Petroleum and Energy Authority
Open in Telegram
Energy, being an engine of development, is important that supplies all of the economic sectors. To be more benefited from the energy sector, it should be regulated in affordable and environmentally friendly manner. For this to happen, the Ethiopian govern
Show more962
Subscribers
+124 hours
-17 days
-130 days
Posts Archive
Petroleum and Energy Authority
Geothermal Resource Development Regulation mandate transferred to Ministry of mines.
Petroleum and Energy Authority announces that activities which have been done by the former Ethiopian Energy Authority under Geothermal Resource Development licensing and Administration directorate are transferred to Ministry of Mines.
The Geothermal resource Development Licensing and Administration mandate was entrusted to former Ethiopian Energy Authority by Proclamation No.981/2016. However following the re-definition of powers and duties of the Executive Organs of the Federal Democratic Republic of Ethiopia the petroleum and Energy Authority is established by Proclamation No. 1263/2021 Article 51(1) and this mandate is transferred to ministry of mines starting from December /2021. Hence any activities related with geothermal Resource regulatory services such as licensing, permits, issuance of competency certifications etc. were taken to Minister of Mines. Therefore the authority announces that; the newly organized Petroleum and Energy Authority will not give any services related with geothermal resource regulations.
የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን
20/2014 ዓ.ም
የጂኦተርማል ሀብት ልማት እና ፈቃድ ማስተዳደር ስራዎች ስራዎች ወደ ማዕድን ሚንስቴር ተላለፉ፡፡…………………………………………………….
የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን በቀድሞ ኢነርጂ ባለስልጣን ጂኦትረማል ሀብት ልማትና ፈቃድ ማስተዳደር ዳይሬክቶሬት ስር ሲሰሩ የነበሩ ስራዎች ወደ ማዕድን ሚንስቴር መተላለፋቸውን አስታወቀ፡፡
የጂኦተርማል ሀብት ልማትና ፈቃድ ማስተዳደር ስራዎች በአዋጅ ቁጥር 981/2016 ለቀድሞ የኢትዮጵያ ኢነርጂ ባለስልጣን ተሰጠው የነበረ ሲሆን አዲሱን የፌድራል መንግስት ስራ አስፈጻሚ አካላትን ስልጣን እና ኃላፊነት ለመወሰን በወጣው አዋጅ 1263/2014 አንቀጽ 51 (1) የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን የተቋቁመ በመሆኑ ከመስከረም 2014 ዓ.ም ጀምሮ የጂኦተርማል ስራ ሃላፊነቶች ወደ ማዕድን ሚንስቴር ተዛዋውረዋል፡፡
