en
Feedback
ግጻዌ

ግጻዌ

Open in Telegram

የየዕለቱን ምስባክ፣መልእክታት፣ቅዳሴ ያገኙበታል፡፡ አስተያየት ጥያቄ ካለዎት፦ @gisaweBot

Show more
742
Subscribers
No data24 hours
+17 days
-330 days
Posts Archive
+ ትሞታለህና ቤትህን አስተካክል + ንጉሥ ሕዝቅያስ በጠና ታምሞ ተኝቶአል::  ነቢዩ ኢሳይያስ ሊጠይቀው መጣ:: ሆኖም እንደ ልማዱ እግዚአብሔር ይማርህ አላለውም:: ለጆሮ የሚከብድ  ቃል ጥሎበት ወጣ:: "ትሞታለህና ቤትህን አስተካክል!" ነቢዩ ይህንን ብሎት ከወጣ በኁላ ሕዝቅያስ ወደ ግድግዳው ዞሮ ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ:: አምላኩ በንግግር ብዛት የሚሰማ አምላክ አይደለምና ፊቱን ወደ መቅደሱ አቅጣጫ አዙሮ አለቀሰ::  ከጥቂት ደቂቃ በኁዋላ ነቢዩ ኢሳይያስ ሌላ መልእክት ይዞ ተመለሰ:: እግዚአብሔር እንዲህ ይላል :- ጸሎትህን ሰምቻለሁ ዕንባህን አይቻለሁ በዕድሜህ ላይ ዐሥራ አምስት ዓመት እጨምራለሁ" (ኢሳ 38:5) ሕዝቅያስ ቤትህን አስተካክል ከተባለ በኁዋላ ፊቱን አዙሮ ከማልቀስ በቀር ምንም አላደረገም:: ሕዝቅያስ ሆይ ከአልጋህ ሳትወርድ ያስተካከልከው ቤት ምን ዓይነት ቤት ነው? ለባሪያዎችህ መመሪያ ሳትሠጥ የምታስተካክለው ቤትስ እንዴት ያለ ነው? በደቂቃዎች ውስጥ ትሞታለህ ከተባልክ በኁዋላ ዐሥራ አምስት ዓመት ያስጨመረልህ ምን ዓይነት ማስተካከያ አድርገህ ነው? ለእኛም ንገረንና ዕድሜ እናስጨምር:: ሕዝቅያስ ከአልጋው ሳይነሣ ያስተካከለው ቤቱ ልቡ ነበር:: ልብህን ካስተካከልህ ቤትህ ይስተካከላል:: እግዚአብሔር እንደሆን ትሞታለህ ቢልህም መሞትህን አይፈልግም:: እርሱ ከኃጢአትህ እንጂ ካንተ ጋር ጸብ የለውም:: "በውኑ ኃጢአተኛ ይሞት ዘንድ እፈቅዳለሁን? ይላል ጌታ እግዚአብሔር፤ ከመንገዱስ ይመለስና በሕይወት ይኖር ዘንድ አይደለምን?" ይላል መሐሪው (ሕዝ 18:23) እርሱ ትሞታለህ የሚልህ መኖርህን ፈልጎ ነው:: አንዴ ብያለሁ ብሎ አይጨክንብህም:: በንስሓ ተመለስ እንጂ ምሬሃለሁ ለማለት ይቸኩላል:: አሁን ትሞታለህ ብዬው አሁን ትድናለህ ብለው ይንቀኛል ሳይል ተመልሶ ይምርሃል:: ኃጢአትህንም ወደ ጥልቁ ይጥለዋል:: በጎ እንድትሠራም ዕድሜ ይጨምርልሃል:: አንተ ብቻ ተመለስና አሁኑኑ ንስሓ ግባ:: ከበደል አልጋ ጋር ያጣበቀህን ፈተናም ድል መንሻው ጊዜ አሁን ነው:: ሕዝቅያስ በደቂቃ ዕንባ ምሕረት አግኝቶ ዕድሜ ካስጨመረ በዐቢይ ጾም ሙሉ የሚያለቅስ ምን ያህል ዕድሜ ያገኝ ይሆን? ወዳጄ አንተም ተነሣና በዚህ ወር ቤትህን አስተካክል:: እንደ ሕዝቅያስ ፈጣሪህ ይጠብቅሃል:: የተቀየምከውን ይቅር በል  የበደልከውን ካስ የሚበቀልህን የማይተኛ ጠላትህን ዲያቢሎስ ተበቀለው:: የዐቢይ ጾም የወንጌል ምንባብ ስለ ዲያቢሎስ ፈተና ሦስቱ ወንጌላት የተናገሩትን ስናስተውል ሦስት ዓይነት ጥቅሶች እናገኛለን:: አርባ ቀን ከዲያብሎስ ተፈተነ። (ሉቃ 4:2) በምድረ በዳም ከሰይጣን እየተፈተነ አርባ ቀን ሰነበተ (ማር 1:13) የሚሉት ቃላት ጌታችን ዐርባውንም ቀን መፈተኑን ያሳያሉ:: አርባ ቀንና አርባ ሌሊትም ከጦመ በኋላ ተራበ። ፈታኝም ቀርቦ እንዲህ አለው (ማቴ 4:2) የሚለው ደግሞ ከጾሙ በኁዋላ የቀረቡለትን ሦስት ፈተናዎች የሚያሳይ ነው:: ሦስተኛው ጥቅስ ደግሞ ከተፈተነ በኁዋላ ያለው ሲሆን ዲያቢሎስም ፈተናውን ሁሉ ከጨረሰ በኋላ እስከ ጊዜው ከእርሱ ተለየ። (ሉቃ 4:13) ይላል:: ዲያቢሎስ ፈተናውን ቢጨርስም የሚተወው ለጊዜው እንጂ መፈተኑን አያቆምም::  የዲያቢሎስ ፈተና ስልቱ ይቀያየራል እንጂ ይቀጥላል:: ዐቢይ ጾም ዲያቢሎስ ድል የተደረገበት የጦር ዐውድማ ነው:: በዚህ ወራት ድል ያላደረግነውን ፈተና በሌላ ጊዜ አናደርገውም:: ሰነፍ ገበሬ በሰኔ ይሞታል እንደሚባለው በዐቢይ ጾም የተኛ ክርስቲያን መቼም አይነቃም:: ከነስሙ ሁዳዴ (ሰፊ እርሻዬ) የምንለው ይህ ጾም ለነፍሳችን ብዙ ዘር የምንዘራበት አጋንንት መድረሻ የሚያጡበት ጾም ነው:: በዐቢይ ጾም ያልተገራ አንደበት መቼም አይገራም:: በዐቢይ ጾም ያልተፈወሰ ቂም መቼም አይፈወስም:: ጌታችን በወንጌል አንዴ ወደ እሳት አንዴ ወደ ውኃ የሚጥል ጋኔን ያለበትን ልጅ ሲፈውስ "ይህ ዓይነቱ ጋኔን ያለ ጾምና ጸሎት አይወጣም" ብሎ ነበር:: ሀገራችንን አንዴ ወደ እሳት አንዴ ወደ ውኃ የሚጥላት የጥላቻ ጋኔንም ያለ ጾምና ጸሎት አይወጣም:: ወዳጄ ከቁስልህ የምትፈወስበት ወር እንደደረሰ ዕወቅ:: አንተስ ብትሆን ልትላቀቀው እየፈለግህ ያቃተህ ክፉ ልማድ የለብህም:: እንደ ቅዱስ ጳውሎስ "የምፈልገውን መልካም ነገር አላደርግም የማልፈልገውን ክፉ ነገር ግን አደርጋለሁ:: ምንኛ ጎስቋላ ለዚህ ለሞት ከተሠጠ ሰውነት ማን ያድነኛል?" ብለህ ምርር እንድትል ያደረገህ ኃጢአት የለም? እንግዲያውስ እወቀው:: ይህ ዓይነቱ ወገን ያለ ጾምና ጸሎት አይወጣም:: ይህ ጾም ቁስል የሚሽርበት ጾም ነው:: ይህ ጾም ሸክም ማራገፊያ ጾም ነው:: እንደ ሕዝቅያስ በዚህ ወር ቤትህን በንስሓ አስተካክል:: ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ የካቲት 15 2012 ዓ ም ዝዋይ ኢትዮጵያ Deacon Henok Haile ይህ ዓይነቱ ጽሑፍ ለእርስዎም ለሌሎችም እንዲደርስ ፔጁን Like Share Comment ያድርጉ:: #henokhaile #deaconhenokhaile #eotc #christian #orthodoxchurch  #ethiopian #bible #gospel

