1 110
Subscribers
No data24 hours
-77 days
-1130 days
Posts Archive
ገናናነቷንና እድሜዋን በሚመጥን ደረጃ ከፍታዋን እያረጋገጠች የምትገኘው የታሪክ ሃብታሟ ሀረር ከተማ
የምስራቋ ፈርጥ ሀረር ከተማ የትላንት ከፍታዋን በሚመጥን ደረጃ በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስን ጨምሮ በከተማዋ በተለያዩ አካባቢዎች ውጤታ የኮሪደር ልማት ስራዎች ተከናውነዋል።
የኮሪደር ልማት ስራዎቹም ትላንትን ከዛሬ የሚያስተሳስሩ ነገንም ታሳቢ ያደረጉ ናቸው።
የገናና ስልጣኔ መነሻ የታሪክ ሃብታሟ ሀረር ከተማ በየቀኑ ገናናነቷንና እድሜዋን በሚመጥን ደረጃ ከፍታዋን እያረጋገጠች ትገኛለች።
በከተማው የተሰሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች ሌሎች የቅርስ ከተሞችም ተሞክሮ በሚሆን ደረጃ የቀደምት አባቶችን አሻራ ሳያደበዝዙ ይልቁንም ተጠብቆ እንዲቆይ በሚያስችልና ተጨማሪ ውበት በሚሆን መልኩ እውን ማድረግ ተችሏል።
በአረንጓዴ አሻራ ለተከልናቸው ችግኞች ዘላቂ እንክብካቤ እናደርጋለን-የሐረሪ ክልል ነዋሪዎች
በሐረሪ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ተሳታፊዎች በመርሃግብሩ ከችግኝ ተከላ ባሻገር ለችግኞች ዘላቂ እንክብካቤ ቁርጠኝነታቸውን ገለጹ።
በሀገር አቀፍ ደረጃ በከፍተኛ መነቃቃትና ህዝባዊ ተሳትፎ እየተከናወነ በሚገኘው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ በንቃት እየተሳተፉ የሚገኙት የሐረሪ ክልል ነዋሪዎች፣ ዋናው ትኩረታቸው ችግኝ መትከል ላይ ብቻ ሳይሆን የተተከሉትን በአግባቡ ተንከባክቦ ማሳደግ ላይ ነው።
የዘመቻው ተሳታፊዎች እንዳሉት፥ አረንጓዴ አሻራ የአካባቢን ልምላሜ እንድናይና ነፋሻማ አየር እንድናገኝ አስችሏል።
"ችግኝ ተክሎ አለመንከባከብ ልጅ ወልዶ አለማሳደግ" መሆኑን በመጠቆም የሚተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ስራው እንደሚያጎለብቱ ተናግረዋል።
በክረምት የምናከናውነው የአረንጓዴ አሻራ ልማት ስራ ሐረርን አረንጓዴ በማልበስ ውበቷ እንዲጨምር አድርጓታል ብለዋል።
በአረንጓዴ አሻራ የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ስራን እቅድን መሰረት ባደረገ መልኩ ለማከናወን መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።
በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሚከናወነው የችግኝ ተከላ ከሀገሪቱ ባለፈ ለጎሮቤት ሀገራትም እንድንተርፍ ያስቻለ ነው ብለዋል።
በሐረሪ ክልል የዘንድሮው ክረምት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ትናንት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ በተገኙበት መጀመሩ ይታወቃል።
በአረንጓዴ አሻራ ለተከልናቸው ችግኞች ዘላቂ እንክብካቤ እናደርጋለን-የሐረሪ ክልል ነዋሪዎች
በሐረሪ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ተሳታፊዎች በመርሃግብሩ ከችግኝ ተከላ ባሻገር ለችግኞች ዘላቂ እንክብካቤ ቁርጠኝነታቸውን ገለጹ።
በሀገር አቀፍ ደረጃ በከፍተኛ መነቃቃትና ህዝባዊ ተሳትፎ እየተከናወነ በሚገኘው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ በንቃት እየተሳተፉ የሚገኙት የሐረሪ ክልል ነዋሪዎች፣ ዋናው ትኩረታቸው ችግኝ መትከል ላይ ብቻ ሳይሆን የተተከሉትን በአግባቡ ተንከባክቦ ማሳደግ ላይ ነው።
የዘመቻው ተሳታፊዎች እንዳሉት፥ አረንጓዴ አሻራ የአካባቢን ልምላሜ እንድናይና ነፋሻማ አየር እንድናገኝ አስችሏል።
