en
Feedback
Petroleum and Energy Authority

Petroleum and Energy Authority

Open in Telegram

Energy, being an engine of development, is important that supplies all of the economic sectors. To be more benefited from the energy sector, it should be regulated in affordable and environmentally friendly manner. For this to happen, the Ethiopian govern

Show more
962
Subscribers
+124 hours
-17 days
-130 days
Posts Archive
እነዚህ ተሽከርካሪዎች በሐምሌ ወር በተወሰነላቸው ዋጋ ቤንዚን በብር 41.26 በሊትር እንዲሁም ነጭ ናፍጣን በብር 40. 86 በሊትር እየገዙ እንዲቀጥሉ ብቻ ሣይሆን ከእጥፍ በላይ ያደገ ድጎማ ከመንግሥት እንዲያገኙ የተደረገ ስለሆነ በሚቀጥው ጊዜ ዋጋ እስኪሻሻል ድረስ በህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ላይ ምንም ዓይነት የታሪፍ ጭማሪ አይደረግም፡፡ በዚሁ መሠረት ባለፉት ሦስት ወራት ለታለመ ድጎማ ተሽከርካሪዎች ሲሰጣቸው የነበረው ድጎማ በሁለተኛው ዙር ከእጥፍ በላይ የሚጨምር ሲሆን ለምሳሌ፡- ለነፍጣ ተጠቃሚ ተሽከርካሪዎች በመጀመሪያ ዙር የተሰጣቸው ድጎማ በሊትር ብር 8.16 ሲሆን ከመስከረም 18/2015 ከሌሊቱ 6፡00 ጀምሮ ብር 10.88 ተጨምሮላቸው በድምሩ በሊትር 19.04 የገንዘብ ድጎማ ከመንግሥት ይሰጣቸዋል፡፡ በተማሳሳይ ሁኔታ የቤንዚን ድጎማም በሊትር ከብር 6.57 ወደ ብር 15.79 እንዲያድግ ተደረጓል፡፡ በአጠቃላይ አዲሱ ዋጋ በሥራ ላይ በሚቆይበት ቀጣይ ወራት የአለም ዋጋ አሁን ባለበት የሚቀጥል ከሆነ መንግሥት ከ15 ቢሊዮን ብር በላይ ድጎማ እንዲሚያደርግ ይጠበቃል፡፡በመጨረሻም ይህ በዝቅተኛ የኑሮ ሁኔታ ውሰጥ ያሉትን ዜጎች ለመደገፍ በመንግሥት የሚደረገው ከፍተኛ ድጎማ ውጤታማ የሚሆነው በድጎማ ሥርዓቱ የታቀፉ አሽከርካሪዎችና ባለንብረቶች ይህን የመንግሥትና የህዝብ አደራ የሆነውን ድጎማ በተተመነላቸው ታሪፍ ለተሳፋሪዎች አገልግሎት በመስጠት ጥቅሙን ወደ ህብረተሰቡ ያስተላለፉ እንደሆነ ብቻ ነው፡፡ ከዚህ አንፃር የሚኒስቴር መ/ቤታችን በታለመ ድጎማ የታቀፉ ተሽከርካሪዎች ይህንን አደራ በታማኝነት እንደሚወጡ ያለውን እምነት እየገለፀ ኃላፊነታቸውን በተገቢው መንገድ በማይወጡት ላይ በየደረጃው ያሉት አስፈፃሚና የፀጥታ አካላት አስተዳደራዊና ህጋዊ እርምጃ በመወሰድ ህግን የማስከበር ሥራ አጠናክረው እንዲያከናውኑና ለህዝቡ ተገቢወን መረጃ በመስጠት የመብቱ ተጠቃሚ እንዲሆን አስፈላገው ድጋፍ እንዲደረግ በጥብቅ ያሳስባል፡፡

