en
Feedback
Petroleum and Energy Authority

Petroleum and Energy Authority

Open in Telegram

Energy, being an engine of development, is important that supplies all of the economic sectors. To be more benefited from the energy sector, it should be regulated in affordable and environmentally friendly manner. For this to happen, the Ethiopian govern

Show more
962
Subscribers
+124 hours
-17 days
-130 days
Posts Archive
ኢነርጂ አጠቃቀምን በተመኹለተ ዚግንዛቀ ማስጚበጫ ስልጠና ተሰጠ። ********************* አዳማ ህዳር 25/2016ዓ.ም (ነ.ኢ.ባ)፡- ዚኀሌክትሪክ መገልገያ እቃዎቜ ኢነርጂ ብቃትና ኣጠቃቀ
+1
ኢነርጂ አጠቃቀምን በተመኹለተ ዚግንዛቀ ማስጚበጫ ስልጠና ተሰጠ። ********************* አዳማ ህዳር 25/2016ዓ.ም (ነ.ኢ.ባ)፡- ዚኀሌክትሪክ መገልገያ እቃዎቜ ኢነርጂ ብቃትና ኣጠቃቀምን በተመለኹተ ኚተለያዩ ክ/ኚተሞቜ ለተውጣጡ ሎቶቜ ለሁለተ ቀን ዹቆዹ ዚግንዛቀ ማስጚበጫ ስልጠና ተሰጠ። ሰልጠናውን ኣስመልክቶ ዚነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ዚሎቶቜና ወጣቶቜ ዳይሬክተር ዚሆኑት ወ/ሮ አይናለም ወልዮ እንደተናገሩት ኢነርጂ ለኢኮኖሚ እድገት ወሳኝ ግብዓት እንደሆነ ገልፀው በሁሉም ዚኢኮኖሚ ዘርፍ ምርታማነትን ለማሚጋገጥ ዚኢነርጂ አቅርቊት አስተማማኘነትን ኚማሚጋገጥ ባሻገር አጠቃቀማቜን ብቃትን መሰሚት ያደሚገ ሊሆን ይገባል በማለት ዚገለጹ ሲሆን ዹአገርን ኢኮኖሚ በማሳደግ ሂደት ውስጥ ሎቶቜ ዚሚኖራ቞ው ተሳትፎ ጉልህ በመሆኑ ዚኢነርጂ ብቃትና ቁጠባ ማደግና አገልግሎቱም በጥራትና ወጪ ቆጣቢ መልክ ማቅሚቡ በተለይ ዚሎቶቜን ህይወት በመለወጥ ኢኮኖሚያዊ ጥንካሬን ዚሚፈጥርላ቞ው ሲሆን ዹበለጠም ምርታማና ብቁ ስለሚያደርጋ቞ው ዚኢነርጂ አገልግሎቱ ኚማሳደግ ጎን ለጎን በዘርፉ ዚሎቶቜን ዹአነርጂ ፍላጎትና አቅርቊት ማጥናትና ተሳትፎ቞ውን ማሳደግ ተገቢ እንደሆነ ተናግሚዋል፡፡ በመጚሚሻምዚኢነርጂ ብቃታ቞ው ዹተሹጋገጠ ዚኀልክትሪክ መገልገያ ዕቃዎቜን መጠቀም በግልሰብፀበማህበሚሰብ እና በአገር ደሹጃ ዹሚኖሹውን ዚኢነርጂብክነትና ብክለት በመቀነስ ዚኀሌክትሪክ ወጪ በመቆጠብና ኀሌክትሪክ ያላገኙ ዚህብሚተሰብ ክፍሎቜን ብማዳሚስ ተጠቃሚ ማድሚግ እንደሚቻል አስሚድተዋል፡፡

ኚፆታ ጥቃት ጋር በተያያዘ በሚፈጠሩ ቜግሮቜ ላይ ግንዛቀ መፍጠር እንደሚያስፈልግ ተገለፀ፡፡ ህዳር 15/2016 ዓ.ም(ነ.ኢ.ባ) በባለስልጣን መ/ቀቱ ዚሎቶቜ፣ህፃናትና አሚጋዊያን ዳይሬክቶሬት ፆታን መ
+4
ኚፆታ ጥቃት ጋር በተያያዘ በሚፈጠሩ ቜግሮቜ ላይ ግንዛቀ መፍጠር እንደሚያስፈልግ ተገለፀ፡፡ ህዳር 15/2016 ዓ.ም(ነ.ኢ.ባ) በባለስልጣን መ/ቀቱ ዚሎቶቜ፣ህፃናትና አሚጋዊያን ዳይሬክቶሬት ፆታን መሠሚት ያደሚጉ ጥቃቶቜ ኹጊዜ ወደ ጊዜ እዚጚመሩ ኚመምጣታ቞ው ጋር በተያያዘ ለመ/ቀቱ ሠራተኞቜ ዚግንዛቀ መፍጠሪያ ስልጠና ሰጥቷል፡፡ በነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ዚሎቶቜ፣ህፃናትና አሚጋዊያን ዳይሬክቶሬት ሥራ አሰፈፃሚ ዚሆኑት ወ/ሮ አይናለም ወልዮ እንደገለፁት ፆታን መሠሚት ያደሚጉ ጥቃቶቜ በሁሉም ዚእድሜ ደሹጃ ላይ ባሉ ዚሕብሚተሰብ ክፍሎቜ ዹሚደሹግ ጥቃት በመሆኑ ትኩሚት ሊደሚግበት እንደሚገባ ገልፀው ቜግሩን ተኚትሎ በሚኚሠቱ አካላዊና አእምሮአዊ ጉዳቶቜ በሕብሚተሰብ ደህንነት እና በሀገር ኢኮኖሚ ላይ መጠነ ሠፊ ቜግር በማስኚተል ለዘላቂ ልማት እንቅፋት መሆናቾውን በንግግራ቞ው አብራርተዋል፡፡

