1 118
Subscribers
-224 hours
-17 days
+430 days
Posts Archive
ደም በመለገስ የዜጎችን ህይወት የማዳን ተግባርን ተጠናክሮ ይቀጥላል አቶ ጌቱ ወዬሳ
ደም በመለገስ የዜጎችን ህይወት የማዳን ተግባርን ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በብልጽግና ፓርቲ የሐረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ
“የማንሰራራት ቀንን” ምክንያት በማድረግ በክልሉ የደም ልገሳ መርሃ-ግብር ተከናውኗል።
በመርሀ ግብሩም የክልሉ ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ሱልጣን አብዱሰላም፣በብልጽግና ፓርቲ የሐረሪ ክልል ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ጌቱ ወየሳ፣ በክልሉ የብልጽግና ፓርቲ የወጣቶችና ሴቶች ክንፍ አባላት፣ በተለያዩ አደረጃጀት የሚገኙ ማህበራትና የማህብረሰብ ክፍሎች ደም በመለገስ ተሳትፈዋል።
በመርሐ-ግብሩ ላይ የተገኙት በብልጽግና ፓርቲ የሐረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ ደም በመለገስ አርአያነታቸውን ያሳዩ ሲሆን በክልሉ በርካታ የልማትና የበጎ ፈቃድ ሥራዎች እየተከናወኑ ስለመሆኑ ገልጸዋል።
የጳጉሜን ቀናትም ለአዲሱ ዓመት አዲስ መነሳሳትን የሚያፈጥሩና የነገዋን ኢትዮጵያ ተስፋ የሚያለምልሙ በጎ ተግባራት የሚከናወኑባቸው ቀናት መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ደም መለገስ የዜጎችን ህይወት ማዳን በመሆኑ ይህ በጎ ተግባር በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ አቶ ጌቱ ተናግረዋል።
የፓርቲው የወጣቶችና ሴቶች ክንፍ አባላት የተለያዩ የወጣቶችና ሴቶ ማህበራት አባላትና ሌሎች ማህበረሰብ በደም እጦት ምክንያት የሚደርሰውን ችግርና አሳሳቢነት በመረዳት በተለያዩ ጊዜያት የደም ልገሳ በማድረግ አስተዋጽዖ እያበረከቱ ይገኛሉ ያሉት የሐረሪ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት የሴቶች ከንፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ዚነት ዩስፍ ናቸው።
በመሆኑም በዛሬው እለትም “የማንሰራራት ቀን” ምክንያት በማድረግ የደም ልገሳ መርሃ-ግብር ማካሄዳቸውን ተናግረዋል።
በመርሃ ግብሩ የተሳተፉት የተለያዩ አካላት በሰጡት አስተያየት የእናቶችና ህፃናትን ሕይወት ለመታደግ ደም መለገስ አስተዋጽዖ ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰዋል።
እንዲሁም ደም መለገስ ለጤናማ ሰው ምንም አይነት ጉዳት እንደሌለውና የሌሎችን ሕይወት በማትረፍ ውስጣዊ እርካታ የሚያስገኝ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
“በሰብዓዊነት የሚደረገው ደም ልገሳ” በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎች ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች የሚሰጠውን ምላሽ የሚያግዝ በመሆኑ በየ 3 ወራቱ ደም እንለግሳለን ብለዋል።
የሰዎችን ሕይወት ለመታደግ ሁሉም የደም ልገሳን ባህል ማድረግ ይገባል ሲሉም አክለዋል።
ኢትዮጵያ የብልጽግና ትልሞቿን በፅኑ መሠረት እየገነባች ነው-የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
ኢትዮጵያ የብልጽግና ትልሞቿን በፅኑ መሠረት እየገነባች መሆኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ።