የነዳጅ ዋጋ ማስተካከያ፤ የታለመ ድጎማ አፈፃፀምና የነዳጅ ውጤቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ማሻሻያን አስመልክቶ የተሠጠ መግለጫ ========================================== የአንደኛ ምዕራፍ (ከሐምሌ እስከ መስከረም) አፈፃፀምመንግሥት ባለፉት አመታት ከነዳጅ ውጤቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ እስከ ግማሽ የሚሆነውን ሲደጉም ከቆየ በኋላ ካለፈው አንድ አመት ተኩል ወዲህ በዓለም ገበያ በታየው ከፍተኛና ቀጣይነት ባለው የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ምክንያት ድጎማውን ማስቀጠል የማይቻልበት ደረጃ ላይ በመደረሱ በበቂ ጥናትና ዝግጅት እንዲሁም በዝቅተኛ የኑሮ ሁኔታ ውሰጥ ያሉትን ዜጎች ተጠቃሚ በሚያደርግ አግባብ የነዳጅ ድጎማን ደረጃ በደረጃ ለማስቀረትና ህገወጥ የነዳጅ ዝውውርን ጨምሮ ለዓመታት የተከማቹ ችግሮችን ለመቅረፍ የሚያስችል ሪፎርም መተግበር ከጀመረ ሦስት ወራት ገደማ ሆኖታል፡፡ በዚህ መሠረት የአገራችንን ወቅታዊ ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎችንና የዓለም የነዳጅ ገበያ ሁኔታን ከግምት በማስገባት የነዳጅ ውጤቶች ዋጋ በየሦስት ወሩ እየተከለሠ በአዳጊ መጠን ወደ ተጠቃሚው እንዲተላለፍ በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት የመጀመሪያ ምዕራፍ ከውስን ክፍተቶች በስተቀር በአጥጋቢ ሁኔታ ተከናውኗል፡፡ በሥራ ላይ ያለው የነዳጅ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በተከለሰበት በሰኔ ወር 2014 መጨረሻ መንግሥት በነዳጅ ላይ በህግ ከተጣሉት ታክሶች የሚሰበሰበውን ገቢ በአነስተኛ መጠን በመገደብና በነዳጅ ዋጋ ላይም ከፍተኛ ድጎማ በማድረግ አንስተኛ መጠን (የልዩነቱ 25 በመቶ ብቻ) ወደ ተጠቃሚው እንዲተላለፍ በማድረግ ነበር የሪፎርም ትግበራውን ያስጀመረው፡፡ በዚሁ መሠረት፡-በወቅቱ በስሌት ከተደረሰበትና የነዳጅ ተጠቃሚዎች ከሐምሌ ወር ጀምሮ መክፈል ከነበረባቸው የቤንዚን ተጨማሪ ዋጋ ብር 43.85 በሊትር ውስጥ 75 በመቶ ወይም ብር 32.89 በሊትር ላለፉት ሦስት ወራት በመንግሥት ድጎማ የተሸፈነ ሲሆን ተጠቃሚዎች ደግሞ 25 በመቶውን ወይም ብር 10.89 በሊትር ብቻ እንዲከፍሉ ተደርጎ አዲስ አበባ ላይ ቤንዚን በብር 47.83 በሊትር እየተሸጠ መቆየቱ ይታወሳል፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ በወቅቱ በስሌት ከተደረሰበት የነጭ ናፍጣ እና የኬሮሲን ተጨማሪ ዋጋ ብር 54.3 በሊትር ውስጥ 75 በመቶውን ወይም ብር 40.75 በሊትር የሚሆነውን ላለፉት ሦስት ወራት በመንግሥት ሲደጎም የቆየ ሲሆን ተጠቃሚዎች ደግሞ 25 በመቶውን ወይም ብር 13.59 በሊትር ብቻ እንዲከፍሉ ተደርጎ አዲስ አበባ ላይ ነጭ ናፍጣና ኬሮሲን በተመሳሳይ ዋጋ በብር 49.02 በሊትር እንዲሸጥ በመደረጉ ከሐምሌ እስከ መስከረም ባሉት ሦሰት ወራት ብቻ መንግሥት ከ25 ቢሊዮን ብር በላይ የነዳጅ የዋጋ ድጎማ ማድረጉን በግልፅ ያሳያል፡፡ የታለመ የነዳጅ ድጎማን በተመለከተ ከፍ ብሎ ከተጠቀሱት ድጎማዎች በተጨማሪ ለተመረጡና አነስተኛ ገቢ ላላቸው ዜጎች አገልግሎት ለሚሠጡ የህዝብ ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች ለቤንዚን በሊትር ብር 6.57 እንዲሁም ለናፍጣ ተሽከርካሪዎች በሊትር ብር 8.16 ተጨማሪ ድጎማ የተደረገ ሲሆን ባለፉት ሦስት ወራት በሥርዓቱ ለታቀፉና ግብይት ለጀመሩት ከ65,000 በላይ ለሚሆኑ ተሽከርካሪዎች ከብር 310 ሚሊዬን በላይ ከመንግሥት የገንዘብ ድጎማ ተከፍሏቸዋል፡፡ እነዚህ ተሽከርካሪዎች በመንግሥት በሚተመን ታሪፍ ለህብረተሰቡ አገልግሎት ከመስጠት አንፃር የሚያስመሰግን ሥራ የሰሩ አሽከርካሪዎችና ባለንብረቶች የመኖራቸው ያህል የመንግሥትን ድጎማ ከወሰዱ በኋላ ተሳፋሪውን ከታሪፍ በላይ በማስከፈል ተገቢ ያልሆነ ተግባር የሚፈፅሙ በርካቶች እንዳሉ ከሕዝብ በሚቀርብ ቅሬታና በጥናት ጭምር ተረጋግጧል፡፡ አንዳንድ የነዳጅ አደዮችም ከጅቡቲ የተረከቡትን ነዳጅ በተለይ ቤንዚንን በማደያ ላይ በመንግሥት በተተመነው ለተሽከርካሪዎች ዋጋ ከመሸጥ ይልቅ በአሳቻ ሰዓት በበርሜልና በጄሪካን በመቸርቸር እጥረት እንዲፈጠር የሚያደረጉና በቴሌ ብር አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ሰው ሠራሽ ችግር የሚፈጥሩ እንዳሉ ለማወቅ ተችሏል፡፡እነዚህ ችግሮች ከመሠረቱ ለመፍታት የሚያስችል ዝግጅት የተደረገ ሲሆን በሁለተኛዉ ምዕራፍ ወደ ተጨባጭ እርምጃ የሚገባ ይሆናል፡፡ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለንብረቶችና ተቆጣጣሪ አካላትም ኃላፊነታቸውን በተገቢው እንዲወጡ ይደረጋል፡፡የታለመ ድጎማ አሠራሩን ቀልጣፋ ለማድረግ በተዘረጋው የቴሌ ብር ሲስተም በመታገዝ ቀልጣፋና አስተማማኝ አገልግሎት ለመስጠት የተቻለ ሲሆን ባለፉት ሦስት ወራት ከሁለት ቢሊዬን ብር በላይ የነዳጅ ሽያጭ ተፈፅሟል፡፡ በአጠቃላይ በነዳጅ ግብይት ላይ መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት የተጀመረው ሪፎረም የመጀመሪያ ምዕራፍ በተረጋጋና በመልካም ሁኔታ የተፈፀመ ሲሆን በአፈፃፀም ያጋጠሙ ችግሮችን በቀጣይ በማስተካከልና ሥርዓቱን ወደ ሌሎች በማስፋት የበለጠ ውጤት ለማስመዝገብ የሚሰራ ይሆናል፡፡የሁለተኛ ዙር የታለመ ድጎማና የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ክለሣን በተመለከተ፡-በአለም ገበያ የነዳጅ ዋጋ በመስከረም ወር መጠነኛ መረጋጋት ያሣየ ቢሆንም በአገራችን በሥራ ላይ ካለው ጋር ሲነፃፀር ልዩነቱ አሁንም ሰፊ እንደሆነ ቀጥሏል፡፡ ይህንኑ ልዩነት ደረጃ በደረጃ ለማጥበብ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋዎቻችን የአለም ገበያን በሚያንፀባርቅ ሁኔታ ማስተካከያ እንዲደረግ የሚንስትሮች ምክር ቤት በሰጠው ውሳኔ መሠረት በመስከረም ወር የነበረውን የአለም የነዳጅ ዋጋ መነሻ ተደርጎ የተሰላውና ከመስከረም 18/2015 ጀምሮ ሥራ ላይ የሚውል የነዳጅ ውጤቶች መሸጫ ዋጋ ማሻሻያ ተደርጓል፡፡ በዚሁ መሠረት የመስከረም ወር በአለም ገበያ የነበረውን የነዳጅ ውጤቶች አማካይ ዋጋ በመውሰድና በዚህኛው ዙር መንግስት የነዳጅ ዋጋን ለማረጋጋት ያደረገውን የ50 በመቶ የታክስ ቅናሽ መነሻ በማድረግ በተደረገው የዋጋ ክለሣ ጥናት መሠረት በሥሌት የተደረሰበት የአንድ ሊትር የነጭ ናፍጣ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በሊትር ብር 81.6 የደረሰ ሲሆን የቤንዚን ደግሞ ብር 66.22 በሊትር ሁኗል፡፡ በዚሁ መሠረት በሥሌት በተደረሰበት ዋጋና ሥራ ላይ ባለው ዋጋ መካከል ካለው ልዩነት የቤንዚን የ50 በመቶ እና በነጭ ናፍጣ የ66.7 በመቶ የዋጋ ድጎማ እንዲደረግ በመንግሥት በተወሰነው መሠረት አዲሱ የችርቻሮ ዋጋ ተዘጋጅቶ ሥራ ላይ እንዲውል ተደርጓል፡፡ በዚሁ መሠረት ከመስከረም 18/2015 ዓ.ም ከሌሊቱ 6፡00 ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ የሚከተለው እንዲሆን ተወስኗል፡፡ ቤንዚን ……………………………………… ብር 57.05 በሊትር ነጭ ናፍጣ…………………………………… ብር 59.90 በሊትር ኬሮሲን ……………………………………... ብር 59.90 በሊትር የሚከተሉት የነዳጅ ውጤቶች በሥራ ላይ የነበረው ዋጋቸው ባለበት የሚቀጥል ይሆናል፡፡ በዚህም መሠረት፡4.1. የአውሮፕላን ነዳጅ ……………………. ብር 76.87 በሊትር 4.2. ቀላል ጥቁር ናፍጣ…………………….. ብር 43.89 በሊትር 4.3. ከባድ ጥቁር ናፍጣ…………………….. ብር 43.06 በሊትር በሌላ በኩል አነስተኛ ገቢ ያላቸውን ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ በተዘረጋው የታለመ ድጎማ አሠራር ታቅፈው ህዝቡን እንዲያገለግሉ የተመረጡት የህዝብ ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች በሚጠቀሙት ነዳጅ ላይ በሁለተኛው ምዕራፍ ምንም ዓይነት የዋጋ ጭማሪ አልተደገረም፡፡

ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባን በተመለከተ ውይይት ተደረገ፡፡*************************** የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን የፈሳሽ ጭነት አሽከርካሪዎች የብሔራዊ መታወቂያ ምዝገባ እንዲያከናው
+1
ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባን በተመለከተ ውይይት ተደረገ፡፡*************************** የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን የፈሳሽ ጭነት አሽከርካሪዎች የብሔራዊ መታወቂያ ምዝገባ እንዲያከናውኑ በሚያስችሉ ቅድመ ሁኔታዎች ላይ መስከረም 9/2015 ዓ.ም በኢነተር ሌግዠሪ ሆቴል ከነዳጅ አቅራቢ ድርጅት፣ ከነዳጅ አቅራቢ ኩባኒያዎች እንዲሁም ከነዳጅ ማደያ ማህበር እና የነዳጅ ጭነት አሽከርካሪዎች ማህበራት ተወካዮች ጋር ውይይት አድርጓል፡፡ ባለስልጣን መ/ቤቱ በነዳጅ እና ኢነርጂ ዘርፍ የሚሰራቸውን የቁጥጥር ስራዎች በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፉ እንዲሆኑ የሚያስችሉ ስራዎችን በመስራት ላይ የሚገኝ ሲሆን ከነዚህ መካከል አንዱ በነዳጅ ዘርፍ የፈሳሽ ጭነት አሽከርካሪዎች የብሔራዊ መታወቂያ እንዲኖራቸው በማድረግ የቁጥጥር ስራውን ቅልጥፍና እንዲኖረው ማስቻል ነው፡፡ የዲጂታል ምዝገባው ይፈታቸዋል ተብሎ ከሚታሰቡ ችግሮች መካከል በነዳጅ ርክክብ ወቅት የሚያጋጥሙ መጉላላቶችን እና ነዳጅ ለመጫን ወደ ጅቡቲ ለመግባት የሚወስደው የጊዜ ርዝማኔ የመሳሰሉ ችግሮችን ለመፍታት እንደሚያስችል በውይይቱ ወቅት ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡ በቅርቡም የምዝገባ ሂደቱ ዝግጅት እንደተጠናቀቀ በጠቅላይ ሚንስቴር ቢሮ ብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ጽ/ቤት በኩል በተመረጡ ቦታዎች ላይ ምዝገባው እንደሚካሄድ ተገልጿል፡፡

