en
Feedback
Petroleum and Energy Authority

Petroleum and Energy Authority

Open in Telegram

Energy, being an engine of development, is important that supplies all of the economic sectors. To be more benefited from the energy sector, it should be regulated in affordable and environmentally friendly manner. For this to happen, the Ethiopian govern

Show more
962
Subscribers
+124 hours
-17 days
-130 days
Posts Archive
ባለስልጣን መ/ቤቱ የ2015 ዓ.ም ዕቅድ አፈፃፀም ገመገመ፡፡ *************** ነሐሴ 26/2015 ዓ.ም (ነ.ኢ.ባ) አዳማ የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም የመ/ቤቱ የበላይ ኃላፊዎች፣
+1
ባለስልጣን መ/ቤቱ የ2015 ዓ.ም ዕቅድ አፈፃፀም ገመገመ፡፡ *************** ነሐሴ 26/2015 ዓ.ም (ነ.ኢ.ባ) አዳማ የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም የመ/ቤቱ የበላይ ኃላፊዎች፣ መካከለኛ አመራር እና ሠራተኛው በተገኙበት ተገምግሟል፡፡ በውይቱ ላይ በዕቅድ አፈፃፀም ወቅት የነበሩ ክፍተቶች እና የተገኙ አበረታች ውጤቶች ላይ አስተያየት ተሰጥቷል:: በዚህም እንደ ክፍተት ከተወሰዱ ነጥቦች መካከል በነዳጅ ዘርፍ የነዳጅ ብክነት እና ህገወጥ የነዳጅ ንግድን ከመከላከል አንፃር ቀሪ ስራዎች መኖራቸው እንዲሁም በኢነርጂ ዘርፍ አፈፃፀም ከኤሌክትሪክ ኃይል አቅራቢ እና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚደረግ ክትትል ማነስ መኖሩ ተጠቅሷል፡፡ በመጨረሻም በዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሠሃረላ አብዱላሂ በቀጣይ ለ2016 በጀት ዓመት የባለስልጣን መ/ቤቱን የቁጥጥር ስራዎች በቴክኖሎጂ ተደግፎ ለመስራት የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አቅጣጫ ተሰጥቶ ውይይቱ ተጠናቋል፡፡

የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪ ሃይል መሙሊያ ጣቢያዎች መሠረት ልማት ኢንስታሌሽን በተመለከተ ውይይት ተደረገ፡: ***********************************************************
+4
የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪ ሃይል መሙሊያ ጣቢያዎች መሠረት ልማት ኢንስታሌሽን በተመለከተ ውይይት ተደረገ፡: *********************************************************************** የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ሰኔ 16/2015 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከግልና መንግስት የተለያየ ዘርፎች ከተውጣጡ አካላት ጋር የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች የሃይል መሙሊያ መሠረተ ልማት ዝርጋታ ረቂቅ መመሪያ ላይ ውይይት አድርጓል፡፡ በመመሪያው የሃይል አቅርቦት፣ሃይል መሙሊያ ጣቢያዎች ቴክኒካል ስታንዳርድ፤ፈቃድ አሰጣጥ እና ታሪፍን የተመለከቱ ጉዳዮች የተካተቱበት ሲሆን በተዘጋጀው ረቂቅ ላይ በቀጣይ መመሪያውን ማዳበር የሚያስችሉ ሃሳቦች ከተሳታፊዎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡ ባለስልጣን መቤቱ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች ከሃይል አቅርቦት ጋር በተያያዘ ችግር ሳይገጥማቸው አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ ለማስቻል የህዝብ አገልግሎት የሚሰጡ የሃይል መሙያ ጣቢያዎች አስፈላጊ እየሆነ ከመምጣቱ ጋር በተያያዘ ከደህንነት፤ከሃይል አቅርቦት እና ከታሪፍ ተመን ጋር በተያያዘ የህግ ማዕቀፍ ማዘጋጀት በማስፈለጉ ረቂቅ መመሪያ ለባለድርሻ አካላት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡

የ 2015 ዓም በጀት ዓምት የዘጠኝ ወር የስራ ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ተገመገመ የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን በአዳማ ከተማ ሚያዚያ 04/2015 ዓም ከፍተኛ የስራ ሐላፊዎች እና ባለሙያዎች በመሳተፍ
+4
የ 2015 ዓም በጀት ዓምት የዘጠኝ ወር የስራ ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ተገመገመ የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን በአዳማ ከተማ ሚያዚያ 04/2015 ዓም ከፍተኛ የስራ ሐላፊዎች እና ባለሙያዎች በመሳተፍ የ ሰባት ዓመት መሪ እቅድና የ 2015 ዓም በጀት ዓመት የዘጠኝ ወር የስራ ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት በዝርዝር ቀርቦ የተሰሩት እና ያልተሰሩት ስራዎች በመለየት ተገምግሟል። አቶ ፍሬው ወርቁ የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን የዕቅድ ክትትልና ግምገማ ክፍል ዳይሬክተር እንደገለፁት የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ እና ያለፉት አመታት የሁሉም ዘርፎች የተናጥል የአፈፃፀም ግምገማ በዝርዝር የተዳሰሰበት መሆኑን በመግለፅ እንዲሁም የውስጣዊ እና የውጫዊ ግምገማ እና ትንተና የተደረገበት ሲሆን በዋናነት የተቐሙን ጥንካሬና ድክመት በተጨማሪም መልካም አጋጣሚና ስጋቶች በጥልቀት መታየታቸውን ገልፀዋል። የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሳህረላ አብዱላሂ የስትራቲጂካል ዕቅድ እና የ2015 በጀት ዓመት የስራ ዕቅድ አፈፃፀም በተመለከተ ያሉንን ሰብሀዊ ሀብቶች እና የፋይናንስ ሀብት እንዲሁም መልካም አጋጣሚዎች በቀጣዮቹ አመታት ለዘርፉ ልማት የሚውሉበትን አቅጣጫ አብራርተዋል። በመጨረሻም መሪ ዕቀዱ የተቐሙን ዋናዋና አላማዎችንና ግቦችን ራዕይ ተልኮዎች እንዲሁም በመንግስት የተሰጠውን ስልጣንና ተግባራት ለማሳካት በሚያስችል መልኩ የተዘጋጀ ሲሆን ለተግባራዊነት በዋናነት የስራ ክፍል ኋላፊዎች እና የመ/ቤቱ ሠራተኞች በተጨማሪም የባለድርሻ አካላት ሁሉ የሚመለከተው የራሱን ሚና በመወጣት የተሻለ ዉጤት ለማምጣት ከፍተኛ ጥረት እንደሚያስፈልግ ተጠቅሷል።

የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈፀም ተገለፀ ። ******************************************** መጋቢት 28/2015 ዓ.ም በአዲስ አበባ እና ዙሪ
+3
የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገዶች ብቻ እንደሚፈፀም ተገለፀ ። ******************************************** መጋቢት 28/2015 ዓ.ም በአዲስ አበባ እና ዙሪያው ለሚገኙ የነዳጅ ማደያዎች ከነዳጅ ግብይት ጋር በተያያዘ የኤሌክትሮኒክስ ክፍያ አፈፃፀም ግንዛቤ ማሰጨበጫ ተሰጠ። በግንዛቤ ማስጨበጫው ላይ በኢትዬ ቴሌኮም የክፍያ አፈፃፀሙን የተመለከተ ገለፃ የተሰጠ ሲሆን በየደረጃዉ ተግባሪዊ የሚደረገውን ዲጅታል ግብይት ስርአት ትግበራ አስመልክቶ በተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎች በነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሣሀረላ አብዱላሂ ማብራሪያ ተሰጥቷል ። በመጨረሻም ወ/ሮ ሣሀረላ አብዱላሂ በሰጡት ማጠቃለያ ከፊታችን ሚያዝያ 16/2015 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ እና ዙሪያዋ በሚገኙ ከተሞች የነዳጅ ግብይቱ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ብቻ የሚፈፀም መሆኑን በመረዳት አገልግሎት የሚሰጡ ማደያዎች አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳስበዋል ።

