Petroleum and Energy Authority
Open in Telegram
Energy, being an engine of development, is important that supplies all of the economic sectors. To be more benefited from the energy sector, it should be regulated in affordable and environmentally friendly manner. For this to happen, the Ethiopian govern
Show more962
Subscribers
+124 hours
-17 days
-130 days
Posts Archive
ሙስናን በመከላከል የአመራር ሚና እና ዘመናዊ የሀብት ማሣወቅና ምዝገባን በተመለከተ ስልጠና ተሰጠ ። 09 /12/2014
ለ"ነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን አመራሮችና ቡድን መሪዎች በቢሾፍቱ ከተማ በዳካ ሆቴል ሙስናን በመከላከል ረገድ የአመራሩ ሚና በሚል እና በሀብት ምዝገባና ማሣወቅ መመሪያ አስፈላጊነት እና ግዴታን በተመለከተ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ለሁለት ተከታታይ ቀናት ተሰጥቷል ::
በኢፌድሪ ህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የንግድ እና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን በመገኘት በተቋሙ ተልዕኮ እና የስራ አፈጻጸም ላይ የቀረቡ ገለጻዎችን አድምጧል፡፡
ቋሚ ኮሚቴው ተቋሙ ከተሰጠው ኃላፊነት አንጻር የቁጥጥር አሰራሩን በተመለከተ ጥያቄዎችን በማንሳት ማብራሪያ ጠይቋል፡፡ ለቀረቡት ጥያቄዎች በነዳጅ እና ኢነርጂ ዘርፍ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች በቀረበው ጥያቄ አግባብ ምላሽ የተሰጠባቸው ሲሆን በአንጻሩ ለቁጥጥር ስራው ተግዳሮት የሆኑ ጉዳዮችን በማንሳት ትኩረት እንዲደረግበት በተቋሙ በኩል ተጠይቋል፡፡
የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን አገልግሎቶችን በበይነ መረብ መስጠት ጀመረ፡፡*****************************************************************************************
የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን በኢነርጂ ዘርፍ ያሉ 46 አገልግሎቶችን በበይነ መረብ ለመስጠት የሚያስችለውን ስርዓት ማበልፀግ ሂደት ተጠናቆ አገልግሎቱን በይፋ መጀመሩን መጋቢት 15 ቀን 2014 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሆቴል አገልግሎት ተጠቃሚ ባለድርሻዎች እና ለሚዲያ አካላት በተዘጋጀው ፕሮግራም ላይ አብስሯል፡፡
የባለስልጣን መ/ቤቱን አገልግሎቶች በበይነ መረብ ለመስጠት የሚያስችለው ስርዓት ዝርጋታ በኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚንስትር አማካኝነት ፔራጎ ቴክኖሎጂ ካንፓኒ ሲሰራ ቆይቶ አግልግሎቱን መስጠት የሚያስችል ስራ በመጠናቀቁ በዕለቱ በተዘጋጀው የማብሰሪያ ፕሮግራም ላይ የመግባቢያ ሠነድ የፊርማ ስነስርዓት ተከናውኗል፡፡ በመግባቢያ ሠነዱ ላይ የኢኖቬሸን እና ቴክኖሎጂ ሚንስትር ሚንስቴር ዲኤታ ክብርት ወ/ሮ ሁሪያ አሊ እና ባለስልጣን መ/ቤቱ በመወከል አቶ ጌታሁን ሞገስ ፊርማቸውን በማኖር አገልግሎቱ በይፋ መጀመሩን በጋራ አብስረዋል፡፡
የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ፈጣን እና ቀልጣፋ ለማድረግ እንዲሁም ተጠያቂነት ያለው አሰራርን ለማስፈን የኤሌክትሮኒክ አገልግሎት አሰጣጥ ስርዓት መተግበር ዲጂታል ኢኮኖሚን ዕውን ማድረግ እንደሚያስችል ክብርት ሚንስቴር ሁሪያ አሊ በንግግራቸው ላይ ገልጸዋል፡፡