ሙስናን በጋራ ለመታገል ዚግንዛቀ ማስጚበጫ ስልጠና ተሠጠ አዳማ ህዳር 14/2016ዓ.ም (ነ.ኢ.በ)፡- ሙስና ዜጎቜን ለስቃይ፣ ለእንግልት እና ለኹፋ ድህነት ዚሚዳርግ አደገኛ ዚህዝብ ጠላትም ወንጀልም
+7
ሙስናን በጋራ ለመታገል ዚግንዛቀ ማስጚበጫ ስልጠና ተሠጠ    አዳማ ህዳር 14/2016ዓ.ም (ነ.ኢ.በ)፡- ሙስና ዜጎቜን ለስቃይ፣ ለእንግልት እና ለኹፋ ድህነት ዚሚዳርግ አደገኛ ዚህዝብ ጠላትም ወንጀልም ስለሆነ ሙስናን በጋራ ለመታገል ለአመራሩና ለአጠቃላይ ሠራተኞቜ ዚግንዛቀ ማስጚበጫ ስልጠና መስጠቱ ተገለፀ ፡፡  ሙስና ዹሀገርን ኢኮኖሚን፣ ፖለቲካንና ማህበራዊ እንቅስቃሎ በማናጋት ሀገርን እስኚ መበተን ዚሚያደርስ ድንበር ዘለል ወንጀል ሰለሆነ እንዳንዱ ዚነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን አመራሮቜና ሠራተኞቜ ዚሙስና ወንጀልን በጋራ ለመኹላኹልና በህብሚት መታገል ዚሚያስቜል ዹአቅም ግንባታ ሥራና ዚጋራ መግባባት  ተሰርቷል፡፡  ዚነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ዚፀሪ-ሙስናና ሥነ-ምግባር መኚታተያ ዳይሬክተር ዚሆኑት አቶ አበራ አዱኛ  እንደ ገለጹት ሙስና ያለልዩነት ሁሉንም ኢትዮጵያውያንን ዚሚጎዳ፣ ውስብስብ፣ ድንበር ተሻጋሪ እና ዓለም ቀፍ ቜግር መሆኑን በመገንዘብ ዚጋራ ጠላት ዹሆነውን ሙስና በጋራ መታገልና ዚጋራ ግንዛቀ በማሳጫበጥ ቜግሩን መቀነስ እንደሚቻል  በአፅንዖት አሳስበዋል፡፡   ሙስና ዚጋራ ጠላታቜን ነውፀ በሕብሚት እንታገል! በሚል መሪ ቃል ዘንድሮም 20ኛው ዓለም አቀፍ ዚፀሚሙስና ቀን በመኹበር ላይ ይገልኛፀ በተጚማሪም ሙስናን ታግሎ ማሾነፍ ዚሚቻለው መንግስት እና ዚሚመለኚታ቞ው አካላት በጋራ በመቀናጀት ሙስናን ለመታገል ቁርጠኝነታ቞ውን በተግባር ሲያሳዩ ብቻ ሰለሆነ እንዳንዱ ዚባለስልጣኑ አመራሮቜና ሠራቶኞቜ በሙሉ ሙስናን በመፀዹፍና በመታገል አስፈላጊውን ሁሉ ሚናቾውን እንዱወጡ ዚእለቱን መልዕክት አስተላልፍዋል፡፡                      