ባላችሁበት እናገለግላችኋለን*********************** የአገልጋይነት ቀን በሀገር አቀፍ ደረጃ ጳጉሜ 4/2014 ዓ.ም እየተከበረ የሚገኘውን የአገልጋይነት ቀን ምክንያት በማድረግ በተቋማችን
+2
ባላችሁበት እናገለግላችኋለን*********************** የአገልጋይነት ቀን በሀገር አቀፍ ደረጃ ጳጉሜ 4/2014 ዓ.ም እየተከበረ የሚገኘውን የአገልጋይነት ቀን ምክንያት በማድረግ በተቋማችን በኤሌክትሮኒክስ (eService) ከሚሰጡ አገልግሎቶች መካከል ጳጉሜ 4/2014 ዓ.ም የተጠናቀቁ አገልግሎቶችን አገልግሎት ጠያቂዎች ካሉበት በመሄድ አድረሰናል፡፡ “ባሉበት ሆነው እናገለግልዎታልን” በሚለው የአገልግሎት ቀን መርህ ተቋማችን ከሚሰጣቸው አገልግሎቶች መካከል በበይነ መረብ ምዘገባቸውን ላከናወኑ ሁለት ደርጅቶች፤ ለምለም ፊያጎ ደረጃ 1 ኤሌክትሮ ሜካኒካል ስራ ተቋራጭ የብቃት ማረጋገጫ ዕድሳት በመኖሪያ ቤታቸው በመሄድ እንዲሁም ደሳለኝ ዳንኤል ኤሌክትሮ ሜካኒካል ደረጃ 5 ስራ ተቋራጭ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ብቃት ማረጋገጫ ዕድሳት ባሉበት የብቃት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት አድርሰናቸዋል፡፡