በሠበታ ከተማ ቁጥር አንድ የሓይል ማከፋፈያ ጣቢያ ተራንስፎርመር ከፍተኛ የመቃጠል አደጋ እንደ ደረሰበት የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ባለሙያዎች ቦታው ድረስ በመሄድና በማየት እንደ አረጋገጡት የእሣት አደጋ ቃጠሎ ሊነሳ ከሚያችለው ምክንያት ውስጥ የሾርት ማድረግ ችግር፤የኼርዝ ፎልት ለአደጋ የተጋለጠ መሆኑ ፤ከፍተኛ ኤሌክትሪክ ጭነት ያላቸው መስመሮች መኖራቸው፤ የዘይት ፍሰት፤በቂ አጥር የለውም ፤በቂ ጠጠር የለውም፤ለእሣት አደጋ የሚያጋልጡ ደረቅ ሣርና የተለያዩ ዕፀዋት መኖራቸው በመስክ ኢንስፔክሽን የታዩ ችግሮች ከብዙ በጥቂቱ መሆናቸው ተረጋግጠዋል፡፡
በኤሌክትሪክ መገልገያ እቃዎች አጠቃቀምን በተመለከተ ለአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ማህበር ስልጠና ተሠጠ
በአዲስ አበባ ከተማ መጋቢት 7/2014 ዓ.ም በነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን እና በአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ማህበር ጋር በመተባበር በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ወጣቶች ማዕከል ጽ/ቤት ለ11አዲስ አበባ ክፍለ ከተማ ወደ 500 ለሚጠጉ የሴቶች ማህበር በነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣ ሓላፊዎችና ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ የስልጠናው ትኩረት ያደረገባቸው ዋና ዋና ጉዳዩች ውስጥ የመብራት አምፖሎች አጠቃቀም፤የኤሌክትሪክ ምጣድና ምድጃ ኢነርጂ አጠቃቀም ችግሮችና መፍትሄቸው እንዲሁም የኤሌክትሪክ አገልግሎት አሰጣጥ በሕጋዊ ማዕቀፍ ስለመብትና ግዴታ በተመለከተ አንዳንድ ሰልጣኞች በሰጡት አስተያየተት መሠረት ስልጠና ጥሩ ግንዛቤ ማስጫበጫ እንደሆነ ገልጧል ፡፡ የዕለቱ የስልጠናው ዋና አላማ ህብረተሰቡ በማሳወቅ ኢነርጂ ሊቆጠብባቸው ከሚያስችሉ ዘዴዎች በመጠቀም ያለ አግባብ የሚባክን ኢነርጂ ማስቀረት የሓይል መቆራረጥ ለመቀነስ፤የአካባቢን የአየር ብክለትን ለመቀነስ እንዲሁም ጊዜና ለኤሌክትሪክ ፍጆታ የሚወጣውን ወጪ ለመቀነስ እንደሚቻል በአሰልጣኞች ተገልጧል፡፡
በኤሌክትሪክ መገልገያ እቃዎች አጠቃቀምን በተመለከተ ለተለያዩ አካላት ስልጠና ተሠጠ
በአዳማ ከተማ መጋቢት 2/2014 ዓ.ም ለነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን የበላይ ሓላፊዎች፤ለባለሙያዎች እንዲሁም ለ11አዲስ አበባ ክፍለ ከተሞች የሴቶች፤ ወጣቶች እና ሕፃናት ጉዳይ ሥራ አስፈፃሚዎችና ባለሙያዎች ጨምሮ የመብራት አምፖሎች አጠቃቀም ምጣድና ምድጃ ኢነርጂ አጠቃቀም ፤ ከፍሪጅ ኢነርጂ እንዴት መቆጠብ ይቻላል እንዲሁም የኤሌክትሪክ አገልግሎት አሰጣጥ በሕጋዊ ማዕቀፍ ስለመብትና ግዴታ በተመለከተ የግንዛቤ ማስጫበጫ ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡የስልጠናው ዋና አላማ ህብረተሰቡ በማሳወቅ ኢነርጂ ሊቆጠብባቸው ከሚያስችሉ ዘዴዎች በመጠቀም ያለ አግባብ የሚባክን ኢነርጂ ማስቀረት የሓይል መቆራረጥ ለመቀነስ፤የአካባቢን ብክለትን መቀነስ እንዲሁም ጊዜና ለኤሌክትሪክ ፍጆታ የሚወጣውን ወጪ መቀነስ እንደሚቻል በአሰልጣኞች ተገልጧል፡፡
የኦን ላይን አገልግሎት ስልጠና ተሰጠ
በአዳማ ከተማ ከጥር18-19/2014 ዓ.ም ጀምሮ ለነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ሓላፊዎችና ባለሙያዎች የኤሌክትሮኒክስ አግልግሎት አሰጣጥ አስመልክቶ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ ለመንግስት መስሪያ ቤቶች የኤሌክትሮኒክስ አገልግሎት መስጠት ከዘርፈ ብዙ ጥቅም ውስጥ በጣም ፈጣን፤ቀልጣፋ፤ ጥራት ያለው፤ጊዜና ገንዘብ ቆጣቢ እንዲሁም የሰዎች ድካምና እንግልት እንደሚቀንስ ትልቅ እድምታ እንዳለው ተገልጧል፡፡
ጥር 27 እና 28 2014 ዓ.ም በአዳማ ከተማ የባለስልጣን መ/ቤቱ የበላይ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች በተገኙበት የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን የስድስት ወር ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ተገምግሟል፡፡