ሙስናን በጋራ ለመታገል ዚግንዛቀ ማስጚበጫ ስልጠና ተሠጠ አዳማ ህዳር 14/2016ዓ.ም (ነ.ኢ.በ)፡- ሙስና ዜጎቜን ለስቃይ፣ ለእንግልት እና ለኹፋ ድህነት ዚሚዳርግ አደገኛ ዚህዝብ ጠላትም ወንጀልም
+8
ሙስናን በጋራ ለመታገል ዚግንዛቀ ማስጚበጫ ስልጠና ተሠጠ    አዳማ ህዳር 14/2016ዓ.ም (ነ.ኢ.በ)፡- ሙስና ዜጎቜን ለስቃይ፣ ለእንግልት እና ለኹፋ ድህነት ዚሚዳርግ አደገኛ ዚህዝብ ጠላትም ወንጀልም ስለሆነ ሙስናን በጋራ ለመታገል ለአመራሩና ለአጠቃላይ ሠራተኞቜ ዚግንዛቀ ማስጚበጫ ስልጠና መስጠቱ ተገለፀ ፡፡  ሙስና ዹሀገርን ኢኮኖሚን፣ ፖለቲካንና ማህበራዊ እንቅስቃሎ በማናጋት ሀገርን እስኚ መበተን ዚሚያደርስ ድንበር ዘለል ወንጀል ሰለሆነ እንዳንዱ ዚነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን አመራሮቜና ሠራተኞቜ ዚሙስና ወንጀልን በጋራ ለመኹላኹልና በህብሚት መታገል ዚሚያስቜል ዹአቅም ግንባታ ሥራና ዚጋራ መግባባት  ተሰርቷል፡፡  ዚነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ዚፀሪ-ሙስናና ሥነ-ምግባር መኚታተያ ዳይሬክተር ዚሆኑት አቶ አበራ አዱኛ  እንደ ገለጹት ሙስና ያለልዩነት ሁሉንም ኢትዮጵያውያንን ዚሚጎዳ፣ ውስብስብ፣ ድንበር ተሻጋሪ እና ዓለም ቀፍ ቜግር መሆኑን በመገንዘብ ዚጋራ ጠላት ዹሆነውን ሙስና በጋራ መታገልና ዚጋራ ግንዛቀ በማሳጫበጥ ቜግሩን መቀነስ እንደሚቻል  በአፅንዖት አሳስበዋል፡፡   ሙስና ዚጋራ ጠላታቜን ነውፀ በሕብሚት እንታገል! በሚል መሪ ቃል ዘንድሮም 20ኛው ዓለም አቀፍ ዚፀሚሙስና ቀን በመኹበር ላይ ይገልኛፀ በተጚማሪም ሙስናን ታግሎ ማሾነፍ ዚሚቻለው መንግስት እና ዚሚመለኚታ቞ው አካላት በጋራ በመቀናጀት ሙስናን ለመታገል ቁርጠኝነታ቞ውን በተግባር ሲያሳዩ ብቻ ሰለሆነ እንዳንዱ ዚባለስልጣኑ አመራሮቜና ሠራቶኞቜ በሙሉ ሙስናን በመፀዹፍና በመታገል አስፈላጊውን ሁሉ ሚናቾውን እንዱወጡ ዚእለቱን መልዕክት አስተላልፍዋል፡፡                      

በኢንደስትሪ ፓርኮቜ ዚኢነርጂ ብቃትና ቁጠባን ተግባራዊ ለማድሚግ ዚሚያስቜል ስምምነት ተፈሚመ፡፡ ****************************************************************
+5
በኢንደስትሪ ፓርኮቜ ዚኢነርጂ ብቃትና ቁጠባን ተግባራዊ ለማድሚግ ዚሚያስቜል ስምምነት ተፈሚመ፡፡ *********************************************************************** ስምምነቱን ዚነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሠሃሹላ አብዱላሂ እና ዚኢንደስትሪ ፓርኮቜ ልማት ኮርፖሬሜን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አክሊሉ ታደሠ ተፈራርመዋል፡፡ በስምምነቱ በኢንደስትሪ ፓርኮቜ እና በኢንደስትሪ ፓርኩ ስር ባሉ አስራ ሶስት ኢንደስትሪዎቜ ላይ ዚኢነርጂ ብቃትና ቁጠባን መሠሚት ያደሚጉ ስራዎቜን በትብብር በመስራት በሶስት ዓመት ውስጥ 10 በመቶ ዹሚሆን ያለአግባብ ዚሚባክን ኢነርጂ ለመቆጠብ ዚሚያስቜል አቅም ለመፍጠር ያስቜላል ተብሏል፡፡ ዚነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሠሃሹላ አብዱላሂ ስምምነቱን አስመልክተው ኢነርጂን በብቃትና በቁጠባ መጠቀም መቻል እንደ ሀገር ዚሚባክን ኢነርጂ መቀነስ ኚማስቻሉ ባለፈ ዚኀሌክትሪክ አቅርቊት ላይ ዹሚፈጠሹውን አላስፈላጊ ጫና መቀነስ እንደሚያስቜል ገልፀዋል፡፡ አቶ አክሊሉ ታደሰ ዚኢንደስትሪ ፓርኮቜ ልማት ኮርፖሬሜን ዋና ስራ አስፈፃሚ በበኩላ቞ው ስምምነቱ በኢንደስትሪ ፓርኮቜ ኢነርጂን በአግባቡ ሳይባክን ለመጠቀም ዚሚያስቜል ኹመሆኑ ባሻገር በቀጣይ ኚባለስልጣን መ/ቀቱ ጋር በመተባበር በፓርኮቜ ዚሚያጋጥም ኚኀሌክትሪክ መቆራሚጥ ቜግርን ለመፍታት በጋራ መስራት እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል፡፡