"ችግኝ ተክሎ አለመንከባከብ ልጅ ወልዶ አለማሳደግ" መሆኑን በመጠቆም የሚተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ስራው እንደሚያጎለብቱ ተናግረዋል።
በክረምት የምናከናውነው የአረንጓዴ አሻራ ልማት ስራ ሐረርን አረንጓዴ በማልበስ ውበቷ እንዲጨምር አድርጓታል ብለዋል።
በአረንጓዴ አሻራ የተተከሉ ችግኞችን የመንከባከብ ስራን እቅድን መሰረት ባደረገ መልኩ ለማከናወን መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።
በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሚከናወነው የችግኝ ተከላ ከሀገሪቱ ባለፈ ለጎሮቤት ሀገራትም እንድንተርፍ ያስቻለ ነው ብለዋል።
በሐረሪ ክልል የዘንድሮው ክረምት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ትናንት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ በተገኙበት መጀመሩ ይታወቃል።
የሆስፒታሉ ማስፋፊያ የክልሉን የሜዲካል ቱሪዝም የሚያጎለብት ነው-ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ
የሀረር ፌደራል ፖሊስ ሆስፒታል ማስፋፊያ ፕሮጀክት የክልሉን የሜዲካል ቱሪዝም ይበልጥ የሚያጎለብት ነው ሲሉ የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ገለፁ።
ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ የሀረር ፌደራል ፖሊስ ሆስፒታል ማስፋፊያ የግንባታና አፈጻጸም ሂደት ተመልክተዋል።
በመስክ ምልከታው ላይም ርዕሰ መስተዳድሩ እንደተገለፀው የሪፈራል ሆስፒታል ግንባታ በታያዘለት የጊዜ ገደብ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ይገኛል።
የሆስፒታሉ ማስፋፍያ ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር የህክምና አገልግሎቱን ወደ ተሻለ ደረጃ የሚያደርስ መሆኑን ነው የተናገሩት።
በክልሉ ለጤና ኮሪደር ልማት እና የጤና አገልግሎት ተደራሽነት ልዩ ትኩረት ተሰቶት ወደ ስራ መገባቱን የጠቆሙት ርዕሰ መስተዳድሩ የሆስፒታሉ ማስፋፊያም በክልሉ በጤና ዘርፍ የሚሰጠውን አገልግሎት ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሳደግ የራሱን አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ገልፀዋል።
በተለይ ሀረር ጎረቤት አገራትን ጨምሮ ከአጎራባች ክልሎች ለህክምና የሚመጡ በርካታ ተገልጋዮች የሚስተናገዱባት የሜዲካል ቱሪዝም ከተማ መሆኗን ጠቅሰው የሆስፒታሉ ማስፋፊያ የሜዲካል ቱሪዝሙን ይበልጥ የሚያጎለብት ነው ብለዋል።
የማስፋፊያ ፕሮጀክቱ ጥሩ በሚባል አፈፃፀም ላይ እንደሚገኝ በማመላከት ፕሮጀክቱ በፍጥነት ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት እንዲችል የክልሉ መንግስት ድጋፍ እንደሚያደርግም ርዕሰ መስተዳድሩ አረጋግጠዋል።
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለነገው ትውልድ አረንጓዴና ምቹ ሀገር ለማውረስ የሚደረግ ጉልህ ስራ ነው -ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለነገው ትውልድ ዘላቂና ምቹ ሀገርን የሚፈጥር ታሪካዊ ተግባር መሆኑን የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ተናገሩ።
በሐረሪ ክልል የዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በሐኪም ጋራ ኢንሼቲቭ ፕሮጀክት ስፍራ ተጀምሯል።