ምኵራብ(3ኛ ሳምንት) #ዘቅዳሴ መልእክታት    -ቆላ.2፡16-ፍ.ም                  -ያዕ.2፡14-ፍ.ም                  -ግብ ሐዋ.10፡1-9 ምስባክ፡-68፡9 እስመ ቅንዓተ ቤትከ በልዐኒ፤ ትእይርቶሙ ለእለ ይትዔየሩከ ወድቀ ላዕሌየ ወቀጻዕክዋ በጾም ለነፍስየ። ወንጌል፡-ዮሐ.2፡12-ፍ.ም ቅዳሴ፡-ዘእግዚእነ @gisawe @gisawe @gisawe

የካቲት 25 ዘነግህ ምስባክ፦106፡6 ወዐውየዉ ኀበ አግዚአብሔር ሶበ ተመንደቡ፤ ወአድኀኖሙ እምንዳቤሆሙ፤ ወአውጽኦሙ እምጽልመት ወጽላሎተ ሞት፡፡ ወንጌል፦ሉቃ.9፡37-44 #ዘቅዳሴ መልእክታት -1 ፊልሞ.1፡1-13                  -2 ጴጥ.1፡10-15                  -ግብ ሐዋ.9፡1-10 ምስባክ፦64፡4 ጸገብነ እግዚኦ እምበረከተ ቤትከ፤ ቅዱስ ጽርሕከ ወመንክር በጽድቅ፤ ስምዐነ አምላክነ ወመድኃኒነ፡፡ ወንጌል፦.9፡12-17 ቅዳሴ፦ግሩም @gisawe @gisawe @gisawe

የካቲት 24 ዘነግህ ምስባክ፦49፡10 ሡዕ ለእግዚአብሔር ወሥዋዕተ ስብሐት፤ ወሀቦ ለልዑል ጸሎተከ፤ ትጼውዐኒ በዕለተ ምንዳቤከ አድኅነከ ወተአኵተኒ፡፡ ወንጌል፦ማር.1፡40-ፍ.ም #ዘቅዳሴ መልእክታት -ሮሜ.13፡1-11                  -1 ጴጥ.2፡16-ፍ.ም                  -ግብ ሐዋ.19፡11-21 ምስባክ፦118፡91 ወበትእዛዝከ ይቀውም ዕለት፤ እስመ ኵሎ ቀነይከ፤ ሶበ አኮ ሕግከ ተመሐርየ ውእቱ፡፡ ወንጌል፦ማር.1፡23-29 ቅዳሴ፦ግሩም @gisawe @gisawe @gisawe

የካቲት 23 ዘነግህ ምስባክ፡78፡10 ወይርአዩ አሕዛብ በቅድመ አዕይንቲነ፤ በቀለ ደሞሙ ለአግበርቲከ ዘተክዕወ፤ ይባዕ ቅድሜከ ገዐሮሙ ለሙቁሓን፡፡ ወንጌል፦ማቴ.26፡46-57 #ዘቅዳሴ መልእክታት -2 ቆሮ.4፡7-ፍ.ም                  -1 ጴጥ.4፡12-ፍ.ም                  -ግብ ሐዋ.9፡23-32 ምስባክ፦79፡6 ወተሣለቁ ላዕሌነ ጸላዕትነ፤ እግዚኦ አምላከ ኃያላን ሚጠነ፤ አብርህ ገጸከ ላዕሌነ ወንድኅን። ወንጌል፦ዮሐ.16፡1-7 ቅዳሴ፦ወልደ ነጎድጓድ @gisawe @gisawe @gisawe

የካቲት 22 ዘነግህ ምስባክ፦142፡1 እግዚኦ ስምዐኒ ጸሎትየ፤ ወአፅምአኒ ስእለትየ በጽድቅከ፤ ወሰምዐኒ በርትዕከ፡፡ ወንጌል፦ሉቃ.14፡1-7 #ዘቅዳሴ መልእክታት -1 ቆሮ.12፡1-12                  -1 ጴጥ.1፡6-10                  -ግብ ሐዋ.16፡16-19 ምስባክ፦142፡8 ዘይሰማዕ ግበር ሊተ ምሕረተከ በጽባሕ፤ እስመ ኪያከ ተወከልኩ እግዚኦ፤ ምርሀኒ እግዚኦ ፍኖተ እንተ ባቲ አሐውር፡፡ ወንጌል፦ሉቃ.13፡10-18 ቅዳሴ፦ግሩም @gisawe @gisawe @gisawe