በኢንደስትሪ ፓርኮቜ ዚኢነርጂ ብቃትና ቁጠባን ተግባራዊ ለማድሚግ ዚሚያስቜል ስምምነት ተፈሚመ፡፡ ****************************************************************
+5
በኢንደስትሪ ፓርኮቜ ዚኢነርጂ ብቃትና ቁጠባን ተግባራዊ ለማድሚግ ዚሚያስቜል ስምምነት ተፈሚመ፡፡ *********************************************************************** ስምምነቱን ዚነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሠሃሹላ አብዱላሂ እና ዚኢንደስትሪ ፓርኮቜ ልማት ኮርፖሬሜን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አክሊሉ ታደሠ ተፈራርመዋል፡፡ በስምምነቱ በኢንደስትሪ ፓርኮቜ እና በኢንደስትሪ ፓርኩ ስር ባሉ አስራ ሶስት ኢንደስትሪዎቜ ላይ ዚኢነርጂ ብቃትና ቁጠባን መሠሚት ያደሚጉ ስራዎቜን በትብብር በመስራት በሶስት ዓመት ውስጥ 10 በመቶ ዹሚሆን ያለአግባብ ዚሚባክን ኢነርጂ ለመቆጠብ ዚሚያስቜል አቅም ለመፍጠር ያስቜላል ተብሏል፡፡ ዚነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሠሃሹላ አብዱላሂ ስምምነቱን አስመልክተው ኢነርጂን በብቃትና በቁጠባ መጠቀም መቻል እንደ ሀገር ዚሚባክን ኢነርጂ መቀነስ ኚማስቻሉ ባለፈ ዚኀሌክትሪክ አቅርቊት ላይ ዹሚፈጠሹውን አላስፈላጊ ጫና መቀነስ እንደሚያስቜል ገልፀዋል፡፡ አቶ አክሊሉ ታደሰ ዚኢንደስትሪ ፓርኮቜ ልማት ኮርፖሬሜን ዋና ስራ አስፈፃሚ በበኩላ቞ው ስምምነቱ በኢንደስትሪ ፓርኮቜ ኢነርጂን በአግባቡ ሳይባክን ለመጠቀም ዚሚያስቜል ኹመሆኑ ባሻገር በቀጣይ ኚባለስልጣን መ/ቀቱ ጋር በመተባበር በፓርኮቜ ዚሚያጋጥም ኚኀሌክትሪክ መቆራሚጥ ቜግርን ለመፍታት በጋራ መስራት እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል፡፡

    ዚኢነርጂ ብቃት  መለያ በተለጣፊ ምልክት ትግበራን አስገዳጅ እዚተደገ ያለውን ዹ ኀሌክትሪክ እንጀራ ምጣድና ምዳጃ   መቆጣጠሪያ ስዓርት በመዘርጋት በተለይም አምራ቟ቜ ዚኀሌክሪክት እንጀራ ምጣድና ምድጃን  ኢነርጂ ብቃታ቞ውን በማስፈተሞ ሓይል ቆጣቢ ዚተለጣፊ ምልክት በመለጠፍ ለተጠቃሚዎቜ ወደ ገበያ እንዲያቀርቡ በማለት ዚሁለትዮሜ  ውይይት ዹተደሹገ ሲሆን አሠራሩን ይበልጥ ውጀታማ ሆኖ እንዲቀጥል አፈፃፀሙን መነሻ በማድሚግ በቀጣይ ሊካተቱ ዚሚቜሉትን ዚማሻሻያ አስተያዚቶቜ እንዲካተቱ አቅጣጫ በመስጠት በሁለቱም ርዕሰ ጉዳዮቜ ላይ ኚአምራ቟ቜ  ጋር ስምምነት ላይ በመድሚስ ውይይቱ ተጠነቋል፡፡  