ዲጂታል የነዳጅ ግብይት ስርዓት ይፋ ተደረገ ። ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨አዲስ አበባ መጋቢት 22/2015 ዓ.ም (ነ.ኢ.ባ) የነዳጅ ግብይትን በዲጂታል የግብይት ማስጀመሪያ መርሀ
ዲጂታል የነዳጅ ግብይት ስርዓት ይፋ ተደረገ ። ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨አዲስ አበባ መጋቢት 22/2015 ዓ.ም (ነ.ኢ.ባ) የነዳጅ ግብይትን በዲጂታል የግብይት ማስጀመሪያ መርሀግብር በአዲስ አበባ ከተማ በተመረጡ ሶስት ማደያዎች ተካሄደ ። በናሽናል ኦይል ኩባንያ (NOC) እና ቶታል ኢነርጂስ ነዳጅ ማደያዎች ላይ በመገኘት የንግድና ቀጠናዊ ትስሰር ሚንስቴር ሚንስትር አቶ ገ/መስቀል ጫላ፣የትራንስፖርት ሚንስቴር ሚንስትር አቶ አለሙ ስሜ፣የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሠሀረላ አብዱላሂ እና የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬ ህይወት ታምሩ በይፋ ዲጂታል ግብይቱን አስጀምረዋል ። በፕሮግራሙ ማጠቃለያ ላይ የነዳጅና ኢነርጂ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሣሀረላ አብዱላሂ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ከሚያዝያ 16/2015 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ሙሉ ለሙሉ የነዳጅ ግብይት በቴሌ ብር ወይም ዲጂታል ግብይት እንደሚሆን በተጨማሪም በክልሎች ከግንቦት 1/2015 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚሆን አስታውቀዋል።

ነዳጅን በሕገወጥ መንግድ ሲያጓጉዙ በነበሩ ተሸከርካሪዎች ላይ እገዳ ተጣለ፡፡******************** ነዳጅን ከተጫነለት መዳረሻ ውጪ በሕገወጥ መንግድ መስመር ቀይረው ሲያጓጉዙ የተገኙ ሁለት የነዳጅ ጭነት አመላላሽ ተሸከርካሪዎች እና የነዳጅ ማደያዎች ከ04/06/2015 ዓ.ም ጀምሮ ጉዳዩ በሕግ እስከሚጣራ ነዳጅ እንዳይጫንላቸው ለነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ማሳወቁን ባለስልጣን መ/ቤቱ ገልጿል፡፡ በቀን 28/06/2015 ዓ.ም የታርጋ ቁጥር 69291 የሆነ የነዳጅ አመላላሽ ተሸከርካሪ የተጫነለትን 47702 ሊትር ቤንዚን ጀርመን አደባባይ ቶታል የነዳጅ ማደያ ማራገፍ ሲገባው በሕገወጥ መንገድ ባልተፈቀደለት ሻሸመኔ መስመር ሲያጓጉዝ በመገኘቱ የተጫነው ነዳጅ እንዲወረስ እና አሽከርካሪውም በቁጥጥር ስር እንዲውል ተደርጓል፡፡ ከዚሁ መረጃ ጋር በተያያዘ በቀን 29/06/2015 ዓ.ም ታርጋ ቁጥሩ 77768 የሆነ ተሸከርካሪ ለጀርመን አደባባይ ቶታል የነዳጅ ማደያ ተጭኖ የነበረን 47548 ሊትር ቤንዚን ከመስመር ውጪ በማጓጓዝ አዳማ ከተማ ሲደርስ ክትትል እየተደረገበት መሆኑን በማወቅ ተመልሶ በመዳረሻው ማደያ ውስጥ መቆሙ እንደተደረሰበት ታውቋል፡፡ በዚህ ሕገወጥ ተግባር ላይ ተሳታፊ የነበሩ ማደያዎችና ተሸከርካሪዎች ጉዳዩ በሕግ ተጣርቶ እስኪወሰን ነዳጅ እንዳይጫንላቸው የሚል ውሳኔ መስጠቱን በባለስልጣን መ/ቤቱ አሳውቋል፡፡