አገልግሎቱ ለጳጉሜን 2 የማንሰራራት ቀን በማስመልከት ባስተላለፈው መልዕክት፣ ኢትዮጵያ በመደመር መንግሥት ፖሊሲዎች እና ዕቅዶች እየተመራች ለሁለንተናዊ ብልጽግና እየተጋች ትገኛለች ብሏል፡፡
በየዘመን አንጓው ያጋጠሟትን ፈተናዎች በተደመረ አቅም እየተሻገረች፤ ከችግሮች እና ፈተናዎች ዕድሎችን መንጭቃ እያወጣች፤ ነገዋን በጠንካራ መሠረት ላይ እያጸናች መሆኑንም ጠቁሟል፡፡
ለዘመናት የኢትዮጵያን ሰንደቅ ከአድማስ እስከ አድማስ የሚያውለበልበው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ነገን ታሳቢ አድርጎ እንደ ቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ባሉ መሠረተ ልማቶች እና ሁለንተናዊ ለውጦች ውስጥ እያለፈ ነው፡፡
ነባር እና አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻዎች እየለሙ እና ተደራሽነታቸው እያደገ ነው፡፡ ግብርናችን ከዝናብ ጥገኝነት እየተላቀቀ እና የገጠሩም የከተሜውም የሥራ ዕድል እየሆነ ነው፡፡
የታዳሽ ኃይል አማራጮቻችን ከውኃ፣ ከነፋስ፣ ከፀሐይ፣ ከጂኦተርማል እና ከኑክሊየር ኃይል እንዲሆኑ የመደመር መንግሥት ሌት ተቀን እየሠራ ነው፡፡
ከተሞቿ ጎስቋላ ገጽታቸው እየተቀየረ እና ነገን እየዋጁ፤ መሠረተ ልማቶቿ እየተስፋፉ እና እየተቀናጁ፤ የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ አቅሟ እየተጠናከረ፤ የቀጣናው የታዳሽ ኃይል ማዕከልነቷ እያደገ፤ የማዕድን ሀብቶቿን በላቀ ደረጃ ጥቅም ላይ እያዋለች ለመጪው ትውልድ ሁለንተናዊ ብልጽግና እየሠራች ነው፡፡
የኢትዮጵያን ማንሰራራት የሚያበስሩ፤ እመርታዊ ዕድገቷን የሚያፋጥኑ ፅኑ መሠረቶች እየተገነቡ ነው፡፡ ኢትዮጵያውያንም ሥርዓቱን ለማጽናት እና መሻታቸውን እውን ለማድረግ ያላቸውን ቁርጠኝነት በመንግሥት ጥሪዎች በሚያሳዩዋቸው ተሳትፎዎች እየገለጹ ነው፡፡
የልማት ኃይላችንን ይበልጥ በማፋጠን የኢትዮጵያን ትንሣኤ ወደ ዘላቂ ብልጽግና ከፍ እናደርጋለን - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
በጀመርነው ታሪካዊ የማንሠራራት ጉዞ የልማት ኃይላችንን ይበልጥ በማፋጠን የኢትዮጵያን ትንሣኤ ወደ ዘላቂ ብልጽግና ከፍ እናደርጋለን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የማንሠራራት ቀንን አስመልክቶ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ቀደም ሲል “ኢትዮጵያ ተነሥታለች” ሲባል የነበረው ምኞት ሳይሆን ዛሬ በተጨባጭ የተረጋገጠ እውነት መሆኑን ተናግረዋል።
ከታላቁ ሕዳሴ ግድብ ማማ እስከ ዘመናዊው የኮሪደር ልማት፣ ከቢሾፍቱ ሜጋ አውሮፕላን ማረፊያ እስከ ማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ድረስ ሀገራዊ መነቃቃታችን በተግባር ተመስክሯል ብለዋል።
ይህ ለውጥ በዜጎቻችን የኑሮ ደረጃ፣ በከተሞች መዘመንና የሥራ ዕድል ላይ እውነተኛ ብርሃን ከመሆኑም በላይ ለልጆቻችን የነገ ብሩህ ተስፋን የሚሰንቅ ታላቅ ርዕይ ነው ሲሉም ገልጸዋል።
ከእንግዲህ ወደኋላ አንመለስም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጀመርነው ታሪካዊ የማንሠራራት ጉዞ የልማት ኃይላችንን ይበልጥ በማፋጠን የኢትዮጵያን ትንሣኤ ወደ ዘላቂ ብልጽግና ከፍ እናደርጋለን ብለዋል።
በርካቶችን የሙያ ባለቤት ያደረገው የሀረር ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ... በቅርብ ቀን