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል፣ የደን ሽፋንን ለማሳደግ እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እየተተገበረ የሚገኝ ታላቅ ሀገራዊ ንቅናቄ ነው።
የሐረሪ ክልልም ይህንን ሀገራዊ ጥሪ በመቀበል በየዓመቱ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ለተለያዩ ጠቀሜታ የሚውሉ ችግኞችን ሲተክል ቆይቷል።
ዛሬ በተጀመረው የዘንድሮው የክልሉ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃግብርም በክልሉ በተለይም በአካባቢ ጥበቃ፣ በከተማ ውበት እና በልማት ስራዎች ላይ ማህበረሰቡን ያሳተፈ ሰፊ ንቅናቄ እየተደረገ ይገኛል።
በማስጀመሪያ መርሃግብሩም የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ፣ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሮዛ ኡመር፣ የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ሱልጣን አብዱሰላም፣ በብልጽግና ፓርቲ የሐረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ጌቱ ወዬሳና ሌሎች አመራሮች ተገኝተዋል።
እንዲሁም በመከላከያ ሰራዊት የምስራቅ እዝ ከፍተኛ መኮንኖች፣ የሴክተር መስሪያ ቤት ሰራተኞች፣ የኃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሸማግሌዎች፣ አርሶ አደሮችና ሌሎችም የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት ርዕሰ መስተዳድሩ ኦርዲን በድሪ እንዳሉት፤ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለነገው ትውልድ ህይወት ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር ነው።
እንዲሁም አንድ ሀገራዊ ዓላማን በትብብር ማሳካት እንደሚቻል ያሳየ ተምሳሌታዊ ተግባር መሆኑንም ተናግረዋል።
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በክልሉ ከተጀመረ ወዲህ በክልሉ የደን ሽፋንን ከማሳደግ ባለፈ የአፈር መሸርሸርን በመከላከል የምግብ ዋስትና እንዲረጋገጥ አስችሏል ብለዋል።
እንዲሁም አካባቢን ወደ ለምነት በመቀየርና ለወጣቶችና ሴቶች የስራ እድል በመፍጠር ተጠቃሚነትን ማጠናከሩን ጠቁመው፤ ዘንድሮም የሚተከሉትን ችግኞች ሁሉም የመንከባከብና የመጠበቅ ስራ ማከናወን ይገባል ብለዋል።
የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ልማት ቢሮ ሃላፊ ወይዘሮ ሮዛ ኡመር በበኩላቸው፤ በክልሉ በዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በዘጠኝ ሺህ ሄክታር መሬት ላይ 1 ነጥብ 7 ሚሊዮን ችግኞች ይተከላሉ።
በዘመቻው በክልሉ ገጠርና ከተማ ከሚተከሉት ችግኞች መካከል 70 በመቶዎቹ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎችን የሚያጠናክሩ የአትክልትና ፍራፍሬ ችግኞች ሲሆኑ፤ ቀሪዎቹ የደንና የእንስሳት መኖ ችግኞች እንደሆኑ አንስተዋል።
እንደ ምክትል ርዕሰ መስተዳድሯ ገለጻ ቀደም ሲል በክልሉ የተተከሉ ችግኞች አርሶ አደሩን ከዝናብ ጠባቂነት በማላቀቅ ምርትና ምርታማነቱን እንዲያሳድግ አስተዋጽኦ አበርክቷል።
በሀረሪ ክልል የቱሪዝም ዘርፉን የሚያጎለብቱ የኢንቨስትመንት ልማት ስራዎች እየተከናወነ ነው - ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ
በሀረሪ ክልል የቱሪዝም ዘርፉን የሚያጎለብቱ የኢንቨስትመንት ልማት ስራዎች እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ተናገሩ
ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ በሀረር ከተማ በመገንባት ላይ ያሉ የተለያዩ ኢንቨስትመንቶችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንዳሉት የክልሉ መንግስት በኢንቨስትመንት አማራጮች ለሚሰማሩ ባለሃብቶች ምቹ ሁኔታዎች መፈጠራቸውን አንስተዋል።
በክልሉ ለኢንቨስትመንት ዘርፍ ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር በተደረገው ጥረትም ለውጥ መምጣቱን ተናግረዋል።
በከተማው በግል ባለሃብቶች እየተገነቡ የሚገኙ ኢንቨስትመንቶችም አበረታች ደረጃ ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል።
የኢንቨስትመንቶቹ የግንባታ ስራዎች በታቀደላቸው የጊዜ ሰሌዳ እየተከናወነ መሆኑ ጠቅሰዋል።
ኢንቨስትመንቶቹም የክልሉን የቱሪዝም ዘርፉን የማጎልበቱና የስራ እድል በመፍጠር ረገድ ጉልህ ፋይዳ እንዳላቸው ገልጸዋል።
በኢንቨስትመንት አማራጮቹ ላይ ተሰማርተው አበረታች ስራ እያከናወኑ ለሚገኙ ባለሃብቶችም የክልሉ መንግስት ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ነው ርዕሰ መስተዳድሩ የገለፁት።
በክልሉ በኢንቨስትመንት ዘርፉ ላይ እየታየ የሚገኘው መነቃቃት የበለጠ ለማጎልበት አስፈላጊውን የክትትል እና ቁጥጥር ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
ባለሃብቱም የጀመሩትን የግንባታ ስራቸውን በፍጥነትና በጥራት አጠናቀው ለአገፈልግሎት ማብቃት እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በጉብኝቱ ላይ የክልሉ ኢንቨስትመንት ቦርድ አባላትና የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
በሐረሪ ክልል የ90 ቀናት ልዩ ልዩ የልማት እና የመልካም አስተዳደር ዕቅድ ወደ ተግባር አስገባ
የሐረሪ ክልል ከመላው የክልሉ አመራሮች ጋር በመሆን የ90 ቀናት የፓርቲ እና የመንግሥት ስራዎች እቅድ ላይ በመወያየት ወደ ተግባር መግባቱን በብልፅግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ አስታወቁ።
ኃላፊው በሰጡት መግለጫ ፥ በድህረ-ምርጫ በፍጥነት ፊትን ወደ ስራ በመመለስ ፈጣን ውጤቶችን ማስመዝገብ፣ ተከታታይና አዳዲስ ስራዎችን መተግበር እንዲሁም ህብረተሰቡ ለሚያነሳቸው ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት በላቀ ትጋትና ያለ እረፍት መፈጸም የሚያስችል ዕቅድ ተዘጋጅቶ በልዩ ትኩረት ወደ ተግባር መገባቱን ገልጸዋል።
የተለዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታት እና አገልግሎትን የማሻሻል ስራን በማጠናከር የ“መሶብ አንድ ማዕከል” ዲጂታል አገልግሎትን ማስፋት ዋነኛ ግቦቹ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ከዚህም በተጨማሪ የኑሮ ውድነትን ማረጋጋት፣ የንግድ ሥርዓቱን መግራት፣ የስራ እድል ፈጠራ እንዲሁም የወጣቶችና ሴቶች ተጠቃሚነት ላይ በትኩረት እንደሚሰራም አብራርተዋል።
በአረንጓዴ ዐሻራ ልማት፣ በቱሪዝም ፣ በግብርና፣ በሌማት ትሩፋት፣ በኮሪደር፣ በሰላም ግንባታ እና በገቢ አሰባሰብ ስራዎች ላይ በስፋት እንደሚረባረብ የገለጹት ኃላፊው፤ ልመናንና ተረጂነትን በመቀነስ የበጎ ፍቃድ መርሃ ግብርን በተቀናጀ የህብረተሰብ ተሳትፎ ለመተግበር መታቀዱን አመላክተዋል።
የተጀመሩ የገጠር ኮሪደር ልማት ስራዎችን በጥራት፣ በተያዘላቸው የጊዜና የበጀት ገደብ ለማጠናከር መዘጋጀቱን አስታውቀዋል።