የበይነ መረብ / eService / አገልግሎቶቻችን******* የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን በነዳጅ እና ኢነርጂ ዘርፍ ህዝብን ለማገልገል የተሰጡትን ተልዕኮዎች ከግብ ለማድረስ የተለያዩ አገልግሎቶችን ለህብረተሰቡ በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡ ከነዚህ አገልግሎቶች መካከል በኢነርጂ ቁጥጥር ዘርፍ የሚሠጡ አገልግሎቶችን በበይነ መረብ (eService) ማስተናገድ የሚቻሉትን በመለየት 46 አገልግሎቶችን eService ስርዓት ውስጥ በማስገባት አገልግሎቱን በበይነ መረብ መስጠት ጀምሯል፡፡ በኢነርጂ ዘርፍ በበይነ መረብ eService አገልግሎት መስጠት የጀመርናቸው አገልግሎቶች፡- • የኤሌክትሪክ ስራዎች የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት መስጠት፤ማደስ፤ማሻሻል እና መተካት፤ - Upgrading Of Electrical works Professional competency Certificate - Lost substitution of Electrical works Professional competency Certificate - Upgrading Of Electrical works Professional competency Certificate - Renewal Of Electrical works Professional competency Certificate - Issuance of New Electrical works Professional competency Certificate • ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት (EEU) የኤሌክትሪክ አገልግሎትን በተመለከተ ቅሬታ አስገብተው ምላሽ ባላገኙበት ጉዳይ ላይ ቅሬታ ለማስገባት፤ - Submission of Customer complain - • የኤሌክትሪክ ሥራዎች የንግድ ሥራ ብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት መስጠት፤ማደስ፤ማሻሻል እና መተካት፤ - Rename of Electrical works Business competency Certificate - Replacement of Electrical works Business competency Certificate - Lost substitution of Electrical works Business competency Certificate - Upgrading of Electrical works Business competency Certificate - Renewal of Electrical works Business competency certificate - Issuance of New Electrical works Business competency Certificate - Replacement of Electrical works Professional competency Certificate • ጊዜያዊ እና ቋሚ ኢነርጂ አገልግሎት ኩባንያ ፈቃድ መስጠት፤ማደስ እና መተካት፤ - Replacement of Energy Service Company License - Lost substitution of Energy Service Company license - Renewal of permanent Energy Service Company license - Issuance of New Permanent Energy Service Company License - Issuance of New Temporary Energy Service Company License - Replacement of Energy Audit license - Lost substitution of Energy Audit license - Renewal of Energy Audit license - Issuance of New Energy Audit license • የባለስልጣን መ/ቤቱን አገልግሎት በተመለከተ መረጃ መስጠት - በeService ስለተሰጠው አገልግሎት አስተያየት የመቀበል አገልግሎት፤ አገልግሎቱን ለማግኘት WWW.eservice.gov.et በመጠቀም ማግኘት ይችላሉ፡፡ ለበለጠ መረጃ www.pea.gov.et በባለስልጣን መ/ቤቱ ድረ-ገጽ ዝርዝር መረጃውን ማግኘት ይቻላል፡፡በተጨማሪም ስልክ 011 5 507735/52/54 0115 536924 መረጃውን ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃልን፡፡ የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን

የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት ይቆያል፦ **** የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ከነሐሴ 26 ቀን 2014 ዓ.ም እስከ መስከረም 30 ቀን 2015 ዓ.ም በነበረበት እንደሚቆይ የንግድ እና ቀጣናዊ ትሥሥር ሚኒስቴር አስታውቋል። በዚሁ መሠረት ከነሐሴ 26 ቀን 2014 ዓ.ም እስከ መስከረም 30 ቀን 2015 ዓ.ም ተግባራዊ የሚደረገው የነዳጅ ምርቶች ዋጋ የአውሮፕላን ነዳጅን ጨምሮ በነሐሴ ወር 2014 ዓ.ም እየተሸጠበት ባለው ዋጋ ያለምንም ለውጥ እንዲቀጥል ተወስኗል፡፡ በተያያዘም ከሰኔ 29 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እየተደረገ ያለው የታለመት የነዳጅ ድጎማ አሠራር በተመሳሳይ በመስከረም ወር 2015 ዓ.ም እንደሚቀጥልም ተገልጿል።

fana digital (mp3cut.net).mp354.24 MB

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 10ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል። ምክር ቤቱ በቀዳሚነት የተወያየው የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣንን አደረጃጀት፣ ስልጣንና ተግባራትን ለመወሰን በቀረበው ደንብ ላይ ሲሆን÷ የፌዴራል መንግስት የአስፈጻሚ አካላትን ሥልጣንና ተግባር ለመወሰን የወጣው አዋጅ ቁጥር 1263/2014 የነዳጅና ኢነርጂ ጉዳዮችን የሚመራ ተቋም በአዲስ መልከ ያቋቋመ መሆኑን ተከትሎ ባለስልጣኑ ሴክተሩን በብቃት መምራት የሚያስችል ስልጣንና ተግባር እንዲኖረው የሚያስችል ደንብ ተዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምከር ቤት ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በደንቡ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣት ቀን ጀምሮ በሥራ ላይ እንዲውል ወስኗል፡፡

ኢትዮጵያ ታመስግን*********************************** የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን የበላይ አመራሮች፤የስራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች ኢትዮጵያ ታመስግን በሚል መሪ ቃል ከቀኑ በ9
+4
ኢትዮጵያ ታመስግን*********************************** የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን የበላይ አመራሮች፤የስራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች ኢትዮጵያ ታመስግን በሚል መሪ ቃል ከቀኑ በ9፡00 የምስጋና መረሀግብር አካሂደዋል፡፡ በፕሮግራሙ ላይ የተቋሙ ዋና ዳይሬክትር ወ/ሮ ሣሃራላ አብዱላሂ ባስተላለፉት መልዕክት አገራችን ብዙ ችግሮችን አልፋ አንድነቷን አስጠብቃ መቀጠል እንድትችል የፈጣሪ ቸርነት ከፈጣሪ በታች የህዝባችን አንድነት ርድቷታል ሲሉ ገልጸዋል፡፡ በማስከተልም አትሌቶቻችን በዓለም አትሌቲክስ ሻንፒዮን ያስመዘገቡት ድልን አስመልክተው እንኳን ደስ ያለን መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

