1 209
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ቀን 19/8/2015 ዓ.ም
"የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ መልቀቂያ ፈተና ሃምሌ ወር ላይ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ይሰጣል" ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ከዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንቶችና ከክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎችጋር ውይይት አካሂዷል፡፡
በውይይቱም የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የ2015 የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ መልቀቂያ ፈተና ሃምሌ ወር ላይ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እንደሚካሄድ ገልጸዋል፡፡
ፈተናው ልክ እንደባለፈው ዓመት በኹለት ዙር የሚሰጥ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በመጀመሪያው ዙር የነበሩ የፈተና ችግሮችን ዘርዝረው ለቀጣዩ የመፍትሄ አቅጣጫ ማስቀመጥና ቅድመ ዝግጅት ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን በአጽንኦት አሳስበዋል፡፡
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) በበኩላቸው የ2015 ዓ.ም ፈተናን ለማስፈፀም ልዩ ልዩ መመሪያዎች እየተዘጋጁ መሆኑንና የተፈታኞች መረጃ በአግባቡ እየተደራጀ መሆኑን አብራርተዋል።
ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) የህብረተሰቡን ችግር ለመቅረፍና አመለካከቱን ለመቀየር፣ ብቁና አገር ተረካቢ ትዉልድ ለመፍጠር አሁን ያለው ባለድርሻ አካል ሚናውን ሊወጣ ይገባል ሲሉ በአንክሮ ተናግረዋል፡፡
በመጨረሻም በ2016 የሚካሄደው ፈተና እንደአካባቢው ሁኔታ ኦን ላይን እንደሚሆን ገልጸዋል፡፡
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!
You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ...
TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc
Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication
Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/
Website: - aaceb.gov.et
Email;- aacaebc@gmail.com
Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/
ለክፍለ ከተማ ፈተና ክፍል
የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ተፈታኞች የምዝገባ ግዜ ሰሌዳ እየተጠናቀቀ ስለሆነ በኘሮግራሙ መሰረት የዶክመንት ምርመራና ማጣራት ስራ ከተከናወነ ቡኋላ ለአገልግሎት መስሪያቤታችን የስራ ክፍሉ በሚያዘጋጀው የርክክብ ፎርምና መተማመኛ መሰረት የምታስረክቧቸውን ሰነዶች ለማስታወስ ያክል :-
1ኛ. በተላከው ፎርማት መሰረት በሁሉም የትምህርት ኘሮግራም በት/ቤቶች ር/መምህራን ና በሚመለከታቸው አካላት የተረጋገጠ የተመሪዎች ስኩል ሊስት(ሮስተር) በተላከው ፎርማት መሰረት
2ኛ. በዶክመንት ምርመራና ማጣራት ወቅት ውድቅ የተደረጉ ተማሪዎች ዝርዝር በተላከው ሪጀክት ፎርም መሰረት
3ኛ. የዶክመንት ምርመራና ማጣራት ስራ የተከናወነበት አጭርና ገላጭ ሪፖርት
4ኛ. የአይነ ስውራን ተፈታኞች እና ልዩ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው(መፃፍ የማይችሉ) ተፈተኞች ዝርዝር በተላከው ፎርማት መሰረት
5ኛ. የተጠቃለለ የተማሪዎች የቁጥር ዳታ(ሰብጀክት ስታት) በፎርማቱ መሰረት
6ኛ. የመከላከያ ተፈታኞች ስኩል ሊስት ዝርዝር ከነ ዶክመንታቸው(የዶክመንት ምርመራው በአገልግሎት መስሪያቤቱ በማዕከል ስለሚካሄድ)
7ኛ. ልዩ ልዩ የሂሳብ ማዎራረጃና ማጠቃለያ ሰነዶች (በፋይናንስ ስራ አስፈፃሚ በኩል የሚፈተሹና የሚረጋገጡ) ሲሆን በአጠቃላይ ከላይ በዝርዝር የተጠቀሱት ሰነዶቸች ርክክብ ተደርገዉ በሰነድነት የሚያዙት ፎርማቱን ጠብቀው በአግባቡ መረጃዎቹ በትክክል መሞላታቸው፣ በበይነ መረብ የተመዘገቡት በየኘሮግራሙ (መደበኛ፣የማታ፣የግል፣የርቀትና የመከላከያ ተፈታኞች ) በሰነድ ከመጣው ጋር ተገናዝቦ በእያንዳንዱ ገፅ ላይ የሚመለከተው አካል ፊርማና ማህተም መኖሩ በስራ ክፍሉ ተረካቢ ባለሙያዎች ሲረጋገጥ በመሆኑ ከአሁኑ አስባችሁበት እናንተም ከት/ቤት ስትረካከቡ ሁሉንም መረጃዎች ማረጋገጥ የሚያስፈልግ መሆኑን አስቀድመን ማሳወቅ እንወዳለን ።
መረጃ ሀብትም ህይወትም ነዉ !!! ማረካከቢያው ለትምህርት ቢሮ እና ለፈተናዎች አገልግሎት ገቢ ይደረግ
