1 209
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
እንዴት ዋላቹሁ ነገ ማለትም በ21/11/2015 የሶሻል ተማሪዎች ለማሲወጣት ከ8 ሰዓት ጀምሮ መኪና ቦታ መያዝ የምትችሉ መሆኑን እየገለፁን በ23/11/2015 ጥዋት 12:30 ላይ የናቹራል ተማሪዎች ይዛቹ በየጣቢያቹ እንዲትገኙ እናሳስባለን።
ጤና ይስጥልኝ
መውለጃ ወራቸው የደረሰ ነፍሰ ጡር እና ጡት የሚያጠቡ ተፈታኞች በሚቀጥለው ዓመት ተዘጋጅተው እንደ መደበኛ ተፈታኝ እንዲፈተኑ እንመክራለን።
ሆኖም ለመፈተን የወሰኑ ሲኖሩ ጡት የሚያጠቡት ተፈታኞች አንድ በግልጽ የሚትታወቅ ሴት ሞግዚት ይዘው በመግባት እንዲፈተኑ ተገቢው ድጋፍ የሚደረግላቸው መሆኑን እናሳውቃለን።
የተፈታኞች መብትና ግዴታ እንዲሁም የተከለከሉ ነገሮች ተግባራዊ ይሆናሉ።
ከአክብሮት ጋር
ማሰተካከያ
ሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ዩንቨርሲቲ መጊብያ እሁድ ማለት በ16/11/15 ሲሆን ፈታአወራሪ ጣብያ እና ሰዲል ጣብያ ሰር የምገኙ በ17/11/15 መሆኑን እያሳወቅን ሰአቱን ነገ የምናሳውቅ ይሆናል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2015ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ኦረንቴሽን በቀን 6/11/2015ዓ.ም አጠቃላይ ኦረንቴሽን ስለምንሰጥ 12ኛ ፎቅ 7፡30
የስርዓተ ትምህርት ቡድኖች አስተባባሪ 1 እና የፈተና ባለሙያ 1
የግል እና የመንግስት አስፈታኝ ት/ቤቶች ዋና ር/መ/ራን በጥሪው መሰረት በተጠቀሰው ስዓት እና ቦታ እንዲገኙ እናሳስባለን፡፡
ለሁሉም ክፍለ ከተማ ትምህርት ፅ/ቤት
የመጨረሻ
የ2015ዓ.ም የ12ኛ ክፍል የመፈተኛ ጣቢያ(ዩኒቨርስቲ ) የትምህርት ምዘናና ፈተና አስተዳዳር ምደባ አከናውኖ የመጨረሻ ስላሳወቅን አስፈታኝ ትምህርት ቤቶች የተመደቡበት በተላከው መሰረት እንድታሳውቁ እናሳስባለን፡፡
እንዴት ዋላችሁ!
ከት/ቢሮ የተላለፈው
1. በየፈተና ጣቢያው የፍተሻ ስራ የሚከናወነው በፖሊስ አባላት ብቻ ነው የደንብ ማስከበር አባላት በዚህ ስራ አይሳተፉም።
2. ምገባ በተመለከተ አንዳንድ የግል ት/ቤቶች ላይ በራሳቸው ምክንያት መመገብ የማይፈልጉ ካሉ ወላጅ ወይም ት/ቤቶቹ ኃላፊነት ወስደው ተመግበው ሲጨርሱ እንዲገቡ ከጸጥታ ኃይሉ ጋር መግባባት የፈጠርን በመሆኑ እንዲስተናገዱ።
3.የመረጃ ልውውጣችን በተመለከተ ነገ ጠዋት ከፖሊስ መመሪያ ወደ ሁሉም የፈተና ጣቢያዎች ፈተናዎች መድረሳቸውን ከ12:00-12:10 ድረስ የማሳወቅ፣ ፈተና ስለመጀመሩ ከ3:00-3:10 ድረስ የማሳወቅ እና የሴሽኑ ፈተና በሰላም ስለመጠናቀቁ ከ5:00-5:10 ድረስ የማሳወቅ ስራ ይከናወናል።
4. የየዕለቱ ሪፖርት በየክ/ከተማ የተመደቡ ሪፖርት ጠማሪዎች መሠረት ተጠምሮ ለቢሮ ሪፖርት ጠማሪዎች በሰዓቱ ያቀርባሉ።
5.የተለዩ ግኝቶች ካሉ በማንኛውም ሰዓት የመረጃ ልውውጥ ማድረግ።
ማሳሰቢያ፦
የመረጃ ልውውጡ ፈጣን እንዲሆን ጉሩፑን ቶሎ ቶሎ መመልከት።
መልካም ምሽት!!
በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት ስር ያሉ የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ተፈታኞችን መረጃ ከዚህ ላይ ማየት ትችላላችሁ::