አዲስ አበባ የካቲት 22/2015 ዓ.ም (ነ.ኢ.ባ) የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ኃላፊዎች እና ሠራተኞች የዐድዋ ድል በዓልን በተለያዩ ዝግጅቶች አክብረዋል። በዓሉ የ127ኛው የዓድዋ ድል በዓልን
+2
አዲስ አበባ የካቲት 22/2015 ዓ.ም (ነ.ኢ.ባ) የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ኃላፊዎች እና ሠራተኞች የዐድዋ ድል በዓልን በተለያዩ ዝግጅቶች አክብረዋል። በዓሉ የ127ኛው የዓድዋ ድል በዓልን ምክንያት በማድረግ ለአገራዊ አንድነት ፣ ጀግንነት እና ፅናት መህልቅ በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀ ወርክሾፕ እና ኪነጥበባዊ ዝግጅቶች በድምቀት ተከብሯል ። በዕለቱ የተዘጋጀዉን ፕሮግራም የከፈቱት የባለሥልጣን መ/ቤቱ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሠሀረላ አብዱላሂ ዓድዋ መላው ጥቁር ህዝብ አንገቱን ቀና አድርጎ እንዲሄድ ያስቻለ የሁላችንም ድል ነው በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል ።

ኢነርጂን በብቃትና ቁጠባ በመጠቀም የሴቶችን ተጠቃሚነት ማሳደግ እንደሚቻል ተገለፀ--- በጌድዬ ዞን ዲላ ከተማ የካቲት 16እና17 /2015 ዓ.ም ለሁለት ቀን የቆየ የግንዛቤ ማሰጨበጫ ስልጠና ሴቶች
+8
ኢነርጂን በብቃትና ቁጠባ በመጠቀም የሴቶችን ተጠቃሚነት ማሳደግ እንደሚቻል ተገለፀ--- በጌድዬ ዞን ዲላ ከተማ የካቲት 16እና17 /2015 ዓ.ም ለሁለት ቀን የቆየ የግንዛቤ ማሰጨበጫ ስልጠና ሴቶች እና ኢነርጂ በሚል ርዕሰ ከተለያዩ ቢሮዎች ለተውጣጡ ሠራተኞች እንዲሰጥ ተደርጓል ። ስልጠናው ከዞኑ ውሃ ፣መስኖና መዕድን ልማት እና የሴቶችና ህፃናት መምሪያ ጋር በመተባበር በነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ተሰጥቷል ። ብሔራዊ ኢነርጂ ብቃትና ቁጠባ ስትራቴጂ ትግበራ ላይ ሴቶች ካላቸው ፆታዊ ሚና አንፃር የሚኖራቸው አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑ በስልጠናው ላይ ተገልጿል ። የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ተግባራዊ እያደረጋቸው ከሚገኙ ኢነርጂ ብቃትና ቁጠባ ፕሮግራሞች መካከል አንዱ የግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራም በፌድራል እና ክልል የሚገኙ የሴቶች አደረጃጀትን በመጠቀም እየተሰጠ እንደሚገኝ የባለስልጣን መ/ቤቱ ሴቶችና ህፃናት ዳይሬክተር ወ/ሮ አይናለም ወልዴ ተናግረዋል ። ስልጠናዉን በሰጡት ባለሙያዎች እንደተገለፀው የቤት ዉስጥ ኤሌክትሪክ አጠቃቀም ቁጠባን መሠረት ያደረገ እንዲሆን እና ኤሌክትሪክን ለብክነት የሚያጋልጥ አጠቃቀምን ለመከላከል ሴቶች በቤት ውሰጥ የሚኖራቸው ኃላፊነት ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል ። ከዚሁ ጋር በተያያዘም የቤት ውሰጥ የኤሌክትሪክ ዕቃዎችን የመግዛት ውሳኔ ላይ ብቃትን ያገናዘበ እንዲሆን ለማስቻል ስልጠናው ለሴቶች አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል ።

የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን በአጋርነት የተሳተፈበት አውደ ርዕይ ተከፈተ፡፡ ******************************************************************* በአፍሪካ ትልቁ
+3
የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን በአጋርነት የተሳተፈበት አውደ ርዕይ ተከፈተ፡፡ ******************************************************************* በአፍሪካ ትልቁ የባለብዙ ዘርፍ ምርቶች እና መሳሪያዎች ንግድ ኤግዚቢሽን ዛሬ ጥር 15/2015 ዓ.ም ሚንስትሮች፤ የሀገራት አምባሳደሮች፤ኢንቨስተሮች፤የተለያዩ መ/ቤቶችና ድርጅቶች ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት በደማቅ ስነስርዓት በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ ተከፍቷል፡፡ የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን በዚህ አለም ዓቀፍ አውደ ርዕይ ስር በሚካሄደው 4ኛው Power and Energy Africa 2023 ዐውደ ርዕይ በአጋርነት የተሳተፈ ሲሆን የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ክብርት ወ/ሮ ሳሀረላ አብዱላሂ እና የኢነርጂ ዘርፍ ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ አህመድ ሰኢድ የመክፈቻ ስነስርዓቱ ላይ በመገኘት ዐውደ ርዕዩን ጎብኝተዋል፡፡ ኢትዮጵያ ከፍተኛ የሆነ የታዳሽ ኢነርጂ እምቅ ሀብት ያላት ሀገር ስትሆን ይህን ዘርፍ በስፋት በማልማት የአገር ውስጥ የኢነርጂ አቅርቦትን ተደራሽ ለማድረግ እንዲሁም የኢነርጂ ኤክስፖርትን ለማስፋፋት የሚያስችል ስራዎች እየተሰሩ ይገኛል፡፡ ባለስልጣን መ/ቤቱ በዚህ ዘርፍ የሚደረገውን ልማት ኢንቨስትመንት ለማሳደግ የሚያስችል ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር የዘርፉን የቁጥጥር ስርዓት የሚያሳዩ የህግ ማዕቀፎች በኢግዚብሽኑ ላይ ለጎብኚዎች ቀርበዋል፡፡