ኚኀሌክትሪክ እንጀራ ምጣድ አምራ቟ቜ ጋር ወይይት ተደሹገ ፡፡ ********************************************* ህዳር 06/2016 ዓ.ም አዳማ (ነ.ኢ.ባ) ዚኢነርጂ ብቃትና ቁ
+9
ኚኀሌክትሪክ እንጀራ ምጣድ አምራ቟ቜ ጋር ወይይት ተደሹገ ፡፡ ********************************************* ህዳር 06/2016 ዓ.ም አዳማ (ነ.ኢ.ባ)  á‹šáŠ¢áŠáˆ­áŒ‚ ብቃትና ቁጣባን ውጀታማነት ለማሳካት ዚተለጣፊ ምልክት ትግበራን አስገዳጅ ለማድሚግ በተመለኹተ ኚኀሌክትሪክ እንጀራ ምጣድ አምራ቟ቜ  ጋር ወይይት ተደሚገ፡፡  á‰ áŠ€áˆŒáŠ­á‰µáˆªáŠ­ እንጀራ ምጣድና ምዳጃ አምራ቟ቜ አማካይነት በመላው ሀገሪቱ ዚለጣፊ ምልክት ትግበራን አስገዳጅ በማድሚግ እንደ ሀገር ዹሐይል ብክነት ለመቀነስ ትልቅ ድርሻ እንዳለው ኚባለድርሻ አካላት ጋር  በተመለኹተ ሰፊ ወይይት ተደርጓል ፡፡  á‹šáŠá‹³áŒ… እና ኢነርጂ ባለስልጣን ዚኢነርጂ ብቃትና ቁጣባ ዳይሬክተር ዚሆኑት ኢንጂነር ዘውገ ወርቁ እንደ ገለጹት ዚተለጣፊ ምልክት ትግበራን  አስገዳጅ በመድሚግ ዚኢነርጂ ብቃትና ቁጠባን በማስፋት በኀሌክትሪክ  አገልግሎት ተተቃሚ አካላት ዚሚባክን እነርጂ እንዲቆጠብ ለማስቻል ቁልፍ ተግባር መሆኑን በመግለፅ  áˆˆá‹ˆá‹°áŠá‰± መስተካኚል እንዳለበት ዚአሌክትሪክ አቅርቊቱና አገልግሎቱን አስተማማኝ ፀደህንነቱ ዹተጠቀበ ፀ ፍታሀዊና ዚኢነርጂ ኢኮኖሚያዊ ደህነትን ቜግርን  ለመቅሹፍ ይሚዳ ዘንድ ለወደ ፊቱም ኚአምራ቟ቜ በመወያዚት ዚኢነርጂ ብክነት ዚጋራ ግንዛቀ በማሳጫበጥ ቜግሩን መቀነስ እንደሚቻል አሳስበዋል፡፡      

ነዳጅን ኚግብይት ስርዓት ውጪ በተገበያዩ ማደያዎቜ ላይ ዕገዳ ተጣለ፡፡ *********************************************************************** ኚዲጂታል ነዳጅ ግብይት ስርዓት ውጪ ነዳጅን በመሞጣ቞ው እና በስማ቞ው ኚተጫነላ቞ው ነዳጅ በላይ በማደያ቞ው በሞጡ አዲስ አበባ እና ሾገር ኚተሞቜ በሚገኙ አርባ ዚነዳጅ ማደያዎቜ ላይ ዚአንድ ወር ዚነዳጅ ጭነት ዕገዳ ዚተጣለባ቞ው ሲሆን ሀምሳ ሰባት ነዳጅ ማደያዎቜ ደግሞ ዹፅሁፍ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷ቞ዋል፡፡ በሁለቱ ኚተሞቜ ኹሚገኙ ማደያዎቜ ዕገዳ ዚተጣለባ቞ው በቁጥር አርባ ዹሚሆኑ ማደያዎቜ ሲሆኑ ለባለስልጣን መ/ቀቱ ኚመስኚሚም 10 እስኚ ጥቅምት 11/2016 ዓ.ም ባለው አንድ ወር ጊዜ ውስጥ በደሹሰው ዚኀሌክትሮኒክስ ነዳጅ ግብይት መተግበሪያ ሪፖርት መሠሚት በስማ቞ው ኚተጫነላ቞ው ነዳጅ በላይ መሞጣ቞ውን ዚሚያሳይ ሪፖርት ያላ቞ው እና ኚዲጂታል መተግበሪያ ውጪ ነዳጅን በሞጡ ማደያዎቜ ላይ ኚቁጥጥር ስርዓቱ ውጪ ግብይት በመፈፀማቾው ዚአንድ ወር ዚነዳጅ ጭነት ዕገዳ ተጥሎባ቞ዋል፡፡ ኚተጫነላ቞ው ነዳጅ ኚሃምሳ እሰኚ ሰማኒያ በመቶ ዹሚሆነውን ነዳጅ ብቻ በዲጂታል ግብይት ለፈፀሙ ሃምሳ ሰባት ዚነዳጅ ማደያዎቜ ደግሞ ዹፅሁፍ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶ቞ዋል፡፡ ዚነዳጅ ህገወጥ ንግድን ለመቆጣጠር ዚሚያስቜል ዲጂታል ዚነዳጅ ግብይት ኹሐምሌ 1/2016 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ እና ሾገር ኚተሞቜ ተግባራዊ ዹተደሹ ሲሆን ይህ ስርዓት ኚማደያ ውጪ ነዳጅ በሕገወጥ መንገድ እንዳይሞጥ ለመቆጣጠር እና ነዳጅ ለታለመለት ዓላማ መንግስት በተመነው ዋጋ ለተገልጋዩ ህብሚትሰብ ማድርስ እንዲቻል ታሳቢ ተደርጎ ዹተዘሹጋ ዚቁጥጥር ሥርዓት ነው፡፡

