነ ነው የተፈራ የጽድቅን ፀሐይ የሚያበራ አለሙ ጸንቷል በስላሴ ትዘምርለት ለርሱ ነፍሴ 🥀 ዘማሪት ፀዳለ ጎበዜ

🌸 በእናቴ እቅፍ 🌸 በእናቴ እቅፍ ልጅ ሆኜ ገና አየሁ ፍቅርሽ እመ ትትና ተራዬ ደርሶ አድጌ ዛሬ እኔም ጠራሁሽ ይዤ ዝማሬ 🌸 አዝ ¤ ¤ ¤ ¤ ¤ ¤ ¤ አይረሳኝም ከልቤ አይጠፋም ያኔ ያየሁት የፍቅርሽ ተስፋ ባለ ግርማዋ ውቧ እመቤቴ (2) ፀጋሽ በዝቶብኝ ያበራል ፊቴ (2) 🌸 አዝ ¤ ¤ ¤ ¤ ¤ ¤ ¤ ተራራማውን የኤፍሬም አገር ሰላምታሽ ሰምቷል የልቤን መንበር ያዘልለኛል ጉልበቴን ፈትቶ (2) ያዜማል አፌ ድምፅሽን ሰምቶ (2) 🌸 አዝ ¤ ¤ ¤ ¤ ¤ ¤ ¤ መዳፍሽ ከአይኔ መቼ ዞር ይላል እንባዬን ሲያብስ ያድራል ይውላል መአዛሽ አለ ሆኖኝ ትዝታ (2) የእናትነትሽ ፍቅር ውለታ (2) 🌸 አዝ ¤ ¤ ¤ ¤ ¤ ¤ ¤ ልሳኔን ቃኝተሽ የዜማ ሰው ነኝ የአለም ዘፈኗ የማይሸፍነኝ የልጅነቴ መክሊቴ አንቺው ነሽ (2) የፀጋን ፍሬ የማተርፍብሽ (2) #share እና #joine ያድርጉ :: 👉@ortodoxtewahdo2127 👉@enatachinmaryam

❤#አዳነኝ_ጌታ❤ አዳነኝ ጌታ አዳነኝ ፈወሰኝ ጌታ ፈወሰኝ(፪) እግዚአብሔር አዳነኝ ኃጢአተኛውን ወደደኝ ያልፋል ያላልኩት አልፎልኝ አይቼ በዕንባ ታጠብኩኝ ከድቅድቅ ወጥቼ እንግዲህ ላንተ ምስክር ሆኛለሁ ሥራህን ለዓለም ሁሌም እነግራለሁ(፪) ክንድህ ብርቱ ነው ደካማን ለመርዳት ታውቅበታለህ የዛለን ማበርታት አይኔን ከሰዎች ማራቄ ጠቅሞኛል ደጅህ ወድቄ መኖር ተሽሎኛል #አዝ የሀዘኔን ማቅ አውልቀህ ጣልክልኝ ሞቴን ስጠብቅ ዕድሜ ጨመርክልኝ ከአልጋዬ ላይ አነሱኝ እጆችህ ተፈውሻለሁ ዛሬ በምህረት (፪) ቃልህ ጽኑ ነው ዳግም ይጠግናል ጎባጣ አቅንቶ ሽባውን ተርትሯል ሕይወቴ ባንተ ዛሬ አዲስ ሆናለች በክብር መዝገብ በእጅህ ተፅፋለች #አዝ የሐሰትን ፍርድ ጌታ ቀለበስከው ተጽናንቷል ባንተ ያ የተገፋ ሰው የግፍን ጽዋ አራቅከው ከፊቱ በእጁ ላይ የለም ዛሬ ሠንሠለቱ (2) በሐማ መስቀል መርዶኪዮስ የለም የናቡቴ ደም በከንቱ አልቀረም የእውነት ዳኛ ጌታ ስትመጣ የሐሰቱ ሰው ግፈኛው ተቀጣ መዝሙር ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ ✥••┈┈••●◉ ✞┈••●◉

#ንዑድ_ክቡር ንዑድ ክቡር የእግዚአብሄር ሰው ቅዱስ ርእሰ ባህታውያን ገብረ መንፈስ ቅዱስ የገዳም መብራት ለቤተክርስቲያን ማህቶት የተጋደልክ በፆም ወፀሎት በቀንና ሌሊት በስራና በቃል ቅዱሳን መላዕክት ሀዋርያትን መስለህ አናብርቱ አናብስት መባርቅት ወነፋሳት የሚታዘዙልህ የአቅሌሲያ ፍሬ የስዖምን በረከት አስራት ሀገርህን ኢትዮጵያን ታደጋት በአማላጅነት   አዝ====== የፈታኙን ውጊያ ፍላፃና ፆር መርዙን አጥፍተህ አይንህን ቢነቁርው በትህትና ሆነህ የተቀናጀህ   በአንድነት ሶስትነት ስላሴ ያየህ ሠው   ፀጋ እንደ ሱራፌል እፁብ ገናና ነው   አዝ======= ኢትዮጵያን አስምራት በአፀደ ነፍስ ሆነህ ዛሬም ለምንላት ህዝቦቿን ከጥፋት ምድሪቱን ከቅጣት እባክህ አስምራት    ዝቋላ እንዳየነው ከባህር ውስጥ ጠልቀህ     በምድረከብድ ሰማይ ከፀሀይ ከፍ ብለህ እንደ ለመንክ @O_AMALAJTU @O_AMALAJTU @O_AMALAJTU