በአንድ ሳምንት ውስጥ ብቻ ከ360 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ ወደ ትግራይ ክልል ተጓጉዟል አዲስ አበባ ታህሳስ 27 ቀን 2015 (ኢዜአ) በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ብቻ ከ360 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ ወደ ትግራይ ክልል መጓጓዙን የኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን አስታወቀ። መንግሥት በክልሉ የነዳጅ አቅርቦቱ እንዳይስተጓጎል ግብረ-ኃይል አቋቁሞ እየሠራ መሆኑም ተጠቁሟል። በመንግሥትና በህወሓት መካከል የተደረሰውን የሰላም ስምምነት ተከትሎ በርካታ የአገልግሎት መስጪያ ተቋማት ዳግም ሥራ መጀመራቸው ይታወቃል፡፡ ለአብነትም ባንክ፣ ቴሌኮም፣ የአውሮፕላን ትራንስፖርት እና ሌሎች አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ዳግም ሥራ የጀመሩ ሲሆን፤ ሰብዓዊ ድጋፍም በስፋት እየቀረበ ነው፡፡ በትግራይ ክልል የነዳጅ አቅርቦትን በተሳለጠ ሁኔታ ለማከናወን ግብረ-ኃይል ተቋቁሞ ወደ ሥራ መገባቱም ተገልጿል። የኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሰሃረላ አብዱላሂ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ መንግሥት ግብረ-ኃይል በማቋቋም ነዳጅ ያለምንም መስተጓጎል ከጂቡቲ ወደ ክልሉ በቀጥታ እንዲገባ እየተደረገ ነው፡፡ ድርጅቱ ከታኅሳስ 19 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ክልሉ ነዳጅ እንዲጓጓዝ ለነዳጅ አቅራቢዎች ፈቃድ መስጠቱን ያስታወሱት ኃላፊዋ፤ ይህን ተከትሎም ባለፈው አንድ ሳምንት በስምንት የነዳጅ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ከ360 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ ወደ ትግራይ ክልል መጓጓዙን ተናግረዋል፡፡ በተለይ በመቀሌ የሚገኙ የነዳጅ ማደያዎች በጦርነቱ ጉዳት ያልደረሰባቸው በመሆኑ፤ ከማደያዎቹ ባለቤቶችና ኩባንያዎች ጋር በመነጋገር ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ እንዲገቡ ማድረግ መቻሉንም ገልጸዋል። በተጨማሪ የነዳጅ አቅርቦቱ በሁሉም የክልሉ ከተሞች እንዲዳረስ እየተሠራ መሆኑንም ነው የጠቀሱት፡፡ በአጠቃላይ መንግስት እያከናወነው ያለው ሥራ የነዳጅ አቅርቦቱን ተደራሽ በማድረግ ረገድ ተጨማሪ አቅም የሚፈጥር መሆኑንም አብራርተዋል፡፡ እስካሁን ባለው ሂደትም ከመቀሌ እስከ ዛልአንበሳ ያሉ ቶታል፣ ኖክ፣ ታፍና ኦይል ሊቢያ ማደያዎች የነዳጅ ጭነት ትዕዛዝ ማስተላለፋቸውንም ጠቅሰዋል፡፡ በክልሉ ለሁለት ዓመታት ያህል የነዳጅ ማደያዎች ተዘግተው የቆዩ በመሆኑ ”እንዲያውቁት” በሚል አሁን ያለውን ሀገራዊ የነዳጅ የመሸጫ ዋጋ ዝርዝር መላኩንም ጠቁመዋል። በቅርቡም ከኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅትና ኩባንያዎች የተውጣጡ አባላት ወደ ክልሉ በመጓዝ የነዳጅ አጠቃቀም እንቅስቃሴ ምልከታ ያደርጋል ብለዋል። በቀጣይም በክልሉ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን የታለመ የነዳጅ አቅርቦት ተግባራዊ ለማድረግ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።

በአንድ ሳምንት ውስጥ ብቻ ከ360 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ ወደ ትግራይ ክልል ተጓጉዟል አዲስ አበባ ታህሳስ 27 ቀን 2015 (ኢዜአ) በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ብቻ ከ360 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ
በአንድ ሳምንት ውስጥ ብቻ ከ360 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ ወደ ትግራይ ክልል ተጓጉዟል አዲስ አበባ ታህሳስ 27 ቀን 2015 (ኢዜአ) በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ብቻ ከ360 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ ወደ ትግራይ ክልል መጓጓዙን የኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን አስታወቀ። መንግሥት በክልሉ የነዳጅ አቅርቦቱ እንዳይስተጓጎል ግብረ-ኃይል አቋቁሞ እየሠራ መሆኑም ተጠቁሟል። በመንግሥትና በህወሓት መካከል የተደረሰውን የሰላም ስምምነት ተከትሎ በርካታ የአገልግሎት መስጪያ ተቋማት ዳግም ሥራ መጀመራቸው ይታወቃል፡፡ ለአብነትም ባንክ፣ ቴሌኮም፣ የአውሮፕላን ትራንስፖርት እና ሌሎች አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ዳግም ሥራ የጀመሩ ሲሆን፤ ሰብዓዊ ድጋፍም በስፋት እየቀረበ ነው፡፡ በትግራይ ክልል የነዳጅ አቅርቦትን በተሳለጠ ሁኔታ ለማከናወን ግብረ-ኃይል ተቋቁሞ ወደ ሥራ መገባቱም ተገልጿል።