የካቲት 21 ዘነግህ ምስባክ፡44፡9 ወትቀውም ንግሥት በየማንከ፤ በአልባሰ ወርቅ ዑጽፍት ወኁብርት፤ ስምዒ ወለትየ ወርእዪ ወአጽምዒ እዝነኪ፡፡ ወንጌል፦ሉቃ.1፡46-57 #ዘቅዳሴ መልእክታት    -ፊልሞ.1፡10-ፍ.ም                  -1 ጴጥ.5፡5-ፍ.ም                  -ግብ ሐዋ.13፡1-7 ምስባክ፦21፡5 ኪያከ ተወከሉ ወኢተኀፈሩ፤ አንሰ ፅፄ ወአኮ ሰብእ፤ ምኑን በኀበ ሰብእ ወትሑት በውስተ ሕዝብ፡፡ ወንጌል፡-ማቴ.22፡24-31 ቅዳሴ፡-ዘእግዝእትነ @gisawe @gisawe @gisawe

በጾመ ህርቃል(1ኛ ሳምንት) የተሰበኩት ምስባኮች ሁሉም ትክክል ናቸው?
Anonymous voting

የካቲት 13 ዘነግህ ምስባክ፦102፡13 ወበከመ ይምሕር አብ ውሉዶ፤ ከማሁ ይምሕሮሙ እግዚአብሔር ለእለ ይፈርህዎ፤ እስመ ውእቱ የአምር ፍጥረተነ። ወንጌል፦ማቴ.5፡42-ፍ.ም #ዘቅዳሴ መልእክታት -2 ጢሞ.3፡1-13                  -1 ጴጥ.5፡1-11                  -ግብ ሐዋ.9፡23-32 ምስባክ፦33፡14 ተገኀሥ እምእኩይ ወግበር ሠናየ፤ ኀሥሣ ለሰላም ወዴግና፤ እስመ አዕይንቲሁ ለእግዚአብሔር ኀበ ጻድቃኑ፡፡ ወንጌል፦ማቴ.5:1-17 ቅዳሴ፦ግሩም @gisawe @gisawe @gisawe

ቅዱሳን መላእክት ለሰዉ ልጆች ድኅነት እጅግ የሚጓጉ ከእግዚአብሔር የተሰጡ ጠባቂዎቻችን ናቸዉ። እርግጥ ነዉ፤ በመጀመሪያ እኛም እንደ መላእክት ክብሩን ለመዉረስ ስሙን ለመቀደስ የተፈጠርን ነበርን ግንኙነታችንም እነርሱ ከእኛ ቀድመዉ በመፈጠራቸዉ ታላላቅ ወንድሞቻችን ናቸዉ። ከሰዉ ልጅ ዉድቀት በኋላ ግን ነገሮች ተለወጡ። በእኛ የባህርይ መጎስቆል ምክንያት ታላቅ ወንድም የታመመ ታናሹን እንደሚጠብቅ ጠባቂዎቻችን ሆኑ። ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ እንዳለዉ፦ የሰዉ ልጅ ከመላእክት ጋር ክቡር ሆኖ ሲፈጠር፤ ጠባቂን አይሻም ነበር፤ ሰዉ በኃጢአት ከወደቀ በኋላ ግን እግዚአብሔር መላእክትን ጠባቂ አደረገለት። ምክንያቱም ዲያብሎስ ሰዉን ለማጥፋት ሁል ጊዜ ምክንያቶችን ስለሚፈልግ ነዉ። እነዚህ መላእክት ከጠባቂነታቸዉ ባሻገር ለሰዉ ልጅ መዳን እጅግ የሚጓጉ ሰዉን ወዳጆች ናቸዉ። አምላክ ሰዉ ሆኖ በተወለደበት በዚያች ምሽት ሲዘምሩ ያደሩት በአምላክ ሰዉ መሆን የሚያገኙት ጥቅም ኖሮ ሳይሆን ለሰዉ ልጅ መዳን ካላቸዉ ፍላጎትና ፍቅር የተነሳ ነዉ። በሰማይ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን በምድርም ሰላም የሚለዉ ዝማሬያቸዉ የእኛ ሰላም ለእነርሱ ምስጋና ምክንያት መሆን የሚያሳይ ምስጋና ነበር። ሉቃ 2:14 የማያገቡትና የማይጋቡት እነዚህ መላእክት በሰማይ የሰርግ ያህል ደስ የሚሰኙት በምድር አንድ ኃጢአተኛ ንሰሓ ሲገባ መሆኑ ምን ያህል የእኛ ወዳጆች መሆናቸዉን ያሳያል ሉቃስ15;10። ሁሉ መዳንን ይወርሱ ዘንድ የተላኩ ስላላቸዉ ለማገዝ የሚላኩ መናፍስት አይደሉምን? ምንጭ ኢትዮጵያዊዉ ጃንደረባ በዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ'