በሀረሪ ክልል በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ያሠለጠናቸውን የሕግ ታራሚዎችና አባላት ተመረቁ
የሀረሪ ክልል ማረሚያ ኮሚሽንና የምሥራቅ ሐረርጌ ዞን ማረሚያ ፖሊስ ከሀረር ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በመተባበር፣ ለመጀመሪያ ጊዜ ያሠለጠናቸውን 108 የሕግ ታራሚዎችና አባላቱን በተለያዩ የሙያ ዘርፎች አስመረቋል።
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የሐረሪ ክልል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ቢሮ ኃላፊ አቶ አዩብ አሕመድ፤ ተመራቂዎች ያገኟቸውን ሙያዎች በመጠቀም በማረሚያ ቤት ቆይታቸው ተቋሙን እንዲያገለግሉ፣ ከማረሚያ ቤት ሲወጡም ራሳቸውንና ማኅበረሰባቸውን እንዲክሱ አሳስበዋል።
ኃላፊው አክለውም የሐረሪ ክልልና የምሥራቅ ሐረርጌ ዞን የአስተዳደር ወሰን ሳይለያያቸው ሁሉንም ታራሚዎች እኩል በማሠልጠን የሙያ ባለቤት ማድረጋቸው፣ ትክክለኛው ታራሚዎችን የማነጽና የማረም ሥርዓት እየተተገበረ መሆኑን ያሳያል ብለዋል።
የሐረሪ ክልል ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አድናን አሕመድ በበኩላቸው፤ ማረሚያ ቤት ማረብ ብቻ ሳይሆን ታራሚዎች ክህሎት ጨብጠው የሚወጡበት ቦታ ሆኗል ብለዋል።
ኮሚሽነሩ አክለውም በዕለቱ ከሰለጠኑት 108 ተመራቂዎች መካከል 14ቱ ሴቶች መሆናቸውን ጠቅሰው፤ በሕይወት ዘመናቸው የሚጠቅሟቸውን በእንጨትና ብረታብረት፣ በልብስ ስፌት፣ በስነ ውበት እንዲሁም በኮንስትራክሽን ሥራዎች ሙያዊ ሥልጠና ማጠናቀቃቸውን አብራርተዋል።
ከዚህ በተጨማሪም 229 ታራሚዎች መደበኛ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ይገኛሉ ብለዋል።
የዕለቱ ተመራቂዎች በበኩላቸው ባገኙት ሙያዎች ተቋሙን ለማገልገል እና ወደ ማኅበረሰቡ ተቀላቀሉም አምራች ዜጋ ለመሆን ትልቅ እድል የሚፈጥር መሆኑን ተናግረዋል።
የሀረሪ ክልል የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ት ቤት እና የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ሰነድ እና የውል ሥምምነት ተፈራረሙ
የሀረሪ ክልል የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ት ቤት እና የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ሰነድ እና የውል ሥምምነት ተፈራርመዋል።
ተቋማቱ ሁሉን አቀፍ የሙያ እና የፋይናንስ አቅሞች፤ የሚዲያ፣ የስቱዲዮ እና የቴክኖሎጂ ድጋፍ እና ልውውጥ እንዲሁም ለተሻለ ሀገራዊ ዕድገት መጎልበት በጋራ እንደሚሠሩ በስምምነቱ ተቀምጧል፡፡
የሚጠበቁበትን ፈጣን መረጃዎች በማቅረብ በኩል ተባባሪ በመኾን በአሚኮ ድረ-ገጽ እና ማኅበራዊ ገጾች ላይ እንዲታተሙ እና ሌሎች ተግባራትን እንደሚወጣም በስምምነቱ ተቀምጧል።
በዚህ ወቅትም የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አሥፈጻሚ ጋዜጠኛ ሙሉቀን ሰጥዬ አሚኮ ከሀረሪ ክልል መንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ጋር በሁሉም የሚዲያ አማራጮቹ እና በሁሉም ቋንቋዎች በጋራ ሢሠራ ቆይቷል ብለዋል።
የሀረሪ ክልል የሥራ ኀላፊዎች የመረጃ ምንጭ እና የአሚኮ ቤተሰብ በመኾን አብራችሁን ስለሠራችሁ ልዩ ክብር አለን ብለዋል።
አሚኮ ባለቤቱ የአማራ ሕዝብ ቢኾንም ሁሉንም ኢትዮጵያዊ የሚያገለግል የሚዲያ ተቋም መኾኑን በሀረሪ ክልል በመገኘት እና በማገልገል አስመስክሯልም ነው ያሉት።