በመሆኑም ከጂኦትርማል ቁጥጥር ስራ ጋር ግንኙነት ያላቸው የምርመራ ፈቃድ ፤የስራ ፈቃድ እና የብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት የመስጠት እና የመሳሰሉ አገልግሎቶች ወደ ማዕድን ሚንስቴር የተዛወሩ በመሆናቸው በአዲስ መልክ የተቋቋመው የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ከጂኦተርማል ሀብት ጋር ግንኙነት ያላቸውን አገልግሎቶች እንደማይሰጥ አስተውቋል፡፡
የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ከኩባንያዎች፤ከነዳጅ ማደያ ባለቤቶችና ልሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ጥር 13 ቀን 2014 ዓ.ም በንግድ ሚ/ር አዳራሽ የውይይት መድረክ አካሄደ
በምንስትሮች ም/ቤት በፀደቀው የነዳጅ ውጤቶች የዋጋ ግንባታና ትርፍ ህዳግ አሰራር እንዲሁም በሌሎች መመሪያዎች ላይ ከሰብሳቢውና ከተሳታፊዎች በተነሱ ጥያቄዎች እና በተሰጡ አስተያየቶች ላይ ውይይት ተደርጓል፡፡
ከነዳጅ ጋር በተያያዘ የተከሰቱ ሀገራዊ ችግሮች ዙሪያ መፍትሄ ይሆናሉ የተባሉ በአጭር በመካከለኛ ጊዜ ተለይተው የቀረቡ ሀሳቦችና ውሳኔዎች ዙሪያ ከተሳታፊዎች የተለያዩ ሀሳብ ቀርቦውይይት ተደርጎ የወደፊት አቅጣጫ በማስቀመጥ ውይይቱ ተጠናቋል
የፌደራል መንግሰት ሰራተኞች አደረጃጀት ድልድል መመሪያ ላይ እና አመለካከት ላይ ለባለስልጣኑ ሰራተኞች ስልጠና ተሰጠ::
ከኢነርጂ ብቃት እና ቁጠባ ስራዎች ጋር በታያያዘ የተሰሩ ጥናቶች ላይ ውይይት ተደረገ፡፡……………………………………………………………………………………
በኢትዮጵያ ኢነርጂ ባለስልጣን እና ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ትብብር እንዲሰሩ በተደረጉ ሁለት ጥናቶች በፀሐይ ኃይል በሚሰሩ የውሃ ማሞቂያዎች በሆቴሎች፤ሆስፒታሎች እና የንግድ አገልግሎት በሚሰጡ ህንጻዎች ላይ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል የአዋጭነት ጥናት እንዲሁም ከኢነርጂ ብክነት ጋር በተያያዘ የመበያጃ ማሽኖች ኢነርጂ ብቃት ላይ የተሰራ ጥናት በዘርፉ ላሉ ባለድርሻ አካላት ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡
ጥናቱ ተጠናቆ ወደ ትግበራ ከመገባቱ አስቀድሞ ለባለድርሻ አካላት ቀርቦ ውይይት መደረጉ በጥናቱ ተመስርቶ ተግባራዊ ሊደረግ በሚፈለገው ስራ ውጤታማነት ከተሳታፊዎች የተገኙ ግብአቶች ጠቃሚ እንደነበሩ በውይይቱ ላይ ተጠቅሷል፡፡
በውይይቱ ማጠቃለያ ላይ እንደተገለጸው የጥናቱ አካሄድ ላይ የታዩ ክፍተቶች እንዲታረሙ አስተያየት የተሰጠ ሲሆን ከጥናቶቹ የሚገኘው ውጤት በኢነርጂ አጠቃቀም ላይ የሚኖር አማራጭን ማየት የሚያስችል እንደሆነ እና በኢነርጂ ብቃት ላይ የተሰራው ጥናትም በቀጣይ ሊወሰዱ ሰለሚገባቸው የቁጥጥር ስራዎች መነሻ ኃሳብ እንደሚሰጥ ተገልጿል፡፡
የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን አደረጃጃት፤ስልጣን እና ተግባር በሚወስን ረቂቅ ህግ ላይ ውይይት ተደረገ፡፡……………………………………………………………………………………………………………………………
የፌደራል መንግሥት አስፈፃሚ አካላትን ሥልጣንና ተግባር ለመወሰን በወጣ አዋጅ 1263/2014 በአዲስ መልክ የተቋቋመው ነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን አደረጃጀት፤ስልጣን እና ተግባራት የሚወስን ረቂቅ ደንብ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ታህሳስ 21 ቀን 2014 ዓ.ም በጊዮን ሆቴል ውይይት ተደረገ፡፡