መዝሙር ዘቅድስት፦ ሃሌ ሉያ(፭) ግነዩ ለእግዚአብሔር ወጸውዑ ስሞ፤ወንግርዎሙ ለአሕዛብ ምግባሮ፤ ሀቡ ስብሐተ ለስሙ፡፡አክብሩ ሰንበተ ተገብሩ ጽድቀ፤ዝግቡ ለክሙ መዝገበ ዘበሰማያት፤ኀበ ፃፄ ኢያማስኖ ወኢይረክቦ ሠራቂ፤ድልዋኒክሙ ንበሩ ዘበላዕሉ ሐልዩ፤ኀበ ሀሎ ክርስቶስ፡፡ የዕለቱ ምስባክ፦ እግዚአብሔርሰ ሰማያተ ገብረ፤ አሚን ወሠናይት ቅድሜሁ፤ ቅድሳት ወዕበየ ስብሐት ውስተ መቅደሱ። መዝ ፺፭፥፭ ትርጉም፦ እግዚአብሔር ግን ሰማያትን ፈጠረ፤ እምነትና በጎነት በፊቱ ናቸው፤ ቅድስና እና የክብር ገናንነት በመቅደሱ ውስጥ ናቸው። @gisawe @gisawe @gisawe   

ዘቅድስት(2ኛ ሳምንት) #ዘቅዳሴ #መዝሙር ዘቅድስት ግነዩ ለእግዚአብሔር መልእክታት -1 ተሰሎ.4፡1-13                  -1 ጴጥ.1፡13-ፍ.ም                  -ግብ ሐዋ.10፡17-30 ምስባክ፡-95፡5 እግዚአብሔርሰ ሰማያተ ገብረ፤ አሚን ወሠናይት ቅድሜሁ፤ እሳት ወዕበየ ስብሐት ውስተ መቅደሱ፡፡ ወንጌል፡-ማቴ.6፡16-25 ቅዳሴ፡-ዘኤጲፋንዮስ @gisawe @gisawe @gisawe

ወወሀብኮሙ ትእምርተ.m4a8.88 KB

በጾመ ሕርቃል ዘቀዳሚት #ዘቅዳሴ መልእክታት -1 ቆሮ.1፡17-25                  -1 ጴጥ.4፡1-7                  -ግብ ሐዋ.20፡28-32 ምስባክ፦59፡3 ወወሀብኮሙ ትእምርተ ለእለ ይፈርሁከ፤ ከመ ያምሥጡ እምገፀ ቅስጥ፤ ወይድኀኑ ፍቁራኒከ። ወንጌል፦ማቴ.16፡21-27 ቅዳሴ፦ @gisawe @gisawe @gisawe

ብፁዕ.m4a9.14 KB

በጾመ ሕርቃል ዘአርብ #ዘቅዳሴ መልእክታት -ዕብ.4፡1-7                  -3 ዮሐ.1፡11-ፍ.ም                  -ግብ ሐዋ.14፡24-ፍ.ም ምስባክ፦111፡1 ብፁዕ ብእሲ ዘኢይፈርሆ ለእግዚአብሔር ፤ ወዘይፈቅድ ትዕዛዞ ፈድፋደ፤ ወይከውን ጽኑዓ ዘርዑ ወስተ ምድር። ወንጌል፦ማቴ.12፡38-42 ቅዳሴ፦ @gisawe @gisawe @gisawe

Watch "🛑ዐቢይ ጾም || ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ" on YouTube https://youtu.be/E3W76kkwNGI