ዹ16ኛው ብሔራዊ ዹሰንደቅ ዓላማ በዓል በድምቀት ተኹበሹ አዲስ አበባ ጥቅምት 5/2016ዓ.ም /ነ.ኢ.ባ./ሰራተኞቜ እና ማዕድን ሚኒስ቎ር ሠራተኞቜ በጋራ በመሆን ዹ16ኛው ብሔራዊ ዹሰንደቅ ዓላማ በዓ
+4
ዹ16ኛው ብሔራዊ ዹሰንደቅ ዓላማ በዓል በድምቀት ተኹበሹ አዲስ አበባ ጥቅምት 5/2016ዓ.ም /ነ.ኢ.ባ./ሰራተኞቜ እና ማዕድን ሚኒስ቎ር ሠራተኞቜ በጋራ በመሆን ዹ16ኛው ብሔራዊ ዹሰንደቅ ዓላማ በዓል “ዹሰንደቅ ዓላማቜን ኚፍታ ለኅብሚ ብሐራዊ እንድነታቜንና ሉዓላዊነታቜን ዋስትና ነው!”በሚል ዚዕለቱን መሪ መልዕክቱን በማስተላለፍ በድምቀት ተኚብሯል

በመሆኑም ዹሃይል አጠቃቀም ብክነትን ለማስቀሚት በሚደሹገው ጥሚት በተለይም ተቋማትና ህብሚተሰቡ ድርሻ቞ውን እንዲወጡ ዳይሬክተሩ ጠይቀዋል። ኚሌሎቜ አገሮቜ አንፃር በኢትዮጵያ ብክነትን ለመኹላኹል ብሎም ለማስቀሚት ዚተሰሩ ስራዎቜ ዝቅተኛ መሆናቾውን ጠቅሰው በቀጣይ በብዙ መልኩ ሰፊ ስራ ይጠይቀናል ብለዋል። ኹፍተኛ ሃይል በሚጠቀሙ ፋብሪካዎቜ ላይ ዹግሉን ዘርፍ በማሳተፍ ዹሃይል አጠቃቀም ኊዲት እዚተደሚገ መሆኑን ዚኢነርጂ ብቃትና ቁጠባ ዳይሬክተሩ ገልጞዋል። በፋብሪካዎቜ ዓለም አቀፍ ዹሃይል አጠቃቀም መስፈርት ተግባራዊ እንዲሆን ስልጠና ዚመስጠት እና ዚክትትል ስራ እዚተደሚገ መሆኑንም ተናግሚዋል። በመኖሪያ ቀቶቜ ውስጥ ያለውን ዹሃይል ብክነት ለማስቀሚትም ሀገር ውስጥ ለሚገቡ ዚኀክትሮኒክስ እቃዎቜ መስፈርት ተዘጋጅቶ እንዲገቡ እዚተደሚገ ነው ብለዋል። ዚአዳዲስ ዹህንፃ ግንባታዎቜ ንድፋ቞ው ዹሃይል ቁጠባን ታሳቢ ያደሚገ እንዲሆን መመሪያ እዚተዘጋጀ ስለመሆኑም ጠቁመዋል።