አያይዘውም የ2018 በጀት ዓመት ማጠቃለያ እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ዝግጅት ላይ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸው፤ "አዲሱ በጀት ዓመት ህዝባችንን ይበልጥ የምናገለግልበት፣ ክልሉን የብልፅግና ተምሳሌት የማድረግ ጉዟችንን የምናረጋግጥበት እንዲሆን ከእቅድ ዝግጅት እስከ ተግባር አፈፃፀም በጠንካራ ክትትልና ድጋፍ የሚፈጸም መሆኑን ገልጸዋል።
በክልሉ በቀጣዮቹ 90 ቀናት የነዋሪውን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላይ በትኩረት ይሰራል
በሐረሪ ክልል በቀጣዮቹ 90 ቀናት የክልሉን ነዋሪዎች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ተግባራት ላይ በትኩረት እንደሚሠራ በብልፅግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ ገለጹ።
በክልሉ በቀጣይ ዘጠና ቀናት ሊከናወኑ በታቀዱ ስራዎች ዙሪያ ውይይት ተካሂዷል።
በውይይት መድረኩ ላይ በብልፅግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ እንዳሉት በመጪዎቹ ሦስት ወራት አመራሩ በተሟላ አግባብ የህዝቡን ኑሮ ማሻሻል በሚያስችሉ ስራዎች ማከናወን ይገባል።
በክልሉ በአሁኑ ወቅት እጅግ በርካታና ዕረፍት የሚነሱ ሥራዎች ያሉበት መሆኑን ጠቅሰው አመራሩ ይህን ሊገነዘብ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
ባለፉት ጊዜያት የተመዘገቡ ስኬቶችን አጠናክሮ ለማስቀጠልና በክልሉ የተጀመሩ የልማትና የሪፎርም ሥራዎችን በላቀ ፍጥነት ለማጠናቀቅ የ90 ቀናት መሪ ዕቅዱ ሚና የጎላ ነው ብለዋል።
ዕቅዱ በዋናነት የሕዝብን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ስትራቴጂካዊ ተግባራት ላይ ትኩረት ማድረጉን ጠቁመዋል።
በገጠር ያልተጠናቀቁ የኮሪደር ልማት ስራዎችን በአፋጣኝ ለ ማጠናቀቅ ይሰራል ብለዋል።
የግብርና ልማት ስራዎችን ማጠናከርና ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ መንቀሳቀስ እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል።
በአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ውጤታማነት፤ የፅዳትና ውበት ስራዎች ማጎልበት፣ ገቢን ማሳደግና የስራ እድል ፈጠራ የበለጠ ለማጎልበት ይሰራል ብለዋል።
የኑሮ ውድነት ጫናን ለማቃለል አላስፈላጊ ዋጋ የሚጨምሩ ነጋዴዎች ላይ የክትትል እና ቁጥጥር ስራዎች ይሰራሉ ብለዋል።
የአምስት ሚሊየን ኮደርስ ስልጠና እና የፋይዳ መታወቂያ አንዱ የርብርብ ማዕከል መሆኑን በማንሳት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤታማ ለማድረግ በትኩረት ይሰራል።
ልመናንና ተረጂነትን በመቀነስ የበጎ ፍቃድ መርሃ ግብርን በተቀናጀ የህብረተሰብ ተሳትፎ ለመተግበር መታቀዱን አመላክተዋል።
በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት አቅመ ደካማ ወገኖችን የመደገፍ ስራ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።
ከዚህ ቀደም በማህበረሰቡ ዘንድ የተነሱ ቅሬታዎችን ለመቅረፍ መንቀሳቀስ እንደ አንድ ቁልፍ ስራ ይሰራል ሲሉ ተናግረዋል።
የታቀዱ ግቦችን ለማሳካት በየደረጃው የሚገኘው አመራር በቁርጠኝነትና በከፍተኛ የኃላፊነት ስሜት መሥራት እንደሚገባውም አጽንኦት ሰጥተዋል።
በመድረኩ ላይም የመንግሥትና የፓርቲ ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