+ ትሞታለህና ቤትህን አስተካክል + ንጉሥ ሕዝቅያስ በጠና ታምሞ ተኝቶአል::  ነቢዩ ኢሳይያስ ሊጠይቀው መጣ:: ሆኖም እንደ ልማዱ እግዚአብሔር ይማርህ አላለውም:: ለጆሮ የሚከብድ  ቃል ጥሎበት ወጣ:: "ትሞታለህና ቤትህን አስተካክል!" ነቢዩ ይህንን ብሎት ከወጣ በኁላ ሕዝቅያስ ወደ ግድግዳው ዞሮ ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ:: አምላኩ በንግግር ብዛት የሚሰማ አምላክ አይደለምና ፊቱን ወደ መቅደሱ አቅጣጫ አዙሮ አለቀሰ::  ከጥቂት ደቂቃ በኁዋላ ነቢዩ ኢሳይያስ ሌላ መልእክት ይዞ ተመለሰ:: እግዚአብሔር እንዲህ ይላል :- ጸሎትህን ሰምቻለሁ ዕንባህን አይቻለሁ በዕድሜህ ላይ ዐሥራ አምስት ዓመት እጨምራለሁ" (ኢሳ 38:5) ሕዝቅያስ ቤትህን አስተካክል ከተባለ በኁዋላ ፊቱን አዙሮ ከማልቀስ በቀር ምንም አላደረገም:: ሕዝቅያስ ሆይ ከአልጋህ ሳትወርድ ያስተካከልከው ቤት ምን ዓይነት ቤት ነው? ለባሪያዎችህ መመሪያ ሳትሠጥ የምታስተካክለው ቤትስ እንዴት ያለ ነው? በደቂቃዎች ውስጥ ትሞታለህ ከተባልክ በኁዋላ ዐሥራ አምስት ዓመት ያስጨመረልህ ምን ዓይነት ማስተካከያ አድርገህ ነው? ለእኛም ንገረንና ዕድሜ እናስጨምር:: ሕዝቅያስ ከአልጋው ሳይነሣ ያስተካከለው ቤቱ ልቡ ነበር:: ልብህን ካስተካከልህ ቤትህ ይስተካከላል:: እግዚአብሔር እንደሆን ትሞታለህ ቢልህም መሞትህን አይፈልግም:: እርሱ ካንተ ጋር ጸብ የለውም:: "በውኑ ኃጢአተኛ ይሞት ዘንድ እፈቅዳለሁን? ይላል ጌታ እግዚአብሔር፤ ከመንገዱስ ይመለስና በሕይወት ይኖር ዘንድ አይደለምን?" ይላል መሐሪው (ሕዝ 18:23) እርሱ ትሞታለህ የሚልህ መኖርህን ፈልጎ ነው:: አንዴ ብያለሁ ብሎ አይጨክንብህም:: በንስሓ ተመለስ እንጂ ምሬሃለሁ ለማለት ይቸኩላል:: አሁን ትሞታለህ ብዬው አሁን ትድናለህ ብለው ይንቀኛል ሳይል ተመልሶ ይምርሃል:: ኃጢአትህንም ወደ ጥልቁ ይጥለዋል:: በጎ እንድትሠራም ዕድሜ ይጨምርልሃል:: አንተ ብቻ ተመለስና አሁኑኑ ንስሓ ግባ:: ከበደል አልጋ ጋር ያጣበቀህን ፈተናም ድል መንሻው ጊዜ አሁን ነው:: ሕዝቅያስ በደቂቃ ዕንባ ምሕረት አግኝቶ ዕድሜ ካስጨመረ በዐቢይ ጾም ሙሉ የሚያለቅስ ምን ያህል ዕድሜ ያገኝ ይሆን? ወዳጄ አንተም ተነሣና በዚህ ወር ቤትህን አስተካክል:: እንደ ሕዝቅያስ ፈጣሪህ ይጠብቅሃል:: የተቀየምከውን ይቅር በል  የበደልከውን ካስ የሚበቀልህን የማይተኛ ጠላትህን ዲያቢሎስ ተበቀለው:: የዐቢይ ጾም የወንጌል ምንባብ ስለ ዲያቢሎስ ፈተና ሦስቱ ወንጌላት የተናገሩትን ስናስተውል ሦስት ዓይነት ጥቅሶች እናገኛለን:: አርባ ቀን ከዲያብሎስ ተፈተነ። (ሉቃ 