ዚኀሌክትሪክ ሃይል ብክነትን ለማስቀሚት ተቋማትና ህብሚተሰቡ ዚድርሻ቞ውን አስተዋጜኊ ሊያደርጉ ይገባል- ዚነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን አዲስ አበባፀ መስኚሚም 18/2016 (ኢዜአ)ፊ በኢትዮጵያ በስፋት
ዚኀሌክትሪክ ሃይል ብክነትን ለማስቀሚት ተቋማትና ህብሚተሰቡ ዚድርሻ቞ውን አስተዋጜኊ ሊያደርጉ ይገባል- ዚነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን አዲስ አበባፀ መስኚሚም 18/2016 (ኢዜአ)ፊ በኢትዮጵያ በስፋት ዚሚስተዋለውን ዚኀሌክትሪክ ሃይል ብክነት ለማስቀሚት ተቋማትና ህብሚተሰቡ ዚድርሻ቞ውን እንዲወጡ ዚነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን አሳሰበ። በኢትዮጵያ ያለው ዚኀሌክትሪክ ሃይል አጠቃቀም በዓለምአቀፍ ደሹጃ ኹተቀመጠው ዹሃይል አጠቃቀም መስፈርት ያነሰና ብክነት ዚሚጎላበት መሆኑን መሚጃዎቜ ያሳያሉ። ዚኀሌክትሪክ ኃይል ብክነት ማለት በምንጠቀመው ዹኃይል መጠን እና ለማምሚት በሚያስፈልው ኃይል መካኚል ያለው ልዩነት ወይም ምርት ለማምሚት ኚሚያስቜለው በላይ ሃይል መጠቀም መሆኑን ዹዘርፉ ባለሙያዎቜ ይናገራሉ። በዚሁ ዙሪያ ለኢዜአ ማብራሪያ ዚሰጡት ዚነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ዚኢነርጂ ብቃትና ቁጠባ ዳይሬክተር አቶ ዘውገ ወርቁፀ በኢትዮጵያ ያለው ዹሃይል አጠቃቀም ኹፍተኛ ብክነት ዚሚታይበት መሆኑን ገልጞዋል። በተለይም ኹፍተኛ ሃይል ዹሚጠቀሙ ፋብሪካዎቜ፣ ዚንግድ ቀቶቜና ህንፃዎቜ ዹሃይል አጠቃቀም ብክነት ዚሚስተዋልባ቞ው መሆኑን ጠቅሰዋል። ዹሃይል መጠቀሚያ እቃዎቜ ኹደሹጃ በታቜ መሆን ሌላኛው ምክንያት ሲሆን ኹኃይል ማሰራጫ እስኚ ተጠቃሚዎቜ ለማድሚስ ባለው ሂደትም ኹፍተኛ ዹኃይል ብክነት አለ ብለዋል።

መስኚሚም 14/2015 ዓ.ም (ነ.ኢ.ባ) አዳማ ዚኀሌክትሪክ መገልገያ ምርቶቜ ዝቅተኛ ኢነርጂ ብቃት ደሹጃ ላይ ስልጠና ተሰጠ፡፡ ********************************************
+3
መስኚሚም 14/2015 ዓ.ም (ነ.ኢ.ባ) አዳማ ዚኀሌክትሪክ መገልገያ ምርቶቜ ዝቅተኛ ኢነርጂ ብቃት ደሹጃ ላይ ስልጠና ተሰጠ፡፡ *********************************************************************** ለአዲስ አበባ ኹተማ አስተዳደር አኚባቢ ጥበቃ ባለስልጣን እና በኹተማዋ ለሚገኙ ክፍለ ኚተሞቜ ኢነርጂ ባለሙያዎቜ በኢንደስትሪና በመኖሪያ ቀት አገልግሎት ላይ ለሚውሉ ኢነርጂ መገልገያ መሳሪያዎቜና ዕቃዎቜ ዝቅተኛ ኢነርጂ ብቃት ደሹጃ እና ዚተለጣፊ ምልክት አተገባበርን በተመለኹተ ስልጠና ተሰጠ፡፡ ዚስልጠናው ዓላማ በዋናነት በፌድራል ደሹጃ ዚወጡ ዚኢነርጂ ብቃትና ቁጠባ አሰራር ስርዓት ለመኚታተል ዚሚያስቜሉ ዚቁጥጥር ስራዎቜን በተዋሚድ ለኹተማ አስተዳደር እና ክልሎቜ ለማውሚድ ዚሚያስቜል ዹአቅም ግንባታና ዚግንዛቀ ማስጚበጥ ነው፡፡ ዚኢነርጂ ብቃትና ቁጠባ ለመተግበር ኹሚኹናወኑ ተግባራት መካኚል አንዱ ዚምርቶቜን ኢነርጂ ብቃትና ደሹጃ ማውጣት ኚአኚባቢ ጥበቃ ስራዎቜ ጋር ኹሚኖሹው ግንኙነት ጋር በተያያዘ በተዋሚድ ለሚደሹጉ ዚቁጥጥር ስራዎቜ ውጀታማነት አስተዋዕፆ እንደሚነሚው ይታመናል፡፡