ስምምነቱ በሚዲያ እና በኮሙዩኒኬሽን ሥራ እንደ ቤተሰብ በጋራ ሥንሠራ የነበረውን የምናጠናክርበት ነው ብለዋል። በሁሉም ቋንቋዎች ከዚህ በፊት ሥንሠራቸው የነበሩ ሥራዎችን በማጠናከር የሀረሪን ገጽታ፤ የቱሪዝም መዳረሻነት፤ አብሮነት እና ጥንታዊነት ለሁሉም የምናሳውቅበት ሥምምነት ነው ብለዋል።
አዲስ ሥራ ለመጀመር ሳይኾን የጀመርናቸውን ሥራዎች ለማጠናከር እና ውጤታማ ለማድረግ ተፈራርመናል ነው ያሉት።
የሀረሪ ክልል የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ሔኖክ ሙሉነህ "ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን" በሚል ድርጅታዊ መርህ የሚታወቀው አሚኮ ለዓመታት በሚዲያ እና ኮሙዩኒኬሽን ታሪክ ውስጥ የራሱን አስተዋጽኦ አስቀምጧል ብለዋል።
ለሀገር ገጽታ ግንባታ ግንባር ቀደም ኾኖ የሚሠራ ጠንካራ ተቋም መኾኑንም ገልጸዋል። አሚኮ በሀረሪ ክልል የሚከናወኑ የልማት ሥራዎችን፤ የአብሮነት እና የመቻቻል እሴቶችን፤ የቱሪዝም ሀብቶችን፤ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተግባራትን ለሀገር ውስጥ እና ለውጭ ሀገራት እንዲደርስ በብዙ ቋንቋ የሚዲያ ሽፋን እንደሚሰጥ ተናግረዋል።
በአሚኮ የዘገባ ሽፋን የሀረሪ ክልል ሕዝብ ደስተኛ ነው ብለዋል። የክልሉ መንግሥት በቀጣይ በይበልጥ ከአሚኮ ጋር ለመሥራት ስምምነት መፈራረሙንም ገልጸዋል። በቀጣይ ሚዲያውን ለመደገፍ የሀረሪ ክልል በትኩረት ይሠራልም ብለዋል።
አሚኮ አሠባሣቢ እና ገዥ ትርክት ላይ በትኩረት የሚሠራ፤ ብሔር ብሔረሰቦችን አቅፎ የያዘ እና በሁሉም ቋንቋ በመሥራት ቀዳሚ የኾነ ሚዲያ መኾኑንም አንስተዋል።
አሚኮ ከሀገር ባለፈ በአፍሪካ እና በዓለም ተጽዕኖ ፈጣሪ ሚዲያ ለመኾን የሚያደርገው ጉዞ ሩቅ አይደለምም ብለዋል።
የተቋማት ኀላፊዎቹ የአሚኮን ተቋም የጎበኙ ሲኾን በግቢ ውስጥ የአረንጓዴ አሻራቸውን አስቀምጠዋል።
የሀረሪ ክልል የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሔኖክ ሙሉነህ ባህርዳር ገቡ
የሀረሪ ክልል የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሔኖክ ሙሉነህ ባህርዳር ከተማ ገብተዋል።
ኃላፊው ባህር ዳር ደጅአዝማች በላይ ዘለቀ አለም አቀፍ ኤርፖርት ሲደርሱ በአማራ ክልል የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ኃላፊ አቶ አባይ መንግስቴ እና በአሚኮ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሙሉቀን ሰጠኝ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
አቶ ሔኖክ ባህርዳር የገቡት ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ለመፈራረም ነው።
የሀረሪ ክልል የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሔኖክ ሙሉነህ ባህርዳር ገቡ
****
የሀረሪ ክልል የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሔኖክ ሙሉነህ ባህርዳር ከተማ ገብተዋል።
ኃላፊው ባህር ዳር ደጅአዝማች በላይ ዘለቀ አለም አቀፍ ኤርፖርት ሲደርሱ በአማራ ክልል የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ኃላፊ አቶ አባይ መንግስቴ እና በአሚኮ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሙሉቀን ሰጠኝ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