4:2) በምድረ በዳም ከሰይጣን እየተፈተነ አርባ ቀን ሰነበተ (ማር 1:13) የሚሉት ቃላት ጌታችን ዐርባውንም ቀን መፈተኑን ያሳያሉ:: አርባ ቀንና አርባ ሌሊትም ከጦመ በኋላ ተራበ። ፈታኝም ቀርቦ እንዲህ አለው (ማቴ 4:2) የሚለው ደግሞ ከጾሙ በኁዋላ የቀረቡለትን ሦስት ፈተናዎች የሚያሳይ ነው:: ሦስተኛው ጥቅስ ደግሞ ከተፈተነ በኁዋላ ያለው ሲሆን ዲያቢሎስም ፈተናውን ሁሉ ከጨረሰ በኋላ እስከ ጊዜው ከእርሱ ተለየ። (ሉቃ 4:13) ይላል:: ዲያቢሎስ ፈተናውን ቢጨርስም የሚተወው ለጊዜው እንጂ መፈተኑን አያቆምም::  የዲያቢሎስ ፈተና ስልቱ ይቀያየራል እንጂ ይቀጥላል:: ዐቢይ ጾም ዲያቢሎስ ድል የተደረገበት የጦር ዐውድማ ነው:: በዚህ ወራት ድል ያላደረግነውን ፈተና በሌላ ጊዜ አናደርገውም:: ሰነፍ ገበሬ በሰኔ ይሞታል እንደሚባለው በዐቢይ ጾም የተኛ ክርስቲያን መቼም አይነቃም:: ከነስሙ ሁዳዴ (ሰፊ እርሻዬ) የምንለው ይህ ጾም ለነፍሳችን ብዙ ዘር የምንዘራበት አጋንንት መድረሻ የሚያጡበት ጾም ነው:: በዐቢይ ጾም ያልተገራ አንደበት መቼም አይገራም:: በዐቢይ ጾም ያልተፈወሰ ቂም መቼም አይፈወስም:: ጌታችን በወንጌል አንዴ ወደ እሳት አንዴ ወደ ውኃ የሚጥል ጋኔን ያለበትን ልጅ ሲፈውስ "ይህ ዓይነቱ ጋኔን ያለ ጾምና ጸሎት አይወጣም" ብሎ ነበር:: ሀገራችንን አንዴ ወደ እሳት አንዴ ወደ ውኃ የሚጥላት የጥላቻ ጋኔንም ያለ ጾምና ጸሎት አይወጣም:: ወዳጄ ከቁስልህ የምትፈወስበት ወር እንደደረሰ ዕወቅ:: አንተስ ብትሆን ልትላቀቀው እየፈለግህ ያቃተህ ክፉ ልማድ የለብህም:: እንደ ቅዱስ ጳውሎስ "የምፈልገውን መልካም ነገር አላደርግም የማልፈልገውን ክፉ ነገር ግን አደርጋለሁ:: ምንኛ ጎስቋላ ለዚህ ለሞት ከተሠጠ ሰውነት ማን ያድነኛል?" ብለህ ምርር እንድትል ያደረገህ ኃጢአት የለም? እንግዲያውስ እወቀው:: ይህ ዓይነቱ ወገን ያለ ጾምና ጸሎት አይወጣም:: ይህ ጾም ቁስል የሚሽርበት ጾም ነው:: ይህ ጾም ሸክም ማራገፊያ ጾም ነው:: እንደ ሕዝቅያስ በዚህ ወር ቤትህን በንስሓ አስተካክል:: ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ የካቲት 15 2012 ዓ ም ዝዋይ ኢትዮጵያ

ወበከመ ይምህር.m4a9.15 KB

በጾመ ሕርቃል ዘሐሙስ #ዘቅዳሴ መልእክታት -ሮሜ.13፡11-14                  -2 ዮሐ.1፡1-13                  -ግብ ሐዋ.13፡1-5 ምስባክ፦102፡13 ወበከመ ይምህር አብ ውሉዶ፤ ከማሁ ይመህሮሙ እግዚአብሔር ለእለ ይፈርህዎ፤ እስመ ውእቱ የአምር ፍጥረትነ። ወንጌል፦ማቴ.7፡7-12 ቅዳሴ፦ @gisawe @gisawe @gisawe