በአንድ ሳምንት ውስጥ ብቻ ከ360 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ ወደ ትግራይ ክልል ተጓጉዟል አዲስ አበባ ታህሳስ 27 ቀን 2015 (ኢዜአ) በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ብቻ ከ360 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ ወደ ትግራይ ክልል መጓጓዙን የኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን አስታወቀ። መንግሥት በክልሉ የነዳጅ አቅርቦቱ እንዳይስተጓጎል ግብረ-ኃይል አቋቁሞ እየሠራ መሆኑም ተጠቁሟል። በመንግሥትና በህወሓት መካከል የተደረሰውን የሰላም ስምምነት ተከትሎ በርካታ የአገልግሎት መስጪያ ተቋማት ዳግም ሥራ መጀመራቸው ይታወቃል፡፡ ለአብነትም ባንክ፣ ቴሌኮም፣ የአውሮፕላን ትራንስፖርት እና ሌሎች አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ዳግም ሥራ የጀመሩ ሲሆን፤ ሰብዓዊ ድጋፍም በስፋት እየቀረበ ነው፡፡ በትግራይ ክልል የነዳጅ አቅርቦትን በተሳለጠ ሁኔታ ለማከናወን ግብረ-ኃይል ተቋቁሞ ወደ ሥራ መገባቱም ተገልጿል። የኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሰሃረላ አብዱላሂ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ መንግሥት ግብረ-ኃይል በማቋቋም ነዳጅ ያለምንም መስተጓጎል ከጂቡቲ ወደ ክልሉ በቀጥታ እንዲገባ እየተደረገ ነው፡፡ ድርጅቱ ከታኅሳስ 19 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ክልሉ ነዳጅ እንዲጓጓዝ ለነዳጅ አቅራቢዎች ፈቃድ መስጠቱን ያስታወሱት ኃላፊዋ፤ ይህን ተከትሎም ባለፈው አንድ ሳምንት በስምንት የነዳጅ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ከ360 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ ወደ ትግራይ ክልል መጓጓዙን ተናግረዋል፡፡ በተለይ በመቀሌ የሚገኙ የነዳጅ ማደያዎች በጦርነቱ ጉዳት ያልደረሰባቸው በመሆኑ፤ ከማደያዎቹ ባለቤቶችና ኩባንያዎች ጋር በመነጋገር ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ እንዲገቡ ማድረግ መቻሉንም ገልጸዋል። በተጨማሪ የነዳጅ አቅርቦቱ በሁሉም የክልሉ ከተሞች እንዲዳረስ እየተሠራ መሆኑንም ነው የጠቀሱት፡፡ በአጠቃላይ መንግስት እያከናወነው ያለው ሥራ የነዳጅ አቅርቦቱን ተደራሽ በማድረግ ረገድ ተጨማሪ አቅም የሚፈጥር መሆኑንም አብራርተዋል፡፡ እስካሁን ባለው ሂደትም ከመቀሌ እስከ ዛልአንበሳ ያሉ ቶታል፣ ኖክ፣ ታፍና ኦይል ሊቢያ ማደያዎች የነዳጅ ጭነት ትዕዛዝ ማስተላለፋቸውንም ጠቅሰዋል፡፡ በክልሉ ለሁለት ዓመታት ያህል የነዳጅ ማደያዎች ተዘግተው የቆዩ በመሆኑ ”እንዲያውቁት” በሚል አሁን ያለውን ሀገራዊ የነዳጅ የመሸጫ ዋጋ ዝርዝር መላኩንም ጠቁመዋል። በቅርቡም ከኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅትና ኩባንያዎች የተውጣጡ አባላት ወደ ክልሉ በመጓዝ የነዳጅ አጠቃቀም እንቅስቃሴ ምልከታ ያደርጋል ብለዋል። በቀጣይም በክልሉ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን የታለመ የነዳጅ አቅርቦት ተግባራዊ ለማድረግ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።