አቶ ሔኖክ ባህርዳር የገቡት ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ለመፈራረም ነው።
29/12/2018
በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት የመደጋገፍ እሴት በማጎልበት የዜጎችን ህይወት በላቀ ደረጃ እየቀየረ ይገኛል :- አቶ ጌቱ ዋዬሳ
በሐረሪ ክልል በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት የመደጋገፍ እሴት በማጎልበት የዜጎችን ህይወት በላቀ ደረጃ እየቀየረ ይገኛል ሲሉ በብልጽግና ፓርቲ የሐረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ጌቱ ዋዬሳ አመለከቱ።
በሀረሪ ከልል በክረምት በጎ ፍቃድ እየተከናወኑ በሚገኙ ተግባራት ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።
በመድረኩ የተገኙት በብልፅግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ እንደገለፁት በክልሉ በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት አብሮነትና መደጋገፍ እሴት በመጎልበት የዜጎችን ህይወት በላቀ ደረጃ እየቀየረ ይገኛል ።
የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በተደመረ አቅም ዜጎችን በማገዝና ሃብትን አቀናጅቶ በመምራት ረገድ የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል ብለዋል።
በተለይም በክረምቱ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በርካታ አቅመ ደካሞችንና አረጋዊያንን ተጠቃሚ ያደረጉ በርካታ ስራዎች እውን ማድረግ መቻሉን አንስተዋል።
በዘንድሮ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎትም የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያጎለብቱ 14 ተግባራት በተጠናከረ መልኩ እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል።
በአሁኑ ወቅት የአረጋውያንና አቅመ ደካሞች መኖሪያ ቤት እድሳትና መልሶ ግንባታ፣ የአካባቢ ንጽህና ጥበቃ፣ ችግኝ ተከላ፣ ደም ልገሳ፣ የማጠናከሪያ ትምህርት የመስጠትና ሌሎች ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል
ከዚህ በተጨማሪም ማዕድ ማጋራት፣ አዳዲስና ነባር የመማሪያ ክፍል ግንባታ እና እድሳት ፣ የትምህርት ቤቶች የተማሪ ወንበሮች ጥገና፣ ጽዳትና ውበት ስራዎችን ጨምሮ የማጣቃሻ መጽሀፍት የማሰባሰብ ስራ በበጎ ፍቃድ አገልግሎቱ የትኩረት የተሰጣቸው ጉዳዮች መሆናቸውን ገልጸዋል።
የበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ መደጋገፍ፣ የመተጋገዝና አብሮነትን ይበልጥ የሚያጠናክር መሆኑን ጠቁመው የዜጎችን እውቀት፣ ገንዘብ፣ ጉልበት እና ሌሎች ምቹ ሁኔታዎችን በሚገባ መጠቀምና ከድህነት መላቀቅ እንደሚያስፈልግ ነው የጠቆሙት።
ይህ የመተጋገዝና የአብሮነት ባህል ድህነትን ለማሸነፍ ትልቅ አቅም የሚፈጥር በመሆኑ፣ አመራሩ የታቀዱትን ግቦች ወደ ሙሉ ተግባር ለመቀየር እያከናወነ የሚገኘውን ተግባራት ማጠናከር እንዳለበት አቶ ጌቱ አሳስበዋል።
እንዲሁም በክልሉ አምስቱ የጳጉሜ ቀናት የሚከናወኑ መርሃ-ግብሮች የተሳኩ እንዲሆኑ ሁሉም የመንግስት ተቋማት፣ በየደረጃ የሚገኝ አመራር፣ የመንግስት ሠራተኞችና መላው ሕዝቡ የሚጠበቅበትን ድርሻ እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