ዚነዳጅ ማኚማቻ ደሹጃ መስፈርትን በሚወስን ሹቂቅ መመሪያ ላይ ኚባለድርሻ አካላት ጋር ወይይት ተደሚገ፡፡ መስኚሚም 08/2016 ዓ.ም (ነ.ኢ.ባ) በአዲስ አበባ ************************
+1
ዚነዳጅ ማኚማቻ ደሹጃ መስፈርትን በሚወስን ሹቂቅ መመሪያ ላይ ኚባለድርሻ አካላት ጋር ወይይት ተደሚገ፡፡ መስኚሚም 08/2016 ዓ.ም (ነ.ኢ.ባ) በአዲስ አበባ *********************************************************************** ለነዳጅ አቅራቢ ኩባንያዎቜ ፀለነዳጅ አዳዮቜ ማህበርፀ እና ኚጉዳዩ ጋር ተያያዥነት ላላቾው አካላት ዚነዳጅ ማኚማቻ/ዮፖ/ ወጥ ዹሆነና ሁሉንም በሚያሰራና ዚሚያስማማ አገራዊ ዹደሹጃ መስፈርት ሹቂቂ መመሪያ ላይ ውይይት ተደሚገ፡፡ ዚነዳጅ ዚነዳጅ አቅርቊትና ሎጂስቲክስ ክትትል ዳይሬክተር ዚሆኑት አቶ ፈቃዱ ሹመት እንደገለፁት ዚአገሪቱ ዚነዳጅ አቅርቊትና ስርጭት፣ ፍትሃዊ ተደራሜ ሆኖ ለሁሉም ዜጋ አገልግሎት ለመስጠት ደሹጃውን ዹጠበቀ ዚነዳጅ ማኚማቻ መኖር እንዳለበት ገልፀዋል፡፡ ለተፈፃሚነቱም ውጥ ዹሆነ አገራዊ ዹደሹጃ አወጥጥ መስፈርት በጣም አሰፈላጊ በመሆኑ ሪቂቅ መመሪያው ዹተዘጋጀ መሆኑን ጠቁመው ዚነዳጅ አቅርቊትና አገልግሎቱን አስተማማኝፀደህንነቱ ዚተጠበቀፀፍትሃዊፀተደራሜ እና ኢኮኖሚያዊ ለማድሚግፀ እንዲሁም ፍቃድ ለመስጠትና ለቁጥጥር ዚሚያስቜል መስፍርት መሆኑን ተናግሚዋል፡፡ በመጚሚሻም ዚነዳጅ ማኚማቻ ዝቅተኛ መስፈርት ውስጥ እንደ ቊታ መሚጣፀአጠቃላይ ዚግንባታው ይዘትና ዚደህንነት መኚላኚያ መሣሪያዎቜን በውስጡ እንደተካተተ በመግለጜ ኚባለድርሻ አካላት ተጫማሪ ግበዓት እንዲሰጡ እና ለመጫሚሻ ጊዜ ለሹቂቅ ደንቡ በማዳበር ዚበኩላ቞ውን ድርሻ እንዲጡ አሳስበዋል፡፡

ዚህንፃዎቜ ኢነርጂ ብቃት ኮድን ለማውጣት ግብሚሀይል ተቋቋመ፡፡ መስኚሚም 08/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ(ነ.ኢ.ባ) ****************************************************
+5
ዚህንፃዎቜ ኢነርጂ ብቃት ኮድን ለማውጣት ግብሚሀይል ተቋቋመ፡፡ መስኚሚም 08/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ(ነ.ኢ.ባ) *********************************************************************** ዚነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ኹGIZ ኢነርጂ ኮኊፕሬሜን ጋር በመተባበር ዚህንጻዎቜ ኢነርጂ ብቃት ኮድን ለማዘጋጀት ዚሚያስቜል ግብሚሃይል ለመቋቋም ኚተለያዩ ዹኹፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ዚሙያ ማህበራትና ዚፌድራል መንግስት መ/ቀቶቜ ዚተውጣጡ አካላት ዚተሳተፉበት ወርክሟፕ ተካሄደ፡፡ በወርክ ሟፑ ላይ ዚተለያዩ ሀገራት ዚህንፃዎቜ ኢነርጂ ብቃት ተሞክሮ እና ጥናቶቜ ቀርበው ውይይት ተደርጎበታል፡፡ ውይይቱን ተኚትሎም ኢነርጂ ብቃት ኮዱን ለማውጣት በሚያስቜሉ ጥናቶቜ ላይ ዚሚሳተፉ ዚባለሙያዎቜ ግብሚሃይል እንዲቋቋም ተደርጓል፡፡

ዚነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ላይ ውይይት አደሚገ። ************ ነሐሮ 25/2015 ዓ.ም ዚባለስልጣን መ/ቀቱ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሠሃሹላ አብዱላሂ በወቅታዊ ሀገራ
+8
ዚነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ላይ ውይይት አደሚገ። ************ ነሐሮ 25/2015 ዓ.ም ዚባለስልጣን መ/ቀቱ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሠሃሹላ አብዱላሂ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ላይ ዚባለሥልጣን መ/ቀቱ ሠራተኞቜን አወያይተዋል። ዋና ዳይሬክተሯ በዉይይቱ ላይ እንዳሳሰቡት እንደ ተቋም ዹተሰጠንን ኃላፊነት መወጣት በህዝብ ላይ ዚመልካም አስተዳደር ቜግር እንዳይፈጠር መስራት ይኖርብናል ሲሉ አሳስበዋል ።

Petroleum and Energy Authority - Statistics & analytics of Telegram channel @eea82