በውይይቱ ላይ የባለስልጣን መ/ቤቱን አደረጃጀት፤በራስ ገቢ መተዳደር፤ነጻና ገለልተኛ ተቋም ሆኖ የቁጥጥር ስራውን ሊሰራ በሚችልበት አግባብ ላይ በደንቡ በሰፈሩ ነጥቦች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል፡፡ በተጨማሪም ከሌሎች ተቋማት ጋር ሰለሚኖሩ የጥቅም ግጭት ሊያስነሱ ይችላሉ በሚሉ ጉዳዮች ላይ አስተያየት ተሰጥቷል፡፡
በማጠቃለያውም የባለስልጣን መ/ቤቱን ስልጣን እና ተግባራት የሚወሰኑ አንቀጾች ትኩረት ተደርጎባቸው እንዲታዩ እና የነበሩ ክፍተቶች ተሞልተው በዘርፉ ጠንካራ ተቆጣጣሪ መ/ቤት እንዲኖር የሚያስችል አቅም መፍጠር እንደሚገባ ተጠቁሞል፡፡
በኢንስፔክሽን ቡድኑ በዋናነት የታዩት ችግሮች ናቸው፡፡
በተመሳሳይ የኢንስፔክሽን ቡድኑ በሁለት የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ ጣቢያ በአርባ ምንጭ ከተማና በሆስዕና ከተማ በአካል በመገኘት ከታዩት ችግሮች በጥቂቱ ከፍተኛ የዘይት ፍሠት ፤በቂ አጥር አለመኖሩ ፤በቂ ጠጠር አለመኖር ፤ለእሣት አደጋ የሚያጋልጡ ደረቅ ሣር መኖሩ ለመመልከት ተችሏል፡፡
በተጨማሪ በሁለት የከተማ የኔትዎርክ አገልግሎት በተደረገው ኢንሰፔክሽን ስራ ከታዩት ችግሮች መካከል ውስጥ መስመር ከዛፎች ያላቸው ርቀት ስታንዳርድ ያልጠበቁ ፤ከግለሰብ መኖሪያ ቤት አጥር በቅርብ ርቀት መገኘታቸው፤ ከቆርቆሮ አጥር ጋር የተገናኙ፤የዘይት ፍሠት፤ከፍተኛ ጭነት ፤ለሰውና እንስሳት ንኪኪ ቅርብ የሆኑ ትራንስፎርመሮች መኖራቸው በኢንስፔክሽን ቡድኑ የታዩ ችግሮች ሰለሆኑ አሰተማማኝነቱ የተረጋገጠ ፤ደህንነቱ የተጠበቀ ብቃትና ብክነትን የቀነሰ ኃይል አቅርቦት እንዲኖር ከወዲሁ እርምት የሚሹ ጉዳዮች ናቸው፡፡
የኃይል አቅርቦት ተቋማት ወቅታዊ ሁኔታ በቁጥጥር ዕይታ፤
የኤሌክትሪክ አቅርቦት እና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ከኢትዮጵያ ኢነርጂ ባለስልጣን በወሰዱት ፈቃድ መሠረት በባለስልጣኑ የተወሰኑትን የጥንቃቄ እና የጥራት አተገባበር ደረጃዎች አክብረው ስለመስራታቸው የክትትል ስራዎች ይሰራሉ፡፡
በኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ተቋማት ላይ የሚደረጉ የቁጥጥር ስራዎች ዓላማቸው የኃይል አቅርቦት ተቋማት በአገልግሎት አሰጣጥ መመሪያው ላይ በተቀመጡ የደህንነት እንዲሁም ቀጣይነት ያለው አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ለመስጠት የሚያስችሉ ደረጃዎችን ተከትለው ስለመስራታቸው ክትትል ለማድረግ ነው፡፡
ባለስልጣን መ/ቤቱ በ2014 በጀት ዓመት ቀዳሚዎቹ ስድስት ወራት በያዘው ዕቅድ መሠረት በኃይል አቅርቦት ተቋማት ላይ በኤሌክትሪክ ስራ ፈቃድ ግዴታዎች መሠረት እየሠሩ ስለ መሆናቸው በአንድ የሓይል ማመንጫ ጣቢያ፤ ግልገል ጊቤ ቁጥር ሶስት እንዲሁም ሁለት የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ ጣቢያ ፤ የአርባ ምንጭ የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ ጣቢያ ፤የሆስዕና የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ ጣቢያ እና ሁለት የከተማ ኔት ዎርክ አገልግሎት /የአርባ ምንጭና ሆስዕና ከተማ/ የኢንስፔክሽን ሽፋን ተሰጥቶ የክትትል ስራዎ ተሰርቷል፡፡
በኢንስፔክሽኑ ወቅት በተቋማቱ ላይ የታዩ ክፍተቶች ጠቅለል ተደርገው ሲታዩ በግልገል ጊቤ ቁጥር ሶስት የኃይል ማመንጫ ጣቢያ በስትራክቸሩ በኩል ከፍተኛ የውሃ ፍሠት/water leakage/መኖር ፤ ማስተንፈሻው በሚለቀቅበት ጊዜ ክፍተኛ ጉልበት ያለው ውሃ ሰለሚወርድ በፓወር ሀውስ አከባቢ ስትራክቸር በከፍተኛ ሁኔታ እየተቦረቦረ Seismometer (software)አለመስራት ወይም የመሳሰሉት ዕቃዎች መበላሸት ፤ከደህንነት ስጋት ጋር በተያያዘ በአብዛኛው አካባቢ ዙሪያውን በጫካ የተከበበ በመሆኑ ለከፍተኛ የእሳት ቃጠሎ ስጋት መኖር