የኢነርጂ አስተዳደር ስርዓት ትግበራን የተመለከተ ስልጠና ተሰጠ፡፡*************************** ከተለያየ የስራ ክፍል ለተውጣጡ የኢትዮጵያ አየርመንግድ ሠራተኞች የኢነርጂ አስተዳደር (E
+7
የኢነርጂ አስተዳደር ስርዓት ትግበራን የተመለከተ ስልጠና ተሰጠ፡፡*************************** ከተለያየ የስራ ክፍል ለተውጣጡ የኢትዮጵያ አየርመንግድ ሠራተኞች የኢነርጂ አስተዳደር (Enregy management system) እና በከፍተኛ ኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ኢንደስትሪዎች ላይ የሚደረግ ኢነርጂ ኦዲትን የተመለከተ ስልጠና በባለስልጣን መ/ቤቱ ኢነርጂ ብቃትና ቁጠባ ዳይሬክቶሬት ባለሙያዎች ተሰጥቷል፡፡ የስልጠናው ዓላማ አየር መንገዱ የሚጠቀመውን ኤሌክትሪከ ኢነርጂ በቁጠባ እና በብቃት መጠቀም የሚያስችል ኢነርጂ አስተዳደር ስርዓት ለመዘርጋት የሚያስችል ግንዛቤ መፍጠር እንደሆነ ተገልጿል፡፡ ወደ ትግበራ ሲገባም አስቀድሞ አየር መንገዱ ኢነርጂ አጠቃቀሙን ኦዲት በማስደረግ ክፈተቶችን መለየት እና ከባለስልጣን መ/ቤቱ ጋር በሚያደርገው የፈቃደኘነት ኢነርጂ ማኔጅመንት ስምምነት በኢነርጂ ኦዲት የተለዩ ክፈተቶችን በማሻሻል የተገኙ ውጤቶችን በቀላሉ መለካት እንደሚቻል ከስልጠናው ለመረዳት ተችሏል፡፡

አሻራችን ለትውልዳችን***************************** አራተኛው ዙር አረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተካላ መርሀ-ግብር በማስመልከት የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ከፍተኛ አመራሮች፤መካከለኛ አመራሮች እና ሠራተኞች ከንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚ/ር እና በስሩ ካሉ ተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን ዛሬ ሐምሌ 6/2014 ዓ.ም በቅሊንጦ ኢንደስትሪያል ፓርክ ችግኝ ተክለዋል፡፡ የችግኝ ተከላውን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚንስቴር ሚንስትር ክቡር አቶ ገ/መስቀል ጫላ፤ከሚንስትር ዲኤታዎች እንዲሁም የተጠሪ ተቋማት ኃላፊዎች ጋር በመሆን ፕሮግራሙን በጋራ አስጀምረዋል፡፡

የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ቀደም ሲል የኢነርጂ ባለስልጣን እና የነዳጅ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሆነው ሲያገለግሉ ለነበሩት አቶ ጌታሁን ሞገስ እና አቶ አህመድ ቱሳ የሽኝት ፕሮግራም በ
የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ቀደም ሲል የኢነርጂ ባለስልጣን እና የነዳጅ ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሆነው ሲያገለግሉ ለነበሩት አቶ ጌታሁን ሞገስ እና አቶ አህመድ ቱሳ የሽኝት ፕሮግራም በማዘጋጀት በክብር የሸኛቸው ሲሆን በምትኩ የነዳጅ እና ኢነርጂ ዋና ዳሬክተር ሆነው የተሾሙትን ወ/ሮ ሳህረላ አብዱላሂን እንዲሁም ም/ዋና ዳይሬክተር ሆነው የተሸሙትን አቶ አህመድ ሰኢድ እና አቶ ሄኖስ ወርቁን አቀባበል ተደርገሎቸዋል፡፡

ዛሬየታለመለት የነዳጅ ድጎማ ተግባራዊ መሆን ጀመረ። ከዛሬ ሰኔ 29 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ፤ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ተሸከርካሪዎችን ብቻ ተጠቃሚ የሚያደርገው የታለመለት የነዳጅ ድ
ዛሬየታለመለት የነዳጅ ድጎማ ተግባራዊ መሆን ጀመረ። ከዛሬ ሰኔ 29 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ፤ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ተሸከርካሪዎችን ብቻ ተጠቃሚ የሚያደርገው የታለመለት የነዳጅ ድጎማ በመላው ሀገሪቱ ተግባራዊ መሆን ጀምሯል፡፡ የነዳጅ ድጎማውን በቴክኖሎጂ ለመደገፍ በኢትዮ ቴሌኮም በኩል መተግበሪያ በልፅጎ አገልግሎት መስጠት መጀመሩ ተገልጿል። በዚህም መሠረት በቴሌ ብር በኩል አገልግሎቱን ለማግኘት የተመዘገቡ ከ160,000 በላይ ተሸከርካሪዎች ከዛሬ ሰኔ 29 /2014 ጀምሮ መተግበሪያውን በመጠቀም ይስተናገዳሉ ተብሏል። የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ የሆኑ ተሽከርካሪዎች ዓመታዊ ነዳጅ ፍጆታ ተቀራራቢ የሊትር መጠን ግምት በጥናት ተለይቷል። ይህም እያንዳንዱ ተሸከርካሪ የሚጠቀመውን የነዳጅ መጠን ያገናዘበ ስሌት በመቀመጡ ተሽከርካሪዎቹ ያለ ብክነት የታለመ የነዳጅ ድጎማን ጥቅም ላይ እንዲያውሉ የሚያግዝ መሆኑ ተገልጿል። የታለመለት የነዳጅ ድጎማ ተጠቃሚ የሆኑ የህዝብ ትራንስፖርት ተሸከርካሪዎች ብቻ ዕለታዊ የነዳጅ መጠን ፦ 👉 ባለ 3 እግር ተሽከርካሪ (ባጃጅ) በቀን 7 ሊትር 👉 መለስተኛ የከተማ ታክሲ (ላዳ) በቀን 25 ሊትር 👉 ሚኒባስ ታክሲ በቀን 65 ሊትር 👉 መለስተኛ አውቶብስ በቀን 94 ሊትር 👉 የከተማ አውቶብስ በቀን 102 ሊትር 👉 የሕዝብ አውቶብስ በቀን 25 ሊትር 👉 ሀገር አቋራጭ አውቶብስ በቀን 65 ሊትር መሆኑ ተገልጿል። ምንጭ፦ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር

የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ ዋጋ ላይ ጭማሬ ተደረገ ከነገ ሰኔ 29 ቀን 2014 ዓ.ም እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2014 ዓ.ም የነዳጅ ምርቶች የመሸጫ ዋጋ ጭማሬ መደረጉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር
የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ ዋጋ ላይ ጭማሬ ተደረገ ከነገ ሰኔ 29 ቀን 2014 ዓ.ም እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2014 ዓ.ም የነዳጅ ምርቶች የመሸጫ ዋጋ ጭማሬ መደረጉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ ቤንዚን - 47.83 በሊትር ነጭ ናፍጣ - 49.02 በሊትር ኬሮሲን - 49.02 በሊትር ቀላል ጥቁር ናፍጣ - 53.10 በሊትር ከባድ ጥቁር ናፍጣ - 52.37 በሊትር የአውሮፕላን ነዳጅ - 98.83 በሊትር

የነዳጅ ቁጥጥር ግብረኃይል በተለያዩ ቦታዎች ቁጥጥር በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ *************************** በነዳጅ ማደያዎች እና በነዳጅ ጫኝ ተሸከርካሪዎች ላይ ቁጥጥር ስራው ተጠናክሮ
+3
የነዳጅ ቁጥጥር ግብረኃይል በተለያዩ ቦታዎች ቁጥጥር በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ *************************** በነዳጅ ማደያዎች እና በነዳጅ ጫኝ ተሸከርካሪዎች ላይ ቁጥጥር ስራው ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ባለፉት ሶስት ቀናት በመተሃራ፤ወለጪቲ፤ሞጆ፤አዳማ፤ቢሾፍቱ እና ዱከም ባደረገው የአሰሳ እና የክትትል ስራ በፋብሪካ፤ት/ቤት፤ሆቴሎች እንዲሁም በመንገድ ላይ ቆመው የነበሩ ነዳጅ የጫኑ ተሸከርካሪዎች የተገኙ ሲሆን ትላንት ባለስልጣን መ/ቤቱ የሰጠውን ማስጠንቀቂያ ተከትሎ በአዲስ አበባ 18 ነዳጅ የጫኑ ተሸከርካሪዎች ለተጫነለት ማደያ ማራገፋቸው ተረጋግጧል፡፡ የቁጥጥር ግብረ ኃይሉ ስራውን ዘሬም ቀጥሎ በተለያዩ ከተሞች አሰሳ የሚያደረግ ሲሆን በነዳጅ ማደያዎች፤ ነዳጅ እያላቸው በዘጉ፤በጀሪካን እና በተለያዩ ዕቃዎች በሚያስቀዱ እና የነዳጅ ማደያው ሁሉም ነዳጅ መቅጃ ዲስፔንሰሮችን ተጠቅሞ እየተሠራ ስለመሆኑ ቁጥጥር በመደረግ ላይ ይገኛል፡፡ ግብረኃይሉ በሚያቀርበው ሪፖርት እና አለአግባብ ነዳጅ ጭነው በቆሙ ተሸከርካሪዎች ላይ አስፈላጊው እርምጃ የሚወሰድ ይሆናል፡፡