በአንድ ሳምንት ውስጥ ብቻ ከ360 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ ወደ ትግራይ ክልል ተጓጉዟል አዲስ አበባ ታህሳስ 27 ቀን 2015 (ኢዜአ) በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ብቻ ከ360 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ ወደ ትግራይ ክልል መጓጓዙን የኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን አስታወቀ። መንግሥት በክልሉ የነዳጅ አቅርቦቱ እንዳይስተጓጎል ግብረ-ኃይል አቋቁሞ እየሠራ መሆኑም ተጠቁሟል። በመንግሥትና በህወሓት መካከል የተደረሰውን የሰላም ስምምነት ተከትሎ በርካታ የአገልግሎት መስጪያ ተቋማት ዳግም ሥራ መጀመራቸው ይታወቃል፡፡ ለአብነትም ባንክ፣ ቴሌኮም፣ የአውሮፕላን ትራንስፖርት እና ሌሎች አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ዳግም ሥራ የጀመሩ ሲሆን፤ ሰብዓዊ ድጋፍም በስፋት እየቀረበ ነው፡፡ በትግራይ ክልል የነዳጅ አቅርቦትን በተሳለጠ ሁኔታ ለማከናወን ግብረ-ኃይል ተቋቁሞ ወደ ሥራ መገባቱም ተገልጿል። የኢትዮጵያ ነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሰሃረላ አብዱላሂ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ መንግሥት ግብረ-ኃይል በማቋቋም ነዳጅ ያለምንም መስተጓጎል ከጂቡቲ ወደ ክልሉ በቀጥታ እንዲገባ እየተደረገ ነው፡፡ ድርጅቱ ከታኅሳስ 19 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ክልሉ ነዳጅ እንዲጓጓዝ ለነዳጅ አቅራቢዎች ፈቃድ መስጠቱን ያስታወሱት ኃላፊዋ፤ ይህን ተከትሎም ባለፈው አንድ ሳምንት በስምንት የነዳጅ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ከ360 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ ወደ ትግራይ ክልል መጓጓዙን ተናግረዋል፡፡ በተለይ በመቀሌ የሚገኙ የነዳጅ ማደያዎች በጦርነቱ ጉዳት ያልደረሰባቸው በመሆኑ፤ ከማደያዎቹ ባለቤቶችና ኩባንያዎች ጋር በመነጋገር ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ እንዲገቡ ማድረግ መቻሉንም ገልጸዋል። በተጨማሪ የነዳጅ አቅርቦቱ በሁሉም የክልሉ ከተሞች እንዲዳረስ እየተሠራ መሆኑንም ነው የጠቀሱት፡፡ በአጠቃላይ መንግስት እያከናወነው ያለው ሥራ የነዳጅ አቅርቦቱን ተደራሽ በማድረግ ረገድ ተጨማሪ አቅም የሚፈጥር መሆኑንም አብራርተዋል፡፡ እስካሁን ባለው ሂደትም ከመቀሌ እስከ ዛልአንበሳ ያሉ ቶታል፣ ኖክ፣ ታፍና ኦይል ሊቢያ ማደያዎች የነዳጅ ጭነት ትዕዛዝ ማስተላለፋቸውንም ጠቅሰዋል፡፡ በክልሉ ለሁለት ዓመታት ያህል የነዳጅ ማደያዎች ተዘግተው የቆዩ በመሆኑ ”እንዲያውቁት” በሚል አሁን ያለውን ሀገራዊ የነዳጅ የመሸጫ ዋጋ ዝርዝር መላኩንም ጠቁመዋል። በቅርቡም ከኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅትና ኩባንያዎች የተውጣጡ አባላት ወደ ክልሉ በመጓዝ የነዳጅ አጠቃቀም እንቅስቃሴ ምልከታ ያደርጋል ብለዋል። በቀጣይም በክልሉ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን የታለመ የነዳጅ አቅርቦት ተግባራዊ ለማድረግ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።

የታለመ ነዳጅ ድጎማ የስድስት ወር ሂደት በተለያዩ አካላት አስተያየት የተሰጠበትና የተዳሰሰበት የቴሌቪዥን ዘጋቢ ፕሮግራም ዛሬ ታህሳስ 23/2015 ዓ.ም በፋና ቴሌቪዥን ከምሽቱ 3፡00 ሠዓት በፋና መድረክ ክፍለ ጊዜ የሚቀርብ በመሆኑ እንድትከታተሉት እንጋብዛለን፡፡